መነሻ - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ሰልጠና ላይ የሚገኙ እጩ የፖሊስ መኮንኖች በደብረ ማርቆስ ከተማ ለአቅመ ደካሞች ቤት ገንብተው አስረከቡ
Jun 4, 2023 26
ደብረ ማርቆስ ግንቦት 27/2015 (ኢዜአ) በአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ሰልጠና ላይ የሚገኙ እጩ የፖሊስ መኮንኖች በደብረ ማርቆስ ከተማ ለሶስት አቅመ ደካሞች ቤት ገንብተው አስረከቡ። የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ተወካይ ረዳት ኮሚሽነር አበበ ደለለ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ህዝባዊነትን የተላበሰ ፖሊስ የህብረተሰቡን ደህንነት ከመጠበቅ ባሻገር በሰብአዊነት ተሳትፎ የማድረግ ሃላፊነት አለበት። በኮሌጁ የሚሰለጥኑ የፖሊስ እጩ መኮንኖች ካላቸው በማዋጣት የማህበረሰብን ችግር ሊቀርፉ የሚችሉ የልማት ስራዎችን መስራታቸውን በማሳያነት ገልጸዋል። ሰልጣኞቹ ካላቸው በማዋጣት በደብረ ማርቆስ ከተማ ሶስት ቤቶችን ገንብተው በማስረከብ አቅመ ደካማ ግለሰቦች ተጠቃሚ እንዲሆኑ መስራታቸውን ተናግረዋል። ቤቶቹ ከ100 ሺህ ብር በላይ ወጭ እንደተደረገባቸው የገለጹ ሲሆን ሰልጣኞቹ በጉልበታቸውና በእውቀታቸው አስተዋጽኦ አበርክተዋል ነው ያሉት። የፖሊስ እጩ መኮንኖቹ ከዚህ በተጨማሪም የደብረ ማርቆስ ከተማ ጽዳትና ውበት በመጠበቅ በኩል ጉልህ ሚና እየተጨዋቱ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል። በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የመንቆረር ክፍለ ከተማ ዋና ስራአስኪያጅ አቶ አስታራቂ መኩሪያው እንዳሉት እጩ የፖሊስ መኮንኖች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ሰዎችን መኖሪያ ቤት ግንባታና እድሳት ላይ እየተሳተፉ ነው። ከፍለ ከተማውም በበጀት ዓመቱ ህብረተሰቡን በማስተባበር ከ4 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ ከ60 በላይ ቤቶች በማስገንባት አሁን ላይ ለተጠቃሚዎች ለማስተላለፍ በዝግጅት ላይ መሆኑን ተናግረዋል። እጬ መኮንን አስቻል ኪዳኔ፣ ''ከምናገኛት ቀንሰን ለችግረኛ ግለሰቦች ቤት መስራታችን የህዝብ ልጆች መሆናችንን ለማሳየት ነው'' ብሏል። በቀጣይም በኮሌጁ እስካሉ ድረስ የአካባቢውን ህብረተሰብ ችግር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግሯል። እጩ መኮንን አብዱ ባልዲቾም እንዲሁ የአቅመ ደካሞችን እና የችግረኞችን ቤት መገንባት ከፍተኛ የአእምሮ እርካታን የሚፈጥር ነው ብሏል። አሁን የተገነቡት ቤቶች መጀመሪያቸው እንጂ መጨረሻ እንዳልሆነ ገልጸው ለወደፊትም የማህበረሰብ አገልግሎታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድቷል።
የኢትዮጵያን መስህቦች የማልማት፣ የመጠበቅና የማስተዋወቅ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው- ቱሪዝም ሚኒስቴር
Jun 4, 2023 33
አዲስ አበባ ግንቦት 27/2015(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን መስህቦች በተለያዩ አማራጮች የማልማት፣ የመጠበቅና የማስተዋወቅ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር ገለጸ። "ላሊበላ በእምነት የታነፀ" በሚል መሪ ሀሳብ የላልይበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ የቋሚ ዐውደ ርዕይ በላልይበላ ከተማ ተከፍቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ፤ በቱሪስት መዳረሻ ታሪካዊ ቅርሶች ዙሪያ ዕሴት የሚጨምሩ ተግባራትን በማከናወን ተወዳዳሪ መዳረሻነት እና ማህበራዊ አቀፍ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም በእንጦጦ ፓርክ የላልይበላ ቨርቹዋል ሪያሊታ ዐውደ ርዕይ ተከፍቶ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መጎብኝታቸውን አስታውሰው በላልይበላ ደግሞ ተመሳሳይ አውደ ርእይ መከፈቱን ጠቅሰዋል። በዩኔስኮ የተመዘገቡ የዓለም ቅርሶችን ማልማትና መጠበቅ ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ገልጸው የላልይበላ አብያተ ክርስቲያናትን የመጠበቅና የቱሪስት መዳረሻነቱን የማልማትና የማሳደግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን መስህቦች የማልማት፣ የመጠበቅና የማስተዋወቅ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትር ዴኤታው የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች፣ የጎንደርና የጅማ አባጅፋር አብያተ መንግስታት ዕድሳትንም ለአብነት ጠቅሰዋል። በዘርፉ አቅም ለመገንባት የሰው ኃይል ስልጠና፣ የቱሪስት አገልግሎት ጥራት ለማሻሻል የሆቴልና ቱሪዝም ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል። በላሊበላ የተለመዱ የቱሪዝም ሀብቶችን ማሳየት ብቻ ሳይሆን የጎብኝዎችን ቆይታ የሚያራዝም የጉብኝት ፓኬጅ በመቅረፅና እሴት በመጨመር ተወዳዳሪ የቱሪስት መዳረሻ ማድረግ የሚያስችልና አካባቢያዊ ተጠቃሚነትን የሚያሳድግ በፈረንሳይ መንግስት ድጋፍ 'የላሊበላ ዘላቂ ፕሮጀክት' እየተተገበረ መሆኑንም አንስተዋል። የጊዜ ገደቡ ለመጠናቀቅ አንድ ዓመት ብቻ የቀረው የዘላቂ ልማት ፕሮጀክት ቀጣይ ምዕራፍ እንዲኖረውም ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር ሕይወት ኃይሉ፤ ቅርሶች ታሪክን ለመዘከር፣ ተፈጥሮና አካባቢን ለመረዳት ፣የመረጃ ምንጭ በመሆንና የገቢ ምንጭነታቸው የማይተካ ሚና አላቸው ብለዋል። ባለስልጣኑ ቅርሶች ለታሪክ ምስክርነት እንዲውሉ ወደ ትውልድ ማስተላለፍ፣ ከጉዳት የመጠበቅ፣ የማጥናትና ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ጥቅማቸውን የማሳደግና ተደራሽ የማድረግ ስራዎችን ከባለድርሻ አካላት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። በፈረንሳይ ልማት ኤጄንሲ ድጋፍ በ22 የትኩረት መስኮች ተለይቶ የሚሰራው 'የላልይበላ ዘላቂ ልማት' ፕሮጀክት ትግበራም ጥሩ ደረጃ ላይ እንደሆነ ተናግረዋል። የላሊበላ ቋሚ ዐውደ ርዕይ ኢትዮጵያን ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል የሚፈጥርና የጎብኚዎችን ቆይታ የሚያራዝም መሆኑን ገልፀው፣ በቀጣይም በሌሎች ቦታዎችም ይከፈታል ብለዋል። የቅርስ መጠበቅና መንከባከብ የዜግነት ኃላፊነት ነው ያሉት ምክትል ዳይሬክተሯ፣ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን ዕድሳትና ጥገና እንዲሁም የቅርሶችን ጊዜያዊ መጠለያ የማንሳት ስራዎች በጥንቃቄ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኤምባሲ ተወካይና የኤምባሲው የባህል ካውንስለር ሶፊ ማካሜ፣ ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ የዘለቀው የኢትዮ ፈረንሳይ ወዳጅነትና ትብብር በታሪካዊ ቅርሶች ዘርፍ ቅድሚያ በመስጠት በታሪካዊ ዲፕሎማሲ ዘርፍ ተጨባጭ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ኢኒሼቲቭ ወደ ትግበራ የገባው የላልይበላ ዘላቂ የልማት ፕሮጀክት፣ የብሔራዊ ሙዚየም መልሶ የማደራጀት እንዲሁም የብሔራዊ ቤተ መንግስት ዕድሳትም ከትብብር ስራዎች ለአብነት አንስተዋል። የላሊበላ ታሪካዊ ቅርስ ብቻ ሳይሆን ለማህበረሰቡ ሁለንተናዊ ፋይዳ እየሰጠ ያለ ሃብት በመሆኑ የአካባቢውና የውጭ ባለሙያዎችን አቅም በመደመር የቅርሱን ቀጣይነት የማረጋገጥ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል። የላሊበላ ቅርስ መጠበቅና መንከባከብ የቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ገልፀው፤ ለዚህም የላሊበላ ዘላቂ ፕሮጀክት ቅርስን ለትውልድ ለማሻገር በሚደረገው ጥረት ፈረንሳይ የድርሻዋን እያበረከተች መሆኑን ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ ትግበራና ቋሚ ዐውደ ርዕዩ ለኢትዮጵያና ለዓለም አቀፍ ጉብኝዎች ታሪካዊና መንፈሳዊ መልኮች በመዘከር ታሪካዊ አረዳድ የሚያጎለብት፣ የወደፊት የመረጃ ቋት ግንባታ መሰረት የሚሆንና ለአካባቢው ማህበረሰብ አካታች ልማት የሚያግዝ መሆኑን ገልፀዋል። በላሊበላ ዘላቂ ፕሮጀክት ትግበራ ሂደት ትብብር ያደረጉ አካላትን አመስግነው፤ ለኢትዮጵያ ቅርሶች መጠበቅ ፈረንሳይ እገዛዋን አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ
Jun 4, 2023 35
አዲስ አበባ ግንቦት 27/2015(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይደረጋሉ። በመርሐ-ግብሩ መሰረት ሀዲያ ሆሳዕና ቀድሞ ከሊጉ መውረዱን ካረጋገጠው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ከቀኑ 7 ሰአት ላይ ይጫወታል። በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ሀዲያ ሆሳዕና በ36 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ12 ነጥብ የመጨረሻውን 16ኛ ደረጃን ይዟል። ሀዲያ ሆሳዕና በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው፤ ሁለት ጊዜ ተሸንፎ ሁለት ጊዜ አቻ ወጥቷል። በአንጻሩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች አራት ጊዜ ሲሸነፍ አንድ ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያ ዙር ያደረጉት ጨዋታ ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ይታወሳል። በ27ኛ ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር የመጨረሻው ጨዋታ በመቻልና ባህር ዳር ከተማ መካከል ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ይደረጋል። በደረጃ ሰንጠረዡ መቻል በ34 ነጥብ 11ኛ ሲሆን ባህር ዳር ከተማ በ50 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። መቻል ካለፉት አምስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ሁለቱን አሸንፎ በአንዱ ሲሸነፍ በሁለቱ አቻ ወጥቷል። ተጋጣሚው ባህር ዳር ከተማ በበኩሉ ባለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል፤ ሁለት ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። ባህር ዳር ከተማ ጨዋታውን ካሸነፈ ከሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ዝቅ ያደርጋል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ መቻል 3 ለ 2 ማሸነፉ ይታወሳል። በተያያዘ ዜና ትናንት በተደረጉ የ27ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ኢትዮጵያ መድን ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 ሲያሸንፍ ወልቂጤ ከተማ እና ፋሲል ከነማ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል። ከዛሬ ጨዋታዎች በኋላ የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሃዋሳ ከተማ ቆይታ እንደሚጠናቀቅ የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል። ከ28ኛ እስከ 30ኛ ሳምንት ያሉ የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ከሰኔ 1 እስከ ሐምሌ 1 2015 በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም እንደሚካሄዱ ገልጿል።
በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም መሽገው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩት እስክንድር ነጋና ግብረዓበሮቹ ላይ በተወሰደው እርምጃ ክልሉን የማተራመስ ሴራቸው መክሸፉን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ
Jun 3, 2023 94
በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም መሽገው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩት እስክንድር ነጋና ግብረዓበሮቹ ላይ በተወሰደው እርምጃ ክልሉን የማተራመስ ሴራቸው መክሸፉን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ)፦ በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ የሚገኘውን የሥላሴ ገዳም ከለላ በማድረግ መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ላይ በተወሰደው እርምጅ በእስክንድር ነጋና በግብረዓበሮቹ ለውጊያ ሲውል የነበረው ምሽግ መሰበሩንና በ200 ታጣቂዎችም ላይ እርምጃ መወሰዱን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡ የታጣቂ ቡድኑ መሪና አስተባባሪ የነበረው እስክንድር ነጋና ጥቂት ግብረዓበሮቹ ከአካባቢው ለመሰወር ቢሞክሩም በዋናነት የመከላከያ ሠራዊት እንዲሁም የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ለማዋል እግር በእግር በመከታተል የተቀናጀ ኦፕሬሽን እያካሄዱ መሆኑንም ግብረ ኃይሉ ገልጿል፡፡ የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ፤ ባልደራስ በሚል የፖለቲካ ፓርቲ ሽፋን ሲንቀሳቀስ የቆየው እስክንድር ነጋ የተባለው ግለሰብ የሐሳብ የበላይነትን በማረጋገጥ ዓላማውን ማሳካት ሲሳነው በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ጊዜያት ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲሞክር እንደነበር አስታውሷል፡፡ ግለሰቡ ይህ እንዳልተሳካለት ሲያውቅ፤ መንግሥትን በኃይል ለመጣል በማቀድ የአማራ ሕዝባዊ ግንባር የተባለ አደረጃጀት በመፍጠር ሽመልስ ስማቸው፣ ሰውመሆን ወረታውና መንበሩ ካሴ ከተባሉ ግብረዓበሮቹ እንዲሁም ከሌሎች ጥቂት የክልሉ ጽንፈኛ ኃይሎች ጋር በመቀናጀትና በህቡዕ በመንቀሳቀስ ታጣቂዎችን ሲመለምል፣ ሲያደራጅና ስምሪት ሲሰጥ እንደነበር መግለጫው ጠቁሟል። ግንባሩን በሀገር ውስጥ ራሱ ሲመራ በውጭ ደግሞ ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ የተባለ ግለሰብ ያስተባብራል ያለው መግለጫው፤ ሁለቱ በፈጠሩት ትስስር በክልሉ የትጥቅ ትግል በማድረግ ሕዝቡን ወደማያባራ ጦርነት ለማስገባት ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውንም የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ማረጋገጡን አመልክቷል፡፡ መሠረቱን ምዕራብ ጎጃም ቡሬና አባይ በረሃ አካባቢ አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰቡ የሃይማኖት ሽፍንና እንደ ከለላ ለመጠቀም ከሌሎች የቡድኑ ታጣቂዎች ጋር ወደ ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ በማቅናት ከሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ በሥላሴ ገዳም አካባቢ ምሽግ ቆፍረው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል በህቡዕ ሲያሴሩ እንደነበር ያመለከተው የግብረ ኃይሉ መግለጫ፤ በተለይ የገዳሙ አስተዳዳሪ የሆኑትን አባ ኤልሳን ለዚህ ሕገወጥ ተግባር ሲጠቀሙ እንደነበር ጠቅሷል፡፡ አስተዳዳሪውም ከሃይማኖቱ አስተምህሮ ውጭ በገዳሙ ውስጥ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ እንዲደረግ ከመፍቀድ ባሻገር ከሌሎች መነኮሳት ጋር በማበርና የጦር መሣሪያ ጭምር በማንገብ ከጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ጋር ተሰማርተው እንደነበርም ጠቁሟል፡፡ መግለጫው አክሎም እነዚህ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን ሕግ የማስከበር ተልዕኮ ለማደናቀፍ በማለም የዜጎችን ሰላማዊ ሕይወት በሚያስተጓጉሉ ቅስቀሳዎችና ተግባራት ተሰማርተው መቆየታቸውን አስታውሷል፡፡ በአማራና በወለጋ አዋሳኝ አካባቢዎችም ግጭት እንዲቀሰቀስ ሲያደርጉ እንደነበርም አመልክቷል፡፡ የጥፋት ቡድኑ አባላት ሕገ ወጥ እንቅስቃሴውን እንዲያቆሙና በውይይት ወደ ሰላም እንዲመጡ ከክልል እስከ ወረዳ በሚገኙ አካላት ተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም አለመሳካቱን የጠቆመው መግለጫው፤ ይልቁንስ ገዳሙን ምሽግ በማድረግ በአካባቢው አስተዳደር፣ በፖሊስ፣በሚሊሻና በማኅበረሰቡ ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት ሲፈጽሙ መቆየታቸውን አስታውቋል፡፡ በሃይማኖት ሽፋን ፖለቲካዊ አጀንዳቸውን ለማስፈጸም እንቅስቃሴ ሲያደርጉ እንደነበር መታወቁንም አመልክቷል፡፡ አነዚህ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ከኅብረተሰቡ ባሕልና ዕሴት እንዲሁም ከሃይማኖታዊ አስተምህሮ ባፈነገጠ መንገድ በደብረ ኤሊያስ ወረዳ በሚገኘው ቅድስት ሥላሴ ገዳም ውስጥ ምሽግ በመቆፈር ሕዝቡ ቅዱስ የሚለውን ሥፍራ የጦር አውድማ በማድረግ ለማርከስ ቢጥሩም በዋናነት የሀገር መከላከያ ሠራዊት እንዲሁም የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በመቀናጀት በወሰዱት ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃ ሴራው መክሸፉን ያስታወቀው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረኃይል፤ በታጣቂዎቹ ጥቅም ላይ ሲውሉ የነበሩ የተለያዩ ከባድና ቀላል መሣሪያዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁሟል፡፡ 200 የጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ታጣቂዎች መደምሰሳቸውነና የቀሩትም ከመማረካቸውና ከመሸሻቸው ውጪ፤ ቡድኑ የሐሰት ፕሮፓጋንዳ በሚነዛባቸው የማኅበራዊ ትስስር ገፆች በመንግሥት ጸጥታ አካላት በገዳሙና በምዕመናን ጉዳት እንዳደረሰ ተደርጎ የሚሠራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል፡፡ የሀገር መከላከያ ሠራዊትና የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በተቀናጀ መንገድ እርምጃ በወሰዱበት በዚህ ሕግ የማስከበር ስምሪት የአካባቢው ማኅበረሰብ መረጃ በመስጠትና በሌሎችም መንገዶች ያደረገው ትብብር የሚደነቅ መሆኑን ያመለከተው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ ለዚህም ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ በቀጣይም ክልሉ ከጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ጸድቶ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲሰፍን ለሚደረገው ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ ኅብረተሰቡ የጋራ ጥረቱንና አጋርነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
በጋምቤላ ክልል የህዝቡን ተሳትፎ በማጠናከር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እንቅስቃሴ ተጀመረ
Jun 3, 2023 60
ጋምቤላ ግንቦት 26 /2015(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የህዝቡን ተሳትፎ በማጠናከር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ የተማሪ ወላጆች ህብረት ሰብሳቢ በበኩላቸው፤ በየደረጃው የሚገኙ የተማሪ ወላጅ ህብረት አደረጃጀቶችን በማጎልበት ለትምህርት ጥራት መሻሻል እንደሚሰራ ገልጸዋል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ኮንግ ጆክ ለኢዜአ እንዳመለከቱት፤ ትምህርት ቤቶችን በበቂ ግብዓትና የሰው ኃይል ባልተደራጁበት ሁኔታ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ አስቸጋሪ ነው። ይህንን ታሳቢ በማድረግ ህዝቡን በማሳተፍ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የንቅናቄ ስራዎችን ለማካሄድ እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል። በክልሉ ከሚገኙ 377 የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በ131 ትምህርት ቤቶች ላይ የደረጃ ግምገማ ተካሄዶ ከአንድ ትምህርት ቤት በስተቀር ሁሉም ከደረጃ በታች እንደሆኑ መለየታቸውን አስታውቀዋል። በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማጎልበት ትምህርት ቤቶችን በበቂ ግብዓትና መሰረተ ልማት አደራጅቶ ደረጃቸውን በማሻሻል የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀውን የንቅናቄ ሰነድ መሰረት በማድረግ ከክልል እስከ ቀበሌ ግብረ ኃይል የማቋቋም ስራ መጀመሩን አስረድተዋል። የክልሉ የወላጆች ማህበር ሰብሳቢ አቶ አስምሮ ደርበው በበኩላቸው፤ ለትምህርት ጥራት መሻሻል የወላጆች ፣ የትምህርት ቤቶችና የዘርፉ አመራሮች ቅንጅታዊ አሰራር ከፍተኛ ድርሻ አለው ብለዋል። በተለይም የወላጆች ግንዛቤ ማሳደግ ከተቻለ ለልጆቻቸው ትምህርት መሻሻል የሚሰስቱት ነገር እንደማይኖር ገልጸው፤ በዚህም የተቻላቸውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። የክልሉ ወላጆች መምህራን ህብረት አደረጃጀቱን እስከ ወረዳና ትምህርት ቤቶች ድረስ በማጠናከር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የበኩላቸውን ጥረት እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ፖለቲካ
በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም መሽገው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩት እስክንድር ነጋና ግብረዓበሮቹ ላይ በተወሰደው እርምጃ ክልሉን የማተራመስ ሴራቸው መክሸፉን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ
Jun 3, 2023 94
በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም መሽገው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩት እስክንድር ነጋና ግብረዓበሮቹ ላይ በተወሰደው እርምጃ ክልሉን የማተራመስ ሴራቸው መክሸፉን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ)፦ በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ የሚገኘውን የሥላሴ ገዳም ከለላ በማድረግ መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ላይ በተወሰደው እርምጅ በእስክንድር ነጋና በግብረዓበሮቹ ለውጊያ ሲውል የነበረው ምሽግ መሰበሩንና በ200 ታጣቂዎችም ላይ እርምጃ መወሰዱን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡ የታጣቂ ቡድኑ መሪና አስተባባሪ የነበረው እስክንድር ነጋና ጥቂት ግብረዓበሮቹ ከአካባቢው ለመሰወር ቢሞክሩም በዋናነት የመከላከያ ሠራዊት እንዲሁም የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ለማዋል እግር በእግር በመከታተል የተቀናጀ ኦፕሬሽን እያካሄዱ መሆኑንም ግብረ ኃይሉ ገልጿል፡፡ የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ፤ ባልደራስ በሚል የፖለቲካ ፓርቲ ሽፋን ሲንቀሳቀስ የቆየው እስክንድር ነጋ የተባለው ግለሰብ የሐሳብ የበላይነትን በማረጋገጥ ዓላማውን ማሳካት ሲሳነው በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ጊዜያት ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲሞክር እንደነበር አስታውሷል፡፡ ግለሰቡ ይህ እንዳልተሳካለት ሲያውቅ፤ መንግሥትን በኃይል ለመጣል በማቀድ የአማራ ሕዝባዊ ግንባር የተባለ አደረጃጀት በመፍጠር ሽመልስ ስማቸው፣ ሰውመሆን ወረታውና መንበሩ ካሴ ከተባሉ ግብረዓበሮቹ እንዲሁም ከሌሎች ጥቂት የክልሉ ጽንፈኛ ኃይሎች ጋር በመቀናጀትና በህቡዕ በመንቀሳቀስ ታጣቂዎችን ሲመለምል፣ ሲያደራጅና ስምሪት ሲሰጥ እንደነበር መግለጫው ጠቁሟል። ግንባሩን በሀገር ውስጥ ራሱ ሲመራ በውጭ ደግሞ ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ የተባለ ግለሰብ ያስተባብራል ያለው መግለጫው፤ ሁለቱ በፈጠሩት ትስስር በክልሉ የትጥቅ ትግል በማድረግ ሕዝቡን ወደማያባራ ጦርነት ለማስገባት ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውንም የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ማረጋገጡን አመልክቷል፡፡ መሠረቱን ምዕራብ ጎጃም ቡሬና አባይ በረሃ አካባቢ አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰቡ የሃይማኖት ሽፍንና እንደ ከለላ ለመጠቀም ከሌሎች የቡድኑ ታጣቂዎች ጋር ወደ ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ በማቅናት ከሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ በሥላሴ ገዳም አካባቢ ምሽግ ቆፍረው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል በህቡዕ ሲያሴሩ እንደነበር ያመለከተው የግብረ ኃይሉ መግለጫ፤ በተለይ የገዳሙ አስተዳዳሪ የሆኑትን አባ ኤልሳን ለዚህ ሕገወጥ ተግባር ሲጠቀሙ እንደነበር ጠቅሷል፡፡ አስተዳዳሪውም ከሃይማኖቱ አስተምህሮ ውጭ በገዳሙ ውስጥ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ እንዲደረግ ከመፍቀድ ባሻገር ከሌሎች መነኮሳት ጋር በማበርና የጦር መሣሪያ ጭምር በማንገብ ከጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ጋር ተሰማርተው እንደነበርም ጠቁሟል፡፡ መግለጫው አክሎም እነዚህ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን ሕግ የማስከበር ተልዕኮ ለማደናቀፍ በማለም የዜጎችን ሰላማዊ ሕይወት በሚያስተጓጉሉ ቅስቀሳዎችና ተግባራት ተሰማርተው መቆየታቸውን አስታውሷል፡፡ በአማራና በወለጋ አዋሳኝ አካባቢዎችም ግጭት እንዲቀሰቀስ ሲያደርጉ እንደነበርም አመልክቷል፡፡ የጥፋት ቡድኑ አባላት ሕገ ወጥ እንቅስቃሴውን እንዲያቆሙና በውይይት ወደ ሰላም እንዲመጡ ከክልል እስከ ወረዳ በሚገኙ አካላት ተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም አለመሳካቱን የጠቆመው መግለጫው፤ ይልቁንስ ገዳሙን ምሽግ በማድረግ በአካባቢው አስተዳደር፣ በፖሊስ፣በሚሊሻና በማኅበረሰቡ ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት ሲፈጽሙ መቆየታቸውን አስታውቋል፡፡ በሃይማኖት ሽፋን ፖለቲካዊ አጀንዳቸውን ለማስፈጸም እንቅስቃሴ ሲያደርጉ እንደነበር መታወቁንም አመልክቷል፡፡ አነዚህ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ከኅብረተሰቡ ባሕልና ዕሴት እንዲሁም ከሃይማኖታዊ አስተምህሮ ባፈነገጠ መንገድ በደብረ ኤሊያስ ወረዳ በሚገኘው ቅድስት ሥላሴ ገዳም ውስጥ ምሽግ በመቆፈር ሕዝቡ ቅዱስ የሚለውን ሥፍራ የጦር አውድማ በማድረግ ለማርከስ ቢጥሩም በዋናነት የሀገር መከላከያ ሠራዊት እንዲሁም የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በመቀናጀት በወሰዱት ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃ ሴራው መክሸፉን ያስታወቀው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረኃይል፤ በታጣቂዎቹ ጥቅም ላይ ሲውሉ የነበሩ የተለያዩ ከባድና ቀላል መሣሪያዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁሟል፡፡ 200 የጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ታጣቂዎች መደምሰሳቸውነና የቀሩትም ከመማረካቸውና ከመሸሻቸው ውጪ፤ ቡድኑ የሐሰት ፕሮፓጋንዳ በሚነዛባቸው የማኅበራዊ ትስስር ገፆች በመንግሥት ጸጥታ አካላት በገዳሙና በምዕመናን ጉዳት እንዳደረሰ ተደርጎ የሚሠራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል፡፡ የሀገር መከላከያ ሠራዊትና የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በተቀናጀ መንገድ እርምጃ በወሰዱበት በዚህ ሕግ የማስከበር ስምሪት የአካባቢው ማኅበረሰብ መረጃ በመስጠትና በሌሎችም መንገዶች ያደረገው ትብብር የሚደነቅ መሆኑን ያመለከተው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ ለዚህም ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ በቀጣይም ክልሉ ከጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ጸድቶ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲሰፍን ለሚደረገው ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ ኅብረተሰቡ የጋራ ጥረቱንና አጋርነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
ቻይናና ኢትዮጵያ ያሏቸው የባህልና የቋንቋ ልውውጥ ለአገራቱ ግንኙነት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ አለው - በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዥዩዋን
Jun 3, 2023 128
አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ)፦ ቻይናና ኢትዮጵያ ያሏቸው የባህልና የቋንቋ ልውውጥ ለአገራቱ ግንኙነት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዥዩዋን ገለጹ። በቻይና መንግሥት አመቻቺነት በኢትዮጵያ የቻይና ቋንቋን በዩንቨርሲቲ ደረጃ ከሚያጠኑ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም ቻይንኛን አንድ ክፍለ ጊዜ በሚወስዱ ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች ዛሬ በቻይንኛ የተለያዩ የመድረክ ሥራዎችን አቅርበዋል። በመድረኩ ተማሪዎቹ በቻይንኛ ቋንቋ ንግግሮች፣ የቻይንኛ ሙዚቃና ስፖርት እንዲሁም ልዩ ልዩ ትዕይንቶችን በውድድር አሳይተዋል። በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዥዩዋን በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ኢትዮጵያና ቻይና በተለያዩ የትብብር መስኮች ያሏቸው ግንኙነት እየተጠናከረ ነው። ቻይናና ኢትዮጵያ ያሏቸው የባህልና የቋንቋ ልውውጥ ለአገራቱ ግንኙነት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በመድረኩ በትምህርት ሚኒስቴር የዓለም አቀፋዊነትና ስኮላርሺፕ ዴስክ የተወከሉት ተረፈ በላይ በበኩላቸው ሁለቱ አገራት የረዥም ዓመታት ግንኙነት አላቸው ብለዋል። አገራቱ ያላቸው አጋርነት በተለይም በኢኮኖሚ መስክ ወደ ላቀ ደረጃ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። በሁለቱ አገራት ሕዝቦች መካከል የባህል ትስስሩ መጠናከሩ ደግሞ የአገራቱን ሁለንተናዊ አጋርነት ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ነው ያስረዱት። በተለይም ደግሞ በአገራቱ መካከል የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፈጠርና ኢኮኖሚያዊ አጋርነቱን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያደርሰው አብራርተዋል። በመድረኩ ላይ ሲሳተፉ የነበሩት ተማሪዎች በበኩላቸው አንዲህ ያለው ተሞክሮ የሁለቱን አገራት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ያደርሳል ነው ያሉት። ቢሾፍቱ ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምርት ቤት ተማሪ የሆነችው ሲያኔ ታደሰ መርሃ ግብሩ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ለማጠናከር እድል እንደሚሰጥ ጠቁማለች። በተለይም ቻይና አሁን ላይ የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆኗን ገልጻ በመሆኑም የቻይና ቋንቋ ማወቅ በዘርፉ ይበልጥ ተባብሮ ለመሥራት እንደሚያግዝ ተናግራለች። ሌላኛው በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የቻይንኛ ቋንቋ ተማሪ ናፍያድ ንጋቱ ቻይንኛ የሚማሩ ኢትዮጵያዊያን መኖራቸው እንዲሁም አማርኛ የሚማሩ ቻይናውያን መኖራቸው ትስስሩን ያጠናክራል ብሏል። በሁለቱ አገራት መካከል ግንኙነቱን ለማጠናከር የባህል ግንኙነቱ ትልቅ ጥቅም አለው ያለው ደግሞ በሀዋሳ ዩንቨርሲቲ የቻይንኛ ቋንቋ ተማሪ በረከት ደመላሽ ነው።
ሰራዊቱ ብቃቱን የሚያሳድግበት ምቹ አካባቢ በመፍጠር የመፈጸም አቅሙን ለማሳደግ እየተሰራ ነው - ሌተናል ጄነራል ብርሃኑ በቀለ
Jun 3, 2023 78
