ኢዜአ - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
በባሌ ዞን በክረምቱ የተገነቡ 46 ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ለመማር ማስተማር ዝግጁ ሆነዋል
Sep 22, 2023 38
ሮቤ፤ መስከረም11 /2016 (ኢዜአ):- በባሌ ዞን በክረምቱ ወራት የተገነቡ 'ቡኡራ ቦሩ' የተሰኙ 46 ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ለዘንድሮ የትምህርት ዘመን ዝግጁ መሆናቸውን የዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት ገለጸ። በዞኑ ካለፈው በጀት ዓመት መገባደጃ አንስተው በክረምቱ የተከናወኑት የትምህርት ቤቶች ደረጃ የማሻሻል ሥራም የተማሪዎች የቅበላ አቅም ከማሻሻሉም በላይ ምቹ የመማር ማስተማር ሂደት እንደሚፈጥሩ ተገልጿል። የዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ጸጋ አለማየሁ እንደገለጹት በዞኑ ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የትምህርት ቤቶች ደረጃ ማሻሻል ስራ እና የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ጎን ለጎን ሲከናወኑ ቆይተዋል። በዚህም በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች ባለፈው ዓመት ክረምቱን ጨምሮ በህዝብ ተሳትፎና በመንግስት በጀት 46 'ቡኡራ ቦሩ' የተሰኙ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ተከናውኗል ነው ያሉት። ትምህርት ቤቶቹም በተያዘው የትምህርት ዘመን ህጻናትን ተቀብለው ለማስተማር ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። በተመሳሳይ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻሉ ተግባር በስፋት መከናወኑን ገልጸው፤ በዚህም 120 አዳዲስ የመማሪያ ክፍሎች ግንባታና ጥገና እንዲሁም 97 የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም 1 ሺህ የሚጠጉ የተማሪዎች መቀመጫ ወንበሮችና 20 ኮምፒዩተሮችን በመጠገን ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረግ መቻሉን አክለዋል። አቶ ጸጋ እንዳሉት፣ የትምህርት ቤቶች ግንባታና ደረጃ ማሻሻል ስራው በአዲሱ የትምህርት ዘመን ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ 50 ሺ ህጻናትን የመቀበል አቅም ፈጥሯል። የትምህርት ቤቶች ደረጃ ማሻሻል ስራው ምቹ የመማር ማስተማር ሂደትን ከማሳለጥ በተጓዳኝ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትልቅ እገዛ እንዳለውም አመልክተዋል። ለትምህርት ዘመኑ የሚያስፈልጉ የትምህርት ግብዓቶችን ከማሟላት አንጻርም በህብረተሰብ ተሳትፎ በርካታ ስራዎች መከናወኑን ጠቁመዋል። በዞኑ በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የተከናወኑት የትምህርት ቤቶች ማሻሻልና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች 560 ሚሊዮን ብር በሚገመት የህዝብ ተሳትፎና የመንግስት በጀት መከናወናቸውንም ገልጸዋል። በዞኑ ጎባ ወረዳ ነዎሪዎች መካከል አቶ ሀሰን አብደላ በሰጡት አስተያየት፣ በአካባቢያቸው የተገነቡ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ህጻናት ከአካባቢያቸው ሳይርቁ መሰረታዊ ትምህርት በጊዜ እንዲቀስሙ ዕድል ይፈጥራል። የትምህርት ቤት መሰረተ ልማት በህብረተሰብ ተሳትፎ ለማመቻቸት የተቋቋመው ኮሚቴ አባል ሆነው ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቁመው፤ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተጎዱ የመማሪያ ክፍሎች መጠገናቸውንም አውስተዋል። በባሌ ዞን በ2016 የትምህርት ዘመን እስከ አሁን ከ290 ሺህ 900 የሚበልጡ ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 134 ሺህ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ከዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት የተገኛው መረጃ ያመለክታል።
የአልጄሪያ አየር መንገድ ከአልጀርስ ወደ አዲስ አበባ የመጀመሪያውን የቀጥታ በረራ አደረገ
Sep 22, 2023 48
አዲስ አበባ፤ መስከረም 11/2016(ኢዜአ)፦የአልጄሪያ አየር መንገድ ከአልጀርስ ወደ አዲስ አበባ የመጀመሪያውን የቀጥታ በረራ ዛሬ አድርጓል። በዚሁ በረራ በአልጄሪያ የትራንስፖርት ሚኒስትር ዮሴፍ ቻሮፍ የተመራ የአልጄሪያ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሃላፊዎች ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ ገብቷል:: የልዑካን ቡድኑ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል አምባሳደር ፍሰሃ ሻውል፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው፣ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር ሞሃመድ ላምኔ ላባስን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውለታል:: ኢትዮጵያና አልጄሪያ እ.አ.አ በ1985 የአየር በረራ አገልግሎት ስምምነት የተፈራረሙ ቢሆንም ለበርካታ ዓመታት ተግባራዊ ሳይሆን ቆይቷል። በዚሁ መሰረት በሁለቱ ሀገራት መካከል የቀጥታ በረራ እንዲኖር ለማስቻል ከዚህ ቀደም የተፈረመው ስምምነት አሁናዊ ሁኔታን ባገናዘበ መልኩ ታድሶ ወደ ስራ እንዲገባ በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል። በኢትዮጵያና አልጄሪያ መካከል የትራንስፖርትና አቪዬሽን ዘርፉን ትስስር ለማጠናከር በቅርቡ በሁለቱ ሀገራት መካከል መግባባት ላይ መደረሱ ይታወሳል፡፡ ዛሬ የተጀመረው በረራ ስምምነቱን ወደ ተግባር ለመቀየሩ አንዱ ማሳያ መሆኑም ተመላክቷል:: የኢትዮጵያና የአልጄሪያ የሁለትዮሽ ግንኙነት የተመሠረተው እ.አ.አ በ1960 ዎቹ ሲሆን አልጄሪያ ኤምባሲዋን እ.አ.አ በ1976 በአዲስ አበባ ከፍታለች ::
በአማራ ክልል በቢራ ገብስ ከለማው መሬት ከ282ሺህ 400 ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል
Sep 22, 2023 40
ባህር ዳር፤ መስከረም 11 ቀን 2016(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በመኸሩ ወቅት በቢራ ገብስ ከለማው መሬት ከ282 ሺህ 400 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ አግደው ሞላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በመኽር ወቅቱ በክልሉ እየለማ ካለው የሰብል ዓይነት ውስጥ የቢራ ገብስ አንዱ ነው። በወቅቱ በ12 ሺህ 270 ሄክታር መሬት ላይ የቢራ ገብስ መልማቱን አመልክተው ከዚህም የሚጠበቀው ምርት ከ282 ሺህ 400 ኩንታል በላይ መሆኑን አስታውቀዋል። ክልሉ በቢራ ገብስ የመልማት ሰፊ አቅም እንዳለው ጠቅሰው፤ የአርሶ አደሩ በቢራ ገብስ የማልማት ፍላጎቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል። ልማቱን ውጤታማ ለማድረግም የግብርና ባለሙያዎች ለአርሶ አደሩ ክትትልና ድጋፍ እየተደረጉ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በደቡብ ጎንደር ዞን ፋርጣ ወረዳ ሳርና ቀበሌ አርሶ አደር የማታ ቢሰጥ በሰጡት አስተያየት፤ በመኸሩ ወቅት ሩብ ሄክታር መሬት ላይ ቢራ ገብስ አልምተው እየተንከባከቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። አንድ ኩንታል ቢራ ገብስ በ6 ሺህ 500 ብር ለማስረከብ ደብረታቦር ከተማ ከሚገኘው መገናኛ ዩኒየን ጋር የውል ስምምነት ይዘው እየሰሩ እንደሆነ ጠቁመዋል። በዘር ከሸፈኑት መሬት እስከ አስር ኩንታል ምርት ለማግኘት ማቀዳቸውን ጠቅሰው፤ አሁን ላይ ሰብሉ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ግማሽ ሄክታር መሬት በቢራ ገብስ እያለሙ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ በዚሁ ወረዳ የማይናት ቀበሌ አርሶ አደር ያለለት ሞላ ናቸው። አሁን ላይ ሰብሉን ከአረምና ፀረ ሰብል ተባይ እየጠበቁ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። የመገናኛ ዩኒየን ስራ አስኪያጅ አቶ ተስፋየ አየነው በበኩላቸው፤ ዩኒየኑ በደቡብ ጎንደር ዞን ፋርጣና ጉና ወረዳዎች ቢራ ገብስ የሚያለሙ አርሶ አደሮች ጋር ቀድሞ ውል በመያዝ ወደ ስራ መግባቱን ገልጸዋል። አንድ ኩንታል የቢራ ገብስ በ6 ሺህ 500 ብር ለመረከብ ውል መያዛቸውንና አርሶ አደሮች የምርታቸውን ጥራት ጠብቀው ማዘጋጀት እንደሚጠበቅባቸው አመልክተዋል። በአማራ ክልል ባለፈው ዓመት ከለማው መሬት 303 ሺህ ኩንታል የቢራ ገብስ በማምረት ለጎንደር ብቅል ፋብሪካ ማቅረብ እንደተቻለ ተመላክቷል።
አውደ-ርዕዩ በዘርፉ ያካበተ ልምድ ካላቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር ለመሥራት እድል ፈጥሯል - የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር
Sep 22, 2023 103
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 11/2016 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ለአንድ ወር የተካሄደው የውኃና ኢነርጂ አውደ-ርዕይ በዘርፉ ያካበተ ልምድ ካላቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር ለመሥራት እድል መፍጠሩን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለጸ። የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር "የውኃ ኃብታችን ለብልጽግናችን" በሚል መሪ ኃሳብ በሳይንስ ሙዚየም ለአንድ ወር ያካሄደው አውደ ርዕይ ትላንት ተጠናቋል። አውደ ርዕዩ ምን አስገኘ? የሚለውን ለማወቅ ኢዜአ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና በአውደ-ርዕዩ አገልግሎታቸውን ያቀረቡ ተቋማትን አነጋግሯል። በሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ጌትነት ጌጡ፤ በአውደ-ርዕዩ ዘርፉን ለማዘመን በትግበራ ላይ ያሉ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለዕይታ ቀርበዋል ብለዋል። ለአብነትም ኢትዮጵያ የውኃ መጠኗን በዲጂታል መተግበሪያ በመታገዝ እንዴት እንደምትከታተልና እንደምትቆጣጠር ማሳየት መቻሏን ጠቁመዋል። አውደ-ርዕዩን የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጨምሮ የዘርፉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች እንዲሁም አምባሳደሮች መጎብኘታቸውን ነው ያረጋገጡት። በመሆኑም አውደ-ርዕዩ አገሪቱ በዘርፉ የምታከናውነውን ሥራ ለማስገንዘብ እድል ሰጥቷል ነው ያሉት። ከዚህ በተጠማሪም አውደ-ርዕዩ በዘርፉ ከተለያዩ ተቋማት ጋር አዳዲስ አጋርነትና ትብብር ለመመሥረት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ገልጸዋል። በመድረኩ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ያቀረቡ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት በበኩላቸው አውደ-ርዕዩ የውኃና ኢነርጂ ዘርፍን በቴክኖሎጂ ለማዘመን የሠሯቸውን ሥራዎች ለሕዝብ ለማቅረብ እድል ሰጥቶናል ብለዋል። በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በመረጃና ክላይማቶሎጂ ክፍል ተመራማሪ የሆኑት ለታ በቀለ ተቋማቸው በአውደ-ርዕዩ በአገሪቱ ያለውን የአየር ፀባይ ሁኔታ ጥናት ለማካሄድ የሚጠቀምባቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶች ማቅረባቸውን ጠቅሰዋል። የተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አውደ-ርዕዩን መጎብኘታቸው ገልጸው ይህም በቀጣይ በሚቲዎሮሎጂ ዘርፍ አብረው መሥራት የሚችሉባቸውን ሁኔታዎች ለመለየት ዕድል መፍጠሩን ነው የገለጹት። የአነጋ ኢነርጃይዝ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የሽያጭ ባለሙያ እየሩሳሌም ደጀኔ በበኩሏ በአውደ-ርዕዩ ኅብረተሰቡ የሚጠቀምባቸውን ኃይል ቆጣቢ ምድጃዎች ማቅረባቸውን ተናግራለች። በዝግጅቱ ላይ መሳተፋቸው ኃይል ቆጣቢ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በቀላሉ ለማስተዋወቅ እንደረዳቸው በመግለፅ እንደ አገር መሰል አውደ-ርዕዮች በተለያዩ አካባቢዎች ሊስፋፉ እንደሚገባ ተናግራለች። በሐፍ አስመጪና አቅራቢ ድርጅት የኦፕሬሽን ማናጀር ሃበን ገብሩ በአውደ-ርዕዩ ምንም አይነት ኤሌክትሪክ ኃይልና የውኃ ማጣሪያ ኬሚካል ሳይጠቀም ውኃን ማጣራት የሚችል ቴክኖሎጂ ለኅብረተሰቡ በስፋት አሳይተናል ብለዋል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች አምስት አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን እንደሚያስገነባ አስታወቀ
Sep 22, 2023 72
አዲስ አበባ፤ መስከረም 11/2016(ኢዜአ)፦የቱሪዝም ሚኒስቴር በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች አምስት አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን እንደሚያስገነባ አስታወቀ፡፡ የሚኒስቴሩ የህዝብ ግኑኙነት ዳይሬክተር ዶክተር ዓለማየሁ ጌታቸው ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ ያላትን የቱሪዝም አቅም በሚፈለገው ደረጃ ጥቅም ላይ ማዋል ሳትችል ቆይታለች፡፡ በመሆኑም አሁን ላይ መንግስት አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን በማስተዋወቅ ከዘርፋ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በዚህም የአገር ውስጥ እና የውጭ አገር ጎብኝዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል። የቱሪዝም ፍሰቱን ይብልጥ ለማሻሻልም የነባር የቱሪዝም ስፍራዎችን ማደስና አዳዲስ የማልማቱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው የገለጹት፡፡ ከዚህ አኳያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተያዘው በጀት ዓመት በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ህዝብን በማስተባበርና የፋይናንስ ምንጮችን በማፈላለግ አምስት አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን የማልማት ስራ እንደሚጀምር ጠቁመዋል፡፡ የሚለሙት የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎች በቀጣይ ይፋ እንደሚደረጉም ነው የተናገሩት፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ "በገበታ ለሀገር" እና "በገበታ ለትውልድ" አማካኝነት እያከናወኗቸው ያሉ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን የማልማት ስራ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ ከዘርፉ የምታገኘውን ገቢ በእጅጉ እንደሚያሻሻልም ተናግረዋል፡፡
ፖለቲካ
በባህርዳር ከተማ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሰላም ውይይት እየተካሄደ ነው
Sep 22, 2023 61
ባህር ዳር ፤ መስከረም 11/2016(ኢዜአ)፡- በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሰላምና የልማት ውይይት እየተካሄደ ነው። ውይይቱ እየተካሄደ ያለው "ሁለንተናዊና ዘላቂ ሰላም ለመገንባት የሁሉንም አካል ርብርብ ይጠይቃል" በሚል መሪ ሃሳብ ነው። በውይይት መድረኩ የባህር ዳርና አካባቢው ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ሜጀር ጄኔራል ሙሉአለም አድማሱ፣ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ናቸው። የከተማ አስተዳደሩ የህዝብ ግንኙነት አማካሪ አቶ ጊዜው ታከለ ባቀረቡት ጽሑፍ፤ በነበረው የጸጥታ ችግር ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል። ችግሮቹ በሰላማዊ መንገድ በዘላቂነት የሚፈቱ ናቸው ያሉት ጽሑፍ አቅራቢው፤ መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ችግሮች እንዲፈቱ ከህዝቡ ጋር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የውይይቱ ዓላማ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የህዝቡን ተሳትፎ ለማጠናከር መሆኑን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ በባለ ብዙ ወገን የትብብር ስርዓት ውስጥ ቁልፍ ሚና ያላት አገር ናት-አንቶኒዮ ጉቴሬዝ
Sep 22, 2023 140
አዲስ አበባ፤ መስከረም 11/2016 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በባለ ብዙ ወገን የትብብር ስርዓት ውስጥ ቁልፍ ሚና የምትጫወት አገር መሆኗን የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ። 78ተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ "ሰላም ፣ብልፅግና፣ ለውጥና ዘላቂነት" በሚል መሪ ሀሳብ በኒው ዮርክ መካሄዱን ቀጥሏል። የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ከጉባኤው ጎን ለጎን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ዋና ፀሐፊው በተመድ የስደተኞች ኮሚሽን የስልጣን ዘመናቸው ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ጥልቅ የሆነ የአጋርነት ስሜት እንደነበራቸው አውስተዋል። ኢትዮጵያ ያሉባትን የማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎችን ለመፍታት እያደረገች ባለው ጥረት ስኬታማ እንድትሆን ተመኝተዋል። ጉቴሬዝ በስልጣን ዘመናቸው ተመድ ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግንኙነት እንዲጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በባለ ብዙ ወገን የትብብር ስርዓት ቁልፍ ሚና ያላት አገር ናት ብለዋል ዋና ፀሐፊው። አቶ ደመቀ ተመድ እና ዋና ፀሐፊው በግል ጥረታቸው ለኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ወቅቶች ያደረጉትን ድጋፍ አድንቀዋል። አቶ ደመቀ ለአንቶኒዮ ጉቴሬዝ የሰላም ስምምነቱን ትግበራ አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። ተመድ የመልሶ ግንባታና መልሶ ማቋቋም ጥረቶችን እንዲሁም ሌሎች የሰብዓዊ ጉዳዮች ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች በንግግር ለመፍታት ለሚደረገው ሀገራዊ ምክክር ስኬት የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል- የወጣት አደረጃጀት ኃላፊዎች
Sep 21, 2023 81