ባህር ዳር ግንቦት 26/2015((ኢዜአ) :- የአገር መከላከያ ሰራዊት ብቃቱን የሚያሳድግበትና ዝግጁነቱን የሚያጠናክርበት ምቹ አካባቢ በመፍጠር የመፈጸም አቅሙን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ብርሃኑ በቀለ ገለጹ። የመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ በሰሜን ምዕራብ ዕዝ መቀመጫ ያከናወነውን የጥገና እና ግንባታ ስራ አጠናቆ ዛሬ ለዕዙ አስረክቧል። የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ብርሃኑ በቀለ በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንዳሉት የአገር መከላከያ ሰራዊት አገርን የመጠበቅ ሕገ መንግስታዊ ተልዕኮውን ለመወጣት ሁልጊዜም ዝግጁ ነው። አገርን ከማንኛውም ችግር ለመከላከል የሚያስችል በቂ ዝግጅት ለማድረግም ለሰራዊቱ ደረጃውን የጠበቀ የመኖሪያና የመዘጋጃ ካምፕ መገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ሰራዊቱ በሰላም ጊዜ ተረጋግቶ የሚኖርበት፣ በስልጠናዎች ብቃቱን የሚያሳድግበትና ለተልዕኮ ዝግጁነቱን የሚያጠናክርበት ምቹ አካባቢ በመፍጠር የመፈጸም አቅሙን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል። የመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ የዕዙ መቀመጫ የሆነውን መኮድ ካምፕ በማደስና የአጥር ግንባታ ሥራ በማከናወን ምቹ መኖሪያና የስራ ቦታ በማስረከቡ ሌተናል ጄነራል ብርሃኑ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄነራል ደስታ አብቼ በበኩላቸው መምሪያው የሰራዊቱንና የአመራሩን የመፈጸም ብቃት የሚያሳድጉ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዚህም የሬጅመንት፣ የክፍለ ጦር፣ የኮር እና የዕዝ ቢሮዎች፣ መኖሪያዎችንና ሌሎች መጠለያ ካምፖችን በመገንባት መንግስት የሰጠውን ተልዕኮ በመወጣት ላይ መሆኑን አመልክተዋል። ከአገራዊ ለውጡ ወዲህ መምሪያው 48 የውሃ ጉድጓዶችን በአገር ደረጃ በማስቆፈር ሰራዊቱ የሚገለገልባቸው ሆስፒታሎች፣ ካምፖችና መኖሪያ አካባቢዎችን ተጠቃሚ ማድረጉንም ሌተናል ጄኔራል ደስታ የተናገሩት። በመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ የኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ ብርጋዴል ጀኔራል ያደታ አመንቴ በበኩላቸው፣ ከመኮድ ካምፕ እድሳት ስራ በተጨማሪ የአጥር ግንባታ ስራ መከናወኑን ገልጸዋል። የቢሮ ሕንጻ፣ የሎጅስቲክስ ክፍሎች፣ መዝናኛዎች እንዲሁም ለተለያየ አገልግሎት የሚውሉ አዳራሾችና የሰራዊት መኖሪያ ቤቶች ሙሉ እድሳት እንደተደረገላቸው አመልክተዋል። የሰሜን ምዕራብ ዕዝ መኖሪያ እና የመኮድ ካምፕ ጥገናና 7 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የአጥር ግንባታ ስራ በ15 ወራት ጊዜ ውስጥ መከናወኑን በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ ተገልጿል።
መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት ብሩህ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን
Jun 3, 2023 84
አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ)፦ “መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት ብሩህ ነው” ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ። የሁለቱን አገራት ትብብር ሁሉን አቀፍ እና ስትራቴጂካዊ ነውም ብለዋል። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራ ከፍተኛ የመንግስት የልዑካን ቡድን በቅርቡ በቻይና ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጉ ይታወቃል። አቶ ደመቀ ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ከቻይናው ሲ ጂ ቲ ኤን 'ሃይ ቶክ' ከተሰኘው ፕሮግራም ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም የኢትዮጵያ እና የቻይና የሁለትዮሽ ትብብር ጠንካራ እና ወዳጅነት ላይ መሰረት ያደረገ ነው ያሉት አቶ ደመቀ፤ ሁለቱ አገራት ያልተነኩ እድሎችን ለመጠቀም ያላቸው ፍላጎት የወደፊቱን የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ብሩህ እንደሚያደርገው ገልጸዋል። የአገራቱ ግንኙነት ሁሉን አቀፍ፣ ስትራቴጂካዊ እና የጋራ ትብብር ያለው መሆኑ ቻይና ለኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትልሞች ድጋፍ ለማድረግ ጥሩ መሰረት እንደጣለ አመልክተዋል። የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት ከሁለትዮሽ ትብብራቸው ባለፈ የኢኮኖሚ ትስስር ላይ የሚያተኩረው የደቡብ-ደቡብ ትብብር ጽንሰ ሀሳብ ማሳያ ነው ያሉት አቶ ደመቀ ይህም ለተቀረው የአፍሪካ አህጉር የልማት ሕልሞች ምሳሌ እንደሚሆን ተናግረዋል። የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ እና የቻይና-አፍሪካ ትብብር ፎረም(ፎካክ) በአፍሪካ እና ቻይና ትብብር አፍሪካውያን ሰላማዊ እና የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድርግ ሕልማቸውን እንዲያሳኩ የሚያግዙ ማዕቀፎች መሆናቸውን ነው አቶ ደመቀ ያስረዱት። የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኪን ጋንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት እና የቻይና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ አምባሳደር ሹ ቢንግ የሰላም ጥረቶች ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የረጅም ጊዜ ግንኙነት ለማጠናከር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የሰላም ሂደቱን ለማጽናት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን ገልጸው በሰላም ሂደቱ የቻይና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክን ጨምሮ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ሚና እንደምታደንቅ ገልጸዋል። ሌሎችም በአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ መርህ በመመራት ድጋፋቸውን እንዲያደርጉ አቶ ደመቀ ጥሪ ማቅረባቸውን የሲጂቲኤን ዘገባ ያመለክታል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም ከትናንት በስቲያ በውጭ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ መስክ በተከናወኑ አበይት ጉዳዮች ላይ በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በቻይና ያደረጉት ጉብኝት የኢትዮጵያና የቻይና ወዳጅነትና ትብብርን ከፍ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ደመቀ በቆይታቸውም ከቻይና መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከባለሀብቶች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸው ውይይቶቹ የሁለቱን አገራት ግንኙነትና ወዳጅነት የበለጠ ለማጠናከር እድል የፈጠሩ መሆናቸውን አመልክተዋል። አቶ ደመቀ በቻይና ባደረጉት ጉብኝት ከቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኪን ጋንግ፣ከቻይና ምክትል ፕሬዝዳንት ሃን ዤንግ እና ከሌሎች ባለስልጣናት ጋር የሁለትዮሽ እና የባለ ብዙ ወገን ግንኙነታቸውን ትብብራቸውን ማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል። በተጨማሪም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በቤጂንግ የተገነባውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መርቀው መክፈታቸው የሚታወስ ነው።
በኢጋድ ቀጣና ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት እንዲፈጠር በሚደረገው ጥረት ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ጉልህ ድርሻ አላቸው--አምባሳደር መለስ ዓለም
Jun 2, 2023 146
አዲስ አበባ ግንቦት 25/2015(ኢዜአ):-በምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ቀጣና ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር በሚደረገው ጥረት የመገናኛ ብዙኃን ሚና የላቀ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ገለፁ። አምባሳደር መለስ ይህን የገለፁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢጋድ ጋር በመተባበር የፀጥታ እና ደህንነት ጉዳዮች ዘገባዎች እና የመገናኛ ብዙኃን ሚና በሚል ከተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ለተውጣጡ ጋዜጠኞች በተዘጋጀ ሥልጠና ላይ ነው። ቃል አቀባዩ "ለዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት የመገናኛ ብዙኃን ሚና" በሚል የመነሻ ጽሑፍ አቅርበዋል። አምባሳደር መለስ የመገናኛ ብዙኃን በኢጋድ እንደ ቀጣና እና እንደ አገር በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን በማቅረብ አብራርተዋል። የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ምሁሩ ዶክተር ዮናስ አዳዬ የኢጋድ ቀጣና ወቅታዊ የጂኦ ፖለቲካ አዝማሚያ ላይ ያተኮረ ማብራሪያ አቅርበዋል። ዶክተር ዮናስ በገለፃቸው የአፍሪካ ቀንድ የተለያዩ ፍላጎቶች ከሚንፀባረቁባቸው ቀጣናዎች መካከል አንዱ መሆኑን አንስተዋል። መገናኛ ብዙኃን መረጃዎችን ለሕዝብ ከማድረሳቸው አስቀድመው የቀጣናውን ትክክለኛ ገፅታ ከተለያዩ መመዘኛዎች አንፃር መፈተሽ እንዳለባቸው አብራርተዋል። በኢጋድ ክልል ውስጥ የግጭት እና የፀጥታ ጉዳዮች ተፈጥሮ እና ተለዋዋጭነት እንዲሁም በኢትዮጵያ የድህረ ግጭት የሰላም ግንባታን በሚመለከትም ዶክተር ዮናስ ገለፃ አድርገዋል። የሥልጠናው ተሳታፊዎችም የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶችን በማንሳት ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት እንዲፈረም ጠየቁ
Jun 1, 2023 151
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ እንዲፈረም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ጠየቁ ሚኒስትር ዴኤታው ዛሬ በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። አምባሳደር ምስጋኑ በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈረም የሚደረገው ዝግጅት እንዲፋጠን ጠይቀዋል። የሁለቱ አገራት የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በሚጀመርበት ሁኔታ ዙሪያም ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከወዲሁም አስፈላጊ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት እና ለማቋቋም እየተደረገ ያለውን ጥረት የኩዌት መንግስት እንዲደግፍም አምባሳደር ምስጋኑ ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢ በበኩላቸው በሁለቱ ሃገራት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ እንዲፈረም የኩዌት መንግስት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የኩዌት የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባው እንዲጀመር አስፈላጊውን ጥረት እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።
ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
Jun 1, 2023 149
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ):- ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚጠበቅባቸውን ሚና በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ጋር በመተባበር ለአገር ውስጥና ለውጭ ጋዜጠኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና እየሰጠ ነው። ሥልጠናው መገናኛ ብዙኃን ጸጥታና ደኅንነት በማረጋገጥ እንዲሁም ድንበር ዘለል የጸጥታ ሥጋት በመከላከል ሚናቸውን ማጎልበት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ትኩረት አድርጓል ተብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው እንቅስቃሴ ዲፕሎማቶች ብቻ ሳይሆን ጋዜጠኞችም ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። በመሆኑም ጋዜጠኞች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ገልጸው በተለይም ደግሞ ትክክለኛ መረጃዎችን በማሰናዳት ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ጀማላዲን መሃመድ በበኩላቸው ሥልጠናው ጋዜጠኞች በጸጥታ ጉዳዮች ያላቸውን ግንዛቤ ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል። በተለይም በግጭትና በፀጥታ ጉዳዮች ላይ ኃላፊነት በተሞላበት አኳኋን እንዲሰሩ እንዲሁም ትክክለኛና ሚዛናዊ ዘገባዎችን ለማቅረብ አስፈላጊውን እውቀትና ክህሎት ለማዳበር የሚረዳ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የኢጋድ አባል አገራት ድንበር ተሻጋሪ የጸጥታ ሥጋቶችን ለመቅረፍ የአባላትን አቅም ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ጋዜጠኞች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ እንደሚረዳ ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) የጸጥታና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ፤ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና በበርካታ ድንበር ዘለል የጸጥታና ደኅንነት ሥጋቶች ያሉበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም መገናኛ ብዙኃን በቀጠናው የሚያጋጥሙ የጸጥታ፣ ደኅንነትና ወንጀል ሥጋት በአግባቡና በትክክለኛው መንገድ በመገንዘብ ገጽታ የሚገነቡና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስከብሩ ሥራዎችን በትኩረት መሥራት አለባቸው ነው ያሉት። በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ደኅንት ማረጋገጥ ብዙኃኑን ያሳተፈ ሁለገብ ሥራን የሚጠይቅ በመሆኑ በዚህ ረገድ የመገናኛ ብዙኃን የድርሻቸውን ጉልህ ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተጠቁሟል። የመገናኛ ብዙኃን ግጭትን መከላከል ብቻ ሳይሆን በድህረ ግጭት የሰላም ግንባታ እንዲሁም ደግሞ ሰላም በዘላቂነት እንዲረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ነው ያሳሰቡት።
አገራዊ ምክክሩ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት መደላድል የሚፈጥር ነው - የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች
May 31, 2023 155
ድሬዳዋ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ):- አገራዊ የምክክር መድረኩ ብሔራዊ መግባባት በመፍጠርና አንድነትን በማጠናከር የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት መደላድል እንደሚፈጥር የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች ገለጹ። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአገራዊ የምክክር ሂደት ላይ አጀንዳ ለማሰባሰብ ስለሚከናወኑ ተግባራትና የውይይት ተሳታፊዎች ልየታን አስመልክቶ በድሬዳዋ ለሁለት ቀናት ያዘጋጀው ስልጠና ተጠናቋል ። በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች እንዳሉት በአገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው የምክክር መድረክ ብሔራዊ መግባባት የሚፈጥር ወሳኝ የሽግግር ምዕራፍ ነው። ከድሬዳዋ መምህራን ማህበር የመጡት መምህርት ሙሉካ ሁሴን ስልጠናው በቀጣይ በሚካሄደው አገራዊ ምክክር ተሳታፊዎችን የመለየት ሂደት ተአማኒነትና አሳታፊነትን ያሟላ ለማድረግ እንደሚያስችል ገልጸዋል። “በአገር ደረጃ የሚካሄደው የምክክር መድረክ በዜጎች መካከል መቀራረብ እና አንድነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ከፍታ ለማረጋገጥ ያስችላል” ብለዋል። አገራዊ የምክክር መድረክ አገራዊ መግባባት ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የድሬዳዋ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ዮናስ በትሩ ናቸው። በሰከነ መንፈስ መወያየት ለአገር ዘላቂ ሰላምና እድገት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንና የጋራ ምክር ቤቱ በቀጣይ የሚካሄዱ የምክክር ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ ይሰራል ብለዋል። የድሬዳዋ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ጥምረት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አንድነት ዘነበ "ኢትዮያዊያን የሚያካሂዱት ምክክር አገራዊ አንድነትን ለማጠናከር መሰረት የሚጥል ነው" ብለዋል። የምክክር መድረኩ ኢትዮጵያዊያን በራሳቸው አጀንዳዎች ላይ መግባባት የሚፈጥሩበት ብቻ ሳይሆን አንድነትና አቅም መፍጠር የሚያስችላቸው መሆኑን አመልክተዋል። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር እንዳሉት ኮሚሽኑ በሚያከናውነው የተሳታፊዎች ልየታ የተለያዩ ተቋማት እና ባለድርሻ አካላት የሂደቱን ግልጸኝነት ፣አሳታፊነትና ተአማኒነት የመታዘብና የማረጋገጥ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። የምክክር መድረኩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጨምሮ ሁሉንም የሚያሳትፍ በመሆኑ ብሔራዊ መግባባት በመፍጠር ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። በሰከነ መንገድ በመወያየት የጋራ አገራዊ መግባባት በመፍጠር ኢትዮጵያን ለማሻገር እንደሚያስችል አመልክተዋል።
ፖለቲካ
በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም መሽገው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩት እስክንድር ነጋና ግብረዓበሮቹ ላይ በተወሰደው እርምጃ ክልሉን የማተራመስ ሴራቸው መክሸፉን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ
Jun 3, 2023 94
በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም መሽገው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩት እስክንድር ነጋና ግብረዓበሮቹ ላይ በተወሰደው እርምጃ ክልሉን የማተራመስ ሴራቸው መክሸፉን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ)፦ በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ የሚገኘውን የሥላሴ ገዳም ከለላ በማድረግ መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ላይ በተወሰደው እርምጅ በእስክንድር ነጋና በግብረዓበሮቹ ለውጊያ ሲውል የነበረው ምሽግ መሰበሩንና በ200 ታጣቂዎችም ላይ እርምጃ መወሰዱን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡ የታጣቂ ቡድኑ መሪና አስተባባሪ የነበረው እስክንድር ነጋና ጥቂት ግብረዓበሮቹ ከአካባቢው ለመሰወር ቢሞክሩም በዋናነት የመከላከያ ሠራዊት እንዲሁም የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ለማዋል እግር በእግር በመከታተል የተቀናጀ ኦፕሬሽን እያካሄዱ መሆኑንም ግብረ ኃይሉ ገልጿል፡፡ የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ፤ ባልደራስ በሚል የፖለቲካ ፓርቲ ሽፋን ሲንቀሳቀስ የቆየው እስክንድር ነጋ የተባለው ግለሰብ የሐሳብ የበላይነትን በማረጋገጥ ዓላማውን ማሳካት ሲሳነው በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ጊዜያት ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲሞክር እንደነበር አስታውሷል፡፡ ግለሰቡ ይህ እንዳልተሳካለት ሲያውቅ፤ መንግሥትን በኃይል ለመጣል በማቀድ የአማራ ሕዝባዊ ግንባር የተባለ አደረጃጀት በመፍጠር ሽመልስ ስማቸው፣ ሰውመሆን ወረታውና መንበሩ ካሴ ከተባሉ ግብረዓበሮቹ እንዲሁም ከሌሎች ጥቂት የክልሉ ጽንፈኛ ኃይሎች ጋር በመቀናጀትና በህቡዕ በመንቀሳቀስ ታጣቂዎችን ሲመለምል፣ ሲያደራጅና ስምሪት ሲሰጥ እንደነበር መግለጫው ጠቁሟል። ግንባሩን በሀገር ውስጥ ራሱ ሲመራ በውጭ ደግሞ ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ የተባለ ግለሰብ ያስተባብራል ያለው መግለጫው፤ ሁለቱ በፈጠሩት ትስስር በክልሉ የትጥቅ ትግል በማድረግ ሕዝቡን ወደማያባራ ጦርነት ለማስገባት ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውንም የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ማረጋገጡን አመልክቷል፡፡ መሠረቱን ምዕራብ ጎጃም ቡሬና አባይ በረሃ አካባቢ አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰቡ የሃይማኖት ሽፍንና እንደ ከለላ ለመጠቀም ከሌሎች የቡድኑ ታጣቂዎች ጋር ወደ ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ በማቅናት ከሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ በሥላሴ ገዳም አካባቢ ምሽግ ቆፍረው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል በህቡዕ ሲያሴሩ እንደነበር ያመለከተው የግብረ ኃይሉ መግለጫ፤ በተለይ የገዳሙ አስተዳዳሪ የሆኑትን አባ ኤልሳን ለዚህ ሕገወጥ ተግባር ሲጠቀሙ እንደነበር ጠቅሷል፡፡ አስተዳዳሪውም ከሃይማኖቱ አስተምህሮ ውጭ በገዳሙ ውስጥ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ እንዲደረግ ከመፍቀድ ባሻገር ከሌሎች መነኮሳት ጋር በማበርና የጦር መሣሪያ ጭምር በማንገብ ከጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ጋር ተሰማርተው እንደነበርም ጠቁሟል፡፡ መግለጫው አክሎም እነዚህ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን ሕግ የማስከበር ተልዕኮ ለማደናቀፍ በማለም የዜጎችን ሰላማዊ ሕይወት በሚያስተጓጉሉ ቅስቀሳዎችና ተግባራት ተሰማርተው መቆየታቸውን አስታውሷል፡፡ በአማራና በወለጋ አዋሳኝ አካባቢዎችም ግጭት እንዲቀሰቀስ ሲያደርጉ እንደነበርም አመልክቷል፡፡ የጥፋት ቡድኑ አባላት ሕገ ወጥ እንቅስቃሴውን እንዲያቆሙና በውይይት ወደ ሰላም እንዲመጡ ከክልል እስከ ወረዳ በሚገኙ አካላት ተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም አለመሳካቱን የጠቆመው መግለጫው፤ ይልቁንስ ገዳሙን ምሽግ በማድረግ በአካባቢው አስተዳደር፣ በፖሊስ፣በሚሊሻና በማኅበረሰቡ ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት ሲፈጽሙ መቆየታቸውን አስታውቋል፡፡ በሃይማኖት ሽፋን ፖለቲካዊ አጀንዳቸውን ለማስፈጸም እንቅስቃሴ ሲያደርጉ እንደነበር መታወቁንም አመልክቷል፡፡ አነዚህ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ከኅብረተሰቡ ባሕልና ዕሴት እንዲሁም ከሃይማኖታዊ አስተምህሮ ባፈነገጠ መንገድ በደብረ ኤሊያስ ወረዳ በሚገኘው ቅድስት ሥላሴ ገዳም ውስጥ ምሽግ በመቆፈር ሕዝቡ ቅዱስ የሚለውን ሥፍራ የጦር አውድማ በማድረግ ለማርከስ ቢጥሩም በዋናነት የሀገር መከላከያ ሠራዊት እንዲሁም የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በመቀናጀት በወሰዱት ጥንቃቄ የተሞላበት እርምጃ ሴራው መክሸፉን ያስታወቀው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረኃይል፤ በታጣቂዎቹ ጥቅም ላይ ሲውሉ የነበሩ የተለያዩ ከባድና ቀላል መሣሪያዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁሟል፡፡ 200 የጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ታጣቂዎች መደምሰሳቸውነና የቀሩትም ከመማረካቸውና ከመሸሻቸው ውጪ፤ ቡድኑ የሐሰት ፕሮፓጋንዳ በሚነዛባቸው የማኅበራዊ ትስስር ገፆች በመንግሥት ጸጥታ አካላት በገዳሙና በምዕመናን ጉዳት እንዳደረሰ ተደርጎ የሚሠራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል፡፡ የሀገር መከላከያ ሠራዊትና የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በተቀናጀ መንገድ እርምጃ በወሰዱበት በዚህ ሕግ የማስከበር ስምሪት የአካባቢው ማኅበረሰብ መረጃ በመስጠትና በሌሎችም መንገዶች ያደረገው ትብብር የሚደነቅ መሆኑን ያመለከተው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ ለዚህም ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ በቀጣይም ክልሉ ከጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ጸድቶ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲሰፍን ለሚደረገው ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ ኅብረተሰቡ የጋራ ጥረቱንና አጋርነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
ቻይናና ኢትዮጵያ ያሏቸው የባህልና የቋንቋ ልውውጥ ለአገራቱ ግንኙነት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ አለው - በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዥዩዋን
Jun 3, 2023 128
አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ)፦ ቻይናና ኢትዮጵያ ያሏቸው የባህልና የቋንቋ ልውውጥ ለአገራቱ ግንኙነት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዥዩዋን ገለጹ። በቻይና መንግሥት አመቻቺነት በኢትዮጵያ የቻይና ቋንቋን በዩንቨርሲቲ ደረጃ ከሚያጠኑ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም ቻይንኛን አንድ ክፍለ ጊዜ በሚወስዱ ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች ዛሬ በቻይንኛ የተለያዩ የመድረክ ሥራዎችን አቅርበዋል። በመድረኩ ተማሪዎቹ በቻይንኛ ቋንቋ ንግግሮች፣ የቻይንኛ ሙዚቃና ስፖርት እንዲሁም ልዩ ልዩ ትዕይንቶችን በውድድር አሳይተዋል። በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዥዩዋን በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ኢትዮጵያና ቻይና በተለያዩ የትብብር መስኮች ያሏቸው ግንኙነት እየተጠናከረ ነው። ቻይናና ኢትዮጵያ ያሏቸው የባህልና የቋንቋ ልውውጥ ለአገራቱ ግንኙነት መጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በመድረኩ በትምህርት ሚኒስቴር የዓለም አቀፋዊነትና ስኮላርሺፕ ዴስክ የተወከሉት ተረፈ በላይ በበኩላቸው ሁለቱ አገራት የረዥም ዓመታት ግንኙነት አላቸው ብለዋል። አገራቱ ያላቸው አጋርነት በተለይም በኢኮኖሚ መስክ ወደ ላቀ ደረጃ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። በሁለቱ አገራት ሕዝቦች መካከል የባህል ትስስሩ መጠናከሩ ደግሞ የአገራቱን ሁለንተናዊ አጋርነት ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ነው ያስረዱት። በተለይም ደግሞ በአገራቱ መካከል የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፈጠርና ኢኮኖሚያዊ አጋርነቱን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያደርሰው አብራርተዋል። በመድረኩ ላይ ሲሳተፉ የነበሩት ተማሪዎች በበኩላቸው አንዲህ ያለው ተሞክሮ የሁለቱን አገራት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ያደርሳል ነው ያሉት። ቢሾፍቱ ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምርት ቤት ተማሪ የሆነችው ሲያኔ ታደሰ መርሃ ግብሩ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ለማጠናከር እድል እንደሚሰጥ ጠቁማለች። በተለይም ቻይና አሁን ላይ የኢንዱስትሪ ማዕከል መሆኗን ገልጻ በመሆኑም የቻይና ቋንቋ ማወቅ በዘርፉ ይበልጥ ተባብሮ ለመሥራት እንደሚያግዝ ተናግራለች። ሌላኛው በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የቻይንኛ ቋንቋ ተማሪ ናፍያድ ንጋቱ ቻይንኛ የሚማሩ ኢትዮጵያዊያን መኖራቸው እንዲሁም አማርኛ የሚማሩ ቻይናውያን መኖራቸው ትስስሩን ያጠናክራል ብሏል። በሁለቱ አገራት መካከል ግንኙነቱን ለማጠናከር የባህል ግንኙነቱ ትልቅ ጥቅም አለው ያለው ደግሞ በሀዋሳ ዩንቨርሲቲ የቻይንኛ ቋንቋ ተማሪ በረከት ደመላሽ ነው።
ሰራዊቱ ብቃቱን የሚያሳድግበት ምቹ አካባቢ በመፍጠር የመፈጸም አቅሙን ለማሳደግ እየተሰራ ነው - ሌተናል ጄነራል ብርሃኑ በቀለ
Jun 3, 2023 78
ባህር ዳር ግንቦት 26/2015((ኢዜአ) :- የአገር መከላከያ ሰራዊት ብቃቱን የሚያሳድግበትና ዝግጁነቱን የሚያጠናክርበት ምቹ አካባቢ በመፍጠር የመፈጸም አቅሙን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ብርሃኑ በቀለ ገለጹ። የመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ በሰሜን ምዕራብ ዕዝ መቀመጫ ያከናወነውን የጥገና እና ግንባታ ስራ አጠናቆ ዛሬ ለዕዙ አስረክቧል። የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ብርሃኑ በቀለ በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንዳሉት የአገር መከላከያ ሰራዊት አገርን የመጠበቅ ሕገ መንግስታዊ ተልዕኮውን ለመወጣት ሁልጊዜም ዝግጁ ነው። አገርን ከማንኛውም ችግር ለመከላከል የሚያስችል በቂ ዝግጅት ለማድረግም ለሰራዊቱ ደረጃውን የጠበቀ የመኖሪያና የመዘጋጃ ካምፕ መገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም ሰራዊቱ በሰላም ጊዜ ተረጋግቶ የሚኖርበት፣ በስልጠናዎች ብቃቱን የሚያሳድግበትና ለተልዕኮ ዝግጁነቱን የሚያጠናክርበት ምቹ አካባቢ በመፍጠር የመፈጸም አቅሙን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል። የመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ የዕዙ መቀመጫ የሆነውን መኮድ ካምፕ በማደስና የአጥር ግንባታ ሥራ በማከናወን ምቹ መኖሪያና የስራ ቦታ በማስረከቡ ሌተናል ጄነራል ብርሃኑ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄነራል ደስታ አብቼ በበኩላቸው መምሪያው የሰራዊቱንና የአመራሩን የመፈጸም ብቃት የሚያሳድጉ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዚህም የሬጅመንት፣ የክፍለ ጦር፣ የኮር እና የዕዝ ቢሮዎች፣ መኖሪያዎችንና ሌሎች መጠለያ ካምፖችን በመገንባት መንግስት የሰጠውን ተልዕኮ በመወጣት ላይ መሆኑን አመልክተዋል። ከአገራዊ ለውጡ ወዲህ መምሪያው 48 የውሃ ጉድጓዶችን በአገር ደረጃ በማስቆፈር ሰራዊቱ የሚገለገልባቸው ሆስፒታሎች፣ ካምፖችና መኖሪያ አካባቢዎችን ተጠቃሚ ማድረጉንም ሌተናል ጄኔራል ደስታ የተናገሩት። በመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ የኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ ብርጋዴል ጀኔራል ያደታ አመንቴ በበኩላቸው፣ ከመኮድ ካምፕ እድሳት ስራ በተጨማሪ የአጥር ግንባታ ስራ መከናወኑን ገልጸዋል። የቢሮ ሕንጻ፣ የሎጅስቲክስ ክፍሎች፣ መዝናኛዎች እንዲሁም ለተለያየ አገልግሎት የሚውሉ አዳራሾችና የሰራዊት መኖሪያ ቤቶች ሙሉ እድሳት እንደተደረገላቸው አመልክተዋል። የሰሜን ምዕራብ ዕዝ መኖሪያ እና የመኮድ ካምፕ ጥገናና 7 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የአጥር ግንባታ ስራ በ15 ወራት ጊዜ ውስጥ መከናወኑን በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ ተገልጿል።
መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት ብሩህ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን
Jun 3, 2023 84
አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ)፦ “መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት ብሩህ ነው” ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ። የሁለቱን አገራት ትብብር ሁሉን አቀፍ እና ስትራቴጂካዊ ነውም ብለዋል። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራ ከፍተኛ የመንግስት የልዑካን ቡድን በቅርቡ በቻይና ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጉ ይታወቃል። አቶ ደመቀ ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ከቻይናው ሲ ጂ ቲ ኤን 'ሃይ ቶክ' ከተሰኘው ፕሮግራም ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም የኢትዮጵያ እና የቻይና የሁለትዮሽ ትብብር ጠንካራ እና ወዳጅነት ላይ መሰረት ያደረገ ነው ያሉት አቶ ደመቀ፤ ሁለቱ አገራት ያልተነኩ እድሎችን ለመጠቀም ያላቸው ፍላጎት የወደፊቱን የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ብሩህ እንደሚያደርገው ገልጸዋል። የአገራቱ ግንኙነት ሁሉን አቀፍ፣ ስትራቴጂካዊ እና የጋራ ትብብር ያለው መሆኑ ቻይና ለኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትልሞች ድጋፍ ለማድረግ ጥሩ መሰረት እንደጣለ አመልክተዋል። የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት ከሁለትዮሽ ትብብራቸው ባለፈ የኢኮኖሚ ትስስር ላይ የሚያተኩረው የደቡብ-ደቡብ ትብብር ጽንሰ ሀሳብ ማሳያ ነው ያሉት አቶ ደመቀ ይህም ለተቀረው የአፍሪካ አህጉር የልማት ሕልሞች ምሳሌ እንደሚሆን ተናግረዋል። የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ እና የቻይና-አፍሪካ ትብብር ፎረም(ፎካክ) በአፍሪካ እና ቻይና ትብብር አፍሪካውያን ሰላማዊ እና የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድርግ ሕልማቸውን እንዲያሳኩ የሚያግዙ ማዕቀፎች መሆናቸውን ነው አቶ ደመቀ ያስረዱት። የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኪን ጋንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት እና የቻይና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ አምባሳደር ሹ ቢንግ የሰላም ጥረቶች ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የረጅም ጊዜ ግንኙነት ለማጠናከር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ የሰላም ሂደቱን ለማጽናት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን ገልጸው በሰላም ሂደቱ የቻይና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክን ጨምሮ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ሚና እንደምታደንቅ ገልጸዋል። ሌሎችም በአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ መርህ በመመራት ድጋፋቸውን እንዲያደርጉ አቶ ደመቀ ጥሪ ማቅረባቸውን የሲጂቲኤን ዘገባ ያመለክታል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም ከትናንት በስቲያ በውጭ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ መስክ በተከናወኑ አበይት ጉዳዮች ላይ በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በቻይና ያደረጉት ጉብኝት የኢትዮጵያና የቻይና ወዳጅነትና ትብብርን ከፍ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ደመቀ በቆይታቸውም ከቻይና መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከባለሀብቶች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸው ውይይቶቹ የሁለቱን አገራት ግንኙነትና ወዳጅነት የበለጠ ለማጠናከር እድል የፈጠሩ መሆናቸውን አመልክተዋል። አቶ ደመቀ በቻይና ባደረጉት ጉብኝት ከቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኪን ጋንግ፣ከቻይና ምክትል ፕሬዝዳንት ሃን ዤንግ እና ከሌሎች ባለስልጣናት ጋር የሁለትዮሽ እና የባለ ብዙ ወገን ግንኙነታቸውን ትብብራቸውን ማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል። በተጨማሪም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በቤጂንግ የተገነባውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መርቀው መክፈታቸው የሚታወስ ነው።
በኢጋድ ቀጣና ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት እንዲፈጠር በሚደረገው ጥረት ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ጉልህ ድርሻ አላቸው--አምባሳደር መለስ ዓለም
Jun 2, 2023 146
አዲስ አበባ ግንቦት 25/2015(ኢዜአ):-በምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ቀጣና ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር በሚደረገው ጥረት የመገናኛ ብዙኃን ሚና የላቀ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ገለፁ። አምባሳደር መለስ ይህን የገለፁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢጋድ ጋር በመተባበር የፀጥታ እና ደህንነት ጉዳዮች ዘገባዎች እና የመገናኛ ብዙኃን ሚና በሚል ከተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ለተውጣጡ ጋዜጠኞች በተዘጋጀ ሥልጠና ላይ ነው። ቃል አቀባዩ "ለዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት የመገናኛ ብዙኃን ሚና" በሚል የመነሻ ጽሑፍ አቅርበዋል። አምባሳደር መለስ የመገናኛ ብዙኃን በኢጋድ እንደ ቀጣና እና እንደ አገር በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን በማቅረብ አብራርተዋል። የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ምሁሩ ዶክተር ዮናስ አዳዬ የኢጋድ ቀጣና ወቅታዊ የጂኦ ፖለቲካ አዝማሚያ ላይ ያተኮረ ማብራሪያ አቅርበዋል። ዶክተር ዮናስ በገለፃቸው የአፍሪካ ቀንድ የተለያዩ ፍላጎቶች ከሚንፀባረቁባቸው ቀጣናዎች መካከል አንዱ መሆኑን አንስተዋል። መገናኛ ብዙኃን መረጃዎችን ለሕዝብ ከማድረሳቸው አስቀድመው የቀጣናውን ትክክለኛ ገፅታ ከተለያዩ መመዘኛዎች አንፃር መፈተሽ እንዳለባቸው አብራርተዋል። በኢጋድ ክልል ውስጥ የግጭት እና የፀጥታ ጉዳዮች ተፈጥሮ እና ተለዋዋጭነት እንዲሁም በኢትዮጵያ የድህረ ግጭት የሰላም ግንባታን በሚመለከትም ዶክተር ዮናስ ገለፃ አድርገዋል። የሥልጠናው ተሳታፊዎችም የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶችን በማንሳት ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት እንዲፈረም ጠየቁ
Jun 1, 2023 151
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ እንዲፈረም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ጠየቁ ሚኒስትር ዴኤታው ዛሬ በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። አምባሳደር ምስጋኑ በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ እና በኩዌት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈረም የሚደረገው ዝግጅት እንዲፋጠን ጠይቀዋል። የሁለቱ አገራት የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በሚጀመርበት ሁኔታ ዙሪያም ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከወዲሁም አስፈላጊ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት እና ለማቋቋም እየተደረገ ያለውን ጥረት የኩዌት መንግስት እንዲደግፍም አምባሳደር ምስጋኑ ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢ በበኩላቸው በሁለቱ ሃገራት መካከል የሰራተኛ ስምሪት ስምምነት በአጭር ጊዜ እንዲፈረም የኩዌት መንግስት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የኩዌት የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባው እንዲጀመር አስፈላጊውን ጥረት እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።
ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
Jun 1, 2023 149
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015 (ኢዜአ):- ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚጠበቅባቸውን ሚና በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ጋር በመተባበር ለአገር ውስጥና ለውጭ ጋዜጠኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና እየሰጠ ነው። ሥልጠናው መገናኛ ብዙኃን ጸጥታና ደኅንነት በማረጋገጥ እንዲሁም ድንበር ዘለል የጸጥታ ሥጋት በመከላከል ሚናቸውን ማጎልበት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ትኩረት አድርጓል ተብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር በሚደረገው እንቅስቃሴ ዲፕሎማቶች ብቻ ሳይሆን ጋዜጠኞችም ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል። በመሆኑም ጋዜጠኞች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ገልጸው በተለይም ደግሞ ትክክለኛ መረጃዎችን በማሰናዳት ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት። የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ጀማላዲን መሃመድ በበኩላቸው ሥልጠናው ጋዜጠኞች በጸጥታ ጉዳዮች ያላቸውን ግንዛቤ ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል። በተለይም በግጭትና በፀጥታ ጉዳዮች ላይ ኃላፊነት በተሞላበት አኳኋን እንዲሰሩ እንዲሁም ትክክለኛና ሚዛናዊ ዘገባዎችን ለማቅረብ አስፈላጊውን እውቀትና ክህሎት ለማዳበር የሚረዳ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም የኢጋድ አባል አገራት ድንበር ተሻጋሪ የጸጥታ ሥጋቶችን ለመቅረፍ የአባላትን አቅም ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ጋዜጠኞች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ እንደሚረዳ ገልጸዋል። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) የጸጥታና ደኅንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ፤ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና በበርካታ ድንበር ዘለል የጸጥታና ደኅንነት ሥጋቶች ያሉበት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም መገናኛ ብዙኃን በቀጠናው የሚያጋጥሙ የጸጥታ፣ ደኅንነትና ወንጀል ሥጋት በአግባቡና በትክክለኛው መንገድ በመገንዘብ ገጽታ የሚገነቡና ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስከብሩ ሥራዎችን በትኩረት መሥራት አለባቸው ነው ያሉት። በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ደኅንት ማረጋገጥ ብዙኃኑን ያሳተፈ ሁለገብ ሥራን የሚጠይቅ በመሆኑ በዚህ ረገድ የመገናኛ ብዙኃን የድርሻቸውን ጉልህ ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተጠቁሟል። የመገናኛ ብዙኃን ግጭትን መከላከል ብቻ ሳይሆን በድህረ ግጭት የሰላም ግንባታ እንዲሁም ደግሞ ሰላም በዘላቂነት እንዲረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ነው ያሳሰቡት።
አገራዊ ምክክሩ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት መደላድል የሚፈጥር ነው - የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች
May 31, 2023 155
ድሬዳዋ ግንቦት 23/2015 (ኢዜአ):- አገራዊ የምክክር መድረኩ ብሔራዊ መግባባት በመፍጠርና አንድነትን በማጠናከር የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት መደላድል እንደሚፈጥር የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች ገለጹ። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአገራዊ የምክክር ሂደት ላይ አጀንዳ ለማሰባሰብ ስለሚከናወኑ ተግባራትና የውይይት ተሳታፊዎች ልየታን አስመልክቶ በድሬዳዋ ለሁለት ቀናት ያዘጋጀው ስልጠና ተጠናቋል ። በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የድሬዳዋ ሕብረተሰብ ተወካዮች እንዳሉት በአገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው የምክክር መድረክ ብሔራዊ መግባባት የሚፈጥር ወሳኝ የሽግግር ምዕራፍ ነው። ከድሬዳዋ መምህራን ማህበር የመጡት መምህርት ሙሉካ ሁሴን ስልጠናው በቀጣይ በሚካሄደው አገራዊ ምክክር ተሳታፊዎችን የመለየት ሂደት ተአማኒነትና አሳታፊነትን ያሟላ ለማድረግ እንደሚያስችል ገልጸዋል። “በአገር ደረጃ የሚካሄደው የምክክር መድረክ በዜጎች መካከል መቀራረብ እና አንድነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ከፍታ ለማረጋገጥ ያስችላል” ብለዋል። አገራዊ የምክክር መድረክ አገራዊ መግባባት ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የድሬዳዋ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ዮናስ በትሩ ናቸው። በሰከነ መንፈስ መወያየት ለአገር ዘላቂ ሰላምና እድገት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንና የጋራ ምክር ቤቱ በቀጣይ የሚካሄዱ የምክክር ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ ይሰራል ብለዋል። የድሬዳዋ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ጥምረት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አንድነት ዘነበ "ኢትዮያዊያን የሚያካሂዱት ምክክር አገራዊ አንድነትን ለማጠናከር መሰረት የሚጥል ነው" ብለዋል። የምክክር መድረኩ ኢትዮጵያዊያን በራሳቸው አጀንዳዎች ላይ መግባባት የሚፈጥሩበት ብቻ ሳይሆን አንድነትና አቅም መፍጠር የሚያስችላቸው መሆኑን አመልክተዋል። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር መሐሙድ ድሪር እንዳሉት ኮሚሽኑ በሚያከናውነው የተሳታፊዎች ልየታ የተለያዩ ተቋማት እና ባለድርሻ አካላት የሂደቱን ግልጸኝነት ፣አሳታፊነትና ተአማኒነት የመታዘብና የማረጋገጥ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። የምክክር መድረኩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጨምሮ ሁሉንም የሚያሳትፍ በመሆኑ ብሔራዊ መግባባት በመፍጠር ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል። በሰከነ መንገድ በመወያየት የጋራ አገራዊ መግባባት በመፍጠር ኢትዮጵያን ለማሻገር እንደሚያስችል አመልክተዋል።
ማህበራዊ
በአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ሰልጠና ላይ የሚገኙ እጩ የፖሊስ መኮንኖች በደብረ ማርቆስ ከተማ ለአቅመ ደካሞች ቤት ገንብተው አስረከቡ
Jun 4, 2023 26
ደብረ ማርቆስ ግንቦት 27/2015 (ኢዜአ) በአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ሰልጠና ላይ የሚገኙ እጩ የፖሊስ መኮንኖች በደብረ ማርቆስ ከተማ ለሶስት አቅመ ደካሞች ቤት ገንብተው አስረከቡ። የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ተወካይ ረዳት ኮሚሽነር አበበ ደለለ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ህዝባዊነትን የተላበሰ ፖሊስ የህብረተሰቡን ደህንነት ከመጠበቅ ባሻገር በሰብአዊነት ተሳትፎ የማድረግ ሃላፊነት አለበት። በኮሌጁ የሚሰለጥኑ የፖሊስ እጩ መኮንኖች ካላቸው በማዋጣት የማህበረሰብን ችግር ሊቀርፉ የሚችሉ የልማት ስራዎችን መስራታቸውን በማሳያነት ገልጸዋል። ሰልጣኞቹ ካላቸው በማዋጣት በደብረ ማርቆስ ከተማ ሶስት ቤቶችን ገንብተው በማስረከብ አቅመ ደካማ ግለሰቦች ተጠቃሚ እንዲሆኑ መስራታቸውን ተናግረዋል። ቤቶቹ ከ100 ሺህ ብር በላይ ወጭ እንደተደረገባቸው የገለጹ ሲሆን ሰልጣኞቹ በጉልበታቸውና በእውቀታቸው አስተዋጽኦ አበርክተዋል ነው ያሉት። የፖሊስ እጩ መኮንኖቹ ከዚህ በተጨማሪም የደብረ ማርቆስ ከተማ ጽዳትና ውበት በመጠበቅ በኩል ጉልህ ሚና እየተጨዋቱ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል። በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የመንቆረር ክፍለ ከተማ ዋና ስራአስኪያጅ አቶ አስታራቂ መኩሪያው እንዳሉት እጩ የፖሊስ መኮንኖች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ሰዎችን መኖሪያ ቤት ግንባታና እድሳት ላይ እየተሳተፉ ነው። ከፍለ ከተማውም በበጀት ዓመቱ ህብረተሰቡን በማስተባበር ከ4 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ ከ60 በላይ ቤቶች በማስገንባት አሁን ላይ ለተጠቃሚዎች ለማስተላለፍ በዝግጅት ላይ መሆኑን ተናግረዋል። እጬ መኮንን አስቻል ኪዳኔ፣ ''ከምናገኛት ቀንሰን ለችግረኛ ግለሰቦች ቤት መስራታችን የህዝብ ልጆች መሆናችንን ለማሳየት ነው'' ብሏል። በቀጣይም በኮሌጁ እስካሉ ድረስ የአካባቢውን ህብረተሰብ ችግር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግሯል። እጩ መኮንን አብዱ ባልዲቾም እንዲሁ የአቅመ ደካሞችን እና የችግረኞችን ቤት መገንባት ከፍተኛ የአእምሮ እርካታን የሚፈጥር ነው ብሏል። አሁን የተገነቡት ቤቶች መጀመሪያቸው እንጂ መጨረሻ እንዳልሆነ ገልጸው ለወደፊትም የማህበረሰብ አገልግሎታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድቷል።
የኢትዮጵያን መስህቦች የማልማት፣ የመጠበቅና የማስተዋወቅ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው- ቱሪዝም ሚኒስቴር
Jun 4, 2023 33
አዲስ አበባ ግንቦት 27/2015(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያን መስህቦች በተለያዩ አማራጮች የማልማት፣ የመጠበቅና የማስተዋወቅ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር ገለጸ። "ላሊበላ በእምነት የታነፀ" በሚል መሪ ሀሳብ የላልይበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ የቋሚ ዐውደ ርዕይ በላልይበላ ከተማ ተከፍቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ፤ በቱሪስት መዳረሻ ታሪካዊ ቅርሶች ዙሪያ ዕሴት የሚጨምሩ ተግባራትን በማከናወን ተወዳዳሪ መዳረሻነት እና ማህበራዊ አቀፍ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም በእንጦጦ ፓርክ የላልይበላ ቨርቹዋል ሪያሊታ ዐውደ ርዕይ ተከፍቶ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መጎብኝታቸውን አስታውሰው በላልይበላ ደግሞ ተመሳሳይ አውደ ርእይ መከፈቱን ጠቅሰዋል። በዩኔስኮ የተመዘገቡ የዓለም ቅርሶችን ማልማትና መጠበቅ ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ገልጸው የላልይበላ አብያተ ክርስቲያናትን የመጠበቅና የቱሪስት መዳረሻነቱን የማልማትና የማሳደግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን መስህቦች የማልማት፣ የመጠበቅና የማስተዋወቅ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትር ዴኤታው የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች፣ የጎንደርና የጅማ አባጅፋር አብያተ መንግስታት ዕድሳትንም ለአብነት ጠቅሰዋል። በዘርፉ አቅም ለመገንባት የሰው ኃይል ስልጠና፣ የቱሪስት አገልግሎት ጥራት ለማሻሻል የሆቴልና ቱሪዝም ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል። በላሊበላ የተለመዱ የቱሪዝም ሀብቶችን ማሳየት ብቻ ሳይሆን የጎብኝዎችን ቆይታ የሚያራዝም የጉብኝት ፓኬጅ በመቅረፅና እሴት በመጨመር ተወዳዳሪ የቱሪስት መዳረሻ ማድረግ የሚያስችልና አካባቢያዊ ተጠቃሚነትን የሚያሳድግ በፈረንሳይ መንግስት ድጋፍ 'የላሊበላ ዘላቂ ፕሮጀክት' እየተተገበረ መሆኑንም አንስተዋል። የጊዜ ገደቡ ለመጠናቀቅ አንድ ዓመት ብቻ የቀረው የዘላቂ ልማት ፕሮጀክት ቀጣይ ምዕራፍ እንዲኖረውም ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር ሕይወት ኃይሉ፤ ቅርሶች ታሪክን ለመዘከር፣ ተፈጥሮና አካባቢን ለመረዳት ፣የመረጃ ምንጭ በመሆንና የገቢ ምንጭነታቸው የማይተካ ሚና አላቸው ብለዋል። ባለስልጣኑ ቅርሶች ለታሪክ ምስክርነት እንዲውሉ ወደ ትውልድ ማስተላለፍ፣ ከጉዳት የመጠበቅ፣ የማጥናትና ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ጥቅማቸውን የማሳደግና ተደራሽ የማድረግ ስራዎችን ከባለድርሻ አካላት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። በፈረንሳይ ልማት ኤጄንሲ ድጋፍ በ22 የትኩረት መስኮች ተለይቶ የሚሰራው 'የላልይበላ ዘላቂ ልማት' ፕሮጀክት ትግበራም ጥሩ ደረጃ ላይ እንደሆነ ተናግረዋል። የላሊበላ ቋሚ ዐውደ ርዕይ ኢትዮጵያን ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል የሚፈጥርና የጎብኚዎችን ቆይታ የሚያራዝም መሆኑን ገልፀው፣ በቀጣይም በሌሎች ቦታዎችም ይከፈታል ብለዋል። የቅርስ መጠበቅና መንከባከብ የዜግነት ኃላፊነት ነው ያሉት ምክትል ዳይሬክተሯ፣ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን ዕድሳትና ጥገና እንዲሁም የቅርሶችን ጊዜያዊ መጠለያ የማንሳት ስራዎች በጥንቃቄ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኤምባሲ ተወካይና የኤምባሲው የባህል ካውንስለር ሶፊ ማካሜ፣ ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ የዘለቀው የኢትዮ ፈረንሳይ ወዳጅነትና ትብብር በታሪካዊ ቅርሶች ዘርፍ ቅድሚያ በመስጠት በታሪካዊ ዲፕሎማሲ ዘርፍ ተጨባጭ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ኢኒሼቲቭ ወደ ትግበራ የገባው የላልይበላ ዘላቂ የልማት ፕሮጀክት፣ የብሔራዊ ሙዚየም መልሶ የማደራጀት እንዲሁም የብሔራዊ ቤተ መንግስት ዕድሳትም ከትብብር ስራዎች ለአብነት አንስተዋል። የላሊበላ ታሪካዊ ቅርስ ብቻ ሳይሆን ለማህበረሰቡ ሁለንተናዊ ፋይዳ እየሰጠ ያለ ሃብት በመሆኑ የአካባቢውና የውጭ ባለሙያዎችን አቅም በመደመር የቅርሱን ቀጣይነት የማረጋገጥ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል። የላሊበላ ቅርስ መጠበቅና መንከባከብ የቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ገልፀው፤ ለዚህም የላሊበላ ዘላቂ ፕሮጀክት ቅርስን ለትውልድ ለማሻገር በሚደረገው ጥረት ፈረንሳይ የድርሻዋን እያበረከተች መሆኑን ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ ትግበራና ቋሚ ዐውደ ርዕዩ ለኢትዮጵያና ለዓለም አቀፍ ጉብኝዎች ታሪካዊና መንፈሳዊ መልኮች በመዘከር ታሪካዊ አረዳድ የሚያጎለብት፣ የወደፊት የመረጃ ቋት ግንባታ መሰረት የሚሆንና ለአካባቢው ማህበረሰብ አካታች ልማት የሚያግዝ መሆኑን ገልፀዋል። በላሊበላ ዘላቂ ፕሮጀክት ትግበራ ሂደት ትብብር ያደረጉ አካላትን አመስግነው፤ ለኢትዮጵያ ቅርሶች መጠበቅ ፈረንሳይ እገዛዋን አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ አረጋግጠዋል።
በጋምቤላ ክልል የህዝቡን ተሳትፎ በማጠናከር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እንቅስቃሴ ተጀመረ
Jun 3, 2023 60
ጋምቤላ ግንቦት 26 /2015(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የህዝቡን ተሳትፎ በማጠናከር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ የተማሪ ወላጆች ህብረት ሰብሳቢ በበኩላቸው፤ በየደረጃው የሚገኙ የተማሪ ወላጅ ህብረት አደረጃጀቶችን በማጎልበት ለትምህርት ጥራት መሻሻል እንደሚሰራ ገልጸዋል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ኮንግ ጆክ ለኢዜአ እንዳመለከቱት፤ ትምህርት ቤቶችን በበቂ ግብዓትና የሰው ኃይል ባልተደራጁበት ሁኔታ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ አስቸጋሪ ነው። ይህንን ታሳቢ በማድረግ ህዝቡን በማሳተፍ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የንቅናቄ ስራዎችን ለማካሄድ እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል። በክልሉ ከሚገኙ 377 የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በ131 ትምህርት ቤቶች ላይ የደረጃ ግምገማ ተካሄዶ ከአንድ ትምህርት ቤት በስተቀር ሁሉም ከደረጃ በታች እንደሆኑ መለየታቸውን አስታውቀዋል። በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማጎልበት ትምህርት ቤቶችን በበቂ ግብዓትና መሰረተ ልማት አደራጅቶ ደረጃቸውን በማሻሻል የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀውን የንቅናቄ ሰነድ መሰረት በማድረግ ከክልል እስከ ቀበሌ ግብረ ኃይል የማቋቋም ስራ መጀመሩን አስረድተዋል። የክልሉ የወላጆች ማህበር ሰብሳቢ አቶ አስምሮ ደርበው በበኩላቸው፤ ለትምህርት ጥራት መሻሻል የወላጆች ፣ የትምህርት ቤቶችና የዘርፉ አመራሮች ቅንጅታዊ አሰራር ከፍተኛ ድርሻ አለው ብለዋል። በተለይም የወላጆች ግንዛቤ ማሳደግ ከተቻለ ለልጆቻቸው ትምህርት መሻሻል የሚሰስቱት ነገር እንደማይኖር ገልጸው፤ በዚህም የተቻላቸውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። የክልሉ ወላጆች መምህራን ህብረት አደረጃጀቱን እስከ ወረዳና ትምህርት ቤቶች ድረስ በማጠናከር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የበኩላቸውን ጥረት እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ለአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጥበቃና ድጋፍ ለመስጠት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ
Jun 3, 2023 68
አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ) ፦ በሰው ሰራሽና ተፈጥሮ አደጋ በሚከሰት መፈናቀል በዜጎች ላይ የሚደርሰውን አሉታዊ ጫና ለመቀነስ የሚያስችል የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጥበቃና ድጋፍ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ። በአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጥበቃና ድጋፍ ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ግብዓት ማሰባሰብ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል። የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ስዩም መስፍን በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት በሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋ እናቶችና ሕፃናትን ጨምሮ በርካታ ዜጎች ተፈናቅለዋል። ረቂቁ አዋጁ በሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት በሚከሰት መፈናቀል ዜጎች የሚያስተናግዱትን ጫና ለመቀነስና ሕጋዊ በሆነ አግባብ ለመምራት ያስችላል ብለዋል። የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ምዝገባና ተያያዥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትም እንዲሁ። ረቂቁ ጸድቆ ወደ ሥራ ሲገባ ለአገር ውስጥ ለተፈናቃይ ዜጎች ተገቢው ሰብዓዊ የመብት ጥበቃና ሌሎች ድጋፎች እንዲያገኙ እንደሚያስችላቸው አስረድተዋል። በፍትሕ ሚኒስቴር ዐቃቢ ሕግና የረቂቅ አዋጁ አርቃቂ ቡድን አባል ጠገነኝ ትርፌ ኢትዮጵያ የፈረመችው የአፍሪካ ኅብረት የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጥበቃና ድጋፍ የካምፓላ ሥምምነት ለረቂቅ አዋጁ መነሻ መሆኑን ገልጸዋል። መደረኩም ለረቂቁ ማጠናከሪያ ግብዓት ለማሰባሰብ እንደሚረዳ ጠቅሰው አዋጁ ሥራ ላይ ሲውል ተፈናቃይ ዜጎችን ችግር በማቃለል አስተዋጽዖ ይኖረዋል ብለዋል። የምክክር መድረኩ ተሳታፊና የሕግ ባለሙያው ሰለሞን ወልደ-ገብርኤል፤ ለተፈናቃይ ዜጎች ጥበቃና ድጋፍ ለማድረግ ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለአስተያየት መቅረቡ መልካም ጅምር መሆኑን ተናግረዋል። ዓለም አቀፍ ሕግ መፈናቀልን መከላከል፣ ጥበቃ ማድረግ ወደ ቦታ መመለስን እንደሚደነግግ ጠቅሰው፤ ለተፈናቃይ ወገኖችም ተገቢ ክብር በመስጠት ዘላቂ መፍጥሄ እንዲያገኙ ማድረግ ይገባል ነው ያሉት። የዋቻሞ የኒቨርሲቲ ፍልሰት ተመራማሪና ሌላኛው የምክክር መድረኩ ተሳታፊ ዶክተር ጸደቀ ላምቦሬ፤ የአገር ውስጥ ተፈናቃይ የህግ ድንጋጌ ባለመኖሩ ከቀያቸው ለሚፈናቀሉ ዜጎች ተገቢው ድጋፍና ጥበቃ ማድረግ እንዳልተቻለ ገልጸዋል። የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጥበቃና ድጋፍ ረቂቅ አዋጅም በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ በሚከሰት ፍልሰት የተፈናቀሉ ወገኖች በተቋማዊ አሰራር ለማገዝ ይረዳል ብለዋል። በረቂቅ አዋጁ መሰረት ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሆነ ብሔራዊ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጥበቃና ድጋፍ ምክር ቤት እንደሚቋቋም ተጠቁሟል። ምክር ቤቱ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራ ሆኖ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማትን፣ የኃይማኖት ተቋማትን፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችንና እንደአግባብነቱ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲካተቱ የሚደረጉ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትን ያቀፈ እንደሚሆን ተጠቁሟል። በመድረኩ የሰብዓዊ መብት ተቋማት፣ የሲቪል ማኅበራት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የአደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ተወካዮችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
ኢኮኖሚ
በቆላማ አካባቢዎች እየጣለ ያለውን ዝናብ በመያዝ ለመኖ ልማት ማዋል ይገባል - ምሁራን
Jun 3, 2023 61
ዲላ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ) በቆላማ አካባቢዎች የድርቅ አደጋን በዘላቂነት ለመቀነስ የዝናብ ውሃን በተለያዩ አማራጮች በመያዝ በመኖ ልማቱ ላይ በስፋት መሰማራት እንደሚገባ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ በተያዘው ዓመት 138 ሺህ ሄክታር የሚሸፍን መሬት በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ እና በመኖ ልማት መሸፈኑም ተገልጿል። ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ "አርብቶ አደርና የአየር ንብረት ለውጥ ተጽኖ" በሚል ያዘጋጀው አውድ ጥናት ተካሂዷል። በአውደ ጥናቱ ላይ የተሳተፉት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት መኖና ስነ ምግብ ተመራማሪ ፕሮፌሰር አዱኛ ቶሌራ እንዳሉት፣ በምስራቅ አፍሪካ ለተራዘሙ ወቅቶች የተከሰተው ድርቅ የአርብቶ አደሩን የመቋቋም አቅም ፈትኖታል። ከድርቁ በተጨማሪ በዝናብ ወቅቶች ሊፈጠሩ የሚችሉ ችግሮችን ታሳቢ ያላደረገ የመኖ አያያዝ ስርአት አቅምን በማዳከም ጉዳቱን ማባባሱን ጠቅሰዋል። "በእዚህም በእንስሳቱና በአርብቶ አደሩ ሕይወት ላይ ከደረሰው ጉዳት ባለፈ በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳርፏል" ብለዋል። እንደ ፕሮፌሰር አዱኛ ገለጻ በቀጣይ ችግሩ እንዳይከሰት አሁን ያለውን መልካም የሚባል የዝናብ ስርጭት በመጠቀም የተቀናጀ ምላሽ መስጠት ያስፈልጋል። የአርብቶ አደሩን የግጦች መሬት አማራጭ በማያሳጣ መልኩ በቅይጥ ግብርና እንዲሰማራ የሚደረገውን ጥረትንም ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅሰዋል። በተለይ እየጣለ ያለውን ዝናብ ያለብክነት በመያዝና የተለያዩ የውሃ አመራጮችን በመጠቀም የመኖ ልማትን በስፋት ማከናወን እንደሚገባ ነው የመከሩት። ለዚህም ከመንግስትና ከባለድርሻ አካላት በተጨማሪ የምርምር ተቋማት የተቀናጀ የመኖ ስርአትን በመዘርጋት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ፕሮፌሰር አዱኛ አስገንዝበዋል። የእንስሳት ልማት ለአርብቶ አደሩ ሕይወቱ ቢሆንም የድርቅ ተጋላጭነት ተጠባቂ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ትንሳኤ ታምራት ናቸው። ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት የድርቅ ጉዳትን ለመቀነስ ዕቅድን መሰረት ያደረገ የተቀናጀ ምላሽ መስጠት ከምርምር ተቋማትና ከባለድርሻ አካላት ይጠበቃል። ዩኒቨርሲቲው ለተጎጂዎች ፈጣን ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ላለፉት ዓመታት በምርታማነት የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን የማላማድ ሥራ እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። አውደ ጥናቱ እየተደረገ ያለውን ጥረት ከማጠናከር ባለፈ የተለያዩ አቅሞችን በማሰባሰብ የተሻለ ምላሽ ለመስጠት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረውም አመላክተዋል። የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አማካሪ አቶ ሰለሞን ዋጋሪ በበኩላቸው ቆላማ አካባቢዎች ለድርቅ ተጋላጭ ቢሆኑም ትልቅ የተፈጥሮ ጸጋ ባለቤቶች መሆናቸውን ጠቀሰዋል። በአካባቢዎቹ የአደጋ ተጋላጭነትን ከመቀነስ ባለፈ በእንስሳትና እርሻ ልማት የሀገር ኢኮኖሚን ለመደገፍ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል። የአርብቶ አደሩን ባህላዊ እሴት ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት ውሃ በመያዝ የመኖ ልማቱን በስፋት ከማከናወን ባለፈ አርብቶ አደሩ በእርሻ ልማት እንዲሰማራ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል። በተለይ በተያዘው ዓመት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት 24 የእንስሳት መኖ ማከማቻና ገበያ ማዕከላት ግንባታ መከናወኑን ነው የገለጹት። ከእዚህ በተጨማሪ በ138 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የመኖ ልማት ሥራ መከናወኑን አስረድተዋል። በዩኒቨርሲቲው ለሁለት ቀናት በተካሄደው አውደ ጥናት የዘርፉ ምሁራን የተሳተፉ ሲሆን 40 የሚጠጉ ጥናታዊ ጽሁፎችም ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በሀገሪቱ ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተገኘ ነው- የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት
Jun 3, 2023 120