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች በንግግር ለመፍታት ለሚደረገው ሀገራዊ ምክክር ስኬት የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ የተለያዩ የወጣት አደረጃጀት ኃላፊዎች ገለፁ። የኢትዮጵያን ሰላም በማጽናት በጥሩ መሠረት ላይ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት በተለይም የወጣቶች ተሳትፎና እገዛ ወሳኝ መሆኑ ይታመናል። በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባት እንዲሁም ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለመፍጠር ደግሞ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወቃል። በመሆኑም ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የድርሻችንን እገዛና ተሳትፎ ለማድረግ ተዘጋጅተናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የወጣት አደረጃጀት ኃላፊዎች ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ፉአድ ገና፤ ወጣቶች በሀገራዊ ምክክር ጉዳዮች ታዳሚ ብቻ ሳይሆኑ የአጀንዳው ባለቤት ሆነው መንቀሳቀስና ማገዝ ይጠበቅባቸዋል ብሏል። ሌላው የምክር ቤቱ አባል ኑር ሁሴን እና 'ዩዝ ካውንስሊንግ ሕብረት' የተሰኘው የወጣት አደረጃጀት ሊቀመንበር አብዲ መገርሳ፤ መሠረታዊ ችግሮችን በውይይት ለመፍታት የወጣቶች ተሳትፎና እገዛ ወሳኝ በመሆኑ ለዚሁ ስኬት መሥራት አለብን ነው ያለው። ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ውጤታማነት የድርሻችንን ለማበርከት ተዘጋጅተናል ሲሉ አረጋግጠዋል። የመላው አፍሪካ ወጣቶች ድርጅት ምክትል ፕሬዝዳንት ወጣት መስፍን ደሴ፤ በሀገራዊ ምክክር መድረኮች የወጣቶች እገዛ፣ ተሳትፎና ትብብር በተጠናከረ መልኩ መቀጠል አለበት ብሏል። የእንደራሴ ወጣቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት ብሩክ አስቻለው፤ ወጣቶች ለሀገራዊ ሰላምና አንድነት በትብብር የመሥራት ሀገራዊ ኃላፊነት አለባቸው ሲል ተናግሯል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እና የማኅበራዊ አንትሮፖሎጂ ምሁሩ ዶክተር ከይረዲን ተዘራ፤ የሀገራዊ ምክክር ዓላማ ትናንትን ማከምና ነገን ማስተካከል በመሆኑ፤ ለዚሁ መልካም ተግባር መሳካት በተለይም የወጣቶች ተሳትፎ የላቀ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። ሀገርን እየፈተኑ ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና ልማትን በማስቀጠል የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አተገባበር ገለልተኛና አካታችነትን መሠረት ያደረገ በመሆኑ በተለይም ወጣቶች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
የግጭት ምክንያቶችን ለይቶ በማውጣትና እልባት በመስጠት ሰላምን ማጽናት ይገባል-የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
Sep 21, 2023 155
ጋምቤላ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፡- የግጭት ምክንያቶችን ለይቶ በማውጣት እልባት በመስጠትና ሰላምን በማጽናት በኩል ሁሉም ዜጋ በአንድነትና በትብብር ሊሰራ እንደሚገባ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አሳሰበ። ኮሚሽኑ በአጀንዳ ልየታ ላይ የሚሳተፉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመምረጥ በጋምቤላ ከተማ ለሦስት ቀናት ያካሄደው መድረክ ዛሬ ተጠናቋል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፈን አርዓያ ባለመግባባት ምክንያት የሚከሰቱ ግጭቶችን ለማስቀረትና ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈን ህዝቦች ችግር ሲገጥም በመነጋገርና በመመካከር ሊፈቱ እንደሚገባ አስገንዘበዋል። በተለይም መሰረታዊ የግጭት መንሰኤ የሆኑ ምክንያቶችን ለይቶ በጋራ መፍታት ከተቻለ ሁሉም የሰላም አሸናፊ እንደሚሆን ኮሚሽነሩ አስረድተዋል። "የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የተቋቋመበት ዋና ዓላማ የግጭት መንስኤ የሆኑ ምክንያቶች ተለይተው እንዲፈቱ በማድረግ በህዝቦች መካከል መግባባትን መፍጠር ነው" ሲሉም ገልጸዋል። ይህንን ግብ ለማሳካት በሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች ከተባባሪ አካላት ጋር በመቀናጀት በአጀንዳ ልየታ መድረክ የሚሳተፉ የህብረተሰብ ተወካዮችን ኮሚሽኑ እያስመረጠ መሆኑን አስታውቀዋል። ኮሚሽኑ ከጋምቤላ ክልል ከሚገኙ 13 ወረዳዎችና ከጋምቤላ ከተማ መስተዳደር በአጀንዳ ልየታ ላይ የሚሳተፉ 504 ተወካዮችን ማስመረጡንም ፕሮፌሰር መስፍን ተናግረዋል። ከመድረኩ ታሳታፊዎች መካከል አቶ ዲድሙ አባላ በሰጡት አስተያየት እንደ ማህበረሰብ ተወካይነታቸው ኮሚሽኑ ለጀመረው ሀገራዊ ምክክር ስኬታማነት የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። "የሚያለያዩን ችግሮችን በማስወገድ፣ በመከባበርና በመደጋገፍ ሰላማችንን ልንጠበቅ ይገባል" ያሉት ደግሞ ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ሰይድ አሊ ናቸው። ኮሚሽኑ በጋምቤላ ክልል ለሦስት ተከታተይ ቀናት ሲያካሄድ በቆየው መድረክ ከጋምቤላ ከተማ እና ከ13ቱ ወረዳዎች በአጀንዳ ልየታ የሚሳተፉ 504 የማህበረሰብ ተወካዮችን በማስመረጥ ዛሬ ተጠናቋል።
ከ300 በላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ተደመሰሱ
Sep 21, 2023 97
አዲስ አበባ፤ መሰከረም 10/2016 (ኢዜአ):- ከ300 መቶ በላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ሲደመሰሱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አባላቱ መቁሰላቸውን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አስታወቀ። በሶማሊያ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ ሃይል ለመቀየር ተልዕኮ ወደ ሚፈፀምበት ቦታ በተንቀሳቀሰው የኢትዮጵያ ሠራዊት ላይ ጠላት ቀድሞ ባገኘው መረጃ መሠረት ደፈጣ ይዞ ሠራዊታችን ላይ ጥቃት ለመሠንዘር የሞከረው አልሸባብ ባላሠበው መልኩ ክፉኛ መመታቱ ተገልጿል። በተሳሳተ ስሌት የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ ቅይይር ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከረው የአልሸባብ ሃይል ከሶስት መቶ በላይ ታጣቂዎቹ ሲገደሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አባላቱም ቆስለዋል። የመከላከያ ሠራዊቱን ምት መቋቋም ያልቻለው አልሸባብ የሞቱ ታጣቂዎቹን አስክሬን እያንጠባጠበ ቁስለኞቹን በመያዝ ወደኋላ ለመፈርጠጥ ተገዷል ። የኢትዮጵያ ሠራዊት የአልሸባብን ደፈጣ እያሥወገደና በየመንገዱ የጠመዱትን ፈንጂና መሠናክሉን እያስወገደ ከተልዕኮው ቦታ ሁዱር መድረስ ችሏል። የአካባቢው ነዋሪዎችም ለመከላከያ ሠራዊታችን ምግብ እና ውሃ በማቅረብ ደስታቸውን እና ምስጋናቸውን ገልፀው፤ በሞራል ያላቸውን ድጋፍም አሳይተዋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ከሥፍራው ደረሰኝ ባለው መረጃ የአልሸባብ ሃይል ሶስት ፈንጂ የጫኑ መኪናዎችን እና 12 ፈንጂ የታጠቁ ታጣቂዎቹን እንዲሁም ከአንድ ሺህ በላይ አሉኝ የሚላቸዉን አባላቱን ለጥፋት በደፈጣ አሰልፏል፡፡ የጥፋት ሃሳቡን ሳያሳካ በሠራዊታችን ክንድ መደምሰሱን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል። አልሸባብ በተለያዩ የምስራቁ የሀገራችን ክፍል ተደጋጋሚ ትንኮሳዎችን የአጥፍቶ መጥፋት ተግባራትን ለመፈፀም ሲሞክር የቆየ ቢሆንም የአሁኑ በታሪኩ ከፍተኛ የሠው ሃይል ያሳተፈበት እና ደፈጣዎች ይዞ ባላሠበው መንገድ የተመታበት መሆኑም ተገልጿል።
የቀይ ባህር ቀጣና ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር በአካባቢው ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው - ሌተናል ጄነራል አለምሸት ደግፌ
Sep 21, 2023 303
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦የቀይ ባህር ቀጣና ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር በአካባቢው ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪና ተኩስ አመራር ኃላፊ ሌተናል ጄነራል አለምሸት ደግፌ ገለጹ። የቀይ ባህር ቀጣና ደኅንነትና ጂኦ-ፖለቲካል ሁኔታን በተመለከተ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትና በመከላከያ ዋር ኮሌጅ ትብብር የተዘጋጀ ውይይት ተካሂዷል። የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪና ተኩስ አመራር ኃላፊ ሌተናል ጄነራል አለምሸት ደግፌ፤ የቀይ ባህር ቀጣና ስትራቴጂካዊ የንግድና የፖለቲካ ማዕከል መሆኑን ገልጸዋል። ጂኦ-ፖለቲካ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታውም የጎላ በመሆኑ የበርካታ አገራትን ትኩረት ስለመሳቡ ተናግረዋል። በቀጣናው ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ሽብርተኝነትና መሰል ችግሮች የጸጥታ ሥጋቶች ሆነው መቀጠላቸውን ጠቅሰዋል። በመሆኑም የቀይ ባህር ቀጣና ሀገራት አካባቢውን ከጸጥታ ስጋት በማውጣት የልማት መዳረሻ ለማድረግ በትብብር መሥራት ይኖርባቸዋል ብለዋል። የአገራቱ የጋራ ትብብር ለቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የእስያና ፓስፊክ አገራት ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር ዶክተር ገበየሁ ጋንጋ፤ የቀይ ባህር ቀጣና አገራት በባህልና ኃይማኖት የተሳሰሩ መሆናቸውን አንስተዋል። የቀይ ባህር ቀጣና በዓለም ካሉት ከፍተኛ የንግድ መስመሮች አንዱ በመሆኑ የአካባቢውን ጸጥታና ደኅንነት በጋራ በመጠበቅ ለጋራ ልማት መጠቀም ይገባል ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሳፍንት ተፈራ፤ የቀይ ባህር ቀጣና በኢኮኖሚ፣ ወታደራዊና መሰል ዓለም አቀፍ ጉዳዮች የጸጥታ ሥጋቱ እየተወሳሰበ መጥቷል ብለዋል። በመሆኑም ለቀጣናዊ ችግሮች ቀጣናዊ መፍትሔ ለመስጠት የአካባቢው አገራት ሁለንተናዊ ትብብር ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል። በአሜሪካ የሰላም ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ አማካሪ ዶክተር ሉካ ኮል፤ አፍሪካ የውኃ ሀብቷን በአግባቡ ተጠቅማ ማልማት ካልቻለች በቀጣይ የከፋ ችግር ላይ ልትወድቅ ትችላለች ሲሉ ተናግረዋል፡፡ አፍሪካ 90 በመቶ የውጭና ገቢ ንግዷን የምታሳልጠው በቀይ ባህር በኩል ቢሆንም በውኃ ሀብት አጠቃቀሟ "የባህር ላይ አይነ ስውር" ሆናለች ነው ያሉት፡፡ በአፍሪካ የባህር ዳርቻ ያላቸው ሀገራት ከዓለም ሀገራት ጋር ሲነፃፀሩ ዝቅተኛ የውኃ ሀብት ተጠቃሚ መሆናቸውን ማሪታይም ደህንነት ኢንዴክስ መረጃን ዋቢ በማድረግ ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም አፍሪካውያን የቀይ ባህርን ጨምሮ የውኃ ሀብታቸውን በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲያውሉ አስገንዝበዋል።
በቀይ ባህር አካባቢ የሚስተዋሉ የጸጥታ ሥጋቶችን በማስወገድ የቀጣናውን ደኅንነት ለማረጋገጥ በጋራ መሥራት ይገባል - ሌተናል ጄኔራል አለምሸት ደግፌ
Sep 21, 2023 103
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦ በቀይ ባህር አካባቢ የሚስተዋሉ የጸጥታ ሥጋቶችን በማስወገድ የቀጣናውን ደኅንነት ለማረጋገጥ በጋራ መሥራት እንደሚገባ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪና ተኩስ አመራር ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል አለምሸት ደግፌ ገለጹ። የቀይ ባህር ቀጣና ደኅንነትና ጂኦ-ፖለቲካል ሁኔታን በተመለከተ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትና በኢፌዴሪ መከላከያ ዋር ኮሌጅ ትብብር የተዘጋጀ ውይይት እየተካሄደ ነው። የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪና ተኩስ አመራር ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል አለምሸት ደግፌ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ የቀይ ባህር ቀጣና ስትራቴጂካዊ የንግድና የፖለቲካ ማዕከል ነው። የቀይ ባህር ቀጣና ጂኦ-ፖለቲካ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጸው ይህም የበርካታ አገራትን ትኩረት መሳቡን ገልጸዋል። ያም ብቻ ሳይሆን ቀጣናው ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ሽብርተኝነትና መሰል የጸጥታ ሥጋቶችም የሚስተዋሉበት ነው ብለዋል። በመሆኑም አሁን ላይ የቀጣናው የደኅንነት ሥጋት ከፍ እያለ መምጣቱን ነው ያስረዱት። በመሆኑ እነዚህን ችግሮች ለመከላከል የቀጣናውን አገራት ትብብር ይፈልጋል ያሉት ሌተናል ጄኔራል አለምሸት የአገራቱ የጋራ ትብብር ለቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ልማት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የእስያና ፓስፊክ አገራት ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ዶክተር ገበየሁ ጋንጋ፤ የቀይ ባህር ቀጣና አገራት በባህልና ኃይማኖት የተሳሰሩ መሆናቸውን አንስተዋል። የቀይ ባህር ቀጣና በዓለም ካሉት ከፍተኛ የንግድ መስመሮች አንዱ በመሆኑ የአካባቢውን ጸጥታና ደኅንነት በጋራ በመጠበቅ ለጋራ ልማት ማዋል ይገባል ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሳፍንት ተፈራ፤ የቀይ ባህር ቀጣና በኢኮኖሚ፣ ወታደራዊና መሰል ዓለም አቀፍ ጉዳዮች የጸጥታ ሥጋቱ እየተወሳሰበ መጥቷል ብለዋል። በመሆኑም ለቀጣናዊ ችግሮች ቀጣናዊ መፍትሔ ለመስጠት የአካባቢው አገራት ሁለንተናዊ ትብብር ማድረግ እንዳለባቸው ነው ምክረ-ኃሳባቸውን የሰጡት።
ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ብልፅግና ስኬት ወጣቶች ግንባር ቀደም ሚና እንዲኖራቸው ጥሪ ቀረበ
Sep 21, 2023 92
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ብልፅግና ስኬት ወጣቶች ግንባር ቀደም ሚና እንዲኖራቸው የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ጥሪ አቀረበ። ዓለም አቀፉ የሰላም ቀን በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በተለያዩ መርሃ-ግብሮች እየተከበረ ነው። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የወጣት አደረጃጀቶችና የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ፉአድ ገና፤ የሰላም ጉዳይ መሠረታዊና ሁሉንም የሚመለከት የጋራ ጉዳያችን ነው ብሏል። በየትኛውም አጋጣሚ ሰላም ከሌለ ሁሉንም በመጉዳት ለሕይወት ማጣት፣ የአካል ጉዳትና የስነ-ልቦና ጫና የሚዳርግ በመሆኑ፤ ሰላምን አጥብቀን መሻትና ለዚያም መሥራት አለብን ነው ያለው። የዜጎችን የእርስ በርስ ግንኙነት ጥርጣሬ ላይ የሚጥል፣ የግጭትና ያለመግባባት መንስኤ የሚሆኑ ነገሮችን ማስወገድ የጋራ ኃላፊነታችን ሊሆን ይገባል ነው ያለው። በተለይም ወጣቶች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ብልፅግና ስኬት ግንባር ቀደም ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል። የሰላም ጉዳይ ከግለሰብ ስብዕና ጀምሮ እስከ ማኅበረሰብ ግንባታ የጋራ ጥረትን የሚጠይቅ መሆኑንም አብራርቷል። በማይገባ ነገር ላይ እርስ በርስ መፈራረጅ፣ የጦርነት ቅስቀሳ፣ ዘረኝነትና ዋልታ ረገጥ እሳቤ ሁሉንም የሚጎዳ የጋራ ችግር መሆኑንም አንስቷል። በመሆኑም በኢትዮጵያ እነዚህና ሌሎችም ለሰላም ማጣት ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በመለየት ዘላቂ መፍትሔ ለመሻት የሚያግዝ የወጣቶች ፎረም የሚካሄድ መሆኑን ጠቅሷል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ዶክተር ቶውፊቅ አብዱላሂ፤ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ግንባታ ወጣቶች ትልቅ ኃላፊነት ወስደው መሥራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። የዓለም የሰላም ቀን እ.ኤ.አ በ1981 በዓለም አቀፍ ደረጃ መከበር የጀመረ ሲሆን፤ የዘንድሮው "የወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም እና ለዓለም አቀፍ ግቦች" በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበር ይሆናል።
ፖለቲካ
በባህርዳር ከተማ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሰላም ውይይት እየተካሄደ ነው
Sep 22, 2023 61
ባህር ዳር ፤ መስከረም 11/2016(ኢዜአ)፡- በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሰላምና የልማት ውይይት እየተካሄደ ነው። ውይይቱ እየተካሄደ ያለው "ሁለንተናዊና ዘላቂ ሰላም ለመገንባት የሁሉንም አካል ርብርብ ይጠይቃል" በሚል መሪ ሃሳብ ነው። በውይይት መድረኩ የባህር ዳርና አካባቢው ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ሜጀር ጄኔራል ሙሉአለም አድማሱ፣ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ናቸው። የከተማ አስተዳደሩ የህዝብ ግንኙነት አማካሪ አቶ ጊዜው ታከለ ባቀረቡት ጽሑፍ፤ በነበረው የጸጥታ ችግር ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል። ችግሮቹ በሰላማዊ መንገድ በዘላቂነት የሚፈቱ ናቸው ያሉት ጽሑፍ አቅራቢው፤ መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ችግሮች እንዲፈቱ ከህዝቡ ጋር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። የውይይቱ ዓላማ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የህዝቡን ተሳትፎ ለማጠናከር መሆኑን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ በባለ ብዙ ወገን የትብብር ስርዓት ውስጥ ቁልፍ ሚና ያላት አገር ናት-አንቶኒዮ ጉቴሬዝ
Sep 22, 2023 140
አዲስ አበባ፤ መስከረም 11/2016 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በባለ ብዙ ወገን የትብብር ስርዓት ውስጥ ቁልፍ ሚና የምትጫወት አገር መሆኗን የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ። 78ተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ "ሰላም ፣ብልፅግና፣ ለውጥና ዘላቂነት" በሚል መሪ ሀሳብ በኒው ዮርክ መካሄዱን ቀጥሏል። የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ከጉባኤው ጎን ለጎን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ዋና ፀሐፊው በተመድ የስደተኞች ኮሚሽን የስልጣን ዘመናቸው ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ጥልቅ የሆነ የአጋርነት ስሜት እንደነበራቸው አውስተዋል። ኢትዮጵያ ያሉባትን የማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎችን ለመፍታት እያደረገች ባለው ጥረት ስኬታማ እንድትሆን ተመኝተዋል። ጉቴሬዝ በስልጣን ዘመናቸው ተመድ ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግንኙነት እንዲጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በባለ ብዙ ወገን የትብብር ስርዓት ቁልፍ ሚና ያላት አገር ናት ብለዋል ዋና ፀሐፊው። አቶ ደመቀ ተመድ እና ዋና ፀሐፊው በግል ጥረታቸው ለኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ወቅቶች ያደረጉትን ድጋፍ አድንቀዋል። አቶ ደመቀ ለአንቶኒዮ ጉቴሬዝ የሰላም ስምምነቱን ትግበራ አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል። ተመድ የመልሶ ግንባታና መልሶ ማቋቋም ጥረቶችን እንዲሁም ሌሎች የሰብዓዊ ጉዳዮች ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች በንግግር ለመፍታት ለሚደረገው ሀገራዊ ምክክር ስኬት የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል- የወጣት አደረጃጀት ኃላፊዎች