ሀዋሳ ግንቦት 26 ቀን 2015 (ኢዜአ)፡- በሀገሪቱ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅማቸውን ለማሳደግ በተደረገው ጥረት ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተገኘ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በ2016 በጀት ዓመት እቅድ ዙሪያ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ ከሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደር የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በሀዋሳ ከተማ እየተወያየ ይገኛል። በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አለባቸው ንጉሴ፤ በሀገሪቱ ምጣኔ ሀብት እድገት የአምራች ኢንዱስትሪዎች ልማት የላቀ አስተዋጽኦ አላቸው። በዚህ ረገድ በሀገሪቱ ላሉ አነስኛ፣መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማትና በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ልዩ ልዩ ድጋፍ በማድረግ የማምረት አቅማቸውን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። እስካሁን በተደረገላቸው ድጋፍ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የማምረት አቅማቸውን ከ48 በመቶ ወደ 53 ነጥብ 5 በመቶ በማሳደግ ተስፋ ሰጪ ውጤት እያስገኙ መሆኑን ተናግረዋል። ይህ ውጤት ሊመጣ የቻለው በሀገር አቀፍ ደረጃ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማወያየት ከፍተኛ ስራ በመስራቱ ነው ብለዋል። በዚህም ከውጭ ይገቡ የነበሩ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካትና ወደ ውጭ የሚላኩትንም ምርቶች በማሳደግ ለዜጎች በርካታ የስራ እድል እንዲፈጠር መደረጉን አመላክተዋል። በ2016 በጀት ዓመት እቅድ ዙርያም ቀደም ብሎ ከባለድርሻ አካላት ጋር መምከር ያስፈለገው በዘመኑ የተሻለ ስራ ለመስራት እንዲቻል ልምዶችን ለመለዋወጥና በእቅድ ላይ መግባባት ፈጥረን ወደ ስራ ለመግባት ነው ብለዋል። በተለይ አምራች ኢንተርፕራይዞች በፋይናስ አቅርቦት በስፋት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በቅርበት እየሠራን ነው ነው ያሉት ዶክተር አለባቸው። ዘርፉን በተሻለ አግባብ ለመምራት ፍኖተ ካርታ ዝግጅት መጠናቀቁንና በቀጣዩ በጀት ዓመት በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ እንደሚደረግ አብራርተዋል። በኢንዲስትሪ ሚኒስቴር የሥራ አመራር ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ እሼቱ ስጦታው በበኩላቸው፤ የውይይት መድረኩ ዓላማ የአምራች ኢንተርፕራይዝ ልማትን የማስፋፋት ተልዕኮን በከፍተኛ ኃላፊነትና በጋራ መወጣት እንዲቻል አንድ እቅድ- አንድ ሪፖርት በጋራ ለማዘጋጀትና በሚኒስቴሩ የተቀመጡ ዋና ዋና ተግባራት ላይ ለመግባባት መሆኑን ገልጸዋል። እቅዱ በዋናነት ለማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች የግብአት አቅርቦት፣የሰው ሃይል ማመቻቸት፣በዘርፉ ጥናትና ምርምር ማካሄድንና አዳዲስ ኢንቨስትመንትን ከውጭ መሳብን እንደሚያካትት አስረድተዋል። አሁን ላይ ግልጽ የሆነ የአምራች ኢንዱስትሪ ፖሊሲና ስትራቴጂዎች ተዘጋጅተው ወደ ስራ መገባቱ ለዘርፉ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ተናግረዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራ ፣ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢዘዲን ሙስበሀ፤ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በዋናነት የሚጠበቀው የስራ እድል መፍጠር መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ ረገድ እንደ ከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ይህ ዘርፍ ለ64 ሺህ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ጠቅሰዋል። ከውጭ ምንዛሪ ግኝት አንፃርም 98 ሚሊዮን ዶላር ከዘርፉ ገቢ መገኘቱን ጠቁመው፤ በተለይ በመዲናዋ የሚገኙ 1 ሺህ 965 አምራች ኢንዱስትሪዎች ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 745 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማዳን መቻሉን አውስተዋል። የሲዳማ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ጎሳዬ ጎዳና በበኩላቸው፤ በበጀት ዓመቱ የአምራች ዘርፉ በየደረጃው ለማጠናከር በተደረገው ጥረት በተተኪ ምርቶች የተሻለ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ በዘርፍ 19 ሺህ ለሚጠጉ ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ በመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ውሰጥ ለ14 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል ማመቻቸት መቻሉን አስረደተዋል። ወደ ውጭ የሚላኩ እንደ ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ እሴት የተጨመረበት ቡና፣የአቮካዳ ዘይትና ሌሎችንም አግሮ ፕሮሰሲንግ የኢንዱስትሪ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ 77 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ከታቀደው ውስጥ 80 በመቶ ማሳካት መቻሉን አመልክተዋል።
በሀዋሳ ከተማ በ250 ሚሊዮን ዶላር የሕክምና ቁሳቁስ ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ ነው
Jun 3, 2023 74
ሐዋሳ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ) ሻሎም ሄልዝ ኬር ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በሀዋሳ ከተማ በ250 ሚሊዮን ዶላር ለሚያስገነባው የሕክምና ቁሳቁስ ማምረቻ ፋብሪካ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ዛሬ ለፋብሪካው የመሰረት ድንጋይ ሲያስቀምጡ እንደገለጹት፣ ፋብሪካው በሕክምና ዘርፍ ያለውን የግብዓት አቅርቦት ችግር ይፈታል። አብዛኞቹ የሕክምና መሳሪያዎችና ግብአቶች በከፍተኛ ዋጋ ከውጭ ሃገር ስለሚገቡ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ እንደሚጠይቁ ገልጸዋል። ሻሎም ሄልዝ ኬር ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የሕክምና ቁሳቀስ ማምረቻ ፋብሪካ በሀዋሳ ከተማ መገንባቱ ችግሩን ለማቃለል ጠቀሜታ እንዳለው ጠቅሰው፣ ለኩባንያው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ፋብሪካው ተገንብቶ ወደ ማምረት ሲገባ እንደ ሃገር በህክምና ዘርፍ የሚታየውን የግብዓት አቅርቦትን ችግር ከመፍታት ባሻገር ለምስራቅ አፍሪካም ምርቱን በማቅረብ የውጭ ምንዛሬን ያስገኛል ብለዋል። የፋብሪካው መከፈት የክልሉን ኢኮኖሚ ለማነቃቃትና በዘርፉ ከፍተኛ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያግዝ በመሆኑ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርግም አቶ ደስታ አረጋግጠዋል። የክልሉ መንግስት ለፋብሪካው ግንባታ የሚያስፈልገውን መሬት በአጭር ጊዜ ውስጥ ማስረከቡን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ፋብሪካው በተቀመጠለት ጊዜ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅም አስገንዝበዋል። የሻሎም ሄልዝ ኬር ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የሕክምና መሳሪያዎች ማምረቻ ፋብሪካ መስራችና ፕሬዚዳንት ዶክተር ዊንታ መሃሪ በበኩላቸው፣ ኩባንያው በአሜሪካና ካናዳ እንደሚሰራና ባለፈው ዓመትም ወደ ኢትዮጵያ መምጣቱን ገልጸዋል። በሃዋሳ ከተማ ለሚያስገነባው የሕክምና መሳሪያዎች ማምረቻ ፋብሪካ 250 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ እንደሚደረግም አስታውቀዋል። የፋብሪካው ግንባታ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ ጠቅሰው፣ "ፋብሪካው ስሪንጅ፣ መርፌ፣ አይቪ ባግና ማስክን ጨምሮ ስድስት የተለያዩ የሕክምና ቁሶችን" ያመርታል ብለዋል። የፋብሪካው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀምር ገልጸው፣ ፋብሪካው ወደ ሥራ ሲገባ ለ5 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርም ተናግረዋል። ፋብሪካው የተለያዩ የግንባታ ምዕራፎች እንዳሉት ዶክተር ዊንታ ጠቅሰው፣ "በየምዕራፉም ወደስራ ይገባል" ብለዋል። በመድረኩ የተገኙት የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ጸጋዬ ቱኬ በበኩላቸው፣ ፋብሪካው ለሀገር፣ ለክልሉና ለከተማ አስተዳደሩ ሰፊ ዕድል ይዞ መምጣቱን ጠቅሰው፣ ለውጤታማነቱ ከተማ አስተዳደሩ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። በሀዋሳ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ አካባቢ በተዘጋጀ 10 ሄክታር መሬት ላይ ለሚገነባው ለእዚህ ፋብሪካ በርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና በዶክተር ዊንታ መሃሪ የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል።
ጋምቤላ ክልልንና አንፊሎ- ደንቢደሎን የሚያገናኘው መንገድ ለአገልግሎት ክፍት ተደረገ
Jun 3, 2023 78
ጋምቤላ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ) በጸጥታና ብልሽት ምክንያት ለሶስት ዓመት ተቋርጦ የቆየው የጋምቤላ ክልልንና አንፊሎ- ደንቢደሎን የሚያገናኘው መንገድ ለአገልግሎት ክፍት ተደረገ። መንገዱ የተከፈተው በአካባቢው ህዝብና በኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት የተቀናጀ ጥረት እንደሆነም ዛሬ በተከናወነው ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገልጿል። በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን የአንፊሎ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ነጋሽ ቀና የመንገዱን መከፈት አስመልክተው እንደገለጹት፤ ወረዳውንና ክልሉን የሚያገናኘው መንገድ በጸጥታና ብልሽት ምክንያት ላለፉት ሶስት ዓመታት ተቋርጦ በመቆየቱ በሁለቱ ህዝቦች ሁለንተናዊ ግንኙነት ላይ ችግር ፈጥሮ ቆይቷል። የጋምቤላ ክልል የሰላምና ጸጥታ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዮናስ አበበ በአሁኑ ወቅት መንገዱ በመከፈቱ በሁለቱ ህዝቦች መካከል የተጀመረው የሰላምና የልማት ትብብር ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል። በኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ 104ኛ ራስ ዳሸን ኮር የ35 ዋሊያ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ኮሎኔል ደሳለኝ ሙላው፤ ክፍለ ጦሩ በጋምቤላና በቄለም ወለጋ ተዋሳኝ አካባቢዎች ያለውን ሰላም የማስጠበቅ የተሰጠውን ተልዕኮ እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም ላለፉት ሶስት ዓመታት በጸጥታና በብልሽት ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን የጋምቤላ ክልልንና የአንፊሎ ወረዳን የሚገናኘው መንገድ በሰራዊቱና በህዝቡ ጉልበት መጠነኛ ጥገና ተደርጎለት እንዲከፋት መደረጉን አስታውቀዋል። ሰራዊቱ በቀጣይም የአካባቢውን ሰላም ይበልጥ በማስጠበቅ የሁለቱ ህዝቦች ያለምንም ስጋት በሰላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነታቸውን እንዲያከናውኑ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
ተማሪዎችና መምህራን የተሳተፉበት ክልል አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ አውደ ርዕይ በባህርዳር ተከፈተ
Jun 3, 2023 62
ባህርዳር ግንቦት 26 /2015 (ኢዜአ)፡- በባህርዳር ከተማ ተማሪዎችና መምህራን የተሳተፉበት ክልል አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ ዛሬ ተከፈተ። በአውደ ርዕዩ ላይ የቀረቡት የፈጠራ ስራዎች ተወዳድረው ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ለሚወጡ የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተመልክቷል። አውደ ርዕዩ ለ4 ቀናት የሚቆይ መሆኑም ተገልጿል። ተወዳዳሪዎቹ ከሁሉም የክልሉ ዞኖች ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 142 ተማሪዎችና መምህራን ይዘው የቀረቡትን የፈጠራ ስራ በ5 ቡድን ተከፍለው መሆኑ ተገልጿል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ማተብ ታፈረ በአውደ ርዕዩ መክፈቻ ላይ እንዳመለከቱት፤ ከድህነት ለመውጣት የሚያግዙ የፈጠራ ባለራዕይ ተማሪዎችንና መምህራንን ለማበረታታት በትኩረት ይሰራል። የፈጠራ አውደ ርዕዩን በመጎብኘት የፈጠራ ባለቤቶችን ማበረታታት ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል። ቢሮውም የፈጠራ ባለራዕዮችን በመደገፍና በማበረታታት በአውደ ርዕዩ ተወዳድረው አሸናፊ ለሚሆኑ ተማሪዎችና መምህራን በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ክልሉን ወክለው እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል። የክልሉ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽነር ዶክተር ሳሌ አያሌው በበኩላቸው፤ ተማሪዎችና መምህራን ለውድድር ይዘዋቸው የቀረቡት የፈጠራ ስራ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል። የቴክኖሎጂ ፈጠራቸውን በአዕምራዊ ንብረት እንዲመዘገቡ ኮሚሽኑ እገዛ ያደርጋል ያሉት ዶክተር ሳሌ፤ ውጤታማ የሆኑትን የድካማቸውን ፍሬ እንዲያገኙ ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። ነዳጅ አልባ ባጃጅ በፀሓይ ሃይል /ሶላር/ የሚሰራና ከወዳደቁ ብረቶች ሰርቶ በአውደ ርዕዩ ለውድድር ይዞ መቅረቡን የተናገረው ከምስራቅ ጎጃም ዞን ሸበል በረንታ ወረዳ የበረንታ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ጌታቸው አባተ ነው። ሁለት ሰው እንድትይዝ አድርጎ በሰራት ባጃጅም ዘወትር ከቤቱ ወደ ትምህርት ቤት፣ ከትምህርት ቤት ወደ ቤቱ ለትራንስፖርት እየተገለገለባት መሆኑን አስረድቷል። በቀጣይ አጋዥ አካል ባገኝ የትራንስፖርት ችግሩን ለማቃለልና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለማቃለል በብዛት አምርቼ ወደ ገበያ በማቅረብ ራሴንና ሀገሬን ለመጥቀም ራዕይ አለኝ ብሏል። ከአዊ ዞን ጓንጓ ወረዳ የስጋዲ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፊዚክስ መምህር መለሰ ግርማ በበኩላቸው፤ በአውደ ርዕዩ ለውድድር ይዞው የቀረቡት ዘመናዊ የእህል ማበጠሪያ ማሽን መሆኑን ገልጸዋል። "ሳድግ እናቴ ጤፍ ለማበጠር ሁልጊዜ ስትቸገር አይ ስለነበር ይህንን ሊያቃልል የሚችል ዘመናዊ የእህል ማበጠሪያ ማሽን ለመስራት አነሳስቶኛል " ብለዋል። በውድድሩም ከየምድቡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ለሚወጡ የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ከትምህርት ቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አቶ ሰለሞን ሶካ በሞሮኮ በተዘጋጀው በጂኣይቴክስ አውደ ርዕይ ኢትዮጵያን ወክለው የተገኙ ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎችን ጎበኙ
Jun 3, 2023 78
አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ)፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ሰለሞን ሶካ በሞሮኮ በተዘጋጀው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ ('ጂ ኣይ ቴክስ') ኢትዮጵያን ወክለው የተገኙ ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎችን ጎብኝተዋል። በሞሮኮ ማራካሽ በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደዉ ኮንፍረንስ ላይ የአቅም ግንባታ ስራ ለሙያዊ ልህቀትና ኢኮኖሚ ልማት በሚል በተዘጋጀው መድረክ ላይ የተካፈሉት የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያውያን ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎችን መጎብኘታቸው ተገልጿል። በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው እና ትኩረቱን በሳይበር ደህንነት፣ በክላውድ ኮምፒውቲንግ ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በፊንቴክ (fintech)፣ በዲጂታል ከተማ፣ አግሪ ቴክ (agritech) መሰል የቴክኖሎጂ ዘርፎች ባደረገው ኮንፍረንስ ላይ ኢትዮጵያ ምርትና አገልግሎቶቿን አስተዋውቃለች። በጉብኝቱ ወቅት በሳይበርና መሰል ጉዳዮች ላይ አቅም ያላቸው አካላት ከኢመደአ ጋር በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባና ተቋሙ ለዚህ ዝግጁ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። በጉብኝቱ የኢመደአ ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶክተር) ተሳትፈዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ከኦራክል እና ቪዛ ኩባንያ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ
Jun 2, 2023 69
አዲስ አበባ ግንቦት 25/2015 (ኢዜአ):-የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶክተር) ከአሜሪካው ዓለም አቀፍ የኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ ኦራክል ኩባንያ እና ከቪዛ የፋይናንስ አገልግሎት ኩባንያ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። በሞሮኮ ማራካሽ ከግንቦት 23 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ(ጂአይቴክስ) ዛሬ ማምሻውን ተጠናቋል። በአውደ ርዕዩ ላይ ከመላ ዓለም የተሰባሰቡ ታዋቂ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እና ጀማሪ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች የታደሙባቸው አውደ ርዕዮች እና አውደ ጥናቶች ተካሄደዋል። በመድረኩ የተሳተፉት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶክተር) እና ልዑካናቸው ከመድረኩ አውደ-ርዕዮች እና የስማርት አፍሪካ አውደ ጥናት ተሳትፏቸው ጎን ለጎን ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይቶችን አድርገዋል። በአውደ ርዕዩ ማጠናቀቂያ ላይ ሚኒስትሩ ከኦራክል እና ከቪዛ ኩባንያዎች የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል። ዶክተር በለጠ በውይይቱ በኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሂደት ላይ ማብራሪያ መስጠታቸውንና ኩባንያዎቹ በዲጂታላይዜሽን ስራዎች እና አገልግሎቶች ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸው ተመላክቷል። መንግስት ለዘርፉ እድገት አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ እና ለኩባንያዎቹ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አስረድተዋል። የኩባንያዎቹ ኃላፊዎች በበኩላቸው የኢትዮጵያ በዲጂታል ገበያ እድል ውስጥ ለመሳተፍ ፍላጎትና እቅድ እንዳላቸው መግለጻቸውን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ድርቅ በአርብቶ አደሩ ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገለጸ
Jun 2, 2023 91
ቡሌ ሆራ ግንቦት 25/2015 (ኢዜአ):- የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ድርቅ በአርብቶ አደሩ ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አስታወቀ። የተፈጥሮ ሃብት አጠባበቅ ስራዎችን ከማጠናከር ባለፈ አማራጭ የውሃ አጠቃቀም ስርዓት በመዘርጋት ችግሩን ለመቅረፍ መሰራት እንደሚገባም ተገልጿል። የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ”አርብቶ አደርና የአየር ንብረት ለውጥ ተጽኖ” በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው ሶስተኛውን ዓለም አቀፍ የጥናት እና ምርምር አውደ ጥናት እያካሄደ ነው። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ፍቃዱ ወልደማርያም እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን በግብርና፣ በጤና፣ማዕድን እና አገር በቀል እውቀቶች የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ ነው ብለዋል ። በተለይም በጉጂ እና ቦረና ዞኖች የአየር ንብረት ለውጥ በግብርና ልማቱ እና በእንሰሳት እርባታ እያደረሰ የሚገኘውን ጉዳት ለመቀነስ ዘርፍ ብዙ ጥረቶች እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በተለይ ምርምርን መሰረት ያደረገ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እንዲጠናከር እንዲሁም በቆላማ አካባቢዎች የሚገኘውን ዝቅተኛ የውሃ መጠን በአግባቡ ለመጠቀም በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል ። አውደ ጥናቱ በዘርፉ ዓለም አቀፍ የእውቀትና የልምድ ልውውጥ በማድረግ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት ያግዛል ነው ያሉት ዶክተር ፍቃዱ። የአፍሪካ የአከባቢ ጤና ማህበር ፕሬዝዳንት ዶክተር ተዋበች ቢሻው በበኩላቸው በአየር ንብረት ለውጥ ችግር የሚፈጠረውን የውሃ እጥረት ከእርባታ ስርዓቱ እና የገበያ ትስስር ውስንነት ጋር ተዳምሮ በኢትዮጵያ የእንስሳት ሀብት ላይ ጫና እያሳደረ ነው ብለዋል። የተፈጥሮ ሀብት አጠባበቅ ስራዎችን ከማጠናከር ባለፈ አማራጭ የውሃ አጠቃቀም ስርዓት በመዘርጋት ችግሩን ለመቅረፍ መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል። በዚህ ረገድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጥናት እና ምርምር ከማድረግ ባለፈ የጥናት ውጤትን መሰረት ያደረገ ትግበራ በማከናወን የበኩላቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው ተናግረዋል። በአውደ ጥናቱ ላይ ምሁራን፣የአገር ውስጥ እና የውጭ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዲሁም የመንግስት እና የግል ድርጅቶች ተሳታፊ መሆናቸው ተገልጿል። እስከ ነገ በሚቆየው አውደ ጥናት ከ40 በላይ የጥናት ውጤቶች ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ስፖርት
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ
Jun 4, 2023 35
አዲስ አበባ ግንቦት 27/2015(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይደረጋሉ። በመርሐ-ግብሩ መሰረት ሀዲያ ሆሳዕና ቀድሞ ከሊጉ መውረዱን ካረጋገጠው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ከቀኑ 7 ሰአት ላይ ይጫወታል። በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ሀዲያ ሆሳዕና በ36 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ12 ነጥብ የመጨረሻውን 16ኛ ደረጃን ይዟል። ሀዲያ ሆሳዕና በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው፤ ሁለት ጊዜ ተሸንፎ ሁለት ጊዜ አቻ ወጥቷል። በአንጻሩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ባለፉት አምስት የሊግ ጨዋታዎች አራት ጊዜ ሲሸነፍ አንድ ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያ ዙር ያደረጉት ጨዋታ ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ይታወሳል። በ27ኛ ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር የመጨረሻው ጨዋታ በመቻልና ባህር ዳር ከተማ መካከል ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ይደረጋል። በደረጃ ሰንጠረዡ መቻል በ34 ነጥብ 11ኛ ሲሆን ባህር ዳር ከተማ በ50 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። መቻል ካለፉት አምስት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች ሁለቱን አሸንፎ በአንዱ ሲሸነፍ በሁለቱ አቻ ወጥቷል። ተጋጣሚው ባህር ዳር ከተማ በበኩሉ ባለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል፤ ሁለት ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። ባህር ዳር ከተማ ጨዋታውን ካሸነፈ ከሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ዝቅ ያደርጋል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት ጨዋታ መቻል 3 ለ 2 ማሸነፉ ይታወሳል። በተያያዘ ዜና ትናንት በተደረጉ የ27ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ኢትዮጵያ መድን ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 ሲያሸንፍ ወልቂጤ ከተማ እና ፋሲል ከነማ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል። ከዛሬ ጨዋታዎች በኋላ የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሃዋሳ ከተማ ቆይታ እንደሚጠናቀቅ የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል። ከ28ኛ እስከ 30ኛ ሳምንት ያሉ የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ከሰኔ 1 እስከ ሐምሌ 1 2015 በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም እንደሚካሄዱ ገልጿል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይካሄዳሉ
Jun 3, 2023 70
አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር የሶስተኛ ቀን ውሎ ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይደረጋሉ። በመርሃ ግብሩም ኢትዮጵያ መድን ከኢትዮጵያ ቡና ከቀኑ 7 ሰአት ላይ ይጫወታሉ። በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ኢትዮጵያ መድን በ45 ነጥብ 3ኛ ሲሆን ኢትዮጵያ ቡና በ38 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ኢትዮጵያ መድን በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሁለቱ አሸንፎ በሁለቱ ሲሸነፍ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። ተጋጣሚው ኢትዮጵያ ቡና በአንጻሩ ካለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ሁለቱን ሲያሸንፍ በአንዱ ተሸንፏል። ሁለት ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያ ዙር ባደረጉት ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። በሌላኛው የ27ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር ወልቂጤ ከተማ ከፋሲል ከነማ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። በደረጃ ሰንጠረዡ ወልቂጤ ከተማ በ32 ነጥብ 13ኛ ደረጃን የያዘ ሲሆን ፋሲል ከነማ በ37 ነጥብ 6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ወልቂጤ ከተማ በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሁለቱ አሸንፎ በሁለቱ ተሸንፎ አንድ ጊዜ አቻ ወጥቷል። ተጋጣሚው ፋሲል ከነማ በበኩሉ ባለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ሁለት ጊዜ ሲያሸንፍ በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ሽንፈት ገጥሞታል። አንድ ጊዜ ደግሞ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር ያደረጉት ጨዋታ ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ የሚታወስ ነው። በተያያዘም ትናንት በተደረጉ የ27ኛ ሳምንት የሊጉ ጨዋታዎች ሃዋሳ ከተማ ወላይታ ድቻን 3 ለ 1 እንዲሁም አዳማ ከተማ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፈዋል።
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ
Jun 2, 2023 80
አዲስ አበባ ግንቦት 25/2015 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር የሁለተኛ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይደረጋሉ። በመርሐ-ግብሩ መሰረት ሃዋሳ ከተማ ከወላይታ ድቻ ከቀኑ 7 ሰአት ላይ ይጫወታሉ። በደረጃ ሰንጠረዡ ሃዋሳ ከተማ በ35 ነጥብ 8ኛ ላይ የተቀመጠ ሲሆን ወላይታ ድቻ በአንጻሩ በ33 ነጥብ 12ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሃዋሳ ከተማ በፕሪሚየር ሊጉ ከ19ኛ ሳምንት በኋላ ባሉ ሰባት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም። በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች አንድ ጊዜ ሲሸነፍ አራት ጊዜ ነጥብ ተጋርቷል። ተጋጣሚው ወላይታ ድቻ በአንጻሩ ባለፉት አምስት ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው፤ በሶስቱ አቻ ሲወጣ በአንዱ ተሸንፏል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር 11ኛ ሳምንት ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው። ሌላኛው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ድሬዳዋ ከተማ እና አዳማ ከተማን ከቀኑ 10 ሰአት ላይ ያገናኛል። ድሬዳዋ ከተማ በ36 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን አዳማ ከተማ በ33 ነጥብ 11ኛ ደረጃን ይዟል። ድሬዳዋ ከተማ በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ሶስቱን ሲያሸንፍ በሁለቱ ተሸንፏል። ተጋጣሚው አዳማ ከተማ ደግሞ ባለፉት አምስት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም፤ በሶስቱ ነጥብ ሲጋራ ሁለት ጊዜ ደግሞ ተሸንፏል። ሁለቱ ክለቦች በመጀመሪያው ዙር በ13ኛ ሳምንት ባደረጉት ጨዋታ አዳማ ከተማ 2 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። በተያያዘም ትናንት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ለገጣፎ ለገዳዲን 2 ለ 1 ሲያሸንፍ ሲዳማ ቡና ከአርባ ምንጭ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል።
በፕሪሚየር ሊጉ ሲዳማ ቡና እና አርባ ምንጭ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል
Jun 1, 2023 101
አዲስ አበባ ግንቦት 24/2015(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር የመጀመሪያ ጨዋታ ሲዳማ ቡና እና አርባ ምንጭ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል። አህመድ ሁሴን በ18ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ አርባ ምንጭ ከተማን መሪ ማድረግ ችሎ ነበር። ይሁንና የመጀመሪያ አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በጭማሪ ሰአት ላይ የአርባ ምንጭ ከተማው አሸናፊ ፊዳ በራሱ ግብ ላይ ያስቆጠራት ግብ ሲዳማ ቡናን አቻ አድርጋለች። ውጤቱን ተከትሎ ሲዳማ ቡና በ35 ነጥብ ከነበረበት 10ኛ ደረጃ ወደ 9ኛ ከፍ ብሏል። በአንጻሩ አርባ ምንጭ ከተማ በ30 ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ27ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከለገጣፎ ለገዳዲ ጋር ከቀኑ 10 ሰአት ላይ ጨዋታውን ያደርጋል።
አካባቢ ጥበቃ
ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከ902 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ተለይቶ ለችግኝ መትከያ ዝግጁ ተደርጓል - የኢትዮጵያ ደን ልማት
Jun 3, 2023 74
አዲስ አበባ ግንቦት 26/2015 (ኢዜአ)፡- ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከ902 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ተለይቶ ለችግኝ መትከያ ዝግጁ መደረጉን የኢትዮጵያ ደን ልማት ገለጸ፡፡ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት ከአራት ዓመት በፊት በጀመረችው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከ25 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል ችላለች፡፡ የሀገሪቱን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ፣ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የደን ሽፋኑን በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ታላሚ ባደረገው በዚህ መርሐ ግብር ከተተከለው አጠቃላይ ችግኝ 55 በመቶ የሚሆነው ለጥምር ደን መሆኑ ይታወቃል፡፡ የኢትዮጵያ ደን ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሞቱማ ቶሌራ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ባለፉት አራት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የተከናወነው ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁሉ በስኬቱና ህዝባዊ ተሳትፎን በማረጋገጥ የሚጠቀስ ፕሮጀክት ነው፡፡ "በኢትዮጵያ በየዓመቱ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች ካልተተከሉ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለከፋ አደጋ የምንጋለጥበት ዘመን በመሆኑ ለኢትዮጵያውያን ችግኝ መትከል የምርጫ ጉዳይ አይደለም" ብለዋል ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፡፡ በኢትዮጵያ ተራራማ አካባቢዎች እየተራቆቱ፤ አፈር እየተሸረሸረ፤ የውኃማ አካላት እየደረቁ፤ መምጣታቸውን ጥናቶች እንደሚያሳዩ ጠቁመው፤ አረንጓዴ አሻራ ቅድሚያ የሚሰጠው ስራ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከ6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኝ ለመትከል ዕቅድ ቢያዝም እስካሁን ከ7 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ለዚህ ደግሞ ምን አይነት ችግኞች በምን አይነት ሥነ ምህዳርና በምን አይነት አፈር ላይ ይተከሉ የሚለው በጥናት ተለይቶ ለተከላ ዝግጅት መደረጉን በማብራራት፡፡ በዚሁ መሰረት እስካሁን ከ902 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት ተለይቶ ለችግኝ መትከያ የተዘጋጀ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 522 ሺህ ሄክታር የሚሆነው ለደን መለየቱን ጠቁመዋል፡፡ ለችግኝ መትከያ ከተለየው መሬት ውስጥ 257 ሺህ ሄክታር የሚሆነው ካርታ እንደተዘጋጀለት ነው የገለጹት፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ በተካሄዱት አራት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሮች ከዘር መረጣ ጀምሮ በችግኝ ተከላና በእንክብካቤ የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን አረጋግጠናል ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አካል በሆነው የበጋ ወቅት የተቀናጀ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ የዜጎች ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱ ለዚህ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ችግኝ መትከል የመርሐ ግብሩ የመጀመሪያ እርምጃ መሆኑን ጠቅሰው፤የተተከሉ ችግኞች ለሚፈለገው አላማ ውለው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ የመጨረሻ ግቡ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በዘንድሮው መርሐ ግብር እስካሁን ወደ 2 ነጥብ 3 ቢሊዮን የሚጠጋ የችግኝ መትከያ ጉድጓድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። እንደ ዶክተር ሞቶማ ገለጻ፤ በ2015 የበልግ ወቅት በኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያና ድሬዳዋ ከ 250 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ባለፉት አራት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች በደን ልማት፣ በምግብ ዋስትና፣ በአፈር ለምነትና መሰል ጉዳዮች ላይ ያመጡትን አዎንታዊ ለውጥ አጥንቶ ይፋ የሚያደርግ ድርጅት መለየቱን ጠቁመዋል።
ከተማዋ ከብክለት የጸዳች ውብና ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ ሁሉም የሚያበረክተውን አዎንታዊ አስተዋጽኦ አጠናክሮ መቀጠል አለበት - ዶክተር ጀማሉ ጀንበሩ
Jun 2, 2023 72
አዲስ አበባ ግንቦት 25/2015 (ኢዜአ) አዲስ አበባ ከተማ ከብክለት የጸዳች ውብና ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ ሁሉም የሚያበረክተውን አዎንታዊ አስተዋጽዖ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተገለጸ። የዘንድሮው የአለም አካባቢ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ50ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ30ኛ ጊዜ እየተከበረ ነው። የአካባቢን ጥበቃ ቀንን አስመልክቶ ከግንቦት 25 እስከ ግንቦት 27 የሚቆይ ኢግዚቢሽን ተከፍቷል። በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማና ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ጀማሉ ጀንበሩ ከተማዋን ምቹ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። በተለይም በመዲናዋ ነዋሪዎችና በተቋማት የሚመነጩ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻዎች የተቀመጡ የጽዳት ሕጎች አክብረው እንዲወገዱ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ከተማዋ ከብክለት የጸዳች ውብና ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ ሁሉም የሚያበረክተውን አዎንታዊ አስተዋጽዖ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ነው ያሳሰቡት። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ዲዳ ድሪባ በበኩላቸው በመዲናዋ የአካባቢ ችግሮች እንዲፈቱ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ ነው። ለዚህም አካባቢያዊ ደንቦችን፣ ደረጃዎችን መመሪያዎችን በማውጣት በማስተዋወቅ እንዲሁም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች በስፋት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ጎን ለጎንም ሕግና ደንብ በሚተላለፉ አካላት ላይ እርምጃ እየተሰራ እየተወሰደ መሆኑን ገልጸዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማና ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ጀማሉ ጀንበሩ ገለጹ።
በአዲስ አበባ በተለያዩ ተቋማት የሚተከሉ 800 ሺህ የሚደርሱ ችግኞች ተዘጋጅተዋል - የጉለሌ እጽዋት ማዕከል
Jun 2, 2023 74
አዲስ አበባ ግንቦት 25/2015 (ኢዜአ)፦ ለዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ በተለያዩ ተቋማት የሚተከሉ 800 ሺህ የሚደርሱ ችግኞችን ማዘጋጀቱን የጉለሌ እጽዋት ማዕከል ገለጸ። የጉለሌ ዕጽዋት ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጉተማ ሞረዳ ለኢዜአ እንደገለጹት በዘንድሮው ዓመት በአዲስ አበባ በተለያዩ ተቋማት የሚተከሉ 800 ሺህ ችግኞች ተዘጋጅተዋል። በዚህም ችግኝ ለሚያፈሉና ለሚያቀርቡ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር ወጣቶቹ ገቢያቸውን ማሳድጉን ነው የገለጹት። ማዕከሉ ለዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አገር በቀል የሆኑ ለአፈርና የውሃ ጥበቃ፣ ለፍራፍሬና ለምግብነት የሚውሉ ጨምሮ አካባቢን ለማስዋብ የሚውሉ ችግኞችን አፍልቶ ማዘጋጀቱን ጠቁመዋል። ማዕከሉ ችግኞችን ከማፍላት ጎን ለጎን ባሉት 705 ሄክታር መሬት ላይ በ2014 ዓ.ም ከተከላቸው ችግኞች ውስጥ 90 በመቶው መጽደቁን ገልጸዋል። በአገር አቀፍ ደረጃ ባለፉት አራት ዓመታት በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር 25 ቢሊየን ችግኞች መተከላቸው ይታወሳል። በዘንድሮም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞች ለመትከል ዝግጅት መደረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መግለጻቸውም እንዲሁ።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረው የእርጥበት ሁኔታ ለበልግና ለመኸር ሰብሎች አመቺ ሁኔታ ይፈጥራል - የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
Jun 2, 2023 63
አዲስ አበባ ግንቦት 25/2015 (ኢዜአ) በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረው የእርጥበት ሁኔታ ለበልግና ለመኸር ሰብሎች እንዲሁም ቋሚ ተክሎች አመቺ ሁኔታ እንደሚፈጥር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ በቀጣዩቹ አስር ቀናት በተለይም በምዕራብ አጋማሽ የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የተስፋፋ የዝናብ መጠንና ሥርጭት ይኖረዋል ብሏል። ይህም በአካባቢዎቹ ላይ እየተከናወነ ለሚገኘውና ለሚጠበቀው የግብርና እንቅስቃሴ በአብዛኛው መልካም ጎን የሚኖረው ሲሆን የሚኖረው የዕርጥበት ሁኔታም የአፈር ውስጥ እርጥበትን ከማሻሻል አንጻር በጎ ሚና የሚጫወት መሆኑም ተመላክቷል። በእነዚህ ቀናት የሚኖረው የእርጥበት ሁኔታ በተለይም ለበልግና ለመኸር ሰብሎች እንዲሁም ቋሚ ተክሎችና የጓሮ አትክልቶች አመቺ ሁኔታ እንደሚፈጥር ነው የተገለጸው። እየተስፋፋ የሚሄደው ዝናብ ሰጪ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታ ቀደም ብለው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴን ለጀመሩ አካባቢዎችም ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑንም እንዲሁ። የሚኖረው እርጥበትም ለአርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ለግጦሽና የመጠጥ ውሃ አቅርቦትም የጎላ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተጠቅሷል። እንዲያም ሆኖ በተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ከሚጠበቀው ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞ የጎርፍ አደጋ ሊያጋጥም ስለሚችል ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አሳስቧል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ፕሬዝዳንት ፑቲን ለአፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የእንኩዋን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
May 25, 2023 252
አዲስ አበባ ግንቦት 17/2015 (ኢዜአ)፦የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሜር ፑቲን ለቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለአሁኑ የአፍሪካ ህብረት 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የእንከዋን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት የእንኩዋን አደረሳችሁ መልዕክት የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት ለአፍሪካውያን የድል ምልክት ነው ያሉ ሲሆን የአፍሪካውያን የነጻነት፣የሰላምና የብልጽግና ፍላጎት ማሳያ ነው ብለዋል። ህብረቱ ከተመሰረተበት ግዜ አንስቶ ለብዙ አስርተ ዓመታት በዓለም አቀፍ መድረኮች አፍሪካውያንን በመወከል የባለብዙ ወገን ውይይቶችንና ትብብርን በማጎልበት ትልቅ ሚና ተጫውቷል ብለዋል። የአፍሪካ ሀገራት ለችግሮቻቸው በጋራ ምላሽ የሚሰጡበትን መንግድ ያመቻቸ መሆኑን ጠቁመው አህጉራዊ ትብብርን በተለያዩ መስኮች እንዲያጠናከሩም መንገድ ከፍቷል ብለዋል። በዚህም ለአፍሪካ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት የላቀ ሚና ማበርከቱንና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ያላትን ተሳትፎ እንድታሳድግ ህብረቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። በመሆኑም ሩሲያ ከአፍሪካ አጋሮቿ ጋር ያላትን ወዳጅነት ለማጠናከር ልዩ ትኩረት ትሰጣለች ያሉት ፕሬዝዳንቱ እ.አ.አ በ2019 የተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ -ሩሲያ ጉባኤ በአፍሪካና በሩሲያ መካከል ያሉ ትብብሮች እንዲጠናከሩ አስችሏል ብለዋል። በመጪው ሃምሌ ወር በሩሲያ የሚካሄደው ሁለተኛ የአፍሪካ ሩሲያ ጉባኤም ሩሲያ ከአፍሪካ ጋር ለሚኖራት ትብብር አዲስ ምዕራፍ እንደሚፈጥር ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ተመድ በሶሪያ በርዕደ መሬት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረበ
Feb 15, 2023 3943
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በሶሪያና ቱርክ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ሶሪያውያንን ለማገዝ የ397 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ጥሪ አቀረቡ። ዋና ጸሓፊው ጥሪውን ያቀረቡት ባሳለፍነው ሳምንት በቱርክና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ በደረሰው ርዕደ መሬት ሳቢያ ከቤታቸው የተፈናቀሉ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሶሪያውያንን ለማገዝ ነው። በኒውዮርክ በሰጡት መግለጫ ሶሪያውያኑን ለማገዝ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ለሶስት ወራት ጊዜ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ጠቅሰው የሚመለከታቸው ሁሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል። ከአደጋው በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ማቅረቡን ገልጸው ተጨማሪ እገዛዎች አሁንም እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በድርጅቱ ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትና አጋር አካላት በጋራ በሚያቀርቡት ገንዘብ፤ አስቸኳይ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሶሪያውያን የመጠለያ፣ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎች እንደሚደረጉ አብራርተዋል። ተመሳሳይ የድጋፍ ማዕቀፍ በቱርክ ድንበር ለሚገኙ ዜጎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ዋና ጸሓፊው ተናግረዋል።
በተርኪዬ በመሬት መንቀጥቀጥ ለደረሰው ጉዳት ጥልቅ ሀዘን የተሰማው መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ
Feb 6, 2023 1729
አዲስ አበባ ኢዜአ ጥር 29/2015፦በደቡባዊ ተርኪዬ በተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት፣ የአካል ጉዳት እና የንብረት መውደም የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። ሚኒስቴሩ በሀዘን መግለጫው በአደጋው ህይወታቸውን ስላጡት ዜጎች የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ፤ ጉዳት የደረሰባቸውም በቶሎ እንዲያገግሙ የመልካም ምኞት መልዕክቱን አስተላልፏል። በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ኢትዮጵያ ከቱርኪዬ መንግሥት እና ህዝብ ጎን የምትቆም መሆኗን መገለጹን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተገለጸ
Dec 20, 2022 1668
አዲስ አበባ ታኅሳስ 11/2015 (ኢዜአ) አህጉራዊው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና አፍሪካ ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ ግንኙነትና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደገው እንደሚገኝ ተመላከተ። የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ከአፍሪካ ጋር ያላት የንግድ ትስስር ከባህረ-ሰላጤው ሃገራት መካከል በቀዳሚነት እንደሚጠቀስም ተገልጿል። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዊሊያም ስቴንሀውስ ከሲ ጂ ቲ ኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በተለይም ዱባይ የአፍሪካን ንግድና ኢንቨስትመንት በተመለከተ ዋና ማዕከል ሆናለች ብለዋል። በዱባይ 25ሺህ ገደማ የአፍሪካ ካምፓኒዎች እንደሚንቀሳቀሱ አመልክተው ይህም ሀገሪቱ በነጻ የንግድ ቀጣናው የቢዝነስ አጋር እንድትሆን አስችሏታል ነው ያሉት። አፍሪካውያን ባለሃብቶች የግብይት ማዕከላቸውን በተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በማድረግና ምርቶችን ወደ አህጉሪቷ በማስገባት በነጻ ንግድ ቀጣናው ስር የገልፍ ሀገራትን ኢኮኖሚያዊ ትስስር እያሳደጉት እንደሚገኝም አስገንዝበዋል። የዱባይ ወደብ በአፍሪካ ያለው ተደራሽነት መስፋፋትም አፍሪካ ከባህረ ሰላጤው ሀገራት ጋር የሚኖራትን የሎጀስቲክስ አቅርቦት እንደሚያሳድግ በመረጃው ተመላክቷል። ከገልፍ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት ከኢኮኖሚያዊ ትስስር ባለፈ ዲፕሎማሲያዊና ወንድማማችነትን መሠረት ያደረገ ነው ያሉት ደግሞ በተባበሩት አረብ ኤሜሬት የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ ናቸው። አምባሳደሩ እንደሚሉት ከመካከለኛው ምስራቅ መነሻቸውን ያደረጉ ባለሃብቶችና የቢዝነስ ሰዎች ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ጋር በልዩ ልዩ ዘርፎች ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ ይገኛል። እ.አ.አ በጥር 2021 ተግባራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ከአጀንዳ 2063 ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው። የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የአህጉሪቱን ወሳኝ የኢኮኖሚ ዘርፎች ማለትም የዲጂታል ንግድ፣ የኢንቨስትመንት ትስስርና ሌሎች የንግድ ግንኙነቶችን በነጻ የንግድ ቀጣና ለማከናውን የተካሄደ ስምምነት ነው።
ሐተታዎች
አፋጣኝ መፍትሔ የሚያሻው የምርታማነት ፀር
May 27, 2023 168
(ኤልያስ ጅብሪል) አሲዳማ አፈር የአፈሩ ኬሚካላዊ ይዘት ወይም ፒ ኤች (pH) መጠን ከሰባት በታች የሆነ እና የሃይድሮጅን (H+) እና አልሙኒየም (Al+3) ንጥረ- ነገሮች የሚበዙበት አፈር ማለት ነው፡፡ የአፈር አሲዳማነት በሀገራችን በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ጫና እያሳደረ የሚገኝ የአፈር ለምነት ችግር ሲሆን፤ ከፍተኛ ዝናብ የሚያገኙና በምርታማነታቸው የተሻሉ ናቸው የሚባሉትን የሀገሪቱን አካባቢዎች ጭምር እየጎዳ መሆኑንም ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት፡፡ የአፈር ጤንነት ችግሮች በሦስት ዋና ዋና መንገዶች ይገለፃሉ፡፡ ይኸውም አሲዳማነት፣ የጨዋማነት ችግር የሚነሳበትና ኮትቻማ/ጥቁር ወይም መረሬ አፈር/ ብሎ ማስቀመጥ እንደሚቻል በግብርና ሚኒስቴር የአፈር ኃብት ልማት የአፈር ጤንነትና ለምነት ዴስክ ኃላፊ ፋኖሴ መኮንን ይናገራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ከ15 ሚሊየን ሄክታር በላይ የሚታረስ መሬት ሲኖር ወደ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በአሲዳማነት የተጠቃ እንደሆነ ነው የጠቀሱት፡፡ አፈር ሰብሎች የሚፈልጓቸውን ንጥረ-ነገሮች በተሟላና በተመጣጠነ መልኩ ሳይዝ ሲቀር ምርታማነት ጥያቄ ውስጥ እንደሚወድቅ አቶ ፋኖሴ ይገልጻሉ። ከዚህ አኳያ በኢትዮጵያ ከ1 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት በአፈር አሲዳማነት ክፉኛ የተጎዳ በመሆኑ ምርታማነቱ ምንም በሚባል ደረጃ የሚቀመጥ መሆኑን ይጠቁማሉ። እፅዋት ከአየር፣ ውሃና የፀሐይ ብርሃን በተጨማሪ 18 ዓይነት ንጥረ-ነገሮችን ከአፈር ውስጥ ሊያገኙ እንደሚችሉ ነው ኃላፊው የገለጹት፡፡ የአፈር አሲዳማነት መንስኤዎች አሲዳማነት በአንድ ጊዜ ተፈጥሮ የሚቆይ ሳይሆን በሂደት እየጨመረ እና እየተስፋፋ የሚሄድ ክስተት ነው፡፡ ለአፈር አሲዳማነት በዋነኝነት የዝናብ መብዛት፣ የአፈር መሸርሸር፣ የሰብል ተረፈ-ምርት ሙሉ በሙሉ ከማሳ ማንሳት እና ፍግ አለመጠቀም፣ እንዲሁም አሲዳማ ዝናብ የመሳሰሉት አፈር ውስጥ ያሉ ለተክሉ እድገት ጠቃሚ ንጥረ-ነገሮች እንዲሟጠጡ እንደሚያደርግ በመንስኤነት ይጠቀሳሉ። የአፈር አሲዳማነት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚስተዋል ሲሆን ለአብነትም አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ተጠቃሾች እንደሆኑ አቶ ፋኖሴ ተናግረዋል፡፡ አሲዳማ አፈርን በኖራ የማከም ዘዴ አሲዳማ አፈርን ለመከላከል በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ መንገዶች ከሚወሰዱ እርምጃዎች ባሻገር አፈሩን በኖራ የማከም ሥራ በዋናነት የሚጠቀስ መሆኑን ነው አቶ ፋኖሴ አፅንዖት ሰጥተው የተናገሩት፡፡ የተለያዩ አፈርን የማከሚያ ግብአቶች ያሉ ቢሆንም በቀላሉ ከመገኘትና ከዋጋው ርካሽነት አንፃር ካልሽየም ካርቦኔት ወይም “ የግብርና ኖራ" እየተባለ የሚጠራው በስፋት አገልግሎት ላይ እንደሚውል ገልጸዋል፡፡ ወደ 15 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር የሚታረስ መሬት ሲኖር፤ ከዚህ ውስጥ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር ወይም ከ43 በመቶ የማያንሰው በአሲዳማ አፈር የተጠቃ መሆኑን ጠቅሰው፤ ወደ 4 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነው በጠንካራ አሲዳማነት የተጠቃ እንደሆነና በኖራ መታከም ያለበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ጠንካራ አሲዳማ አፈር ስንል የአፈሩ ኬሚካላዊ ይዘት ወይም ፒ ኤች (pH) መጠን ከ 5 ነጥብ 5 በታች የሆነ እና የሃይድሮጅን (H+) እና አልሙኒየም (Al3+) ካታየኖች የሚበዙበት አፈር ሲሆን፤ የእነዚህ ካታየኖች መብዛት የሰብሎችን ሥር በመመረዝ በዕድገታቸው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖን እንደሚፈጥር ነው ከግብርና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ የሚጠቁመው፡፡ ፒ ኤች መጠኑ ከሰባት ወደ ዜሮ እየቀነሰ ሲሄድ የአሲድነቱ ጥንካሬ የሚጨምር ሲሆን ከሰባት ወደ 14 ሲጨምር የጨዋማነቱ ባህሪ እንደሚጨምር ነው የዘርፉ ባለሙያዎች የሚያስቀምጡት። በአገራችን ሁኔታ አሲዳማ አፈርን ለማከም ኖራ መጠቀም የሚያስፈልገው የአፈሩ ፒ ኤች መጠን ከ5 ነጥብ 5 በታች ሲሆን ነዉ፡፡ ኖራ በተፈጥሮ የሚገኝ የካልሲየም እና የማግኒዚየም ካርቦኔት ሃይድሮኦክሳይድ ውህድ ሲሆን፤ አሲዳማ አፈር ውስጥ በሚጨመርበት ወቅት አሲዳማ አፈር ውስጥ የሚገኙትን አልሙኒየም እና ሃይድሮጂን አሉታዊ እንቅስቃሴዎችን በመግታት የአፈሩን ፒ ኤች መጠን ከፍ በማድረግ ለእፅዋት እድገት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ በአማካይ በአፈር አሲዳማነት የተጎዳ መሬትን ለማከም በሄክታር 30 ኩንታል የግብርና ኖራ እንደሚያስፈልግ ባለሙያዎች ይመክራሉ። በአሲዳማነት የተጠቃ መሬት አሲዳማነትን የሚቋቋሙ ሰብሎች ካልተዘሩበት ወይም አፈሩን በኖራ የማከም ሥራ ካልተሰራ የሚሰጠውን የአፈር ማዳበሪያ ከጥቅም ውጭ በማድረግ ለኪሳራ ይዳርገናል ነው ያሉት፡፡ እንደ አኩሪ አተር፣ ካሳቫ፣ አናናስ፣ ዳጉሳ፣ ቡና፣ ሻይ እንዲሁም የስንዴ ዝርያዎች አሲድን የመቋቋም ባህሪ እንዳላቸውም ተመላክቷል፡፡ ግብርና ሚኒስቴር በአሲዳማነት ከተጠቃው 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት 4 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነውን በአሥር ዓመት ውስጥ ለማከም ዕቅድ የያዘ ቢሆንም በዕቅዱ መሰረት በዓመት 400 ሺህ ሄክታር መሬት ለማከም ወደ 5 ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት፡፡ ከበጀት አንጻር ይህን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በየዓመቱ ከመንግሥት ካዝና ማግኘት ከባድ በመሆኑ ከእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች፣ ከአጋር አካላት ድጋፍ ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን ነው ያስታወቁት። ምንም እንኳን በአሲዳማነት የተጠቃውን አፈር ማከም ወጪው ከፍተኛ ቢሆንም አፈሩ ሳይታከም በቆየ ቁጥር ከምርት ውጭ የመሆን ዕድሉ እየጨመረ ስለሚሄድ አገርን የሚያሳጣው ዋጋ ከፍተኛ እንደሚሆን በውል መረዳት ያሻል። በዚህም የአፈር አሲዳማነት ጉዳይ መፍትሔ ካልተሰጠው ምርታማነትን ከ50 በመቶ እስከ 100 በመቶ ሊያሳጣ እንደሚችል ነው በግብርና ሚኒስቴር የአፈር ኃብት ልማት የአፈር ጤንነትና ለምነት ዴስክ ኃላፊው ፋኖሴ መኮንን የሚናገሩት፡፡ ከአፈር አሲዳማነት የተነሳ በየዓመቱ ወደ 9 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በኢትዮጵያ ደረጃ በስንዴ ከሚሸፈነው መሬት ብቻ እየታጣ እንደሆነ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ይህ በስንዴ ብቻ ከሚሸፈን መሬት የተወሰደ ግምት ሲሆን በገብስ፣ ጤፍ ወዘተ… ቢታሰብ ምን ያህል የምርት ማሽቆልቆል እንደሚያስከትል ማወቅ ይቻላል፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ የስንዴ ምርት በአማካይ በሄክታር እስከ 40 ኩንታል ምርት ሊሰጥ ይችላል፤ ሆኖም ግን የአፈር ጤንነቱን በመጠበቅ አስፈላጊውን ግብአት የምንጠቀም ከሆነ በሄክታር 60 ኩንታል በማምረት አገራችን የጀመረችውን ምርትና ምርታማነትን የማረጋገጥ ሥራ ማከናወን ያስችለናል ነው ያሉት፡፡ ይህንንም ከግብ ለማድረስ የግብርና ሚኒስቴር የመጀመሪያው የትኩረት አቅጣጫው የአሲዳማ አፈር ልማት መሆኑን ነው አቶ ፋኖሴ ያስረዱት፡፡ አሲዳማ አፈሩን ለመከላከል በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ባለፉት ሦስት ዓመታት 38ሺህ 369 ሄክታር መሬት በኖራ የማከም ሥራ መከናወኑ ተገልጿል። ይህ ከሚኒስቴሩ ዕቅድ አኳያ ሲታይ በጣም ዝቅተኛ አፈጻጸም ነው። የአፈር አሲዳማነትን ለማከም የግብርና ኖራ ምርት ላይ የተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች አቅርቦቱን በሚፈለገው ደረጃ ቢያቀርቡም፤ የኖራ ምርቱ በብዛት ያለበት ቦታ እና አሲዳማ መሬቱ የሚገኝበት ርቀት በተቃራኒው በመሆኑ ከትራንስፖርት አንጻር ያለው ችግር ሥራውን አድካሚ እንዳደረገው ነው የሚኒስቴሩ መረጃ የሚያመለክተው። ነገር ግን አርሶ አደሩ አንድ ጊዜ መሬቱን በኖራ ማከም ከቻለ እስከ አምስት ዓመት ሊያገለግለው ይችላል። ከዚያም በኃላ ቢሆን የተወሰነ የምርት መቀነስ እንጂ በምርታማነት ላይ የጎላ ችግር አይኖረውም ነው ያሉት። ስለሆነም ኖራን የመጠቀም ሁኔታ አቅም ያለው አርሶ አደር በግዥ መልክ እንዲጠቀም፤ አቅም የሌለው ደግሞ መንግሥት ድጋፍ በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል። እንደ ምዕራብ ኦሮሚያ ነጁ፣ መንዲ፣ ምዕራብ ወለጋ እንዲሁም በአማራ ክልል አዊ ዞን፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አብዛኛውን ወረዳዎች በአፈር አሲዳማነት ክፉኛ የተጠቁ በመሆናቸው ምርት ለመስጠት የማይችሉበት ደረጃ ላይ እየደረሱ መሆኑን አቶ ፋኖሴ ገልጸዋል። ዝዋይ፣ ሐዋሳ፣ መራቤቴ፣ ደጀን፣ ጉደርና የመሳሰሉት በመንግሥትም ሆነ በግል የግብርና ኖራ ምርት የሚቀርብባቸው ቦታዎች መሆናቸው ነው የተጠቆመው። በእነዚህ ቦታዎች የምርትና የጥሬ ዕቃ ችግር የሌለና የግብርና ኖራ ዋጋም በኩንታል እስከ 350 ብር እየተሸጠ ነው ብለዋል። የአፈር አሲዳማነት በረዥም ጊዜ የተፈጥሮ መዛባት ሂደት ውስጥ የሚከሰት እንደመሆኑ መጠን አንዴ ችግሩ ከተከሰተ በኋላ መፍትሔ በመስጠት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ወጪ እና ርብርብ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም ችግሩ ከመከሰቱ በፊት የአፈር አሲዳማነትን ለመከላከል የሚያስችሉ እርምጃዎችን መውሰድ ተገቢነት ያለው ጉዳይ እንደሆነ ነው የተጠቆመው፡፡ መንግሥት በያዘው የሌማት ትሩፋትና የግብርና ኢኮኖሚ አቅጣጫ በተለይም የስንዴ ምርት ከራስ ፍጆታ አልፎ ለሌሎች አገራት ምርቱን በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት በሚደረገው ጥረት የአፈር ምርታማነትን/ጤንነቱን መጠበቅ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑ የግድ ነው። “ለም አፈር በሌለበት ምርትና ምርታማነት የማይታሰብ ነው” የሚሉት አቶ ፋኖሴ፤ ግብርና የመሪነት ተግባሩን እንዲወጣ በቅድሚያ የአፈር ጤንነት ሊጠበቅ ይገባል ብለዋል። በመሆኑም ከዚህ በፊት ያለውን የግንዛቤ ችግርና ከአመራሩ እስከ አርሶ አደሩ ያለውን ክፍተት በመቅረፍ ችግሩን ለመቀነስ እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል። ሁሉንም ነገር ከመንግሥት መጠበቅ የለብንም የሚሉት አቶ ፋኖሴ፤ በቅድመ-መከላከል ሥራ ችግኝ በመትከል፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ በማከናወን፣ በተፈጥሮ ማዳበሪያ (ኮምፖስት) የራስን ማሳ በመንከባከብ፣ አማራጭ ሰብሎችን እያፈራረቁ በመዝራት፣ አሲዳማነትን መቋቋም የሚችሉ ተክሎችን በመምረጥ ማልማት እንዲሁም የግብርና ኖራ በመጠቀም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ አብራርተዋል። በሀገራችን በተለያዩ የምርምር ተቋማት የተሰሩ ምርምሮች እንደሚያሳዩት አሲዳማ አፈርን ለማከም የተፈጥሮ ማዳበሪያዎችን ከኖራ ጋር አቀናጅቶ በመጠቀም በዋና ዋና ሰብሎች ላይ እስከ ሁለት እጥፍ የምርት ጭማሪ ማግኘት እንደሚቻል ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በመሆኑም አርሶ አደሮች ኖራ በግዥና በብድር የሚያገኙበትን ሥርዓት በተጠናከረ አግባብ መተግበር ያስፈልጋል። ልክ እንደ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በግዥ ወይም በብድር የግብርና ኖራ በማቅረብና በአሲዳማነት የተጎዳው መሬት እንዲያገግም ማድረግ ላይ አትኩሮ መስራት ሌላው የመፍትሄ አካል ተደርጎ መወሰድ ይኖርበታል። የእርሻ መሬት አያያዝና እንክብካቤ ጉዳይ የህግ ማዕቀፍ ኖሮት በዚያ አግባብ ተግባራዊ ማድረግም በተለይ በአሲዳማነት የመጠቃት አዝማሚያ የተጋረጠበትን የእርሻ መሬት ለመታደግና የተጎዳውንም እንዲያገግም ለማከም የሚሰሩ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ያስፈልገዋል። ከዚህ ባለፈም በአንድ የእርሻ ቦታ ላይ የተለያዩ ሰብሎችን መዝራት፣ አፈር ውስጥ ህይወት ያላቸው ነገሮች እንዲኖሩ ማድረግና የአፈሩን እርጥበታማነት ማዝለቅ ተገቢ ይሆናል።
አገር በቀል ዕውቀቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታና አብሮነት
May 3, 2023 971