Sep 21, 2023 81
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ችግሮች በንግግር ለመፍታት ለሚደረገው ሀገራዊ ምክክር ስኬት የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ሲሉ የተለያዩ የወጣት አደረጃጀት ኃላፊዎች ገለፁ። የኢትዮጵያን ሰላም በማጽናት በጥሩ መሠረት ላይ ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት በተለይም የወጣቶች ተሳትፎና እገዛ ወሳኝ መሆኑ ይታመናል። በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባት እንዲሁም ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለመፍጠር ደግሞ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወቃል። በመሆኑም ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የድርሻችንን እገዛና ተሳትፎ ለማድረግ ተዘጋጅተናል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ የወጣት አደረጃጀት ኃላፊዎች ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ፉአድ ገና፤ ወጣቶች በሀገራዊ ምክክር ጉዳዮች ታዳሚ ብቻ ሳይሆኑ የአጀንዳው ባለቤት ሆነው መንቀሳቀስና ማገዝ ይጠበቅባቸዋል ብሏል። ሌላው የምክር ቤቱ አባል ኑር ሁሴን እና 'ዩዝ ካውንስሊንግ ሕብረት' የተሰኘው የወጣት አደረጃጀት ሊቀመንበር አብዲ መገርሳ፤ መሠረታዊ ችግሮችን በውይይት ለመፍታት የወጣቶች ተሳትፎና እገዛ ወሳኝ በመሆኑ ለዚሁ ስኬት መሥራት አለብን ነው ያለው። ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ውጤታማነት የድርሻችንን ለማበርከት ተዘጋጅተናል ሲሉ አረጋግጠዋል። የመላው አፍሪካ ወጣቶች ድርጅት ምክትል ፕሬዝዳንት ወጣት መስፍን ደሴ፤ በሀገራዊ ምክክር መድረኮች የወጣቶች እገዛ፣ ተሳትፎና ትብብር በተጠናከረ መልኩ መቀጠል አለበት ብሏል። የእንደራሴ ወጣቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት ብሩክ አስቻለው፤ ወጣቶች ለሀገራዊ ሰላምና አንድነት በትብብር የመሥራት ሀገራዊ ኃላፊነት አለባቸው ሲል ተናግሯል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እና የማኅበራዊ አንትሮፖሎጂ ምሁሩ ዶክተር ከይረዲን ተዘራ፤ የሀገራዊ ምክክር ዓላማ ትናንትን ማከምና ነገን ማስተካከል በመሆኑ፤ ለዚሁ መልካም ተግባር መሳካት በተለይም የወጣቶች ተሳትፎ የላቀ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። ሀገርን እየፈተኑ ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና ልማትን በማስቀጠል የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አተገባበር ገለልተኛና አካታችነትን መሠረት ያደረገ በመሆኑ በተለይም ወጣቶች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
የግጭት ምክንያቶችን ለይቶ በማውጣትና እልባት በመስጠት ሰላምን ማጽናት ይገባል-የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
Sep 21, 2023 155
ጋምቤላ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፡- የግጭት ምክንያቶችን ለይቶ በማውጣት እልባት በመስጠትና ሰላምን በማጽናት በኩል ሁሉም ዜጋ በአንድነትና በትብብር ሊሰራ እንደሚገባ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አሳሰበ። ኮሚሽኑ በአጀንዳ ልየታ ላይ የሚሳተፉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመምረጥ በጋምቤላ ከተማ ለሦስት ቀናት ያካሄደው መድረክ ዛሬ ተጠናቋል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፈን አርዓያ ባለመግባባት ምክንያት የሚከሰቱ ግጭቶችን ለማስቀረትና ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈን ህዝቦች ችግር ሲገጥም በመነጋገርና በመመካከር ሊፈቱ እንደሚገባ አስገንዘበዋል። በተለይም መሰረታዊ የግጭት መንሰኤ የሆኑ ምክንያቶችን ለይቶ በጋራ መፍታት ከተቻለ ሁሉም የሰላም አሸናፊ እንደሚሆን ኮሚሽነሩ አስረድተዋል። "የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የተቋቋመበት ዋና ዓላማ የግጭት መንስኤ የሆኑ ምክንያቶች ተለይተው እንዲፈቱ በማድረግ በህዝቦች መካከል መግባባትን መፍጠር ነው" ሲሉም ገልጸዋል። ይህንን ግብ ለማሳካት በሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች ከተባባሪ አካላት ጋር በመቀናጀት በአጀንዳ ልየታ መድረክ የሚሳተፉ የህብረተሰብ ተወካዮችን ኮሚሽኑ እያስመረጠ መሆኑን አስታውቀዋል። ኮሚሽኑ ከጋምቤላ ክልል ከሚገኙ 13 ወረዳዎችና ከጋምቤላ ከተማ መስተዳደር በአጀንዳ ልየታ ላይ የሚሳተፉ 504 ተወካዮችን ማስመረጡንም ፕሮፌሰር መስፍን ተናግረዋል። ከመድረኩ ታሳታፊዎች መካከል አቶ ዲድሙ አባላ በሰጡት አስተያየት እንደ ማህበረሰብ ተወካይነታቸው ኮሚሽኑ ለጀመረው ሀገራዊ ምክክር ስኬታማነት የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። "የሚያለያዩን ችግሮችን በማስወገድ፣ በመከባበርና በመደጋገፍ ሰላማችንን ልንጠበቅ ይገባል" ያሉት ደግሞ ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ሰይድ አሊ ናቸው። ኮሚሽኑ በጋምቤላ ክልል ለሦስት ተከታተይ ቀናት ሲያካሄድ በቆየው መድረክ ከጋምቤላ ከተማ እና ከ13ቱ ወረዳዎች በአጀንዳ ልየታ የሚሳተፉ 504 የማህበረሰብ ተወካዮችን በማስመረጥ ዛሬ ተጠናቋል።
ከ300 በላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ተደመሰሱ
Sep 21, 2023 97
አዲስ አበባ፤ መሰከረም 10/2016 (ኢዜአ):- ከ300 መቶ በላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ሲደመሰሱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አባላቱ መቁሰላቸውን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አስታወቀ። በሶማሊያ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ ሃይል ለመቀየር ተልዕኮ ወደ ሚፈፀምበት ቦታ በተንቀሳቀሰው የኢትዮጵያ ሠራዊት ላይ ጠላት ቀድሞ ባገኘው መረጃ መሠረት ደፈጣ ይዞ ሠራዊታችን ላይ ጥቃት ለመሠንዘር የሞከረው አልሸባብ ባላሠበው መልኩ ክፉኛ መመታቱ ተገልጿል። በተሳሳተ ስሌት የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ ቅይይር ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከረው የአልሸባብ ሃይል ከሶስት መቶ በላይ ታጣቂዎቹ ሲገደሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አባላቱም ቆስለዋል። የመከላከያ ሠራዊቱን ምት መቋቋም ያልቻለው አልሸባብ የሞቱ ታጣቂዎቹን አስክሬን እያንጠባጠበ ቁስለኞቹን በመያዝ ወደኋላ ለመፈርጠጥ ተገዷል ። የኢትዮጵያ ሠራዊት የአልሸባብን ደፈጣ እያሥወገደና በየመንገዱ የጠመዱትን ፈንጂና መሠናክሉን እያስወገደ ከተልዕኮው ቦታ ሁዱር መድረስ ችሏል። የአካባቢው ነዋሪዎችም ለመከላከያ ሠራዊታችን ምግብ እና ውሃ በማቅረብ ደስታቸውን እና ምስጋናቸውን ገልፀው፤ በሞራል ያላቸውን ድጋፍም አሳይተዋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ከሥፍራው ደረሰኝ ባለው መረጃ የአልሸባብ ሃይል ሶስት ፈንጂ የጫኑ መኪናዎችን እና 12 ፈንጂ የታጠቁ ታጣቂዎቹን እንዲሁም ከአንድ ሺህ በላይ አሉኝ የሚላቸዉን አባላቱን ለጥፋት በደፈጣ አሰልፏል፡፡ የጥፋት ሃሳቡን ሳያሳካ በሠራዊታችን ክንድ መደምሰሱን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል። አልሸባብ በተለያዩ የምስራቁ የሀገራችን ክፍል ተደጋጋሚ ትንኮሳዎችን የአጥፍቶ መጥፋት ተግባራትን ለመፈፀም ሲሞክር የቆየ ቢሆንም የአሁኑ በታሪኩ ከፍተኛ የሠው ሃይል ያሳተፈበት እና ደፈጣዎች ይዞ ባላሠበው መንገድ የተመታበት መሆኑም ተገልጿል።
የቀይ ባህር ቀጣና ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር በአካባቢው ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው - ሌተናል ጄነራል አለምሸት ደግፌ
Sep 21, 2023 303