በጣፋጩ ሰለሞን አገራችን ኢትዮጵያ የተለያየ ቋንቋ፣ ባህልና እምነት ያላቸው በርካታ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ተቻችለው፣ ተከባብረው፣ ተዋደው፣ በአንድነትና በአብሮነት በፍቅር የሚኖርባት አገር ነች። በዚህም የብሄር ብሄረሰቦች ሙዝዬም ነች የሚል አድናቆትን ተጎናፅፋለች-ኢትዮጵያ። እነዚህ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች የራሰቸው መገለጫ የሆኑ ቱባ ባህል አላቸው። ኢትዮጵያውያን ለዘመኑ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ጥበብ መሰረት የሆኑ የአያሌ አገር በቀል ዕውቀቶች ባለቤቶች ናቸው። ባህላዊ የመድኃኒት ቅመማና የህክምና ጥበብ ኢትዮጵያ ለዓለም ካበረከተቻቸው ትሩፋቶች መካከል አገር በቀል ዕውቀቶች ተጠቃሽ እንደሆኑ የታሪክ ድርሳናትና ሌሎች የየዘርፉ ተጓዳኝ መረጃዎች ያስረዳሉ። በተለይ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የተጠቀሙባቸውና እየተጠቀሙባቸው ያሉ ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለሌሎችም ጭምር በአርዓያነት የሚጠቀሱ ናቸው። በጂንካ ዩኒቨርስቲ 5ኛው አገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፈረንስ ሰሞኑን ተካሂዷል። በኮንፈረንሱ በአገር በቀል ግጭት አፈታት ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም፣ለአብሮነት ትስስር እና ለአገራዊ ዕድገት ያላቸው ሚና የሚል እሳቤን ዓላማ ያደረገ ጥናት ቀርቧል። ጥናቱ እ.ኤ.አ ከ2018 እስከ 2022 ባሉ ዓመታት በመስቃን እና በማረቆ ህዝቦች ባህላዊ የግጭት አፈታት ላይ መሰረት አድርጎ የተካሄደ ነው። ጥናቱን ያካሄዱት "አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለሰላም፣ ለፀጥታ እና ለዕድገት ያላቸው አስተዋፅኦ፤The Role of Indigenous conflict resolution Mechanism for peace,Security ,and Sustainable Development in Ethiopia " በሚል ርዕስ ያካሄዱት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ ዮሐንስ ተስፋዬ ናቸው። የጥናቱ ግኝት እንደሚያመለክተው ዘመናትን ተሻግረው እዚህ የደረሱ የሰላም ግንባታና ማጠናከሪያ የሆኑ አገር በቀል ዕውቀቶች አሁን ለደረስንበት ሳይንሳዊ ጥበብ መጎልበት እያገለገሉ ነው። የጥናት አቅራቢው ለኮንፈረንሱ ታዳሚዎች እንዳብራሩት ጥናቱ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ለአብሮነትና ለዕድገት አይተኬ ሚና አላቸው። እነዚህን አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች በአግባቡ መጠቀም ይገባል። እሳቸው እንዳብራሩት በአገራችን ሶስት አይነት የግጭት አፈታት ዘዴዎችን እንጠቀማለን። የወንጀልና የፍትሐብሔር ህጎች፣ እንደ ሽምግልና ያሉ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች እና ከሃይማኖታዊው ደግሞ ሸርዓ ከምንጠቀምባቸው የግጭት መፍቻ ዘዴዎች ግንባር ቀደም ተጠቃሾች ናቸው። ተመራማሪ ዮሐንስ እንዳሉት ጥናቱ በተካሄደበት በጉራጌ ዞን በመስቃን እና በማረቆ መካከል አጋጥሞ የነበረውን አለመግባባት ከመፍታት አኳያ ከዘመናዊ እውቀቶች ይልቅ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ትልቅ ሚና ነበራቸው። በመስቃን እና በማረቆ ያጋጠመውን አለመግባባት ለመፍታት ከመስቃን፤ ከማረቆ እንዲሁም ከአጎራባች የኦሮሚያና ስልጤ ዞኖች የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ተሳትፈዋል። በመስቃን እና በማረቆ መካከል ያጋጠመውን አለመግባባት ለመፍታት የተሳተፉት የሀይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች ግጭቱን ለመፍታት የተጠቀሙት ጥበብ አገር በቀል ዕውቀቶች በዘመናዊ ህግና አሰራር የማይቻሉትን የመፈጸምና ማህበራዊ አንድነትን ከማጠናከር አንፃር ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የጥናቱ ግኝት አመላክቷል። አለመግባባቱን ለመፍታት 26 ዙር ለመሸምገል ተቀምጠዋል። በማሸማገሉ ሂደት የተሳተፉት የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሁለቱን ማህበረሰቦች ለማቀራረብና በአካባቢው እረቀ-ሰላም ለማወርድ የከፈሉት መስዋዕትነት ቀላል አለመሆኑን በአጽኖኦት አስረድተዋል። የትኛውንም ውጣ ውረድና ጫና ተቋቁመው ሳይታክቱ ችግሩን የፈቱበት መንገድ ለዘመናዊው አስተዳደር ትምህርት የሚሰጥና በቅርስነት ለትውልድ የሚተላለፍ ሰናይ ተግባር መሆኑንም አስረድተዋል። ግጭቶች ቀደም ሲል የነበሩ፣ አሁንም ያሉና ወደፊትም የሚኖሩ ናቸው። በተለያዩ ምክንያቶች የሚያጋጥሙ ግጭቶችን ፖለቲካዊ ትርጉም በመስጠት ከማጦዝ ይልቅ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን ተጠቅሞ ለማርገብ መስራት አዋጭና ተመራጭ መንገድ መሆኑን የጥናቱን ግኝት ዋቢ አድርገው ተመራማሪ ዮሐንስ መክረዋል። ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ለአገር በቀል እውቀቶች ተገቢውን ዕውቅና መስጠት ይገባል። አገር በቀል ዕውቀቶችን በትምህርት ሥርዓት ውስጥ አካቶ ለማጎልበት የተጀመረው አበረታች ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል። አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ከቂም በቀል በፀዳ መልኩ አብሮነትን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ትልቅ አስተዋጽኦ አላቸው ያሉት ደግሞ የጂንካ ዩኒቨርስቲ የባህል ተመራማሪና የዩኒቨርስቲው የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ኤሊያስ ዓለሙ ናቸው። አክለውም ዘመናዊ ሕግን ተከትሎ በሚሰጡ ብያኔዎች አንዱ ወገን የሚደሰትበት ሌላኛው ደግሞ ቅር ተሰኝቶ የሚከፋበት ናቸው ይላሉ። በማህበራዊ ሸንጎ ግን ሁለቱም ወገን የሚደሰቱበት፣ ከልብ ይቅር ተባብለው ችግሮቻቸውን የሚፈቱበትና ዘላቂ እርቀ-ሰላም የሚያወርዱበት እንደሆነም ያስረዳሉ። ዶክተር ኤሊያስ አክለውም ይህም ማህበራዊ አንድነት ለማጠናከር ፋይዳው የላቀ ነው። የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን ለመፍታትና በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በአገራችን ቱባ ባህሎች ውስጥ ያሉ አገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎችን መጠቀም ይገባል። በባህላዊ እሴቶቻችን ውስጥ ያሉ አገር በቀል ዕውቀቶች ቀጣይነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ እንዲውሉና ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆኑ ዕውቅና መስጠት፣ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ማካተት፣ በአግባቡ አደራጅቶና ሰንዶ ለትውልድ ማስቀመጥ እንደሚገባ አመላክተዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራን የሚጠበቅብንን ኃላፊነት በአግባቡ ልንወጣ ይገባል ይላሉ። አቶ መምህሩ ገዙሜ በጂንካ ዩኒቨርስቲ በሶሻል አንትሮፖሎጂ የትምህርት ክፍል የሶሽዮሎጂ መምህር ናቸው። አገር በቀል ዕውቀቶች ለአገራዊ ችግሮቻችን መፍቻ መንገዶች ናቸው ይላሉ። የሳይንሳዊ ምርምሮች ፅንሰ-ሀሳብ መነሻው አገር በቀል ዕውቀቶች እንደሆኑ ይጠቅሳሉ። በአገራችን በርካታ አገር በቀል ዕውቀቶች ቢኖሩም እንዳለመታደል በአግባቡ መጠቀም አልቻልንም ሲሉም ያክላሉ። እሳቸው እንዳሉት መንግሥት አሁን ለአገር በቀል ዕውቀቶች የሰጠው ዕውቅና ለአገር በቀል ዕውቀቶች መጎልበትና ጥቅም ላይ መዋል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ይህን ዕድል በመጠቀም አገር በቀል እውቀቶች ጎልተው እንዲወጡና በትምህርት ሥርዓቱ ተካተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መስራት ይገባል። በተለይ የማህበረሰቡ የግጭት አፈታት ዘዴና በምክክር ችግሮችን የመፍታት ጥበብ የታሰበው አገራዊ የምክክር መድረክ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። በመሆኑ አገር በቀል ዕውቀቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ፣ ለኢትዮጵያውያን የአብሮነት ትስስርና መስተጋብር መጠንከር እንዲሁም ለአገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና እጅግ የላቀ ድርሻ ያላቸው መሆኑን ተገንዝቦ ተገቢውን ዕውቅና በመስጠት መጠቀም ይገባል።
የሽግግር ፍትህና የአፍሪካውያን ተሞክሮ
Apr 2, 2023 1517
የሽግግር ፍትህና የአፍሪካውያን ተሞክሮ በሰለሞን ተሰራ በታሪክ ተመዝግበው የምናገኛቸው አያሌ መልካምና በጎ ነገሮች የመኖራቸውን ያህል በተቃራኒው ደግሞ የሰው ልጆች ግፍና በደል ሲፈጽሙና ሲያስተናግዱ ኖረዋል። በዚህም በተለይ በበደሉ ገፈት ቀማሾች ላይ የሚደርሰው ድንጋጤ፣ ሰቆቃና ሀዘን ሰዎችን ለበቀል እያነሳሳ ሌላ ጥፋት ሲያስከትል ማስተዋልም እንግዳ ነገር አይደለም። በዚያው ልክ ሰዎች የደረሰባቸውን ግፍና መከራ ለማራገፍ ፍትህን ሲሹና ሲጠይቁ ይስተዋላል። እምባቸው የሚታበሰው፣ ቁስላቸው የሚሽረው ለደረሰባቸው በደል ካሳ የሚሆን ፍትህ ሲያገኙ ብቻ እንደሆነም ያምናሉ። በርካታ አገራትም በታሪክ ውስጥ ላጋጠሟቸው ስብራቶች የሽግግር ፍትህን አማራጭ አድርገው በመጠቀም ለችግሮቻቸው መፍትሄ ያበጃሉ። እኤአ በ1970 ዎቹ መጀመሪያ በምስራቅ አውሮፓ እና ደቡብ አሜሪካ ተግባራዊ በተደረገው የሽግግር ፍትህ በጦርነትና በግፍ አገዛዝ የተበደሉ አካላት ፍትህ እንዲያገኙ የተደረገበት መንገድ ተጠቃሽ ነው። ከዚህ ጊዜ በኋላ የሽግግር ፍትህ በተለይ በመደበኛ የህግ ስርአት ብቻ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስቸግሩ ጉዳዮችን ጭምር በተጠያቂነት፣ በይቅርታ፣ በካሳ ወዘተ መፍትሄ በመስጠት የፍትህ ማስፈኛ መንገድ ተደርጎ ተወስዷል። የሽግግር ፍትህ ማለት በማህበረሰቡ ውስጥ በስፋት ለተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ምላሽ የሚሰጥበት አካሄድ መሆኑን ምሁራን ያስረዳሉ። ይህንን ሂደት ሰላማዊ፣ አካታችና ተደራሽ ለማድረግ የሁሉም ጥረትና አጋርነት ቀዳሚ መነሻ ሊሆን እንደሚገባውም ይገልጻሉ። የሽግግር ፍትህ በአንድ ጊዜ የሚያልቅ ሳይሆን ጊዜ የሚጠይቅና ዓመታትን ሊወስድ የሚችል ነው። ይህም ለተበዳዮች ፍትህ በመስጠት፣ ካሳ በመክፈል፣ የወደሙ ንብረቶችን መልሶ በመገንባትና በመሰል ሂደቶች ሊፈጸም ይችላል። የሽግግር ፍትህ ሀገራት ከብጥብጥ፣ ከፀብና ጥላቻ አዙሪት እንዲወጡ በማድረግ በኩል የማይተካ ሚና እንዳለው የተለያዩ ሀገራት ተሞክሮዎች ያሳዩናል። በ2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ የፀደቀው የአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ማዕቀፍ፣ የሽግግር ፍትህ ሀገራት የተለያዩ መደበኛ እና ባህላዊ ወይም መደበኛ ያልሆኑ የፖሊሲ እርምጃዎችንና ተቋማዊ አሠራሮችን በመጠቀም የተፈጸሙ ጥሰቶችን፣ ክፍፍሎችንና አለመመጣጠኖችን ለማስወገድና ለደኅንነትም ሆነ ለዴሞክራሲያዊና ማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሥርዓት ግንባታ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የሚደረግ ጠቃሚ እና አስፈላጊ ሂደት እንደሆነ ይገልጻል። የሽግግር ፍትህ በግጭት፣ በጦርነት ወይም ጨቋኝ ሥርዓት በነበረበት ወቅት ለተፈፀመ ጥቃት፣ መጠነ-ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና በደል የተሟላ መፍትሄ መስጠት መቻል ነው። ይህም በዋናነት ሙሉ ፍትህ የሚሰጥበትን መንገድ በመዘርጋት ዘላቂ ሰላም፣ እርቅ፣ መረጋጋት እና የህግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት መገንባት የሚቻልበትን ሁኔታ የሚመለከት ነው። በኢትዮጵያ ተግባራዊ ሊደረግ የታሰበውና በፖሊሲ አማራጭ ዝግጅት ሂደት ላይ የሚገኘው የሽግግር ፍትሕ በአራት ዋና ዋና ምክንያቶች አስፈላጊ መሆኑን ፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል። አንደኛው ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሀገራዊ አውድ ሲሆን በዚህም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ አለመረጋጋት፣ ግጭትና የእርስ በርስ ጦርነት ተከስቷል። ይህም ዜጎችን ለሞት፣ ለአካል ጉዳት፣ ለመፈናቀል ያጋለጠ መሆኑ በገፊ ምክንያትነት ይጠቀሳል። ለነዚህ ችግሮች ከዚህ በፊት የተሰጡ ምላሾች ሙሉ አለመሆናቸው የአጥፊዎችና የተጎጂዎችን ቁጥር ማብዛቱ፣ የበደሎች መደራረብ እና የጥፋቶች ማህበረሰባዊ ቅርጽ መያዝ በመደበኛው የፍትሕ ሥርዓት እና አካሄድ ፍትሕ መስጠትንም ሆነ ይቅርታ እና እርቅን ማከናወን አላስችል ማለቱ የሽግግር ፍትህ ትኩረት እንዲሰጠው አድርጓል። ሁለተኛው የተሳካ የሽግግር ፍትሕ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ ማለትም ባለፉ በደሎች ይቅር ለመባባል፣ እርቅ ለማውረድ፣ ሕዝብ ለማቀራረብ፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እና ለተፈጸመ በደል እውቅና ለመስጠት አስፈላጊ በመሆኑ ነው። ሶስተኛው ምክንያት የተሳካ የሽግግር ፍትሕ ሂደት ሳይተገበር የዴሞክራሲ ሽግግርም ሆነ ዘላቂ ሰላም ማስፈን አይቻልም የሚል ነው። የመጨረሻው በገፊ ምክንያትነት የሚጠቀሰው ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር እና የሕግ የበላይነትን ለማስፈን የሽግግር ፍትህ ወሳኝ በመሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በነዚህ ምክንያቶች የሽግግር ፍትሕን ለማስፈን እየሰራች መሆኑ በበርካቶች ዘንድ በአዎንታዊ መልክ ይጠቀሳል። በተለይ የሽግግር ፍትህን ተግባራዊ ካደረጉ አገራት ተሞክሮ በመውሰድ ለውጤታማነቱ ከተሰራ በርግጥም አይነተኛ መፍትሄ ነው። ከአፍሪካ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴራሊዮን፣ ላይቤሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ በቅርቡ ደግሞ ጋምቢያ የሽግግር ፍትህን ለችግሮቻቸው መፍቻነት ከተጠቀሙ አገራት መካከል ናቸው። ሩዋንዳ ሩዋንዳ እኤአ በ1994 በመቶ ቀናት ብቻ ከነበሯት 7 ሚሊዮን ዜጎቿ 800 ሺዎቹን በግፍ ተነጥቃለች። 2 ሚሊዮን የሚጠጉት በስደት ሀገራቸውን ለቀው ሲወጡ በዚህ የጭካኔ ተግባር ተሳትፎ ነበራቸው የተባሉ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ላይ ክስ በመመስረት ፍትህ ፊት አቅርባቸዋለች። በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት በሀገር ውስጥ ችሎትና በባህላዊ መንገድ በተዳኙት ወንጀለኞች ላይ የተሰጡት የፍትህ ውሳኔዎች አሁን ላይ ሀገሪቱን በዲሞክራሲና በሰላም እንዲሁም በብልፅግና መንገድ መራመድ እንድትችል አድርጓታል። ሩዋንዳውያን በቆየ ሀገራዊ ብሂላቸው ”ሁላችንም የአንድ አባትና እናት ልጆች ነን ይላሉ”። ይህንኑ ብሂል መመሪያቸው በማድረግ በሀገሪቱ ያሉት “ቱትሲ” እና “ሁቱ” የተባሉት ዋነኛ ብሄሮች በአብሮነት ለዘመናት ኖረዋል። ሩዋንዳ በጀርመን የቅኝ አገዛዝ ስር እንደወደቀች የዘር ልዩነቱን ወደፊት ያመጡት ቅኝ ገዥዎች ሁለቱን ብሄሮች የሚያጋጩ ሴራዎችን በመጎንጎን ቱትሲዎችን መግደል የፖለቲካቸው ስልት ማስፈጸሚያ አደረጉት። ይህ ከፋፋይ የፖለቲካ ሴራ በቤልጂየም የእጅ አዙር አገዛዝ ዘመንም እንደቀጠለ ይነገራል። በዚህም ማንነትን መሰረት ያደረገ የፖለቲካ አደረጃጃት፣ የመታወቂያ ወረቀት፣ ቱቲስዎችን በስልጣን ወደፊት ማምጣትና ሁቱዎችን አሳንሶ መመልከትን ባህል አደረጉት። በዚሁ መርዘኛ ሀሳብ መነሻነት ከነጻነት በኋላ እኤአ ከ1959 እስከ 1967 አካባቢ በመንግስት በተደገፈ የዘር ማጥፋት 20ሺ የሚጠጉ ቱትሲዎች ሲገደሉ 300ሺ የሚጠጉ ሀገራቸውን ለቀው ተሰደዱ። በዚህም እኤአ በ1987 በቱትሲዎችና ለዘብተኛ ሁቱዎች የተቋቋመው የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር እኤአ በ1993 የመንግስትን ስልጣን ለመጋራት በቃ። ነገር ግን እኤአ በሚያዚያ 6 ቀን 1994 የሀገሪቱ መሪ የነበሩት ሃባይሪማና በቅጥረኞች በመገደላቸው በሀገሪቱ አመጽ እንዲቀጣጠል ምክንያት ሆነ። ይህን ተከትሎ “ኢንተርሀሞይ” በመባል የሚጠራው የሚሊሽያ ቡድን በቱትሲዎችና በለዘብተኛ ሁቱዎች ላይ ዘመን የማይሽረው ግፍና ጭካኔ በመፈጸም 800ሺ የሚጠጉትን ከምድር ላይ ለዘለአለሙ አሰናብቷቸዋል። ይህ ደግሞ የዘር ማጥፋት ወንጀል በመሆኑ አጥፊዎቹ በተለያዩ የፍትህ አደባባዮች ተከሰው ቅጣታቸውን ለመቀበል በቅተዋል። ነገር ግን ይህ ብቻውን በህዝቡ ውስጥ ስር የሰደደውን ቁስል እንዳማይሽረው በመታመኑ ሩዋንዳ የሽግግር ፍትህን በመከተል አመርቂ ስራ ሰርታለች። በተለይም ክስና ይቅርታ ትልቅ ቦታ ነበራቸው። በክስ ሂደቱ ሁሉንም ተጠያቂ ማድረግ ቢከብድም በዋናነት ተሳታፊ የነበሩትን በመለየትና ተጠያቂ በማድረግ ፍትህ እንዲሰፍን ተደርጓል። መንግስት ውጫዊና ውስጣዊ ግፊት ቢበዛበትም ከፍተኛ ግፍ የፈጸሙትን በመለየት እንዲቀጡ አድርጓል። ይቅርታውንም በተጠና መንገድ በማከናወን ለጥቂቶች ምህረት አድርጓል። በጊዜ ሂደት የእስራት ጊዜአቸውን ላገባደዱ፣ ለአዛውንቶች፣ ለታማሚዎችና ለወጣቶች ምህረት በማድረግ ቁርሾው እንዲሽር ተደርጓል። ምህረት የተደረገላቸው ሰዎች ስለብሄራዊ እርቅ፣ አብሮነት፣ ሀገራዊ ማንነትና ሰብዓዊ ክብር እንዲማሩ በማድረግ እርቁን ሙሉ ማድረግ ተችሏል። የሩዋንዳ የሽግግር ፍትህ በዋናነት እውነትን ማፈላለግ፣ ነገሮችን መልሶ ማስታወስ ወይም የመታሰቢያ ቦታዎችን በመመስረትና ቀን በመሰየም ሁኔታው ታስቦ እንዲውል ማድረግ፣ መልሶ ማቋቋምና እርቅ ማውረድ የተቋማት ማሻሻያ ማድረግ ላይ ያተኮረ ነበር። ሴራሊዮን እኤአ ከ1991 አስከ 2002 የዘለቀው የሴራሊዮን የእርስ በርስ ግጭት በትንሹ የ100ሺ ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ አልፏል። ሌሎች በ100ሺ የሚቆጠሩ ዜጎችን ለከፋ የአካል ጉዳት፣ ድህነትና የአዕምሮ መቃወስ ዳርጓል። ግጭቱ የተጀመረው ራሱን “የተባበሩት አብዮታዊ ቡድን” ብሎ በሚጠራው የታጣቂዎች ስብስብ ሲሆን በወቅቱ ቡድኑ በላይቤሪያ መንግስት ይደገፍ እንደነበር ይነገራል። የተቃውሞአቸው መነሻ ደግሞ የመንግስት ብልሹ አስተዳደር፣ የገጠሩ ማህበረሰብ ከኢኮኖሚና ፖለቲካ ተሳትፎ መገለል እና መጠነ ሰፊ የህግ ጥሰቶች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ። የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሃብት በተለይም የአልማዝ ማዕድኗን በህገወጥ መልኩ ሲበዘብዙ የነበሩ አመራሮች ቁርሾውን በማባባስ ህልውናቸውን ለማስቀጠል ቢጥሩም እኤአ በ2002 በተደረሰ የሰላም ስምምነት ከ 76 ሺ ያላነሱ ታጣቂዎች መሳሪያቸውን በማስረከብ ህብረተሰቡን እንዲቀላቀሉ ተደርገዋል። በዚያው ዓመት የሴራሊዮን የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን የተቋቋመ ሲሆን በተመሳሳይ የሴራሊዮን ልዩ ችሎት ተመስርቷል። ሴራሊዮን በእርስ በርስ ግጭት ውስጥ በነበረችባቸው 12 ዓመታት አራት መፈንቅለ መንግስት የተካሄደባት ሲሆን የስልጣን መንበሩን የተፈራረቁበት የተለያዩ ወታደራዊ አመራሮች ለችግሩ መፍትሄ ከማበጀት ይልቅ በቤንዚን ላይ እሳት የሚያርከፈክፉ ሆነው ታይተዋል። በሴራሊዮን ለደረሰው እልቂት እኩል ኃላፊነት የሚወስዱት መንግስትና ታጣቂዎች በወቅቱ ሴቶችን በመድፈር፣ ህፃናትን በግዳጅ ለጦርነት በመመልመል፣ ንብረት በማውደምና በ100ሺ ለሚቆጠሩ ሰዎች መሞት ተጠያቂ ተደርገዋል። ከዚህ ባለፈ በቅድሚያ ታጣቂዎችን የጦር መሳሪያ ለማስፈታት የተሄደበት ርቀት ለሰላም መስፈን ትልቅ እገዛ ማድረጉ የሚገለጽ ሲሆን ከ70 ሺ ያላነሱ ታጣቂዎችን መሳሪያ ማስፈታት መቻሉ ግጭቱን ለማስቆም በራሱ ታላቅ ስኬት ነበረው። በወቅቱ ግፉን የፈጸሙት ታጣቂዎች በመንግስት ቅጣታቸውን እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን ህብረተሰቡም ወንጀለኞችን ከማህበረሰቡ በማግለል የስነ ልቦና ቅጣት እንደጣለባቸው መረጃዎች ያሳያሉ። በዚህም ታጣቂዎቹን ወደ ህብረተሰቡ መልሶ ለመቀላቀል የተደረገው ጥረት በፈተና ቢታጀብም በህዝቡ ይሁንታ ውጤታማ ሆኗል። በሴራሊዮን የሽግግር ፍትህን ለማስፈን የተቋቋሙት የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን፣ የሴራሊዮን ልዩ ፍርድ ቤት፣ በፀጥታ ተቋማት ላይ የተደረገው ማሻሻያ፣ የመልሶ ማቋቋምና የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ምስረታ ከፍተኛ አበርክቶ ነበራቸው። የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን በተሰጠው ስልጣን መሰረት ተጎጂዎችን ከሰቆቃ መታደግና ችግሩን በዕርቅ መፍታት፣ ብዙሀኑ ላይ ለደረሰው ግፍ ምላሽ መስጠት፣ ግፉ በቀጣይ እንዳይደገም መፍትሄ ማበጀት ላይ አተኩሮ ሰርቷል፡፡ በዚህም ከተጎጂዎች ቃለ ምልልስ በመነሳት በደረሰበት ድምዳሜ የመንግስት አካላት የመልካም አስተዳደር መጓደል፣ ሙስና፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ከነፃነት በኋላ የነበረው አመራር ብቃት ማነስ ለብጥብጡ መንስኤ እንደሆነ አመላክቷል። ልዩ ፍርድ ቤቱም በቅድሚያ ተጎጂዎችን ሰብስቦ በማናገር እንዲሁም የሲቪል ማህበራትን ህብረተሰቡንና መገናኛ ብዙሃንን በማካተት ሁሉንም የሚያስማማ ውሳኔ በመስጠት ችግሩ ከቂም በቀል በፀዳ መልኩ መፍትሄ እንዲያገኝ አስችሏል። የመልሶ ማቋቋም ሂደቱ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበርና ልዩ በጀት በመመደብ የተከናወነ ሲሆን የተጎጂዎችን ሰቆቃ ሊጠግን በሚችል መልኩ መተግበሩንም ብዙዎች ይመሰክራሉ። በዚህም ተጎጂዎች ነፃ የጤና አገልገሎት፣ ትምህርት፣ መኖሪያ ቤትና መቋቋሚያ እንዲያገኙ ተደርጓል። በአብነት የተነሱት የሩዋንዳና ሴራሊዮን ተሞክሮዎች የሽግግር ፍትሕ መልከ ብዙ ግጭቶችን ያስተናገዱ ሀገራት የተሻለ ነገን እንዲገነቡ ሁነኛ መፍትሔ ስለመሆኑ አመላካች ናቸው። በተመሳሳይ የሽግግር ሂደት ያለፉና ተሞክሮ ያላቸው የደቡብ አፍሪካ እና ጋምቢያ ምሁራንም ይህንኑ እውነት የሚያረጋግጥ ሀሳባቸውን ለኢዜአ ሰጥተዋል። በደቡብ አፍሪካው ፍሪታውን ዩኒቨርሲቲ የፍትሕና ዕርቅ ኢንስቲትዩት ኃላፊ እና በአፍሪካ ጥናትና ምርምር የካበተ ልምድ ያላቸው ፕሮፌሰር ቲም ሙሪቲ በአፍሪካ ሽግግር ፍትህ ዙሪያ ጥልቅ ምርምር አድርገዋል። ኢትዮጵያ ታሪካዊና የአፍሪካ ተምሳሌት ሀገር ናት የሚሉት ፕሮፌሰሩ፤ የገጠማትን ችግር ለመፍታት የሽግግር ፍትህ ሂደት መጀመሯን አድንቀዋል። የሽግግር ፍትሕ መልከ ብዙ ግጭትና ግፎችን ባሳለፉ ማህበረሰቦች ትናንትን በይቅርታ የነገውን ተሰፋ ለመሻገር አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን በማንሳት ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ፣ ባርነት እና ቅኝ ግዛት የጭቆና ስርዓት ነጻ ስትወጣ ስርዓቱ በጥቁሮች ላይ ለፈጸመው ግፍ፣ መገለልና ብዝበዛ መፍትሄ ለመስጠት ሽግግር ፍትህ ሂደት መተግበሩን ይጠቅሳሉ። ፕሮፌሰር ሙሪቲ፤ የወቅቱ ፕሬዝዳንት ኔልሰን ማንዴላ በጥቁሮች ላይ የተፈጸሙ በደሎችን በሽግግር ፍትህ ሂደት መልክ ለመስጠት ብሎም ህዝባዊ አብሮነት እንዲቀጥል በሊቀጳጳስ ዴዝሞንድ ቱቱ መሪነት የዕውነትና ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን መቋቋሙን ያስታውሳሉ። የሽግግር ፍትሕ ሂደቱ ከአፈጻጸም ጋር የተያያዙ ክፍተቶች ቢኖሩበትም አካታችና የአገሪቱን የቀጣይ ጉዞ ለመቀየስ መሰረት የጣለ እንደነበር ገልጸዋል። ይህም ኢትዮጵያ ተሞክሮ ልታደርገው የምትችለው ነው ይላሉ። በጋምቢያ በቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ያህያ ጃሜህ ዘመነ መንግስት ለ22 ዓመታት የተፈጸሙ ግፎችን በሽግግር ፍትህ ሂደት የፈቱት የዕውነት፣ ዕርቅና ካሳ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ጋምቢያዊው ዶክተር ባባ ጋሌህ ጃሎው፤ የሽግግር ፍትህ አስፈላጊነት በተለይም ኢትዮጵያን ለመሰሉ ሀገራት አጠያያቂ አለመሆኑን ይላሉ። በተመሳሳይ በጋምቢያ አምባገነን መንግስት የተፈጸሙ በደሎችን መልክ ለማስያዝ የተቋቋመው የዕውነት፣ ዕርቀ ሰላምና ካሳ ኮሚሽን ዜጎች ዕውነቱን እንዲረዱ፣ በዳዮች እንዲጠየቁና ተበዳዮች እንዲካሱ የሚያስችል ሰነድ ለሀገሪቷ መንግስት ማቅረቡን ዶክተር ባባ ጋሌህ ይገልጻሉ። እነዚህ ምሁራን ኢትዮጵያ ለማድረግ ያሰበችው የሽግግር ፍትህ ሂደት ከአፍሪካ ሕብረት የሽግግር ፍትሕ ፖለሲ እና የሀገራትን ልምድ የቀመረ፣ አካታች፣ ተበዳዮችን የሚክስና ሀገርና ህዝብ ወደፊት በሚያሻግር አግባብ እንዲፈጸም አስተያየታቸውን ጠቁመዋል። ለዚህ ደግሞ ምሁራኑ ያላቸውን ልምድና ተሞክሮ ለሚመለከተው አካል እንደሚያጋሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያውያን ባለፉት ጥቂት ዓመታት በህዝቦች የተባበረ ክንድ ለውጥ በማምጣት አዲስ ምእራፍ የጀመርንበት፣ አዲስ መንግስት ስልጣን ተቀብሎ ያለፉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በይፋ በማመን ይህንኑ ለማሻሻል ቃል የገባበት፣ የዲሞክራሲ ሽግግር ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት የተጀመሩበት እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያት የደረሱ በደሎችን በሽግግር ፍትህ ለማለፍ መንገድ የጀመርንበት ወቅት ላይ መሆናችን ይታወቃል። የሽግግር ፍትህ የተበዳዮችን እምባ ከማበስ ባለፈ ሁሉን አቀፍ መፍትሄ በማስቀመጥ ከቂም በቀል የጸዳ ትውልድ ለመፍጠርና ለአገረ መንግስት ግንባታ በጋራ ለመሰለፍ መፍትሄ መሆኑን ከላይ የተጠቀሱት አብነቶች ምስክሮች ናቸው። ለአፍሪካ ጉዳዮች አፍሪካዊ መፍትሄን የምታስቀድመው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገራት ተሞክሮዎችን በመቀመር፣ ካለፈችባቸው መንገዶች ትምህርት በመውሰድ፣ ውጤታማ የሆነ የሽግግር ፍትህ ስርዓትን እውን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል። የሽግግር ፍትሕ በተለይም በሽግግር ላይ ያሉ ሀገራት ህዝቦች ከነበሩበት ግጭት እንዲሁም ከደረሰባቸው ግፍ እና ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ወጥተው ወደ አዲስ ሰላማዊ እና አብሮነት ጉዞ ለመጀመር የሚደረግ የፍትሕ ክዋኔ አይነት በመሆኑ በትኩረት ሊሰራበት ይገባል።
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 2601
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
ትንታኔዎች
የረቂቅ ሙዚቀኛዋ መናኒት ሲታወሱ
Jun 2, 2023 95
የረቂቅ ሙዚቀኛዋ መናኒት ሲታወሱ አየለ ያረጋል መንደርደሪያ... እማሆይ ጽጌማርያም 'ዓለም በቃኝ' ብለው በምንኩስና ሕይወት መንነዋል። በቅድመ ምነናም ሆነ ድሕረ ምነና ሕይወታቸው ግን በረቂቅ ሙዚቃ ከመራቀቅ ቦዝነው አያውቁም ነበር። ለዚህ ነው 'የረቂቅ ሙዚቃ ተራቃቂዋ መናኒት' የሚሰኙት። በእማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ ፋውንዴሽን ድጋፍ ሰሞኑን በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 'ዝክረ እማሆይ ጽጌማርያም' መርሐ ግብር ተደርጎ ነበር። የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች መርሐ ግብሩን አሰናድተዋል። በሕይወት ዘመናቸው ከ300 በላይ የረቂቅ ሙዚቃ ስራዎችን ለአድማጭ ጆሮ ያበረከቱት እማሆይ ጽጌማርያም ያረፉት ባሳለፍነው መጋቢት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ነበር። ስርዓት ቀብራችው የተፈጸመውም ለ40 ዓመታት በገዳማዊ ሕይወት በኖሩባት ሀገረ-እስራኤል ኢየሩሳሌም ነው። የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሙዚቃ ትምህርት ክፍል ስያሜውን 'እማሆይ ጽጌማርያም የሙዚቃ ትምህርት ክፍል' በሚል ሰይሟል። እኛም እማሆይን በወፍ በረር መዘከር ወደድን!! የ'የውብዳር' ሙዚቃ ልክፍት ሙዚቃ ኅይል ነው-ውስጥን የሚፈነቅል፤ መንፈስን የሚሰረስር። የየውብዳር የሙዚቃ ውበትና ቃና ልክፍትም በዘመነ ደቂቅነት የተጸነሰ ነው። የሙዚቃ ፍቅራቸው ጠሊቅ፣ ስራቸውም ረቂቅ ነው። ግና በጨቅላነት የ'ግዳይ ጣይ' አዳኞችን ባህላዊ ዜማ ተከትለው ሮጠዋል። በቤተ ክርስቲያን ማህሌታዊ ዜማዎች ቀልብና ልባቸው ተማርኳል። የልጅነት ዕዝነ ልቦናቸው በሙዚቃ ቃና ተለክፏል። የደቂቅነት ዐይነ ልቦናቸው ተፈጥሯዊ ውበት በረቂቅ ሙዚቃ እንዲራቀቁ ሰበብ ሆኗቸዋል። 'ከሰፈር እስከ ማዶ-ሀገር' ኑረታቸው በዕዝነ ልቦናቸው ያቃጨለ የድምጽ ርግብግቢት በረቂቅ ሙዚቃ እንዲመንኑ መሰረት ሆኗቸዋል። የየውብዳር ዑደት ሕይወት ከዓለማዊ ወደ ሰማያዊ ሕይወት ብቻ ሳይሆን በመሳሪያ ወደ ተቀነባበሩ ረቂቅ ሙዚቃ ዳርቻም መንኗል። የወላጅ እናታቸው ካሳዬ የለምቱ በገና ደርዳሪነት፣ የአባታቸው ከንቲባ ገብሩ ደስታ የረቂቅ ሙዚቃ አጣጣሚነት በሙዚቃ ጣዕም የመለከፋቸውን ልክ አንሮታል። ሙዚቃን "የስሜት መግለጫ ቋንቋዬ፤ የሀዘንና ደስታዬ ጓድ” ይሉታል-የኋላዋ እማሆይ ጽጌማርያም፤ የያኔዋ የውብዳር ገብሩ! እማሆይ ጽጌማርያም ውልደታቸው ከደህና ቤተሰብ መደብ ነው። አባታቸው ከንቲባ ገብሩ ደስታ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ጉልህ አሻራ አላቸው። ዕውቁ የታሪክ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ከንቲባ ገብሩ ደስታን ከ20ኛው ከፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ትምህርት ፋናወጊዎች መካከል አንዱ ናቸው ይሏቸዋል። በአጼ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግስት በጣና ሐይቅ ምዕራባዊ ዳርቻ አለፋ ጣቁሳ የተወለዱት ገብሩ ደስታ ገና በልጅነታቸው በሚሲዮናዊያን ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ተወስደው የተማሩ፤ በተለያዩ ሀገራት ተዘዋውረው ያስተማሩና በኋላም ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው ከአጼ ዮሐንስ እስከ አጼ ኅይለስላሴ ዘመነ መንግስት ሀገራችውን ያገለገሉ ጎምቱ ባለታሪክ ናቸው። ከንቲባ ገብሩ ደስታ የሀረር እና የጎንደር ከንቲባ፤ በአሜሪካና በአውሮፓ ሀገራት የዲፕሎማቲክ ልዑክ መሪ፣ የመጀመሪያው ሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ በኋላም ዋና አፈ ጉባዔ ነበሩ። ከንቲባ ደስታ በየዘርፋቸው ኢትዮጵያን ያገለገሉ ልጆችን በእግራቸው ተክተዋል። ኮሎኔል ዳዊት ገብሩ፣ ገነት ገብሩ፣ ደስታ ገብሩ፣ የውብዳር ገብሩና ስንዱ ገብሩ ተጠቃሽ ናቸው። የውብዳርም የሕይወት ውጣውረድና አቀበት አልፈው፤ መክሊታቸውን ፈልገው የኖሩ ተምሳሌታዊ መናኒት ሆነዋል። ልደታቸው ታኅሣሥ 13 ቀን 1916 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ነበር። ገና በ6 ዓመታቸው በኋላ የጦር አርበኛ፣ ፀሐፊ ተውኔት፣ ደራሲ፣ የመጀመሪያዋ ሴት የፓርላማ ተመራጭና ዲፕሎማት ከነበሩት ታላቅ እህታቸው ስንዱ ገብሩ ጋር ስዊዘርላድ ለትምህርት አቀኑ። የውብዳር ወደ የባሕር ማዶ ጉዟቸውን ሲያስታውሱ "ከጅቡቲ ጉዞ በጀመርንበት ጀልባ ላይ የተሳፈርን ብቸኛዎቹ ጥቁሮች እኛ ነበርን። በዚያ ድቅድቅ ጨለማ ሰማዩ ላይ የፈካችውን ሙሉ ጨረቃና ማዕበል የሚንጠውን ባህር በተመስጦ ነበር የምመለከተው። ከዚያ በመነሳት በኋላ ላይ “የባህር ላይ ዘፈን- Song of the sea' የሚለውን ሙዚቃ ደረስኩ" ብለው ነበር። የተፈጥሮን ውበት ልክ በሙዚቃ ኅይል በመግለጥ የተካኑ ጠቢብ ናቸውና ገጠመኛቸውን በረቂቅ ሙዚቃ ተራቀቁበት። በስዊዘርላንድ 'ሞንትሚሬል ትምህርት ቤት' በዕድሜ ትንሿ ተማሪ ነበሩ። አንድ ዕለት የቫዮሊን ድምፅ ሰምተው ተማረኩና መጫወት ጓጉ። በሌላ ዕለት አንዲት ፒያኖ አግኝተው ቁልፉን በጣቶቻቸው እየደቆሱ ምስቅልቅል ስሜታቸውን አስተጋቡበት። ሙዚቃውንም 'ማዕበል' ብለውታል። እናም ከቀለም ትምህርቱ በተጓዳኝ ቫዮሊንና ፒያኖ አጠኑ።ገና በ10ኛ ዓመታቸው የመጀመሪያ የሙዚቃ ትርዒት አቀረቡ። “ከንቲባ ገብሩ የኢትዮጵያ ባለውለታ” በተሰኘው የወንድማቸው ኮሎኔል ዳዊት ገብሩ መጽሃፍ ውስጥ የተጠቀሰው የእማሆይ ጽጌማርያም ማስታወሻ "... በሰባት እና በስምንት ዓመት ዕድሜዬ፣… ከሥነ ፍጥረት ጋር ወዳጅነት ነበረኝ፡፡ አበቦች ውብ ልዕልቶች፣ ዛፎች… እንደ ዘበኞቻቸው፣ ነፋስ… ወጣት መልዕክተኛ፣ ፀሐይ… ደግሞ የዓለም ኹሉ ንግሥት ኾነው ይታዩኝ ነበር፡፡ ያን ጊዜ በአዳሪ ትምህርት ቤቱ ውስጥ በኔ ዕድሜ ልጅ ስላልነበረ…ብቸኝነት የሕጻንነት ጓደኛዬ ኾኖ አብሮኝ አደገ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አንድ የኀዘን ስሜት፣ የመንፈስ ዕረፍት ዕጦት አደረብኝ፡፡ ሙዚቃ እወድ ነበርና ስሰማው የኀዘን ስሜት ያመጣብኝ ነበር" ይላል። የፒያኖ ትምህርታቸውን አዲስ አበባ ተመልሰው በእቴጌ መነን አዳሪ ትምህርት ቤት አጠናክረዋል። ልምምዳቸው ግን በጣሊያን ወረራ ምክንያት ተቋረጠ። የ13 ዓመት ልጃገረድ ነበሩ። በፋሺስት ኢጣሊያ ጦር ከነቤተሰቦቻቸው በፖለቲካ እስረኛነት ወደ ኢጣሊያ አሲናራ ደሴት ወህኒ ቤት ተጋዙ። በግዞት ሆነው ግን ከካቶሊክ ሲስተሮች ጋር ኦርጋን ይጫወቱ ነበር። ሙዚቃ ልክፍታቸው ነውና!! ከሶስት ዓመት ግዞት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ቢመለሱም የሙዚቃ ቃና ልክፍታቸው ግን ወደ ውጭ ሀገር ተመልሶ የመማር ጉጉታቸው ናረ። እናም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጸሃፊነት ስራቸውን አቋርጠው የትምህርት ዕድል ተፈቅዶላቸው ወደ ግብጽ ካይሮ አመሩ። በካይሮ ቆይታቸው “ቬሉኑስ ኮንሰርቫቶሪ ኦፍ ሉቺኒያ” በተሰኘ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ቫዮሊንና ፒያኖ ተምረው ዲፕሎማ ተቀበሉ። "በየዕለቱ ቫዮሊን ለአራት ሰዓታት፤ ፒያኖ ደግሞ ለአምስት ሰዓታት ያህል እጫወታለሁ። በየመሃሉ ደግሞ ወደ ሬስቶራቶችና ፊልም ቤቶች እየሄድኩ እዝናና ነበር" ብለዋል በአንድ ወቅት ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ። በካይሮ ሙቀት ምክንያት ወደ አዲስ አበባ እስኪመለሱ ድረስ የሙዚቃ ናፍቆታቸውን በቅጡ አጣጠመዋል። የውብዳር የሙዚቃ ጥማቸውን አልቆረጡም። አውሮፓ ተሻግሮ የመማር ፍላጎታቸው አልተቋረጠም። በእንግሊዝ ነፃ የሁለት ዓመት የትምህርት ዕድል ቢያገኙም ሳይፈቀድላቸው ቀረ። ክፉኛ አዘኑ። ከከባድ ህመምና ድባቴም በህክምና ዳኑ። በሂደትም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውብ ዝማሬዎች እየተሳቡ መጡ። የሙዚቃ ትምህርት ምናኔያቸው ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ምናኔ ተለወጠ። ውሎ አዳራቸው ቤተ መቅደስ ሆነ። ".... የዚህ ዓለም ፍቅር እና የመኖር ፍላጎት ከኅሊናዬ ፈጽሞ ተወገደ" ብለዋል በማስታወሻቸው። ከ'የውብዳር ወደ 'እማሆይነት' ምናኔ በወቅቱ የ19 ዓመት ልጅ ነበሩ። በአንድ ዕለት ወጣቷ የውብዳር ለንግስ በዓል ከአዲስ አበባ ወሎ ግሸን ማርያም ተጓዙ። ለሁለት ዓመታት ሰዓታትና ቅዳሴ ሳያቋርጡ ተማሩ፤ ፀለዩ። ታሪክን እንዲህ ያወሳሉ። “…ሁሉንም ነገር ዕርግፍ አድርጌ ትቼ ከዓለም ተነጠልኩ። እቅዴ በጫካ ውስጥ ባህታዊ ሆኜ ኑሮን ለመግፋት ነበር። ግሸን ማርያም እንደደረስን መነኮሳቱን ቀሳውስቱንና አቡነ ሚካኤልን አገኘሁ። ለመመንኮስ እንደመጣሁ ለአቡነ ሚካኤል ነገርኳቸው። እርሳቸው ግን ፈቃደኛ አልነበሩም። እኔም ውሳኔዬ መሆኑን አስረግጬ ነገርኳቸው.... በሀሳቤ የፀናው መሆኑን ካረጋገጡ በኋላ ተስማሙ" ይላሉ። እናም መስከረም 21 ቀን 1940 ዓ.ም. በ20ዎቹ ዕድሜያቸው መጀመሪያ ለማዕረገ ምንኩስና በቁ። 'የውብዳር' የተሰኘው ስማቸው በክርስትና ስማችው እማሆይ ጽጌማርያም ተቀየረ። እማሆይ ሙሉ ጊዜያቸውን ለሙዚቃ ቅማሬ እና መንፈሳዊው ግልጋሎት ሰጡ። "... ሙዚቃውን እንዳላጣው ፈለገ። ሁሉም በእርሱ ሞገስ ነው የሆነው" ይላሉ። ለአስር ዓመታት በግሸን ማርያም ገዳም ያለ ጫማ ተጉዘዋል። እማሆይ ፅጌማርያም በመንፈሳዊ ሕይወትም፤ በረቂቅ ሙዚቃም መንነዋል። የሙዚቃ ስራዎቻችውም ከአፍሪቃ ቀንድ አልፎ በምዕራቡ ዓለም ናኝቷል። ስራዎቻቸውም ታዲያ ከመንፈሳዊ ተመስጦ ባሻገር ለሰብዓዊ ርዳታ ተልዕኮ የሚውል ነበር። እማሆይ ጽጌማርያም ከመጀመሪያ አልበማቸው ጀምሮ ከአልበም ሽያጭ የተገኘ ገቢ ለግላቸው ተጠቅመው እንደማያውቁ ይነገራል፤ ለህጻናት እርዳታ ያውላሉ እንጂ። “በደርግ ዘመን ከታተመው አራተኛ አልበሜ ያገኘሁትን ገንዘብም ኢየሩሳሌም ውስጥ ያለችውን የኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ለመደገፍ አዋልኩት። ዘቪዥነር ከተሰኘው አልበሜ ያገኘሁትን ገንዘብም በወቅቱ የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ከወዲያ ወዲህ ይል ለነበረው ኢጂኤም ፋውንዴሽን ድጋፍ አድርጌበታለሁ። ሶቨኔርስ የተሰኘ ስድስተኛ አልበሜ የተገኘው ገቢም በኢየሩሳሌም ለሚገኝ ቤተክርስቲያን ድጋፍ የሚውል ነው” ብለዋል እማሆይ። ሙዚቃ በሸክላ ለማስቀረጽ የወሰኑትም በጎንደር በነበሩበት ወቅት ከቅዳሴ መልስ ባጋጠማችው ክስተት እንደነበር እንደህ አውስተዋል። "ጎንደር በነበርኩበት ጊዜ በየቤተክርስቲያኑ የማይጠገበውን ማኅሌት ሰምቼ ስመለስ፤ እደጅ የአገር ቤት ተማሪዎች በየሜዳው ጥቅልል ብለው ተኝተው አያለሁ፡፡ ብጠይቅ ሌሊት ቤተክስቲያን ያደሩ ናቸው፣ ቤት የሌላቸው፡፡ በዚህም ልቤ ተነካ፣ አዘንኩ፡፡ እኔ ሀብት የለኝ፤ ያለችኝ ያቺው ሙዚቃዬ፡፡ ስለዚህ እስኪ ሙዚቃዬን ላስቀርጽ እና ሽያጩን እነዚህ ልጆች ገብተው በነጻ የሚያድሩበት ቤት ላቋቁም አልኩ" ይላሉ። እማሆይ ጽጌማርያም እስከ ሕልፈተ ሕይወታቸው ድረስ ለአራት አስርት ዓመታት ገዳማ ኑሯቸውን በሀገረ-እስራኤል ኢየሩሳሌም በሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት አድርገው ቆይተዋል። 'የፒያኖዋ እመቤት' ረቂቅ አሻራዎች እማሆይ ጽጌማርያም የአንድ ምዕተ ዓመት ምድራዊ ሕይወት ዘላለማዊ አይረሴ ስራዎች አቅርበዋል። በፒያኖ ረቂቅ ሙዚቃ ቅማሬያቸውም 'የፒያኖዋ እመቤት' የሚል ስም አትርፈዋል። እማሆይ ጽጌማርያም ከዓለማዊ ወደ መንፈሳዊ ሕይወትን የዘነቁ፣ ሀገርኛ ወደ ባህር ማዶ ረቂቅ ጥበብን አዋህደው የተራቀቁ፣ የፒያኖ ቀማሪ፣ የቫይሊን ደርዳሪ፣ የኖታቸው ቃና መንፈስን ኮርኳሪ፣ ስክነትና ጥልቅ ተመስጦን መካሪ፣ መክሊታቸውን የኖሩ፣ በስራዎቻቸው አድማስ ዘለል አድናቆትና ሞገስ የተቸሩ፣ ... የረቂቅ ሙዚቃ እመቤት ናቸው። የኢትዮጵያን ሙዚቃ ለመጀመሪያ ጊዜ በጀርመን ሀገር በሸክላ ካስቀረጹት ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ቀጥሎ እማሆይ ፅጌ ማርያምም የኢትዮጵያን ክላሲካል ሙዚቃዎች በሲዲ በማስቀረፅ ለዓለም ሕብረተሰብ ያስተዋወቁ የመጀመሪያዋ እንስት ናቸው። በአጠቃላይ ስድስት የሙዚቃ አልበሞችን አሳትመዋል። በ1955 ዓ.ም. “ሆምለስ ወንደረር-ቤት አልባ መንገደኛ” እና “ሶንግ ኦፍ ዘ ሲ-የባሕሩ ዜማ” ሁለት አልበሞች ጀርመን ውስጥ አስቀርጸዋል። ዕውቁ የሙዚቃ ሊቅ ሞዛርት በተጫወተበት ፒያኖ የመጫወት ዕድል ገጥሟቸዋል። የቤቶቨንን፣ የሞዛርትንና ሽትራውዝን ጨምሮ የአያሌ ክላሲካል ሙዚቃ ሊቆችን ስራዎች ተጫውተዋል። ከ1950ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን አቅርበዋል። በኢየሩሳሌም ሁለት ኮንሰርቶች አቅርበዋል። ስራዎቻቸው 'ኢትዮፒክስ' በተሰኘው የፈረንሳዊው አቀናባሪ ፍራንሲስ ፋልሴቶ ተከታታይ የሙዚቃ አልበሞች ውስጥ ተካተዋል። የእማሆይ ጽጌማርያም ሙዚቃ 'ፓሲንግ' የተሰኘው የሆሊውድ ፊልም እና የፔጆ መኪና ማስታወቂያን አጅቧል። እማሆይ ስራዎቻቸውና ስብዕናቸውም የተጣጣመ ነው። በ1950 ኮንሰርታቸው በወሎ ረሀብ አደጋ ተጎጂ ዜጎች ድጋፍ ለማሰባሰብ ታልሞ በተዘጋጀው ኮንሰርት ላይ የቬትሆንን 'ፓቲክ' እና 'ሆምለስ ወንደረር' የተሰኘ ስራዎች ተጫውተዋል። ወደ ወሎ ሂደው በርሀብ አለንጋ የተገረፉ ህጻናትን በአካል በማየት ‘የድርቅ እልቂት-famine disaster' የተሰኘ ሙዚቃ ደርሰዋል። የፒያኖዋን እመቤት ሥራዎች ለቀጣይ ትውልድ ለመዘከር የተቋቋመው 'የእማሆይ ጽጌማርያም ፋውንዴሽን' በረቂቅ የሙዚቃ ዘርፍ ዕድገት የበኩሉን ሚና ሲጫወት ቆይቷል። በእማሆይ የሙዚቃ መንበር ለመቀመጥና ለረቂቅ ሙዚቃ መራቀቅ የሚሹ ወጣቶችን ይደግፋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት እና በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር በሚገኘው የሙዚቃ ትምህርት ክፍል ፒያኖን ጨምሮ ለሙዚቃው እምርታ የሚያግዝ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል። ለዓመታት ሲገለገሉበት የነበረው ፒያኖም ለያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት እንዲሰጥ በመናዘዛቸው በቅርቡ ለትምህር ቤቱ ተሰጥቷል። ከሕልፈተ ሕይወታቸው በኋላ “ኢየሩሳሌም” የተሰኘ 10 የፒያኖ ትራኮች የያዘ አልበማቸው በሚሲሲፒ ሪከርድስ አማካኝነት እንደሚወጣ ተገልጿል። እማሆይን የሚዘክሩ መፃሕፍት በተለያዩ ወገኖች ታተመዋል፤ ጥናትና ምርምር ስራዎችም እየተሰሩ ነው። እማሆይ በሙዚቃ ጠበብቶች ሲዘከሩ... እማሆይ አራቱን የኢትዮጵያ ቅኝቶች በአንድ ድርሰት በመቀመማቸው የሙዚቃ ጠበብት ያደንቋቸዋል። ከሰሞኑ "የፒያኖዋ እመቤት" እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ በሕይወት ዘመናቸው ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ኢንዱስትሪ ዕድገት የነበራቸውን አበርክቶ የሚዘክር መርሐግብር በእንጦጦ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ ሲካሄድ በርካታ ታዋቂ ሰዎችና የኪነ ጥበብ ሰዎች ታድመው ነበር። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን እማሆይ ጽጌማርያም በጠላት ወረራ የአርበኝነት ዘመን ክፉውን ጊዜ የቀመሱ፣ ሕይወታቸውም አልጋ ባልጋ ሳይሆን በውጣ ውረድ የተሞላ፣ በሀገር አንድነትና በኅይማኖት በጽኑ የሚያምኑ እንደሆኑ ገልጸዋል። "የሙዚቃ ስራዎቻቸው ፍትህን፣ አንድነትን፣ መንፈሳዊነትን እና ሰላምን የሚገልጹ ናቸው። የእማሆይ የሙዚቃ ስራ በተጨነቅን ጊዜ ስናደምጥው መንፈስ የሚያረጋጋ ሕያው ስራ ነው፤ ተማሪዎች ፈለጋቸውን እንደሚከተሉ ተስፋ አደርጋለሁ" ሲሉ ተደምጠዋል። የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሰብሳቢ አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ "የእማሆይ ጽጌማርያም ስራ በወረቀት ተጽፎ የሚቀር ሳይሆን በልብና በአዕምሯችን ታትሞ የሚቀር ነው" ሲሉ ገልጸውታል። በረቂቅ ሙዚቃ አጨዋውታቸው ዓለምን ያስደነቁ፤ የህያው ስራ ባለቤት እንደሆኑም እንዲሁ። በእንጦጦ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሙዚቃ ባለሙያው በላይ አለማየሁ እማሆይ ጽጌማርያም "ዘመናዊ ሙዚቃ ባልተለመደበት ዘመን አዲስ የሙዚቃ ስነ ዘዴ ያመጡ፤ የሙዚቃ ስራዎቻቸውም ኢትዮጵያዊውን ቃና ከአውሮፓ ሙዚቃ በማዋሀድ በሁለት ቅኝቶች ውህደት አዲስ ፈጠራ ያመጡ፣ የሙዚቃ ዕውቀታቸው የሚያስደንቅ፣ ዋጋ ከፍሎ ህልምና ማሳካት እንደሚቻል በሙዚቃ ልህቀት ላይ በመድረስ በተግባር ያሳዩ የጥበብ ሰው፣ ለሙዚቃው ዘርፍ ተግባራዊ ምሳሌ ናቸው" በማለት ይገልጸዋቸዋል። የሙዚቃ ትምህርት ክፍል አሰልጣኟ ዊንታና ንጉሴ በበኩሏ "እማሆይ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ትልቅ ሚና የተጫወቱ ስራዎቻቸውም የሚዘከሩ ናቸው፤ እንደ ሙዚቃ መምህርነቴም አርዓያዬ ናቸው" ትላለች። በእማሆይ ጽጌማርያም ስራዎች ላይ የመመረቂያ ስራዋን ያዘጋጀቸው ሰዓሊና ዲዛይነር ሀበሪ እጅጉ በበኩሏ "እማሆይ ምድራዊና ሰማያዊ ሕይወት አቻችለው የኖሩ፤ ሁለት ድል ያሳዩ ናቸው። ጥቁር ኢትዮጵያዊ ሆነው በዓለም የታወቁ፣ ለዓላማችው ስኬት ትልቅ ተጋድሎ ያደረጉ፣ በመክሊት መኖርን የሚያስተምሩ እናት" ትላቸዋለች። የኢትዮ ጃዝ አባት የሚሰኘው አንጋፋው ሙዚቀኛ ሙላቱ አስታጥቄ ከወራት በፊት ለቢቢሲ በሰጠው ቃለ መጠይቅ "እማሆይ በእውነት እጅግ የማደንቃቸው እና የማከብራቸው ታላቅ ባለሞያም፤ ታላቅ ሰው ናቸው። ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል.... የእማሆይ ጽጌ ማርያም ሥራ ተጠንቶ በየትምህርት ቤቱ እንዲቀመጥ፣ እንዲጠና ማድረግ የግድ አስፈላጊ ነው ብዬ አምናለሁ። የሙዚቃ ትምህርት ካሪኩለም ውስጥ እንዲገባ እና ወጣቶቹ እንዲማሩት ማድረግ ያስፈልጋል" ይላል። ዕውቁ የሙዚቃ ባለሙያ ሃያሲ ሰርፀ ፍሬስብሃት በአንድ ወቅት በፃፈው መጣጠፍ እማሆይ ጽጌ ማርያም ገብሩ በክላሲካል ሙዚቃ ዘርፍ በብቸኛ የሙዚቃ ቀማሪነት እና ፒያኒስትነት ጉልህ የታሪክ ቦታ እንደያዙ ገልጿል። "እማሆይ ጽጌ ማርያም በሙዚቃ ምክንያት ብዙ ተፈትነዋል፡፡ ከመንፈሳዊ ሕይታቸው ጋር የሚቃረን የሚመስላቸው አንዳንዶች፣ ሙያቸውን እና የሙዚቃ ፍቅራቸውን አጣጥለውባቸዋል፡፡ የሕይወታቸውን አቅጣጫ ፍጹም በማይገመት መንገድ እንዲጓዝ ያደረገም ነው፡፡ ከሀገራቸው አሰድዶ ተነጥለው እንዲኖሩ ያደረገ ነው፡፡ ግን ከዚህ ኹሉ በኋላ የስማቸው ትንሣኤ፣ ከዘጠኝ ዐሥርት ዓመታት በኋላ በታላቅ ክብር ለብዙዎች ታይቷል" ብሏል፡፡ እማሆይ ራሳቸውም "አንዳንድ ሰዎች ይቃወሙታል። ነገር ግን ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው የሚሆነው። ይሄ የክላሲካል ሙዚቃ ነው። እግዚአብሔርንም በተለያዩ የሙዚቃ መሳሪያዎች ማወደስ ይቻላል" ሲሉ ለቢቢሲ ራዲዮ ፎር ተናግረዋል። ሰሞን ታዋቂው ጋዜጣ ኒወርክ ታይምስ "ባለልዩ ተስጥኦ ኢትዮጵያዊ መነኩሲት" በሚል ሰፊ ሀተታ ጽፏል። በዚሁ ጋዜጣ ላይ ኖራ ጆንስ የተባለ ሙዚቀኛ "የእማሆይ አልበም እስካሁን ከሰማኋቸው ውብ ሙዚቃዎች ሁሉ የላቀ ስራ ነው" ሲል አድንቆታል። እስራኤላዊት ሙዚቀኛ ማያ ዱኔትዝ እማሆይ "የምዕራቡን ዓለም ረቂቅ ሙዚቃ ከኢትዮጵያዊ ባህላዊ ሙዚቃ ቅርስ ጋር በመቀመር ለዓለም ጆሮ አዲስ ድምጽ አፍልቀዋል። …ሙዚቃዎቻቸው በስፋት መንፈሳዊ መልክ አላቸው። የእማሆይ ሙዚቃዎች የጥሞና፣ ትህትና፣ የጥልቅ ተመስጦ፣ የሰላማዊ ድባብ፣ አሳዛኝ ግን በፍቅርና በእምነት የተዋጡ ... ድምጾች" በሚል ትገልጻቸዋለች። እማሆይ ጽጌማርያም የሙዚቃ ኅይል በርግጥም ውስጥን የሚፈነቅል፤ መንፈስን የሚሰረስር መሆኑን በዘመናቸው ሁሉ ከሙዚቃ ጋር ላይነጣጠል ከህይወታቸው የተጋመደ በሰሯቸው ዘመን አይሽሬ ስራዎች አሳይተውናል። የእማሆይ ጽጌማርያም የአንድ ምዕተ ዓመት ምድራዊ ሕይወት ዘላለማዊ አይረሴ ስራዎች በትውልዱ ውስጥ እንደረቀቁ ይኖራሉ።
የአፍሪካ ህብረት የ60 ዓመታት የውጣ ውረድ ጉዞና ቀጣይ የቤት ስራዎች
May 26, 2023 177
የአፍሪካ ህብረት የ60 ዓመታት የውጣ ውረድ ጉዞና ቀጣይ የቤት ስራዎች ሰለሞን ተሰራ አውሮፓዊያን ለጥቁሮች ከነበራቸው ዝቅተኛ አመለካከት በመነጨ እብሪት “የአፍሪካ ቅርምት” እየተባለ በሚታወቀው አጀንዳቸው አህጉሪቱን ለመከፋፈል ቁጭ ብለው የመከሩት በ18ኛው ክፍለ ዘመን ማገባደጃ ላይ ነበር፡፡ በጀርመን መዲና በርሊን የተሰበሰቡት ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ፖርቱጋል፣ ቤልጂየም እንዲሁም ዘግይተው የተቀላቀሉት ጣልያን እና ጀርመን አቅማቸው የፈቀደውን ያህል አህጉሪቱን በመቆጣጠር ሀብቷን ለመመዝበር ሕልም አንግበው የወል ቃል ገብተዋል፡፡ እነዚህ ሀገራት አፍሪካን አንድ አድርጎ ለመግዛት ሕልማቸውን አስተሳስረው ቢነሱም በመሀከላቸው በነበረው ፉክክር የተነሳ ምኞታቸው ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡ አውሮፓውያን በአህጉሪቱ የዘረጉትን የቅኝ አገዛዝ መዋቅር በጣጥሶ ለመጣል በቅድሚያ አህጉሪቱን አንድ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን የሚያምኑ አፍሪካውያን መሪዎች ህብረት ለመመስረት ቢነሱም ሀሳባቸው ለሁለት በመከፈሉ ሁለት ቡድን እንዲፈጠር ምክንያት ሆኖ አልፏል፡፡ ይህን ተከትሎ የተፈጠሩት ሁለት ቡድኖች በአንድ ወገን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ሀገራቱ በፍጥነት ተዋሕደው አፍሪካ አንድ ልትሆን ይገባል የሚለው የካዛብላንካ ቡድን፤ እንዲሁም አንድ ከመሆን በፊት ሌሎች ትብብሮች ሊቀድሙ ይገባል የሚለው የሞኖሮቪያ ቡድኖች ነበሩ፡፡ ሁለቱም ቡድኖች የአፍሪካ አንድነት እንዲመሰረት ጽኑ አቋም ቢኖራቸውም፣ እንዴት ነው መመስረት ያለበት የሚለው ጥያቄ ግን የልዩነታቸው ወሰን ሆኖ ወደ ንትርክ የገቡበት ጊዜ ነበር። በ1961 የተመሰረተው የካዛብላንካው ቡድን በጋናዊው ኩዋሜ ኑኩርማህ የሚመራ ሲሆን ዓላማቸው አፍሪካ አሁን መዋሃድ (አንድ መሆን) አለባት የሚል ሲሆን ከአባላቱ መካከል ጊኒ፣ ሊቢያ፣ ግብጽ፣ ሞሮኮ፣ ማሊ፣ አልጄሪያ ይገኙበታል። የሞኖሮቪያው ቡድን ደግሞ በሴኔጋላዊው መሪ ሴንጎር የሚመራ ሲሆን በስሩም ሃያ አራት ሃገራትን፣ ማለትም ናይጄሪያ፣ ሴኔጋል፣ ካሜሮን፣ አይቮሪኮስት፣ ቶጎ፣ ላይቤሪያ እና ሌሎች ብዙ የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበሩ ሃገራትን ያቀፈ ነበር፡፡ የዚህ ቡድን የውህደት መርህ ደግሞ “አፍሪካ መዋሃድ የምትችለው በኢኮኖሚያዊ ትብብር ሆኖ በቀስታ በምታደርገው ጉዞ ነው” የሚል ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ወገኖች ፍጥጫ አርግባ ወደ ውህደት ያመጣቻቸው ኢትዮጵያ ስትሆን ድርጅቱ የዛሬ 60 ዓመት እ.ኤ.አ ግንቦት 25 ቀን 1963 ሲመሰረት የመጀመሪያው ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት አጼ ኃይለስላሴ ነበሩ፡፡ የፓን አፍሪካኒዝም ልጅ የሆነው የያኔው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ዋና ዋና ዓላማዎቹ ቅኝ ገዢዎችን ማስወገድ፣ በአፍሪካ ሃገራት መካከል አንድነትና ሕብረትን ማበረታታት፣ ለአፍሪካዊያን የተሻለ ህይዎት እና እድገት ለማምጣት፣ ሉዓላዊነትንና የወሰን አንድነትን ማስጠበቅ፣ ሰብዓዊ መብቶችን ማስከበር፣ በአፍሪካ ሃገራት መካከል የሚካሄዱትን ግጭቶች በሰላማዊና በዲፕሎማሲ መፍታት የሚሉ ነበሩ። የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀደምት መሪዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን የሚተካ አዲስ አህጉራዊ ድርጅት ለመመስረት እ.አ.አ በ1999 ያሳለፉትን ውሳኔ መሠረት በማድረግ የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት እ.አ.አ በሐምሌ 2002 በደርባን ደቡብ አፍሪካ በይፋ መመስረቱ ይታወቃል። የአፍሪካ ኅብረት ራዕይም፤ የተቀናጀች፣ የበለጸገች እና ሰላማዊ፣ በራሷ ዜጎች የምትመራ እና በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ተፎካካሪ የሆነች አፍሪካን መመስረት ነው። እ.አ.አ በ2013 የአፍሪካ መሪዎች በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት አጀንዳ 2063 የተሰኘውን አህጉራዊ እቅድ ነድፈዋል። እቅዱ ከሁሉም በላይ በአህጉሪቱ ላይ የሚቃጡ ጦርነቶችን ማስቆምና መሰረተ ልማት ዝርጋታ ላይ የሚያተኩር ሲሆን በአህጉሪቱ ዜጎች ከአገር አገር ነፃ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ራዕይ የሰነቀ ነው። ሌላው ወሳኝ ፕሮጀክት የአፍሪካ ነፃ ገበያ ምህዳርን መክፈት ሲሆን ይህ የነፃ ገበያ ማዕቀፍ በርካታ አገራትን አሳታፊ በማድረግ የዓለም ትልቁ የነፃ ገበያ ማዕቀፍ ስምምነት ሲሆን አሁን ላይ ተግባራዊ ሊደረግ ከጫፍ ደርሷል። ይህ የነፃ ገበያ ስምምነት በአፍሪካ አገራት መካከል የሚደረግ ንግድን ለማስፋፋት የታለመ ከመሆኑ በላይ የሀገራቱን ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድገው ታምኖበታል። የአፍሪካ ነፃ ገበያ ስምምነት አገራት የውስጥ ገበያቸውን ለመጠበቅ ባወጧቸው ቀደምት ህጎችና እንዲሁም በደካማ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ምክንያት ከፍተኛ ችግር እንደሚገጥመው አስተያየት ቢሰጥበትም ያዘለው ተስፋ ግን ከችግሩ የገዘፈ ነው። ሁሉንም የአፍሪካ አገራት መዲናዎች እና የንግድ ማዕከሎች በፈጣን የባቡር መስመር ማገናኘት፣ በአፍሪካ አገራት መካከል የሚደረግ ንግድን ማበረታታት እንዲሁም የአፍሪካ አገራት በዓለም አቀፍ የንግድ ገበያ ያላቸውን ተሳትፎ ማጎልበት አጀንዳ 2063 ካስቀመጣቸው ግቦች መካከል ቀዳሚዎቹ ናቸው። አፍሪካውያን በአህጉሪቱ በነፃነት የመዘዋወር፣ የመስራት እና የመኖር መብት እንዲኖራቸው ማድረግ እንዲሁም በአህጉሪቱ ያሉ ግጭቶችን ማስቆም እና ሌሎችም በርካታ ግቦች በእቅዱ ላይ ተቀምጠዋል። ነገር ግን የአፍሪካ ሕብረት እነዚህን አጀንዳዎች ለማስፈፀም በእጅጉ እየተፈተነ ሲሆን ለዚህ ዋነኛ መንስኤው የሕብረቱ አባል አገራት በገቡት ስምምነት መሰረት ነገሮችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ማስገደድ አለመቻሉ እንደሆነ ይነገራል። ተንታኞች እንደሚሉት የአፍሪካ አገራት ያለባቸውን ከፍተኛ የእዳ ጫና ለመክፈል የሚያደርጉት ትግል ትልቁን አህጉራዊ አጀንዳ ችላ እንዲሉ ግድ ብሏቸዋል። የህብረቱ በጎ ርምጃዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ዋነኛ ዓላማው በቅኝ አገዛዝ ስር የነበሩ ሀገሮችን ነጻ ማውጣት ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር የተሳካ ተግባር ማከናወኑ በታሪክ ሲወደስለት የሚኖር ስኬቱ ነው፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ሆኖ ከሞላ ጎደል ውጤት ያስመዘገበባቸው ዘርፎች አሉ። ሀ. ሰላምና ደህንነት የአፍሪካ ህብረት ሰላምንና ደህንነትን ለማረጋገጥ በተለይም የአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ኃይል በተለያዩ የአህጉሪቱ ክፍሎች ያደረገው ተጋድሎ በአዎንታ ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡ ለማሳያም ላይቤሪያ፣ ሴራሊዮን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን ተሰማርቶ የነበረው የአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ኃይል ከሌሎች የተሻለ አፈጻጸም እንዳለው ይገለጻል፡፡ ለ. ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት በተለያዩ የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ መረጋጋት እንዲፈጠር ለማድረግና ዴሞክራሲን ለመገንባት የሚደረገው ጥረት እና የተፈጥሮ ሃብቷ ለፈጣን ዕድገቱ በምክንያትነት ይነሳሉ፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋና ኢኮኖሚው እንዲያድግ የወሰዳቸው ተቋማዊ እርምጃዎች ወሳኝ ሚና ሲኖራቸው የአፍሪካ ልማት ባንክን በማቋቋም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መደገፉ ተጠቃሽ ነው፡፡ በተለይም ለመንገድና ለውኃ ሃይል ማመንጫ ባንኩ ያደረገው ድጋፍ ተገቢው ቦታ የሚሰጠው ሲሆን ለአፍሪካ የእርስ በርስ የንግድ ግንኙነት መሻሻል ማነቆ የሆኑትን ታሪፍ በመቀነስም የተሻለ ስራ ሰርቷል፡፡ ሐ. ዓለም አቀፍ ተሰሚነት የአፍሪካ ህብረት በዓለም አቀፍ መድረኮች በተለይም የዓለም ኢኮኖሚንና የአየር ንብረት ለውጥን በተመለከተ አንድ አቋም መያዙ ከህብረቱ ታሪክ ተጠቃሽ ስኬቶች አንዱ ነው፡፡ አፍሪካ የአየር ንብረት ተፅዕኖውን ለመላመድና ለመቋቋም የሚረዳትን ተገቢውን ክፍያ እንድታገኝ ህብረቱ ውጤታማ ስራ ሰርቷል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ የልማት ችግሮችን ለመፍታት ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ጥረት አድርጎ ባስመዘገበው ውጤትም ይመሰገናል፡፡ በተለይም የተባበሩት መንግስታት የሚሊኒየም የልማት ግቦች እንደ መገለጫ ይነሳሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደግሞ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ለማግኘት እንዲሁም የአፍሪካ ድምጽ የሚጎላበት ሚዲያ እንዲኖር የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች በአዎንታ የሚነሱ ናቸው። መ. ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር የአፍሪካ ህብረት በአህጉሪቱ ዴሞክራሲንና መልካም አስተዳደርን በማስፈን በኩልም ከነጉድለቶቹም ቢሆን በመልካምነት የሚጠቀሱ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይገለጻል፡፡ በአህጉሪቷ ከ30 ዓመት በፊት አምስት ሀገራት ብቻ ዴሞክራት የነበሩ ሲሆን አሁን ከአፍሪካ ሀገሮች 95 በመቶዎቹ ወቅቱን ጠብቀው ምርጫ የሚያካሂዱ ሀገራት ናቸው፡፡ የምርጫ ታዛቢዎችን በአባል ሀገራት እየላከ መታዘቡም እንደ ጥሩ ጅምር መታየት ያለበት ነው፡፡ በተለይ ደግሞ የአፍሪካ የእርስ በርስ መገማገሚያ መድረክን /APRM/ ማቋቋሙ በጥንካሬ ሲነሳ በዚህ መድረክ አማካኝነት ሀገራት በራሳቸው ተነሳሽነት ስለሀገራቸው የመልካም አስተዳደር አፈጻጻም ሪፖርት የሚያደርጉበትና ልምድ የሚለዋወጡበት እድል ተፈጥሯል፡፡ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በሀገሮች ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ያለመግባት መርህ በማሻሻል በመፈንቅለ መንግስት የሚመጡ ቡድኖችን ላለመቀበል መወሰኑ ህብረቱ በዴሞክራሲ ላይ ያለውን አቋም ያሳያል፡፡ መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች በርግጥ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት አንግቦት ከነበረው አባል ሀገራቱን ከቅኝ ገዥዎች ነፃ የማውጣት ተልዕኮ አንስቶ እስከ ወቅታዊው የአየር ንብረት ለውጥ ድርድር አበጀህ የሚያስብሉትን ስኬቶች አስመዝግቧል፡፡ በቀዝቃዛው የዓለም ጦርነት ጊዜ አብዛኛው ሃገራት የገለልተኛ ሀገሮች ማህበር አባል ቢሆኑም የአፍሪካ ሀገሮች እርስ በእርሳቸው ተከፋፍለው አፍሪካን የጦርነት አውድማ አድርገዋት ነበር፡፡ አንዱ የአፍሪካ ሀገር የምዕራቡ ካምፕ ደጋፊ ከሆነ ሌላኛው የምስራቅ ካምፕ ደጋፊ ነበር፡፡ ሁለቱም ካምፖች ለርዕዮተ ዓለም ተከታዮቻቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ በማድረግ አፍሪካ እርስ በእርስ እንድትባላ አድርገዋል፡፡ ይህም ህብረቱ የተቀደሰ ሃሳብ ቢኖረውም የማስፈፀም አቅሙ ያን ያህል የተጠናከረ አለመሆኑን ያሳያል፡፡ ለህብረቱ የማስፈጸም አቅም ማነስ አንደኛው ምክንያት ከአባል ሀገራት የሚጠበቀውን ገንዘብ በአግባቡ አለመሰብሰቡ ነው፡፡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የህብረቱ የ2023 በጀት 654 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር እንዲሆን በዛምቢያ በተደረገ ጉባኤ ውሳኔ የተላለፈ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 60 በመቶ የሚልቀው በጀት ከለጋሾች እንደሚሰበሰብ በወቅቱ ይፋ ተደርጓል፡፡ በሌላ በኩል አፍሪካ በየዓመቱ 50 ቢሊዮን ዶላር በሙስና እንደምታጣ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ 1 በመቶ እንኳን ማዳን ቢቻል የህብረቱን የ2 ዓመት ወጪ መሸፈን ይቻላል ይላሉ ባለሙያዎች፡፡ ጥቂት በማይባሉ የህብረቱ አባል ሀገራት ሙስና ዛሬም አደጋ መሆኑ፣ የርስ በርስ ግጭት በሚፈለገው ደረጃ አለመፈታቱ፣ ድህነት አሁንም የአህጉሪቱ ቀንደኛ ጠላት መሆኑ፣ የትምህርትና ጤና አገልግሎቶች ተደራሽ አለመሆንና ጥራቱም የተጓደለ መሆን፣ በህብረቱ የሚወሰኑ ውሳኔዎች አፈጻጸም የተለያየና የሚፈለገውን ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ ውስንነት ያለበት መሆኑ ወዘተ የህብረቱና አባል ሀገራት ጉድለት ሆነው ቀጥለዋል። ትኩረት የሚያሻቸው ጉዳዮች የአፍሪካ ህብረት ከስኬቱም ሆነ ከልምዱ ለመማር የሚያስችለው ከግማሽ ክፍለ ዘመን የዘለቀ የእድሜ ባለፀጋ ሆኗል፡፡ እናም የወደፊት አቅጣጫውን ሲተልም ያለፈውን ጉዞ ዞር ብሎ ማየት፤ የቆመበትን ነባራዊ ሁኔታ ጠንቅቆ መረዳትና መጭውን አቅርቦ ማሰብ ይጠበቅበታል። ለዚህ ደግሞ የማስፈጸም አቅምን ማጠናከር፣ ለስራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት መስጠት፣ ተሳትፎን ማሳደግ፣ የገቢ አቅምን ማሳደግ ወሳኝ ናቸው። ሀ. የማስፈጸም አቅም የአፍረካ ህብረት ከአፍሪካ አንድነት ደርጅት የተሻለ አደረጃጀትና አሰራር እንዳለው የሚቀበሉ አሉ፡፡ ለምሳሌ በሀገሮች ጣልቃ ያለመግባት መርህን በማሻሻል ህብረቱ በመፈንቅለ መንግስት የመጡ ቡድኖችን በአባልነት አይቀበልም ነገር ግን በአፍሪካ አሁንም የእርስ በርስ ግጭት የሚታይባቸው ሀገሮች አሉ፡፡ ስለሆነም ይህንኑ ችግር ሊቀርፍ የሚችልና ነባራዊ ሁኔታውን ያገናዘበ አደረጃጀትና አሰራር ሊኖረው ይገባል፡፡ የህብረቱ በጀት በሌሎች አካል መሸፈን አሉታዊ ተፅዕኖ ስለሚኖረው አባል ሃገራት የሚጠበቅባቸውን መዋጮ በወቅቱ በመክፈል የህብረቱን የማስፈፀም አቅም ማሳደግም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለ. የስራ እድል ፈጠራ የአፍሪካ ህብረት በተለይ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል ማዕከል ያደረገ እድገትን ማበረታታት ግድ የሚለው ወቅት አሁን ነው፡፡ ሆኖም ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ከማረጋገጥ አኳያ ብዙ የሚቀሩ ስራዎች እንዳሉ እሙን ነው። በተለይም ወጣቶችን ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ መሰራት ያለባቸው የቤት ስራዎች በአግባቡ አለመሰራታቸው በጉልህ ይጠቀሳሉ፡፡ እንደ አፍሪካ ኢኮኖሚ አውትሉክ መረጃ በአፍሪካ እድሜያቸው ከ15 እስከ 25 ዓመት ያሉ ወጣቶች ከአህጉሪቱ አጠቃላይ ህዝብ ከ70 ከመቶ በላይ ይሸፍናሉ፡፡ የዓለም ባንክ ያወጣው መረጃ እንደሚያሳየው በአፍሪካ 200 ሚሊዮን የሚጠጉ እድሜአቸው ከ15 እስከ 25 የሚጠጋ ወጣቶች ሲኖሩ ከነዚህ መካከል 60 በመቶ የሚጠጉት ስራ ፈላጊ መሆናቸው ደግሞ ህብረቱ የሚጠብቀውን ከባድ ስራ ያሳያል፡፡ የአፍሪካ ህብረትም በየሃገሮቹ ለወጣቶች ምን ያህል የስራ እድል እንደተፈጠረ መጠየቅን የእርስ በእርስ መገማገሚያ መድረኩ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ ሊያደርገው እንደሚገባ ምሁራን ይመክራሉ፡፡ ሐ. የህዝብ ተሳትፎና የውክልና ዴሞክራሲ ህብረቱ ሊያሳካ ያሰባቸውን ግቦች እውን ማድረግ የሚቻለው በሁሉም የነቃ ተሳትፎ መሆኑ አያጠያይቅም። በመሆኑም አባል አገራት ችግሮችን ከመለየት ጀምሮ እስከ ክትትልና ግምገማ ስርአት ህብረተሰቡን በሁለንተናዊ መርሃ ግብሮች ማሳተፍ ይገባቸዋል፡፡ ይህ ሲደረግ ነው በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ውስጥ ያሉ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የፈጠራ ችሎታዎችን ማውጣትና ሀገሬ ለእኔ ምን አድርጋለች ሳይሆን እኔ ለሀገሬ ምን አደረግሁ የሚሉ ዜጎችን መፍጠር የሚቻለው፡፡ በአፍሪካ በየቦታው የሚታዩ የእርስ በእርስ ግጭቶች መንስኤ በዋነኛነት የህዝብ ፍላጎት አለመሟላት ሲሆን በተለይም የአናሳዎች መብት አለመከበር የግጭት መንስኤ ሲሆን ይታያል፡፡ ለዚህ ደግሞ በየአካባቢው አስተዳደር ህዝቡን በየጊዜው ማማከር ያስፈልጋል፡፡ መ. ውስጣዊ የገቢ አቅምን ማሳደግ በዋናነት አራት የገቢ ምንጮች ያሉ ሲሆን እነሱም የሃገር ውስጥ ብድር፤ ግብርና ታክስ፣ የውጭ ብድር እና እርዳታ ናቸው፡፡ ከግብርና ታክስ በስተቀር ሌሎች የገቢ ምንጮች አሉታዊ ተጽዕኗቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ግብርና ታክስን በአግባቡ መሰብሰብ የአንድ ሀገር የሁለንተናዊ ብቃት መለኪያ ነው፡፡ ግብርና ታክስ የመንግስት ወጪ በመሸፈን ነጻነትን ከማጎናጸፉም በተጨማሪ ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍልን ለማረጋገጥ ሁነኛ መሳሪያ ነው፡፡ አልጀዚራ ባወጣው መረጃ መሰረት አፍሪካ በእርዳታና በብድር ከምታገኘው ይልቅ በታክስ ማጭበርበርና ስወራ የምታጣው ከ10 እጥፍ በላይ ይበልጣል፡፡ ለዚህ ደግሞ የታክስ ህጎች ክፍተት መኖርና በሙስና የተጨማለቁ ባለስልጣናት እንዲሁም ብቃት ያለው የሰው ኃይል አለመኖር አስተዋፆኦ ያደርጋሉ፡፡ የገቢ አሰባሰብ ስርአቱን በማሻሻል የአፍሪካን ነጻነት ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአፍሪካን የእርስ በርስ ንግድ ማስፋፋት፤ የታሪፍና ቀረጥ ምጣኔን ማሻሻል፤ የወጪ ገበያ የምርት አይነቶችን ማስፋትና ሃገራቱን በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር የየሃገራቱን የተናጠል ጥረትና የህብረቱን አመራሮች የጋራ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራቱን በማስተባበር ባለፉት 60 ዓመታት ያለፈበትን የውጣ ውረድ ጉዞ በማጤን የተሻለ ነገን ለመገንባትና የአፍሪካን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከትላንቱ በበለጠ መትጋት ይገባዋል።
"እንሰትና ሁለገብ ጠቀሜታው"
May 6, 2023 1088
በፍሬዘር ጌታቸው እንሰት በኢትዮጵያ ከ10 ሺህ ዓመታት በላይ ያስቆጠረ፤ በተለይ በደቡቡ የሀገሪቱ ክፍሎች በስፋት የሚመረት ተክል እንደሆነ የታሪክ ድርሳናትና በዘርፉ የተካሄዱ ጥናቶች ያስረዳሉ። እንሰት በደቡብ የሀገራችን ክፍል በሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝብች ዘንድ በስፋት የሚታወቅ ነውና የምግብ ዋስትና አለኝታ ተደርጎ የሚወሰድ ተክል ነው። ተፍቆ ለምግብነት ወሳኝ የጤንነት መጠበቂያና የጥንካሬ መሰረት ተደርጎ ይወሰዳል። የእንሰት ተክል የሚጣል ነገር የለውም። ተረፈ ምርቱ ለእንሰሳት መኖ ጭምር ያለው ፋይዳ የላቀ ነው። እያንዳንዱ የእንሰት ተክል ክፍል ከምግብነት ባሻገር ለተለያዩ አገልግሎቶች ይውላል። የእንሰት ተክል ለም አፈር በንፋስና በጎርፍ ታጥቦ እንዳይወሰድ የመከላከል አቅሙ ከፍተኛ ነው። ከዚህም ባሻገር የአፈር ለምነትን እና እርጥበት ጠብቆ በማቆየት ለምርታማነት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው በመሆኑ ከደቡብ የሀገሪቱ ክፍሎች ሕዝቦች ጋር ያለውን ቁርኝት ዘመን ተሻጋሪ ያደርገዋል። ለአብነትም እንሰት በወላይታ ብሄር ከሰውና ከእንስሳት ምግብነት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን በአካባቢው "ኡታ" ተብሎ ይጠራል። እንሰት ወይም "ኡታ" የባለፀጋነት መገለጫም ነው። የመኖሪያ ቤቱን ዙሪያ፣ ቀዬውን በእንሰት የከለለና ያስዋበ፣ ማሳውን በእንሰት ያለማ አባወራ ባለጠጋ እንደሆነ ይታመናል። አባወራውም "አላ ኡታ ጎዳው" በማለት ይሞካሻል። እንሰት ለምግብነት፣ ለመደኃኒትነት፣ ለአካባቢ ውበት፣ ለአፈር እርጥበትና ለምነት ለመጠበቅ፣ ለእንሰሳት መኖነት፣ ለባህላዊ ቤት ስራ ጣራና ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት ያገለግላል። እንዲሁም ኮባው (ቅጠሉ) እንደ ዳቦ ለመሳሰሉት ምግብ ማብሰያና ለተለያዩ የግብርና ዉጤቶች መጠቅለያነት ግልጋሎት ይውላል። ከእንሰት ተረፈ ምርቶች የመቀመጫና የወለል ምንጣፎችን ጨምሮ በርካታ መገልገያዎች ይሰራሉ። የእንሰት ተክል በተለያዩ አካባቢያዊ ሁኔታ መብቀል ከመቻሉ ባሻገር ድርቅን የመቋቋም አቅሙ ከፍተኛ ነው። በዚህም አካባቢው ላይ ድርቅ በተከሰትበት ወቅት "ነፍስ አድን" የሚል ስያሜም ተሰጥቶት እንደነበር በታሪክ ይናገራል። የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር መለሰ መኮንን እንሰት ምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥና የልማት ችግሮችን ከማቃለል አንጻር ከፍተኛ ሚና ያለው ነው ይላሉ። ተክሉ በደቡብ፣ በደቡብ ምዕራብና በሲዳማ ክልሎች በስፋት እንደሚለማና በሀገሪቱ ከ3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በላይ በተለያየ የእንሰት ዝርያ መሸፈኑን ያስረዳሉ። ከሀገሪቱ ህዝቦች ከ25 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት የእንሰት ተዋፅኦን የሚመገቡና የሚገለገሉ ናቸው። የእንሰት ተክል በባህሪው የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም የከፍተኛ አቅም ያለው በመሆኑ፤ ለዝናብ እጥረትና ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ተክሉን በስፋት በማልማት የምግብና ዋስትናን በዘላቂነት ማረጋገጥ ይቻላል ይላሉ። እንሰትን ለምግብነት ከመጠቀም ባሻገር ለገበያ በማቅረብ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ ሀብት በመሆኑ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የተሻለ አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ ጥረት ማድረግ ይጠይቃል ሲሉ ያስረዳሉ ሚኒስትር ዴኤታው ዶክተር መለሰ። እንሰት በአካባቢው ማስገኘት ከሚገባው ጠቀሜታ አንፃር ሲታይ እየሰጠ ያለው ጥቅም ከአቅም በታች ነው የሚሉት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የእንሰት ሰብል ተመራማሪ ዶክተር አብርሃም ቦሻ ናቸው። በመሆኑም የእንሰትን ምርታማነት ለማሳደግ ዩኒቨርሲቲው የምርምር፤ የማህበረሰብ አገልግሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎችን በትኩረት እየሰራ ነው ይላሉ። በኢትዮጵያ ከባህር ጠለል በላይ ከ1 ሺህ 500 እስከ 3 ሺህ 100 ሜትር ከፍታና አማካይ የዓመት ዝናብ መጠን ያለው አካባቢ ለእንሰት ተክል ምቹ ሲሆን፤ እንሰት ዝናብን የሚተካ አማራጭ የውሃ ምንጮች ባሉበት አካባቢ ከ1 ሺህ 500 ሜትር በታች በሆኑ ቆላማ አካባቢዎችም ምርት ሊያስገኝ ይችላል ይላሉ። እንደ ተመራማሪው ገለጻ እንሰት በሀገሪቱ ከሚገኙና ዋና ዋና ሰብሎች ከሚባሉት መካከል አንዱና ከ10 ሺህ ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው ነው። ተክሉ ተራራማ ቦታዎች ላይ ጭምር በምቾት የሚያድግ ሲሆን እንደ ዝርያው ዓይነት ከሶስት እስከ አምስት ዓመት ውስጥ ምርቱ ውጤታማ መሆን ይችላል። ዝርያው "ወንዴ" እና "ሴቴ" ተብሎ የሚከፈል ሲሆን፤ 60 ያህል የእንሰት ዝርያዎች አሉ። ከምርት አያያዝና ብቃት አንጻር ሲታይ ከእያንዳንዱ የእንሰት ተክል ከ40 ኪሎ በላይ ዱቄት ይገኝበታል። እንሰት ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ጉልህ አስተዋፅኦ ያለው ሰብል ነው፤ ከዛም አልፎ ለሰውና ለእንስሳት ከተለያየ በሽታ የመከላከልና ከጉዳት ለማገገም የሚያስችል መድኃኒት ነው። ተክሉን የማባዛት ስራ በባህላዊ መንገድ የሚከወን ሲሆን፤ የእንስሳትና ሌሎች የሚወገዱ ተረፈ ምርቶችን በመጨመር እድገቱን ውጤታማ ማድረግ ይቻላል። ከእንሰት ምርት የሚገኘው ዱቄት ቡላ ወይም በአካባቢው አጠራር "ኢቲማ" ለልጆችና ለአዋቂዎች ጤና ተስማሚ ሲሆን፣ ገንፎ፤ የክትፎ የአይብና ጎመን ማባያ ቆጮ "ኡንጫ" እንዲሁም ሙቾና ባጭራ ለምግብነት ከሚውሉት ተጠቃሽ ናቸው። የእንሰት ተክል በተለያዩ የአፈር ዓይነቶች ላይ የሚለማ፣ የአየር ንብረት ለውጡን የመቋቋም አቅም ያለው ተክል ነው። የወላይታ ዞን እንሰት አብቃይ ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ ሲሆን በተለይም በባይራ ኮይሻ፣ በቦሎሶ ሶሬና በአንዳንድ የሶዶ ዙሪያ ወረዳዎች በተደረገ የዳሰሳ ጥናት የእንሰት ተክል የመመናመንና የበሽታ አደጋ እንደተጋረጠበት ዶክተር አብርሃም አብራርተዋል። ለዚህም ምርቱን መልሶ ለማስፋፋትና ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ከዞኑ ግብርና መምሪያ ጋር በመሆን በትብብር እየተሰራ መሆኑን ያስረዳሉ። የወላይታ ዞን የግብርና መምሪያ እርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ዓለሙ እንዳሉት በወላይታ ዞን ከ28 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በእንሰት ተክል የተሸፈነ ነው። የእንሰት ተክል የሚፈለገውን ምርትና ውጤት እንዳይሰጥ ከሚያደርጉ ተግዳሮቶች መካከል ዋነኞቹ የአጠውልግና የአምቾ አበስብስ በሽታ፣ የተለያዩ ተባዮች፣ ፍልፈልና ጃርት ይጠቀሳሉ። የእንሰት አጠውልግና የአምቾ አበስብስ በሽታ በሁሉም የእንሰት አብቃይ ስነ-ምህዳር የሚገኝ፣ በሁሉም የእድገት ደረጃ ላይ ያለን የእንሰት የሚያጠቃና ከአንዱ ወደ ሌላው ተክል የሚተላለፍ መሆኑ ችግሩን የከፋ ያደርገዋል። በመሆኑም ችግሩን ለማስወገድ ጤነኛ የእንሰት ተክሎችን በላቦራቶሪ የማባዛት፣ የበሽታ አምጪ ተህዋሲያን የማጥናትና በጄኔትክ ምህንድስና በሽታን የሚቋቋም ቅንጣት ወደ እንሰት የማስገባት ሥራ እየተሰራ ነው። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፣ ከሶዶ ግብርና ኮሌጅ እንዲሁም ከአረካ የምርምር ማዕከል ጋር በመሆን በጋራ እየተሰራ ነው። ኃላፊው እንዳስረዱት ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በሽታን የሚቋቋሙ ከ20 ሚሊዮን በላይ የእንሰት ችግኞችን አባዝቶ በመትከል የተሻለ ውጤት እየታየ ነው። ይህን ሥራ በማጠናከር ከእንሰት ዘርፍ ሊገኝ የሚገባውን ጥቅም ለማግኘት አርሶ አደሩ ያለውን አገር በቀል ዕውቀቱን በአግባቡ እንዲጠቀም በከፍተኛ ንቅናቄ እየተሰራ ይገኛል። በዚህም የአካባቢውን የእንሰት ሽፋን ማሳደግ ብቻ ሳይሆን የአርሶ አደሩን ጥያቄ መመለስና ጥቅሙን ለማላቅ የተጀመረው የንቅናቄ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ወሳኙ ስራ ተደርጎ እየተከናወነ ነው። ማህበረሰቡ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የአየር ንብረት ፋይናንስ-አፍሪካውያን ገፍተው ያልሄዱበት መንገድ
Feb 18, 2023 1598
/በገዛኸኝ ደገፉ/ የአፍሪካ ቀንድ ከ40 ዓመታት ወዲህ ተከስቶ አያቅም የተባለለትን የድርቅ አደጋ እያስተናገደ ይገኛል፡፡ በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊ ሆነዋል። የድርቁ አደጋ የከፋበት የአፍሪካ ቀንድ ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ተሸክመዋል። በተጨማሪም የከተሞች መስፋፋትና የከተሜነት የኑሮ ዘይቤን እያስተናገደች ባለችው አፍሪካ የኃይል እጥረት፣ በቂ የመሰረተ ልማት አውታሮች ዝርጋታ አለመኖር፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ፍልሰት፣ ሥራ አጥነት ብሎም የወንጀሎች መስፋፋት አሕጉሪቱን ክፉኛ እየፈተኗት ይገኛሉ። የገጠር መሬት ምርታማነት መቀነስ ከገጠር ወደ ከተማ ለሚደረገው ፍልሰት አንደኛው ገፊ ምክንያት ሲሆን ለመሬቱ ምርታማነት መቀነስ ሰበብ ተደርጎ በዋናነት የሚጠቀሰው ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥና የበረሃማነት መስፋፋት የሚወልዳቸው የውኃ ኃብት መቀነስና ለተከታታይ ዓመታት የሚዘልቁት የድርቅ አደጋዎች መሆናቸው ጉዳዩን ይበልጥ አወሳስቦታል። እንደ አህጉር ከ4 በመቶ ያነሰ የካርቦን ልቀት ያላት አፍሪካ 65 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ የችግሩ ቀጥተኛ ገፈት ቀማሽ መሆን ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። ከዚህ ችግር ሙሉ ለሙሉ መውጣት ባይቻልም ትርጉም ባለው ደረጃ መቀነስ እንዲቻል አህጉሪቱ ያላትን የተፈጥሮ ኃብትና ወጣት የሰው ኃይል በማስተሳሰር ለውጥ ማምጣት ግድ ይላታል። በአፍሪካ የማይቀረውን የከተሞች መስፋፋትም ሆነ የህዝቦቿን የመልማትና የመለውጥ ፍላጎት ማሟላት ካለባት የአየር ንብረት ፋይናንስን የበለፀጉ ሀገራት ገቢራዊ ሊያደርጉት ይገባል። የአየር ንብረት ፋይናንስ (Climate Finance) የአካባቢ፣ ብሔራዊ ወይም ድንበር ተሻጋሪ ፋይናንስን የሚመለከት ሲሆን ከሕዝብ፣ ከግል እና ከአማራጭ የገንዘብ ምንጮች የተውጣጣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቅረፍ እና ለማስተካከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን የሚደግፍ ዓለም አቀፍ ስምምነት ነው። የኪዮቶ ፕሮቶኮል እና የፓሪስ ስምምነት ደግሞ ሰፊ የገንዘብ አቅም ካላቸው አገራት አነስተኛ የኃብት አቅም ላላቸው እና ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ አገራት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ስምምነት ነው። ስምምነቱ “የጋራ ግን ደግሞ ልዩነት ያለው ኃላፊነትና አቅም” በሚለው መርህ መሰረት ያደጉ አገሮች አዳጊ አገራትን ለመርዳት የገንዘብ ምንጮችን እንዲያቀርቡ ይጠይቃል። ፋይናንሱ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ወሳኝ ድጋፍ እንደሚሆን ታምኖበታል። ምክንያቱም ልቀትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ላቅ ያለ የኢንቨስትመንት አቅም የሚጠይቅ በመሆኑ። በተመሳሳይ ከአሉታዊ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎች ጋር ለመላመድ እና ተለዋዋጭ ጫናዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ይጠይቃል። ከጥቂት አሥርት ዓመታት በፊት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተዘጋጅቶ የቀረበው የምእተ ዓመቱ የልማት ግብ ሰነድም ሆነ በቅርቡ በሚጠናቀቀው ዘላቂ የልማት ግቦች ላይ ለጉዳዩ ከፍ ያለ ትኩረት ቢሰጠውም እስካሁን ግን የፈየደው ነገር የለም። አፍሪካ የአየር ንብረት ተጽዕኖዎችን ለመላመድ ዓመታዊ 41 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የፋይናንስ ክፍተት ይገጥማታል። ይህን ክፍተት ለመሙላት አዲስ አበባ እያስተናገደች ባለችው 36ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ ላይ የአየር ንብረት ፋይናንስ ገቢራዊ ማድረግን ቀዳሚ ትኩረታቸው መሆን እንዳለበት የአንድ ዘመቻ (ONE Campaign) አጽንኦት ሰጥቶ ምክረ ሃሳቡን ሰንዝሯል። የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የአንድ ዘመቻ ዳይሬክተር ዶሪን ኒኒናሃዝዌ የአፍሪካ መሪዎች የአየር ንብረት ለውጥን ለመላመድ ፋይናንስ ድጋፍን በማረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥን አስከፊ ተጽዕኖ የመቋቋም አቅም እንዲገነቡ መክረዋል። አፍሪካ ባልፈጠረችው የአየር ንብረት ለውጥ ህዝቦቿ ለከፋ ጥቃት እየተዳረጉ ይገኛሉ። ስለዚህ የአፍሪካ መሪዎች የበለጸጉ አገሮች የገቡትን የማላመድ ፋይናንስ ድጋፍ ቃል እንዲፈጽሙ ከማግባባት ባለፈ ማሳሰብ ይኖርባቸዋል ብለዋል። ይህ ማለት እኤአ ከ2020 እስከ 2025 በዓመት 100 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገመተውን ግብ የማሳካት ተግባር የሚጠይቅ ነው። ከዚህ ባሻገር በቀጣዮቹ ዓመታት በተጨመሩ መዋጮዎች የሚስተዋሉ ጉድለቶችን መፍታት እና በግብጿ ሻርም ኤል ሼክ ከተማ ባስተናገደችው COP-27 ላይ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ለመላመድ በእጥፍ ፋይናንስን የማቅረብ ቁርጠኝነት የማቅረቢያ ዕቅድ ሊነድፉ ይገባል ነው ያሉት። የአፍሪካ አገሮች ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ከሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት እና ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች ጋር ሲታገሉ ቢቆዩም አሁን ላይ “አፍሪካ በአፈፃጸሙ ላይ መጠነኛ መሻሻል አሳይታለች” ብለዋል። እናም በ36ኛው የመሪዎቹ ጉባዔ የተገኙ ስኬቶች እና የጠፉ ዕድሎች እንዲሁም የድርጅቱን ዓላማዎች ለማሳካት በአየር ንብረት ፋይናንስ በጥልቀት መክረው ለተሻለ ስኬት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዋና ዳይሬክተር አንቶኒዮ ቪቶሪኖ በአየር ንብረት ምክንያት የሚፈጠሩ መፈናቀልን ለመግታት የተሻሻሉ የመላመድ እና የተጽዕኖ ቅነሳ ተነሳሽነት ገቢራዊ ለማድረግ በአገራት መካከል ጠንካራ አጋርነትን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ያሰምሩበታል። በተለይ በአፍሪካ ቀንድ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በተፈጥሮ ሃብት ላይ ኑሯቸውን መሰረት ባደረጉ ህዝቦች ላይ አውደ-ተኮር መላመድ እና የመቋቋም አቅም ግንባታ መፍጠር ይገባል። ለዚህ ደግሞ መላመድን የሚደግፉ ፋይናንስ ለማግኘት የሚረዱ መመሪያዎች ይበልጥ የተፍታቱ መሆን ይኖርባቸዋል ሲሉ ቪቶሪኖ ይሞግታሉ። ከ 36ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በተጓዳኝ በተካሄደው ከፍተኛ የውይይት መድረክ (High-Level Forum) ላይ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በሻርም ኤል ሼክ በተካሄደው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ መላመድን፣ መከላከልን እና ዝግጁነትን ለማሻሻል ዓለም አቀፍ ትብብር ማጎልበት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አውስተዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥን አስመልክቶ ያወጣቸው የስምምነት ማዕቀፎች (United Nations Framework Convention on Climate Change (UNFCCC)) በርካታ ዝርዝርና ሚዛናዊ አካሄዶችን የያዙ ናቸው። ያም ሆኖ አተገባበራቸው እዚህ ግባ የማይባል በመሆኑ የሚታሰበውን ያህል ለውጥ ማምጣት ሳይችል ቀርቷል። በዚህም ቦረና ዞንን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች ለከፋ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የአየር ንብረት መዛባት፣ የሙቀትና የባህር ጠለል መጨመር፣ ጎርፍ፣ ድርቅ እንዲሁም ያልተገመቱ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ለመቀነስ የአየር ንብረት ፋይናንስ ዓይነተኛ አማራጭ እንደሆነ ብዙዎቹ ይስማሙበታል። ዳሩ ግን አገራትን፣ አህጉርን፣ ዓለምን እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ግዙፍ ኩባንያዎችን ያስተሳስራል የተባለለት የአየር ንብረት ፋይናንስ በቅጡ ገቢራዊ ማድረግ ባለመቻሉ የአፍሪካ ቀንድን ጨምሮ በርካታ ህዝቦች ዳፋውን ለመጋፈጥ ተገደዋል። የአየር ንብረት ፋይናንስን በመተግበር በመስኩ የተጎጂዎችን ቁጥር ሊቀንሱና የዓለምን ሥነ-ምህዳር ከተቻለ ወደ ቀድሞው ሊመልሱ አሊያም አሁን ባለበት አረጋግተው ሊያቆዩ የሚያስችሉ በርካታ አማራጮች ተግባራዊ ሊደረጉ ይገባል። ለአብነትም ለድሃ ሃገራት አርሶ አደሮች የግብርና ምርቶች ተገቢውን ዋጋ በመክፈል የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን እንዲቋቋሙ ማድረግ ከአማራጮቹ መካከል አንዱ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ግዙፎቹ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ለሚያስወግዷቸው በካይ ጋዞች ተመጣጣኝ የጤና ሥርዓት በመዘርጋት የታዳጊ ሃገራት ዜጎችን የጤና አገልግሎት ማሻሻል ሌላው አማራጭ ነው። የተፈጥሮ ኃብቶችን የሚጎዱ የኢንዱስትሪ ዘርፎች ተፈጥሮን በሚንከባከቡ ዘዴዎች መተካት እንዲሁም ብክለትን የሚያስቀሩ የምርት ሂደቶች መለማመድ ጥቂቶቹ የመፍትሄ አማራጮች ተደረገው የሚወሰዱ ናቸው። በፓሪስ ከተደረሰውን የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ቀደም ብሎ በፈረንጆቹ 1994 ዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም (Global Environment Facility-GEF) COP-16 ዓለም አቀፍ ጉባዔ በኋላ በ2010 አረንጓዴ የአየር ንብረት ፈንድ (Green Climate Fund-GCF) እንዲሁም በ2001 ደግሞ ልዩ የአየር ንብረት ለውጥ ፈንድ (Special Climate Change Fund-SCCF) እና የመላመድ ፈንድ (Adaptation Fund-AF) የተባሉ ማዕቀፎች የተዘጋጁ ቢሆንም ስለጉዳዩ የሚያስረዱ ተከታታይ ስብሰባዎች ከማዘጋጀት በዘለለ ብዙ ርቀት መጓዝ ሳይችሉ ቀርተዋል። በቅርቡ በአለም ባንክ አሰባሳቢነት በኬንያ ናይሮቢ ተዘጋጅቶ በነበረው የአህጉሪቱን መሪዎች ባለሃብቶችንና ምሁራንን ባካተተውና “One Planet Summit” በተሰኘ መሰል ጉባዔ ላይም አፍሪካውያን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚገጥማቸውን ችግሮች ተከላክለው ሁለንተናዊ ዕድገታቸውን እንዲያፋጥኑ ካስፈለገ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የምጣኔ ኃብት ፖሊሲ አዘጋጅተው መተግበር እንደሚኖርባቸው መግባባት ላይ የተደረሰ ቢሆንም አሁንም ጥያቄ ያስነሳው አፈጻጸሙ ስለመሆኑ ብዙ ተብሎለታል። ክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ የተባለ ድርጅት ይፋ ያደረገው ሪፖርት እንደሚያመለክተው አፍሪካ እንደ ፈረንጆቹ የጊዜ ቀመር ከ 2020 እስከ 2030 ባሉት አሥር ዓመታት 2 ነጥብ 8 ትሪሊየን የአሜሪካ ዶላር አሊያም በየዓመቱ ከ2 መቶ ሃምሳ ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያስፈልጋት ሲሆን አህጉሪቱ ከዘርፉ እያገኘችው ያለው ገንዘብም ከሚያስፈልጋት 12 በመቶውን ወይም 30 ቢሊየን ዶላር ብቻ ስለመሆኑ አስነብቧል። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ተቋቁመው ሊሰሩ የሚችሉ በርካታ ተግባራት እንዳሏት የሚያትተው ሪፖርቱ ከአየር ንብረት ፋይናንስ የሚገኘው ገንዘብ በትራንስፖርት፣ በኃይል ልማት፣ በኢንዱስትሪ ብሎም በግብርና፣ በአፈርና በደን ኃብት አጠቃቀም ውጤታማ በሆነ መንገድ ከዋለ የአህጉሪቱን የተፈጥሮ ኃብቶች መንከባከብ ከማስቻሉም ባለፈ ላቅ ያለ ፋይዳ ይኖራዋል ብሏል። ይህ ሲሆን የሥራ ዕድል በመፍጠር የሥራ አጥ ቁጥርን በመቀነስ ለአህጉሪቱ ሰላምና መረጋጋት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖው ያስረዳል። ላለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ገቢራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራን የማስፋፋትና የተጎዱ አካባቢዎችን የማከም ሥራ እንዲሁም አይቀሬ የሆኑትን ከተሜነትና የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ታሳቢ ያደረጉ የአየር ንብረት ፖሊሲዎች ተግባራዊ መደረጋቸው ለአፍሪካ ሃገራት እየፈጠረው ያለው በጎ ተጽዕኖ በግልጽ እየታየ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ጥረት ግን በአየር ንብረት ፋይናንስ እንዲደገፍ አገራዊና የተቀናጀ አሕጉራዊ ጥረት ማድረግን ይጠይቃል። ከአጠቃላይ የአፍሪካ አገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ግብጽ ብቻ 151 ቢሊየን ዶላር ከአየር ንብረት ንብረት ፋይናንስ ማግኘት እንደሚኖርባቸው የክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሽየቲቭ ሪፖርቱ ይገልጻል። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በመጭው የCOP-28 ጉባዔ የራሷንና የአፍሪካን ፍላጎት የሚያስጠብቁ የፋይናንስ ትልሞችን የመንደፍ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባታል፡፡ የ COP-27 ጉባዔ ለአፍሪካ ያስገኘውን ውጤት እና አንድምታ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የመሪዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ እና አስተባባሪ በሆኑት በኬንያው ፕሬዝዳንት ሰብሳቢነት በኅብረቱ የአዲስ አበባ ጉባዔ ላይ በጥልቀት ይገመግማል ተብሎ ይጠበቃል። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ ጥረቷን የሚያጎለብት የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ጠንካራ ተሳትፎ ልታደርግ ይገባል። የአፍሪካ አገራት ገፍተው ረጅም ርቀት ያልሄዱበት የአየር ንብረት ፋይናንስ እና ሌሎች የድጋፍ አማራጮችን በፍትሃዊነትና በምክንያታዊነት በመጠቀም የአየር ንብረት ተጽዕኖን የሚቋቋሙበት ጠንካራ አቅም ሊገነቡ ግድ ይላቸዋል። በእርግጥም አፍሪካውያን መሪዎች በሚያደርጉዋቸው ስብሰባዎች በየማዕዝናቱ በድርቅ ሳቢያ ለምግብ እጦት የተዳረጉ ህዝቦቻቸውን የሚታደጉበት ሁነኛ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙበትን ዘዴ ነድፈው ረጅም ርቀት ሊጓዙ ይገባል። ”
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 1826
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 3164
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት። እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 1845
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል። “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 2011
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
መጣጥፍ
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 2488
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ)
Jan 25, 2023 2418
ሽሬ ወአክሱም (የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ) አየለ ያረጋል (ኢዜአ) መዳረሻዬ ሽሬ እንዳስላሴ ነው። ለዘገባ ሥራ ከባህርዳር- ጎንደር- ደባርቅ- ሸሬ መንገድ ከሚዲያ ባልደረቦች ጋር እየተጓዝኩ ነው። የጥምቀት ሙሽራዋ ጎንደር እየተኳኳለች ነበር። ደባርቅ ከመድረሴ በፊት ዳባት ትገኛለች-የደጃች አያሌው ብሩ ቁርቁር ከተማ። ደጃች አያሌው ትውልዳቸው በጌምድር ጋይንት ቢሆንም ግዛታቸውና ኑሯቸው ዳባት ነበር። ሞገደኛው ደጃዝማች አያሌው ብሩ በጎንደር ማኅበረሰብ ዘንድ ዝናቸው የናኘ ነው። ደጃዝማች አያሌው በ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ (ከልጅ ኢያሱ እስከ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ-መንግሥት) ታሪካዊ ክንውኖች ጉልህ ተሳትፎ አላቸው። አንዷን ብቻ ልምዘዝ። ራስ ተፈሪ ‘ንጉሠ-ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ’ ደጃች አያሌው የቅርብ ዘመዳቸውን ራስ ጉግሳ ወሌ ብጡልን (የንግሥት ዘውዲቱን ባለቤት) ወግተው የጎንደር ግዛት ‘ራስ’ ተብለው ለመሾም ቃል ቢገባላቸውም፤ ተልዕኳቸውን ተወጥተው ቃሉ ባለመፈጸሙ ደጃዝማቹ ከአጼው ጋር መቀያየማቸው አልቀረም። በዚህም:- "አያሌው ሞኙ፣ ሰው አማኙ ሰው አማኙ፣ የአያል ጠመንጃ፣ ስሟን እንጃ ስሟን እንጃ…” በማለት የጎንደር አዝማሪ አዚሟል። ዛሬም ይህ ግጥም የብዙ ባህላዊ ዘፈኖች አዝማች ነው። ደጃች አያሌው ብሩ ደፋር ናቸው ይባላል። ከአጼ ኃይለሥላሴ ጋር ቢቀያየሙም በ1928 ዓ.ም ፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ሲመጣ ቅድሚያ ለአገሬ ብለዋል። ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘው የዶክተር ሀራልድ ናይስተሮም (ትርጉም ገበየሁ ተፈሪ እና ደሳለኝ አለሙ) መጽሐፍ እንደተጠቀሰው ደጃች አያሌው “ንጉሡ እንደኛ ሰው ናቸው። ኢትዮጵያ ግን የሁላችንም ናት" ብለው ጦራቸውን መርተው በሽሬ ግንባር ዘምተዋል። ጉዟችን ቀጥሏል። ደባትን እያለፍን ነው። ‘እንኳን ደህና መጡ፤ ወደ ጭና ታሪካዊቷ ሥፍራ’ የምትለዋን ታፔላን በስተግራ እያየን ወደ ደባርቅ ገሰገስን። የሰሜን ተራሮች የብርድ ወጨፎ ያረሰረሳትን ደባርቅን ከማለፋችን ሊማሊሞ ጠመዝማዛ ቁልቁለት ተቀበለን። አስፈሪ የሊማሊሞ መልክዓ ምድር የደጋው ሰሜን ውርጭ እና የተከዜ በርሃ ኬላ ነው። ባለቅኔው ጸጋዬ ገብረመድህን “የሰማይ የምድሩ ኬላ፣ የየብስ የጠፈሩ ዋልታ አይበገር የዐለት ጣራ፣ አይመክተው መከታ ሊማ-ሊሞ አድማስ ሰበሩ፣ በጎማ ፈለግ ይፈታ? በትሬንታ እግር ይረታ?…” ብሎ የመኪና መንገድ ተገንብቶበት በማየቱ ግርምቱን የተቀኘለትም ለዚህ ይመስላል። ከሊማሊሞ ቁልቁለት በኋላ አዲ-አርቃይ፣ ዛሪማ፣ ማይፀብሪ እና ሌሎች የጠለምት ወረዳ ከተማዎችን አልፈን፤ የዋልድባ ረባዳማ አካባቢዎችን ተሻግረን ተከዜ ወንዝ ደረስን። የዚህን መንገድ እና ተከዜ ወንዝን ሳስብ የሀዲስ ዓለማየሁ ትዝታ አስተከዘኝ። የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ጦር የወገንን ጦር ፊት ለፊት መቋቋም ሲሳነው በሰው ልጆች ላይ ተደርጎ የማያውቅ መርዝ በጅምላ የፈጀበት አሳዛኝ ታሪክ ነበር። በተከዜ ወንዝ ውሃን በመመረዝ የወገን ጦር ያለቀበት ሥፍራ ነው። የተከዜ ሸለቆ በኢትዮጵያዊያን ደምና አጥንት ዋጋ የተከፈለበት ነው። ሀዲስ ዓለማየሁ በአንድ ዕለት የተመለከቱትን እንዲህ ጽፈውታል። “የተከዜ ውሀ እመሻገሪያው ላይ ሰፊና ፀጥ ያለ ነው። ታዲያ ያ ሰፊ ውሀ፤ ገና ከሩቅ ሲያዩት ቀይ ቀለም በከባዱ የተበጠበጠ ይመስላል። “ምን ነገር ነው፤ ምን ጉድ ነው?” እየተባባልን ቀረብ ስንል መሻገሪያው በቁሙም በወርዱም ከዳር እስከ ዳር ሬሳ ሞልቶበት የዚያ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው። የሰው ሬሳ፣ የፈረስ እና የበቅሎ ሬሳ፣ ያህያ ሬሳ፣ ያውሬ ሬሳ፥ ሬሳ ብቻ! እግር ከራስ ራስ ከእግር እየተመሰቃቀለ እየተደራረበ ሞልቶበት፥ የዚያ ሁሉ ሬሳ ደምና ፈርስ ነው”። ይሉናል። ቀጥለውም “በእውነቱ እንዲህ ያለውን መሳሪያ ምንም ጠላት ቢሆን በሰው ላይ ለማዋል የሚጨክን ሰው፥ ሰብዓዊ ስሜት የሌለው፣ አለት ድንጋይ የተፈጠረበት መሆን አለበት፤ እንዲህ ያለውን መሳሪያ በሰው ላይ ማዋል ሰብዓዊ ህሊና ሊሸከመው የማይችል እጅግ ከባድ መሆኑን ዓለም ሁሉ ያወቀውና ያወገዘው በመሆኑ የኢጣሊያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ ከማድረጉ በቀር “ሌላ መንግሥት በሌላ አገር ላይ አደረገ’ ሲባል ተሰምቶ የሚያውቅ አይመስለኝም” ብለዋል። ከተከዜ ባህር ማዶ ጉዞዬ ያገኘኋት ሌላዋ ታሪካዊ ሥፍራ እንዳባጉና ናት። እንዳባጉና የወገን ጦር ትልቅ ገድል የፈጸመበት ነው። ጀግኖች አባቶቻችን የጠላት ታንክ ሳያስፈራቸው የጠላት ጅምላ ጨራሽ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ተቋቁመው ጠላትን ድባቅ የመቱበት፤ ወደ አክሱም እንዲያፈገፍግ ያደረጉበት ሥፍራ ነው። “የጠላት ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በጦር ሜዳው ትንንሽ ቦምቦች አውቶማቲክ ጠመንጃ ይተኩስ ነበር። አቢሲኒያኖች ደግሞ ከጠላት ጋር ግብግብ ገጥመው ጉዳይም አልሰጡትም ነበር…” ይላል ዶክተር ሀራልድ ‘የተደበቀው ማስታወሻ’ በተሰኘ መጽሐፉ። ይህ አካባቢ በሀገር ፍቅር የነደዱ ኢትዮጵያዊያን ደም ያፈሰሱበት፣ አጥንት የከሰከሱበት፤ ለኢትዮጵያ መስዕዋትነት የከፈሉበት ነው። ይህ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ የተከፈለበት ቀጣና ነው። ቀኑ ተገባዷል። ጉዟችን እንደቀጠለ ነው። እኔም የማሽላ ማሳዎችን ግራ ቀኝ እየተመለከትኩ ለዕለቱ መዳረሻችን ወደሆነችው ሽሬ ከተማ ገባን። ሽሬ በትግርኛ ‘ሽረ’ ሲሉት ይደመጣሉ። በእርግጥ ሽሬን ለመጀመሪያ ጊዜ መርገጤ ነው። ዕለቱም ጥር ሥላሴ ነው። ሽሬ በጥር ሥላሴ ትደምቃለች፤ ሙሉ ስሟም ሽረ እንዳስላሴ ነው። የሽሬ ሥላሴ ጠበል ሽሬ ደርሰን ማረፊያችንን ያዝን። ጊዜው በጣም አልመሸምና ከተማዋን በቀላሉ መቃኘት ይቻላል። ሽሬ ሰፊና ደማቅ የዞን ከተማ ናት። ከመካከላችን የአንደኛው ባለሙያ ቤተሰቦች ሽሬ ነበሩና አስጠሩን። ለሥላሴ ጠበል ግብዣ። ባል እና ሚስቱ ከልክ በላይ መስተንግዶ አደረጉልን። ‘ጠብ እርግፍ አድርገው አስተናገዱን’ ማለት ይቀላል። እንግዳ መቀበል ነባር ኢትዮጵያዊ እሴታችን ቢሆንም ጦርነት ውስጥ ለቆየ አካባቢ የተለየ መልክ ነበረው። እንግዳ አቀባበላቸው በእርግጥም የመሃል አገር ሰው የናፈቃቸው ይመስላል። የተትረፈረፈ እህልና ውሃ አቅርበው በ’ብሉልን፤ ጠጡልን’ ተማጽኗቸው የተነፋፈቀ ቤተ-ዘመድ ግብዣ አስመሰሉት። የሥላሴው ጠበል የሸሬ ጠላ ቀረበ። የሸሬ ጠላ ሳስታውስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ታወሱኝ። የወቅቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምሀሩ ፕሮፌሰር ሽብሩ በዘመነ ደርግ በዕድገት በሕብረት ዘመቻ ተማሪዎቻቸውን ይዘው ሽሬ ዘምተው ነበር። በወቅቱ ታዲያ የሸሬ ጠላ ፍቅር ይዟቸው በየጊዜው ሲኮመኩሙ የተመለከቱ ሰዎች ‘ፕሮፌሰሩ ከጠፉ የሚገኙት ጠላ ቤት ነው’ ሲባሉ እንደነበር ‘ከጉሬ ማርያም እስከ አዲስ አበባ’ በተሰኘው ግለ ታሪካቸው አስፍረዋል። ከግብዣ መልስ ከማረፊያ ሆቴል ላይ ሆኜ ከተማዋን ስቃኛት ከጦርነት ድባቴ የተላቀቀች ይመስላል። የአመሻሽ ሕዝቡ እንቅስቃሴም ሆነ እስከ ሌሊቱ አጋማሽ የሚሰሙ የመዝናኛ ቤቶች ሙዚቃዎች የከተማዋን አሁናዊ መልክ የገለጠልኝ ነበር። ንጋት ላይ በቁርስና ቡና ሰዓታት ከሰዎች ጋር መስተጋብሬ ጀመረ። በጦርነት አዙሪት የከረመችው ሽሬና አካባቢው ኑሮ እጅጉን የከበደ ነበር። መልከ-ብዙ ማህበራዊ ቀውሶች አስተናግደዋል። አሁናዊ ምላሻቸው “ተመስገን፤ ያ ሁሉ አለፈ” የሚል ነው። ገበያው ተረጋግቷል፤ ማህበራዊ ኑሮ ተመልሷል። ድህረ-ሰላም ስምምነት ለሽሬ ነዋሪዎች ሁለንተናዊ እፎይታን አንብሯል። ከቀናት በኋላ በአክሱም የታዘብኩትም እንዲህ ነው። ኑሮን ያቀለለው የተቋማት አገልግሎት ጅማሮ በመጀመሪያ ዘገባ ስራዬ መሰረተ ልማትን አገልግሎት ቃኘሁ። ባንክ፣ ቴሌ፣ ሆስፒታል… መሰሎቹን። ተጠቃሚዎችንም፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ስራ ሃላፊዎችንም አነጋገርሁ። ከሰላም ስምምነቱ ማግስት ጀመሮ ተቋማቱ ወደስራ መመለሳቸው ከሁለንተናዊ ችግር እንደታደጋቸው ያነሳሉ። በትራንስፖርት እየተንቀሳቀሱ፣ በኤሌክተሪክ ስራዎቻቸውን እየከወኑ ነው። ለሁለት ዓመታት የተቋረጠው አገልግሎት አቅርቦት እና የአገልግሎት ፈላጊዎች ፍላጎት ግን አሁንም ሙሉ በሙሉ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ የተጠቃሚዎችም፤ የአገልግሎት ሰጭዎችም ሀሳብ ነው። በሽሬ ስሁል ሆስፒታል የተመለከትኳቸው፤ ያነጋገርኳቸው፤ ከታዳጊዎች እስከ አዛውንት ዕድሜ ያሉ ህሙማን የሰላም አየር ማግኘታቸው የሕይወታቸው ዑደት እንዲቀጥል አድርጓል። ድንገተኛም ሆነ ነባር ህመም ያለባቸው ሰዎች በነጻ እየታከሙ ነው ያገኘኋቸው። ሰላም ከሌለ መታከም ቀርቶ በቅጡ ማስታመም፤ በወጉ መቀበርም እንደማይቻል ገልጸውልናል። የጤና፣ የባንክና የቴሌኮም አገልግሎት የግብዓት ክፍተቶች የማሟላት ሰራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም በፌዴራል ደረጃ በየተቋማቱ የተመደቡ አስተባባሪዎች አረጋግጠውልኛል። የጸጥታ አካሉና የህብረተሰቡ ትብብርም የሚያስቀና እንደሆነ ግለሰቦችም፤ የጸጥታ አካላትም ነግረውኛል። አክሱም ጺዮን ማርያም፣ ሽሬ ስላሴ ንግስ፣ የጥምቀት በዓላት ከሶስት ዓመታት በኋላ በአደባባይ ታቦት ወጥቶ ተከብሯል። የፌዴራል ፖሊስ ተወካዮችም ይህንኑ ነው ያረጋገጡልኝ። የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከከተማ ነዋሪዎች ጋር ያላቸው ግንኙነት ቤተሰባዊ የሆኑ ይመስላል። እንቅስቃሴያቸውም የሰላማዊ ቀጠና መልክ ያለው ነው፤ ዩኒፎርም ከመልበሳቸው በስተቀር ጀሌያቸውን ይንቀሳቀሳሉ። ይህ ደግሞ መተማመን ከመፍጠር ባለፈ ጦርነት ውስጥ ለቆየ ማህበረሰብ ከስነ ልቦና ጫና እንዲላቀቅ አይነተኛ ሚና እንደላው ይሰማኛል። ኢ-መደበኛ የሽሬና አክሱም ወጎች ያረፍኩበት ሆቴል ባለቤት ‘አደይ’ ተግባቢ ናቸው። ደግ እናት ይመስላሉ። ከገባን ጀምሮ ‘ጠላ ተጎንጩ፤ ቡና ጠጡ’ ጭንቃቸው ነው። ሁለት ቀን ቡና አስፈልተውልናል፤ ጠላ አቅርበው ዘክረውናል። ይህ ሁሉ ሲሆንም ለከተማው እንግዳ መሆናችንን እንጂ ስለሙያችንም ሆነ ስለሌላ ማንነታችን አያውቁም ነበር። ብዙ መጨዋወትና ውሎ አዳር በኋላ ነው ጋዜጠኛ ስለመሆናችን ያወቁት። አደይ ተጨዋች ናቸው። አማርኛ ያዝ ቢያደርጋቸውም ጨዋታቸው ‘ኩርሽም’ ነው- ተሰምቶ የማይሰለች። በአጋጣሚ ‘ሰለክላካ’ ስለምትባለዋ ታሪካዊ ሥፍራ ጠይቄያቸው እያወጋን ነበር። ‘እንደእናንተ ወጣቶች ሳለን ‘ሰለክላካን ያላዬ ሸዋን ያመሰግናል’ ይባል ነበር። ታዲያ አንድ የሸዋ ሰው መጣና ሰለክላካን አየና ‘በቃ ይቺ ናት’ ሰለክላካ’ ብሎ ተገረመ” ብለው አሳቁን። (የፍቅር እስከ መቃብር መሪ ገጸ-ባህሪው ‘በዛብህ’ ወደ ዲማ ጊዮርጊስ ሄዶ ‘የዲማ መልኳ እና ዝናዋ’ ተጣርሶበት እንደተገረመበት ቅጽበት መሆኑ ነው)። አደይ የተጀመረው ሰላም ፍጹም ምሉዕ ሆኖ ወደ ቀደመ ኢትዮጵያዊ መልካችን የምንመለስበት ጊዜ እንዲመጣ ይሻሉ። ከጦር-ነት ወደ ሰላም-ነት! ቆንጂዬዋ ፊዮሪ የኮሌጅ ተማሪ ነበረች። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ጀምሮ በኋላም በጦርነት ሳቢያ ትምህርቷን ካቆመች ሦስት ዓመታት ሆኗታል። ጦርነቱ ከቆመ በኋላ የጀበና ቡና ጀምራለች። ደንበኞቿ ሰብሰብ ብለን እንቀመጣለን። ፊዮሪ ከስኒ ማቅረቢያዋ ላይ አነስተኛ ጀበናዋን፤ የሚያማምሩ ስኒዎቿን እና መዓዛው ከሚያውድ የዕጣን ማጨሻዋ ጋር ሰድራ ይዛ ትቀርባለች። ከመካከላችን ካለው ጠረጴዛ ላይ ታስቀምጥና እርሷም ወንበር ይዛ ከመካከላችን ትቀመጣለች። ቡናው እስኪሰክን ጨዋታዋን ታስኮመኩመናለች። ቡናው ከሰከነ በኋላ ቡናዋን ቀድታ ለእያንዳንዳችን በእጃችን እያነሳች ትሰጣለች። በሽሬ ቡና የሚቀርበው በዚህ መልክ ነው። ለፊዮሪ እና መሰሎቿ ጦርነቱ ክፉ ጠባሳ መጣሉ፤ ተስፋቸው ላይ መጥፎ አሻራ ማስቀመጡን ታነሳለች። አሁን ግን ብሩህ ተስፋ ሰንቃለች። ስለነገዋም “ሰላሙ ይዝለቅልን፤ ትምህርቴን ለመቀጠል እመኛለሁ” ትላለች። አክሱም ከሽሬ በስተሰሜን 60 ኪሎ ሜትር ይርቃል። ከሽሬ አክሱም ስንንቀሳቀስ ከጥምቀት ዕለት በስተቀር ገበሬው የግብርና ሥራዎቹን እየከወነ ነበር። አርሶ አደሩ ያርሳል፤ መስኖውን ያለማል። የተዘራውን ውሃ ያጠጣል። የበቀለ ቡቃያውን ይኮተኩታል። ከጦርነት ወደ ልማት መዞሩን ዐይኔ ታዝቧል። በጥምቀት ዋዜማ፤ የከተራ በዓል ዕለት ሁለት ጎራማይሌ የረፋድ ትዕይንቶችን ላንሳ። ከአክሱም ከተማ ወደ አድዋ እና ሽሬ መገንጠያ አካባቢ ሰፊ የቀንድ ከብት ገበያ ነበር። እውነተኛ የዓመት በዓል ገበያ መልክ ያለው ትዕይንት ነበር። በተለይም የፍየል ዋጋ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተገበያዩ እንደነበር ሰምቻለሁ። ታሪካዊቷን አክሱም ከተማ ለመጨረሻ ጊዜ የረገጥኳት/የተሳለምኳት ከአራት ዓመት በፊት በ2011 ዓ.ም ይመስለኛል። ከገበያው ቀጥሎ በታቦተ-ጽዮን መገኛዋ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ደጅ፣ በጥንታዊያኑ የአክሱም ሐውልት መገኛ አደባባይ ነበር። ከጽዮን በስተምዕራብ በአርባቱ እንሰሳ በኩል፤ በቅዱስ ያሬድ ዋርካ… አድርጌ በጽዮን ዋናው በር ደረስኩ። ማራኪ የአክሱም የኮብልስቶን መንገዶች ኦና ናቸው። የወትሮው ግርግር ናፍቋቸዋል። ከጽዮን ቅጥር ግቢ በዋናው በር በስተውጭ አነስተኛ እና ብቸኛ ዋንዛ በኮብልስቶን መሃል ነበረች። ዛሬም ለምልማ አለች። በዚህ አካባቢ ድሮ የነጭ ጎብኚ ጋጋታ፣ የጽዮን ደጅ ጠኚ ምዕመን… የተጨናነቀ ነበር። እንደ ድሮው የፎቶ አንሺ ግርግር፣ የአክሱም መስቀል ቀርጸው የሚሸጡ ወጣቶች ጫጫታ የለም። ይልቁንም እርጥባን የሚሹ አቅመ ደካሞችና ህፃናት ነበሩ። ጦርነት የሥፍራዋን መልክ አጠይሞታል። ያም ሆኖ ከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ሙሉ በኩሉሄ ባይባልም ወደነበረበት እየተመለሰ ነው። የግልም ሆነ የመንግሥት ባንኰች ሥራ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ከአክሱም ሐውልት ወደ ሌላ ሰፈር አቀናሁ። ትርሐስ ገና ታዳጊ ልጅ ነች። ጠይም፤ ስርጉድ፣ ሳቂታና ተረበኛ አይነት ልጅ ነች። እንደ ሽሬዋ ፊዮሪ መንገድ ዳር የጀበና ቡና እየሰራች ነው። ከሩቅ የመጣን እንግዶች መሆናችንን ስታውቅ፤ ደስታዋ ከገጿ ይነበብ ነበር። ያለፉ ጊዜያትን ሰቆቃ አጫወተችን። ስለቀጣይ ዕጣ ፈንታዋ እና ዕቅዷ ስታወራ ትቆይና “የሰው ልጅ ግን በጣም ከሃዲ ነው። ከወራት በፊትኮ ስለቢዝነስ አላስብም ነበር። መቼ እሞታለሁ እንጂ” ብላ ራሷን ትወቅሳለች። ወደ ሰማይ አንጋጣ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች። ጦርነት ተራውንም ሕዝብ ለመልከ-ብዙ ቀውስ ዳርጎት እንደቆየ ታነሳለች። ዛሬ ሁሉ አልፎ ሰላም መውረዱ ለመጨዋወት መብቃቷ ለእርሷ ትልቅ ብሥራት ነው። ይህ ለትርሐስ ብቻ ሳይሆን ለመላው አክሱማዊያን መሆኑ እሙን ነው። አክሱም ከተማ በመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር ሥር ከዋለችበት ጊዜ ጀምሮ በከተማዋ በሻለቃ አዛዥነት የተሰማራ የፌደራል ፖሊስ አባልም ያጋጠመውን አሳዛኝ ገጠመኞች አጫውቶኛል። ጦርነቱ ቢራዘም ኖሮ በተራው ሕዝብ ላይ ምን ያህል የከፋ ጉዳት ይደርስ እንደነበር በአሳዛኝ ሁኔታ ገልጾልኛል። አክሱሞች ያን ሁሉ አልፈው ሰላም አየር ነፍሶ፣ ከስጋት ቆፈን ተላቀው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ተመልሰዋል። የዛሬ ሳምንት ሰርክ(11 ሰዓት) ላይ አክሱም የከተራ በዓል በድምቀት አክብራለች። ታቦተ-ጽዮን ወደ ባህረ- ጥምቀቱ ስትወርድ፤ ወግና ሥርዓቱ ተጠብቆ፣ ሕዝቡ በሀበሻ ነጫጭ አልባሳት፣ ካህናት በልብሰ ተክህኖ ደምቀው … እየተከወነ ነበር። አንዲት እናት ለአማርኛ ተናጋሪ በቀረበ አነጋገር እያለቀሱ ታቦት እየሸኙ ነው። ትኩር ብዬ ሳያቸውም ዕንባቸው ዱብ ዱብ ይላል። “ከዚያ ሁሉ መከራ አልፎ ለዚህ በቃን፤ ተመስገን” እያሉ እልልታውን ያቀልጡታል። በደስታ እያነቡ ነበር። ይህ ስሜት የብዙኃኑ አክሱማዊያን እናቶች እንደሆነ መገመት ቀላል ነው። አክሱም በኮቪድ እና በኋላም በጦርነቱ ምክንያት ባህረ-ምቀት ታቦት ወጥቶ ሲከበር ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። ከወትሮው በተለየ ድምቀትና ውበት በሰላምና በደስታ፤ በአደባባይ እልልታና ሆታ በማክበራቸው ልዩ ስሜት ፈጥሮባቸዋልና! እናም በአክሱም የከተራ ሆነ የበዓለ-ጥምቀት ክብረ-በዓላት በሰላም ስምምነቱ ማግስት በድምቀት ተከውኖ አለፈ። የሃይማኖት አባቶቹም ሆኑ ምዕመኑ በሰጡት ቃለ መጠይቅም የዘንድሮው ክብረ-በዓል ካለፉት ዓመታት ነባራዊ ሁኔታ ጋር እያነጻጸሩ፤ ትልቅ ብሥራትና መልክ እንዳለው ገልጸዋል። ሰላም እንዲጸና፤ ነባር ኢትዮጵያዊ አንድነትና መተባበር እንዲመለስ ጽኑ መሻታቸውን ነግረውናል። በበጎ ቀን የማውቃትን አክሱም፤ ከረዥም ጊዜ በኋላ አሁናዊ መልኳን ታዝቤ፤ የነገ ትዝታ ሰንቄ ተመለስኩ!! ሰላም ለኢትዮጵያ!!