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦የቀይ ባህር ቀጣና ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር በአካባቢው ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪና ተኩስ አመራር ኃላፊ ሌተናል ጄነራል አለምሸት ደግፌ ገለጹ። የቀይ ባህር ቀጣና ደኅንነትና ጂኦ-ፖለቲካል ሁኔታን በተመለከተ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትና በመከላከያ ዋር ኮሌጅ ትብብር የተዘጋጀ ውይይት ተካሂዷል። የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪና ተኩስ አመራር ኃላፊ ሌተናል ጄነራል አለምሸት ደግፌ፤ የቀይ ባህር ቀጣና ስትራቴጂካዊ የንግድና የፖለቲካ ማዕከል መሆኑን ገልጸዋል። ጂኦ-ፖለቲካ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታውም የጎላ በመሆኑ የበርካታ አገራትን ትኩረት ስለመሳቡ ተናግረዋል። በቀጣናው ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ሽብርተኝነትና መሰል ችግሮች የጸጥታ ሥጋቶች ሆነው መቀጠላቸውን ጠቅሰዋል። በመሆኑም የቀይ ባህር ቀጣና ሀገራት አካባቢውን ከጸጥታ ስጋት በማውጣት የልማት መዳረሻ ለማድረግ በትብብር መሥራት ይኖርባቸዋል ብለዋል። የአገራቱ የጋራ ትብብር ለቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የእስያና ፓስፊክ አገራት ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር ዶክተር ገበየሁ ጋንጋ፤ የቀይ ባህር ቀጣና አገራት በባህልና ኃይማኖት የተሳሰሩ መሆናቸውን አንስተዋል። የቀይ ባህር ቀጣና በዓለም ካሉት ከፍተኛ የንግድ መስመሮች አንዱ በመሆኑ የአካባቢውን ጸጥታና ደኅንነት በጋራ በመጠበቅ ለጋራ ልማት መጠቀም ይገባል ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሳፍንት ተፈራ፤ የቀይ ባህር ቀጣና በኢኮኖሚ፣ ወታደራዊና መሰል ዓለም አቀፍ ጉዳዮች የጸጥታ ሥጋቱ እየተወሳሰበ መጥቷል ብለዋል። በመሆኑም ለቀጣናዊ ችግሮች ቀጣናዊ መፍትሔ ለመስጠት የአካባቢው አገራት ሁለንተናዊ ትብብር ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል። በአሜሪካ የሰላም ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ አማካሪ ዶክተር ሉካ ኮል፤ አፍሪካ የውኃ ሀብቷን በአግባቡ ተጠቅማ ማልማት ካልቻለች በቀጣይ የከፋ ችግር ላይ ልትወድቅ ትችላለች ሲሉ ተናግረዋል፡፡ አፍሪካ 90 በመቶ የውጭና ገቢ ንግዷን የምታሳልጠው በቀይ ባህር በኩል ቢሆንም በውኃ ሀብት አጠቃቀሟ "የባህር ላይ አይነ ስውር" ሆናለች ነው ያሉት፡፡ በአፍሪካ የባህር ዳርቻ ያላቸው ሀገራት ከዓለም ሀገራት ጋር ሲነፃፀሩ ዝቅተኛ የውኃ ሀብት ተጠቃሚ መሆናቸውን ማሪታይም ደህንነት ኢንዴክስ መረጃን ዋቢ በማድረግ ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም አፍሪካውያን የቀይ ባህርን ጨምሮ የውኃ ሀብታቸውን በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲያውሉ አስገንዝበዋል።
በቀይ ባህር አካባቢ የሚስተዋሉ የጸጥታ ሥጋቶችን በማስወገድ የቀጣናውን ደኅንነት ለማረጋገጥ በጋራ መሥራት ይገባል - ሌተናል ጄኔራል አለምሸት ደግፌ
Sep 21, 2023 103
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦ በቀይ ባህር አካባቢ የሚስተዋሉ የጸጥታ ሥጋቶችን በማስወገድ የቀጣናውን ደኅንነት ለማረጋገጥ በጋራ መሥራት እንደሚገባ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪና ተኩስ አመራር ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል አለምሸት ደግፌ ገለጹ። የቀይ ባህር ቀጣና ደኅንነትና ጂኦ-ፖለቲካል ሁኔታን በተመለከተ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትና በኢፌዴሪ መከላከያ ዋር ኮሌጅ ትብብር የተዘጋጀ ውይይት እየተካሄደ ነው። የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ወታደራዊ አማካሪና ተኩስ አመራር ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል አለምሸት ደግፌ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ የቀይ ባህር ቀጣና ስትራቴጂካዊ የንግድና የፖለቲካ ማዕከል ነው። የቀይ ባህር ቀጣና ጂኦ-ፖለቲካ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጸው ይህም የበርካታ አገራትን ትኩረት መሳቡን ገልጸዋል። ያም ብቻ ሳይሆን ቀጣናው ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ሽብርተኝነትና መሰል የጸጥታ ሥጋቶችም የሚስተዋሉበት ነው ብለዋል። በመሆኑም አሁን ላይ የቀጣናው የደኅንነት ሥጋት ከፍ እያለ መምጣቱን ነው ያስረዱት። በመሆኑ እነዚህን ችግሮች ለመከላከል የቀጣናውን አገራት ትብብር ይፈልጋል ያሉት ሌተናል ጄኔራል አለምሸት የአገራቱ የጋራ ትብብር ለቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ልማት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የእስያና ፓስፊክ አገራት ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ዶክተር ገበየሁ ጋንጋ፤ የቀይ ባህር ቀጣና አገራት በባህልና ኃይማኖት የተሳሰሩ መሆናቸውን አንስተዋል። የቀይ ባህር ቀጣና በዓለም ካሉት ከፍተኛ የንግድ መስመሮች አንዱ በመሆኑ የአካባቢውን ጸጥታና ደኅንነት በጋራ በመጠበቅ ለጋራ ልማት ማዋል ይገባል ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር መሳፍንት ተፈራ፤ የቀይ ባህር ቀጣና በኢኮኖሚ፣ ወታደራዊና መሰል ዓለም አቀፍ ጉዳዮች የጸጥታ ሥጋቱ እየተወሳሰበ መጥቷል ብለዋል። በመሆኑም ለቀጣናዊ ችግሮች ቀጣናዊ መፍትሔ ለመስጠት የአካባቢው አገራት ሁለንተናዊ ትብብር ማድረግ እንዳለባቸው ነው ምክረ-ኃሳባቸውን የሰጡት።
ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ብልፅግና ስኬት ወጣቶች ግንባር ቀደም ሚና እንዲኖራቸው ጥሪ ቀረበ
Sep 21, 2023 92
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ብልፅግና ስኬት ወጣቶች ግንባር ቀደም ሚና እንዲኖራቸው የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ጥሪ አቀረበ። ዓለም አቀፉ የሰላም ቀን በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በተለያዩ መርሃ-ግብሮች እየተከበረ ነው። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የወጣት አደረጃጀቶችና የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል። የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ፉአድ ገና፤ የሰላም ጉዳይ መሠረታዊና ሁሉንም የሚመለከት የጋራ ጉዳያችን ነው ብሏል። በየትኛውም አጋጣሚ ሰላም ከሌለ ሁሉንም በመጉዳት ለሕይወት ማጣት፣ የአካል ጉዳትና የስነ-ልቦና ጫና የሚዳርግ በመሆኑ፤ ሰላምን አጥብቀን መሻትና ለዚያም መሥራት አለብን ነው ያለው። የዜጎችን የእርስ በርስ ግንኙነት ጥርጣሬ ላይ የሚጥል፣ የግጭትና ያለመግባባት መንስኤ የሚሆኑ ነገሮችን ማስወገድ የጋራ ኃላፊነታችን ሊሆን ይገባል ነው ያለው። በተለይም ወጣቶች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ብልፅግና ስኬት ግንባር ቀደም ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል። የሰላም ጉዳይ ከግለሰብ ስብዕና ጀምሮ እስከ ማኅበረሰብ ግንባታ የጋራ ጥረትን የሚጠይቅ መሆኑንም አብራርቷል። በማይገባ ነገር ላይ እርስ በርስ መፈራረጅ፣ የጦርነት ቅስቀሳ፣ ዘረኝነትና ዋልታ ረገጥ እሳቤ ሁሉንም የሚጎዳ የጋራ ችግር መሆኑንም አንስቷል። በመሆኑም በኢትዮጵያ እነዚህና ሌሎችም ለሰላም ማጣት ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በመለየት ዘላቂ መፍትሔ ለመሻት የሚያግዝ የወጣቶች ፎረም የሚካሄድ መሆኑን ጠቅሷል። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ዶክተር ቶውፊቅ አብዱላሂ፤ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ግንባታ ወጣቶች ትልቅ ኃላፊነት ወስደው መሥራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። የዓለም የሰላም ቀን እ.ኤ.አ በ1981 በዓለም አቀፍ ደረጃ መከበር የጀመረ ሲሆን፤ የዘንድሮው "የወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም እና ለዓለም አቀፍ ግቦች" በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበር ይሆናል።
ማህበራዊ
በባሌ ዞን በክረምቱ የተገነቡ 46 ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ለመማር ማስተማር ዝግጁ ሆነዋል
Sep 22, 2023 38
ሮቤ፤ መስከረም11 /2016 (ኢዜአ):- በባሌ ዞን በክረምቱ ወራት የተገነቡ 'ቡኡራ ቦሩ' የተሰኙ 46 ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ለዘንድሮ የትምህርት ዘመን ዝግጁ መሆናቸውን የዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት ገለጸ። በዞኑ ካለፈው በጀት ዓመት መገባደጃ አንስተው በክረምቱ የተከናወኑት የትምህርት ቤቶች ደረጃ የማሻሻል ሥራም የተማሪዎች የቅበላ አቅም ከማሻሻሉም በላይ ምቹ የመማር ማስተማር ሂደት እንደሚፈጥሩ ተገልጿል። የዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ጸጋ አለማየሁ እንደገለጹት በዞኑ ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የትምህርት ቤቶች ደረጃ ማሻሻል ስራ እና የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ጎን ለጎን ሲከናወኑ ቆይተዋል። በዚህም በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች ባለፈው ዓመት ክረምቱን ጨምሮ በህዝብ ተሳትፎና በመንግስት በጀት 46 'ቡኡራ ቦሩ' የተሰኙ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ተከናውኗል ነው ያሉት። ትምህርት ቤቶቹም በተያዘው የትምህርት ዘመን ህጻናትን ተቀብለው ለማስተማር ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። በተመሳሳይ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻሉ ተግባር በስፋት መከናወኑን ገልጸው፤ በዚህም 120 አዳዲስ የመማሪያ ክፍሎች ግንባታና ጥገና እንዲሁም 97 የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም 1 ሺህ የሚጠጉ የተማሪዎች መቀመጫ ወንበሮችና 20 ኮምፒዩተሮችን በመጠገን ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረግ መቻሉን አክለዋል። አቶ ጸጋ እንዳሉት፣ የትምህርት ቤቶች ግንባታና ደረጃ ማሻሻል ስራው በአዲሱ የትምህርት ዘመን ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ 50 ሺ ህጻናትን የመቀበል አቅም ፈጥሯል። የትምህርት ቤቶች ደረጃ ማሻሻል ስራው ምቹ የመማር ማስተማር ሂደትን ከማሳለጥ በተጓዳኝ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትልቅ እገዛ እንዳለውም አመልክተዋል። ለትምህርት ዘመኑ የሚያስፈልጉ የትምህርት ግብዓቶችን ከማሟላት አንጻርም በህብረተሰብ ተሳትፎ በርካታ ስራዎች መከናወኑን ጠቁመዋል። በዞኑ በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የተከናወኑት የትምህርት ቤቶች ማሻሻልና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች 560 ሚሊዮን ብር በሚገመት የህዝብ ተሳትፎና የመንግስት በጀት መከናወናቸውንም ገልጸዋል። በዞኑ ጎባ ወረዳ ነዎሪዎች መካከል አቶ ሀሰን አብደላ በሰጡት አስተያየት፣ በአካባቢያቸው የተገነቡ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ህጻናት ከአካባቢያቸው ሳይርቁ መሰረታዊ ትምህርት በጊዜ እንዲቀስሙ ዕድል ይፈጥራል። የትምህርት ቤት መሰረተ ልማት በህብረተሰብ ተሳትፎ ለማመቻቸት የተቋቋመው ኮሚቴ አባል ሆነው ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቁመው፤ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተጎዱ የመማሪያ ክፍሎች መጠገናቸውንም አውስተዋል። በባሌ ዞን በ2016 የትምህርት ዘመን እስከ አሁን ከ290 ሺህ 900 የሚበልጡ ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 134 ሺህ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ከዞኑ ትምህርት ጽህፈት ቤት የተገኛው መረጃ ያመለክታል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች አምስት አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን እንደሚያስገነባ አስታወቀ
Sep 22, 2023 72
አዲስ አበባ፤ መስከረም 11/2016(ኢዜአ)፦የቱሪዝም ሚኒስቴር በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች አምስት አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን እንደሚያስገነባ አስታወቀ፡፡ የሚኒስቴሩ የህዝብ ግኑኙነት ዳይሬክተር ዶክተር ዓለማየሁ ጌታቸው ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ ያላትን የቱሪዝም አቅም በሚፈለገው ደረጃ ጥቅም ላይ ማዋል ሳትችል ቆይታለች፡፡ በመሆኑም አሁን ላይ መንግስት አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን በማስተዋወቅ ከዘርፋ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። በዚህም የአገር ውስጥ እና የውጭ አገር ጎብኝዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል። የቱሪዝም ፍሰቱን ይብልጥ ለማሻሻልም የነባር የቱሪዝም ስፍራዎችን ማደስና አዳዲስ የማልማቱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው የገለጹት፡፡ ከዚህ አኳያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተያዘው በጀት ዓመት በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ህዝብን በማስተባበርና የፋይናንስ ምንጮችን በማፈላለግ አምስት አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን የማልማት ስራ እንደሚጀምር ጠቁመዋል፡፡ የሚለሙት የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎች በቀጣይ ይፋ እንደሚደረጉም ነው የተናገሩት፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ "በገበታ ለሀገር" እና "በገበታ ለትውልድ" አማካኝነት እያከናወኗቸው ያሉ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን የማልማት ስራ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ ከዘርፉ የምታገኘውን ገቢ በእጅጉ እንደሚያሻሻልም ተናግረዋል፡፡
ቢሮው ከበጎ ፈቃደኞች ያሰባሰበውን የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ልጆች እያከፋፈለ መሆኑን ገለጸ
Sep 22, 2023 45
አዳማ፤ኢዜአ መስከረም 11/2016፡- የኦሮሚያ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ከበጎ ፈቃደኞች ያሰባሰበውን የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ልጆች እያከፋፈለ መሆኑን ገለጸ። የኦሮሚያ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወይዘሮ ሰሚራ ፋሪስ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናትና በትምህርት ላይ የሚገኙ ተማሪዎች በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ እንዳይሆኑ ሲሰራ ቆይቷል። ''አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ'' በሚል መሪ ቃል በክረምቱ ከክልሉ የዘርፍ መስሪያ ቤቶች ጀምሮ እስከ ወረዳ፣ ከተሞችና ዞኖች ድረስ የዘላቂ ንቅናቄ በማካሄድ ውጤታማ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። የክልሉ የወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀት፣ ባለሃብቶችና የክልሉን ነዋሪ በማስተባበር ደብተር፣ እስክሪፕቶ እና ቦርሳዎች፣ አልባሳትና ጫማዎች መሰብሰብ መቻሉን አንስተዋል። ከተለያዩ አካላት ተሰባስቦ እየተከፋፈለ ያለው የትምህርት ቁሳቁስ ከ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ የዋጋ ግምት ያለው ነው ብለዋል። የተሰበሰበው የትምህርት ቁሳቁስም ከ2 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የአቅመ ደካማ ወላጆች ተማሪዎች እየተከፋፈለ መሆኑን አብራተዋል። በተጨማሪም ህፃናት በምግብ ችግር ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ የዘንድሮውን የተማሪዎች ምገባ ለማሳካት ቢሮው ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የማስተባበር ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በአዳማ ከተማ የገዳ ሮበሌ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ምንዳ ረገሳ በበኩላቸው በትምህርት ቤቱ ለሚማሩ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰብ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል ብለዋል። በተለይ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናትና በመማር ላይ የሚገኙ ልጆች ደብተር፣ ቦርሳና እስክሪፕቶን ጨምሮ የተለያዩ የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማግኘታቸውን ገልጸዋል። ከትምህርት ቤቱ የቀድሞ ተማሪዎችና ከበጎ አድራጊ ወጣቶች ጭምር በርካታ የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ለትምህርት ቤቱ ተማሪዎች ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ኮሌጆች ከረዥም ጊዜ ስልጠና ይልቅ አጫጭር የሙያና የንግድ ሐሳብ ስልጠና ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑ ተገለጸ
Sep 22, 2023 77
አዳማ ፤(ኢዜአ) መስከረም 11/2016:-በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ኮሌጆች ከረዥም ጊዜ ስልጠና ይልቅ አጫጭር የሙያና የንግድ ሐሳብ ስልጠና ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን የክልሉ የስራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ገለፀ ። ቢሮው በየኮሌጆች እየተከናወኑ ያሉ የፈጠራና የክህሎት ስራዎችን መሰረት ያደረገ ከ6ሺህ 800 በላይ የኢንተርፕረነርሺፕ አሰልጣኞችን ማብቃቱን ገልጿል። የቢሮው አመራሮች ከኢንተርፕረነርሺፕ አሰልጣኞችና ከዘርፉ ባለሙያዎች ጋር በመሆን በቢሾፍቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተመረቱ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች እንዲሁም ጨርቃ ጨርቅ ምርቶችን ጎብኝተዋል። የኦሮሚያ የስራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ሀብታሙ ካሣ እንደገለፁት በዘንድሮው ዓመት ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ሴቶች የሙያና ኢንተርፕረነርሺፕ ስልጠናና ክህሎት ለመስጠት ወደ ተግባር ተገብቷል። ቢሮው ከግብርና፣ ንግድና ገበያ ልማት፣ ከኮሌጆችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በክልሉ ያሉ የስራ አማራጮችና አቅሞች ላይ ጥናት ማድረጉንም ገልጿል። በዚህም ሰፊ የስራ ዕድሎችና አማራጮች ቢኖሩም ከጠባቂነት አስተሳሰብ ጀምሮ ማነቆ ሆኖ የቆየውን የወጣቶችም ሆነ የህብረተሰቡ የስራ ባህል መለወጥ እንደሚገባ ጥናቱ ማመላከቱን ተናግረዋል። ችግሮቹን ለመቅረፍ ኮሌጆች ከረዥም ስልጠና ይልቅ አጫጭር የሙያና የንግድ ሐሳብ ስልጠና ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ የሚረዱ የስልጠና ስልቶችን ማዘጋጀቱን ነው የገለጹት። ስራ አመራር፣ አማራጭ የገቢ ምንጭ፣ ማህበራዊ ኢንተርፕረነርሺፕና የተቀናጀ የኮሌጆች ኢንተርፕረነርሺፕ ደግሞ የስልጠና ስልቶቹ የተዘጋጁባቸው ዘርፎች መሆናቸውን ምክትል ሃላፊው ገልጸዋል። በዚህም ወጣቶች፣ ሴቶችና አርሶ አደሮችን ጨምሮ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች በዚህ ዓመት የኢንተርፕረነርሺፕ ክህሎትና የሙያ ስልጠና የሚያገኙ ይሆናል ብለዋል። አክለውም በዘንድሮው ዓመት ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በሙያና ንግድ ልማት የተደገፈ የስራ ዕድል ይፈጠራል ብለዋል። ለእነዚህ የስራ እድሉ ተጠቃሚዎች ደግሞ የብድር፣ የመስሪያና መሸጫ ማዕከላት፣ የእርሻ መሬቶች፣ ግንባታና ማዕድን ልማት እንዲሁም የማሽን ሊዝ ጭምር ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። የቢሾፍቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ደበላ ተስፋ እንደገለፁት ኮሌጁ የሙያና የክህሎት ስልጠና ለመስጠት 16 የሙያ አይነቶችን ለይተን ወደ ተግባር ገብተናል ብለዋል። በተለይም ቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ ጨርቃ ጨርቅ፣ ማኑፋክቸሪንግ ወዘተ ዘርፎች ላይ አጭርና ረዥም ስልጠና በመስጠት ኮሌጁ የስራ ዕድል ፈጠራ አማራጮች ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል። በዚህም መስከረም 26 እና 27 ቀን 2016 ዓ.ም በሚከበረው የኢሬቻ በዓል ላይ ከ1ሺህ በላይ በኮሌጁ የተመረቱ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች እንዲሁም ጨርቃ ጨርቅ ምርቶችን ለገበያ ለማቅረብ ዝግጅት አጠናቀናል ነው ያሉት። በዚህም በክህሎትና ሙያ የዳበረና ገበያ መር ሰራተኛ ዜጎችን ከመፍጠር ባለፈ ኮሌጁ 28 ሚሊዮን ብር የውስጥ ገቢ ለማግኘት አቅዶ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። በክልሉ የሚገኙ ከ200 በላይ ኮሌጆችን በ22 ክላስተር በማደራጀት ተቋማቱ የገንዘብና የሙያ ምንጭ እንዲሆኑ የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንሼቲቭ ተቀርጾ ወደ ተግባር መገባቱንም የቢሮው መረጃ ያስረዳል።
ኢኮኖሚ
የአልጄሪያ አየር መንገድ ከአልጀርስ ወደ አዲስ አበባ የመጀመሪያውን የቀጥታ በረራ አደረገ
Sep 22, 2023 48
አዲስ አበባ፤ መስከረም 11/2016(ኢዜአ)፦የአልጄሪያ አየር መንገድ ከአልጀርስ ወደ አዲስ አበባ የመጀመሪያውን የቀጥታ በረራ ዛሬ አድርጓል። በዚሁ በረራ በአልጄሪያ የትራንስፖርት ሚኒስትር ዮሴፍ ቻሮፍ የተመራ የአልጄሪያ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሃላፊዎች ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ ገብቷል:: የልዑካን ቡድኑ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል አምባሳደር ፍሰሃ ሻውል፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው፣ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር ሞሃመድ ላምኔ ላባስን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውለታል:: ኢትዮጵያና አልጄሪያ እ.አ.አ በ1985 የአየር በረራ አገልግሎት ስምምነት የተፈራረሙ ቢሆንም ለበርካታ ዓመታት ተግባራዊ ሳይሆን ቆይቷል። በዚሁ መሰረት በሁለቱ ሀገራት መካከል የቀጥታ በረራ እንዲኖር ለማስቻል ከዚህ ቀደም የተፈረመው ስምምነት አሁናዊ ሁኔታን ባገናዘበ መልኩ ታድሶ ወደ ስራ እንዲገባ በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል። በኢትዮጵያና አልጄሪያ መካከል የትራንስፖርትና አቪዬሽን ዘርፉን ትስስር ለማጠናከር በቅርቡ በሁለቱ ሀገራት መካከል መግባባት ላይ መደረሱ ይታወሳል፡፡ ዛሬ የተጀመረው በረራ ስምምነቱን ወደ ተግባር ለመቀየሩ አንዱ ማሳያ መሆኑም ተመላክቷል:: የኢትዮጵያና የአልጄሪያ የሁለትዮሽ ግንኙነት የተመሠረተው እ.አ.አ በ1960 ዎቹ ሲሆን አልጄሪያ ኤምባሲዋን እ.አ.አ በ1976 በአዲስ አበባ ከፍታለች ::
በአማራ ክልል በቢራ ገብስ ከለማው መሬት ከ282ሺህ 400 ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል
Sep 22, 2023 40
ባህር ዳር፤ መስከረም 11 ቀን 2016(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በመኸሩ ወቅት በቢራ ገብስ ከለማው መሬት ከ282 ሺህ 400 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ አግደው ሞላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በመኽር ወቅቱ በክልሉ እየለማ ካለው የሰብል ዓይነት ውስጥ የቢራ ገብስ አንዱ ነው። በወቅቱ በ12 ሺህ 270 ሄክታር መሬት ላይ የቢራ ገብስ መልማቱን አመልክተው ከዚህም የሚጠበቀው ምርት ከ282 ሺህ 400 ኩንታል በላይ መሆኑን አስታውቀዋል። ክልሉ በቢራ ገብስ የመልማት ሰፊ አቅም እንዳለው ጠቅሰው፤ የአርሶ አደሩ በቢራ ገብስ የማልማት ፍላጎቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል። ልማቱን ውጤታማ ለማድረግም የግብርና ባለሙያዎች ለአርሶ አደሩ ክትትልና ድጋፍ እየተደረጉ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በደቡብ ጎንደር ዞን ፋርጣ ወረዳ ሳርና ቀበሌ አርሶ አደር የማታ ቢሰጥ በሰጡት አስተያየት፤ በመኸሩ ወቅት ሩብ ሄክታር መሬት ላይ ቢራ ገብስ አልምተው እየተንከባከቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። አንድ ኩንታል ቢራ ገብስ በ6 ሺህ 500 ብር ለማስረከብ ደብረታቦር ከተማ ከሚገኘው መገናኛ ዩኒየን ጋር የውል ስምምነት ይዘው እየሰሩ እንደሆነ ጠቁመዋል። በዘር ከሸፈኑት መሬት እስከ አስር ኩንታል ምርት ለማግኘት ማቀዳቸውን ጠቅሰው፤ አሁን ላይ ሰብሉ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ግማሽ ሄክታር መሬት በቢራ ገብስ እያለሙ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ በዚሁ ወረዳ የማይናት ቀበሌ አርሶ አደር ያለለት ሞላ ናቸው። አሁን ላይ ሰብሉን ከአረምና ፀረ ሰብል ተባይ እየጠበቁ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። የመገናኛ ዩኒየን ስራ አስኪያጅ አቶ ተስፋየ አየነው በበኩላቸው፤ ዩኒየኑ በደቡብ ጎንደር ዞን ፋርጣና ጉና ወረዳዎች ቢራ ገብስ የሚያለሙ አርሶ አደሮች ጋር ቀድሞ ውል በመያዝ ወደ ስራ መግባቱን ገልጸዋል። አንድ ኩንታል የቢራ ገብስ በ6 ሺህ 500 ብር ለመረከብ ውል መያዛቸውንና አርሶ አደሮች የምርታቸውን ጥራት ጠብቀው ማዘጋጀት እንደሚጠበቅባቸው አመልክተዋል። በአማራ ክልል ባለፈው ዓመት ከለማው መሬት 303 ሺህ ኩንታል የቢራ ገብስ በማምረት ለጎንደር ብቅል ፋብሪካ ማቅረብ እንደተቻለ ተመላክቷል።
በተያዘው ዓመት በክልሉ በ30ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የሻይ ቅጠል ችግኝ ይተከላል- ቢሮው
Sep 22, 2023 114
መቱ መስከረም 11/2016 (ኢዜአ):-በተያዘው ዓመት በክልሉ በ30ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ወደ 400 ሚሊዮን የሚጠጋ የሻይ ቅጠል ችግኝ ለመትከል ዕቅድ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱን የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው በምዕራቡ የክልሉ አካባቢ ከሚገኙ ስድስት ዞኖች ለተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች በሻይ ልማት ዙሪያ በተግባር የተደገፈ ስልጠና ሰጥቷል። በሻይ ተክል አዘገጃጀት ላይ ያተኮረ በተግባር የተደገፈ ስልጠና የተሰጠውም ከኢሉ ባቦር፣ ቡኖ በደሌ፣ ጂማ፣ ምዕራብ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋና ምስራቅ ወለጋ ለተውጣጡ ባለሙያዎች መሆኑን በኦሮሚያ ግብርና ቢሮ የቡናና ሻይ ልማት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ አቦሴ ተናግረዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በክልሉ መንግስት ለመስኩ እየተሰጠ ባለው ትኩረት የሻይ ተክል ልማትን በእነዚሁ ዞኖች በማላመድ ረገድ መልካም ጅማሮዎች እየተመዘገቡ መሆናቸውንም አንስተዋል። በ2016 በጀት ዓመትም በክልሉ በ30 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ወደ 400 ሚሊዮን የሚደርስ ችግኝ እንደሚተከል ነው ያነሱት። ዕቅዱን ለማሳካትም ቀድመው መከናወን ከሚገባቸው ስራዎች አካል የሆነው የባለሙያዎችን ብቃትና ግንዛቤ የማሳደግ ተግባር ተኮር ስልጠና ስራው በስፋት እየተከናወነበት መሆኑን ገልጸዋል። ተግባር ተኮር ስልጠናውም በኢሉባቦር ዞን በተዘጋጁ የሻይ ችግኝ ጣቢያዎች ላይ መሆኑንም ገልፀዋል። የኢሉባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አስጨናቂ አድማሱ ዞኑ በሻይ ልማትና በችግኝ አዘገጃጀት ላይ ያለውን ልምድና ተሞክሮ ለሌሎች አጎራባች ዞኖች በማጋራት ለመስኩ ስኬታማነት የድርሻውን እንደሚወጣ አንስተዋል። በዞኑ ባለፉት ዓመታት በሻይ ልማት ዙሪያ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንና በተያዘው ዓመትም ወደ 200 ሚሊዮን የሚጠጉ የሻይ ተክል ችግኝ መዘጋጀቱን ገልፀዋል። ከተለያዩ ዞኖች መጥተው በስልጠናው ላይ የተካፈሉት ባለሙያዎችም ስልጠናው በሻይ ልማት ዙሪያ የነበራቸውን ክህሎት የሚያሳድግና ክፍተቶቻቸውን የሚሞላ መሆኑን አንስተዋል። ከጅማ ዞን የመጡት አቶ መሐመድፋቱ አባጎጃም ስልጠናው በዞናቸው የተያዘውን የሻይ ቅጠል ልማት ዕቅድ በስኬት እንዲያከናውኑ የሚረዳቸውን ግንዛቤ ያገኙበት መሆኑን ገልፀዋል። የችግኝ አዘገጃጀት፣ አተካከልና የእንክብካቤ ተግባሩ ውጤታማ በሆነ መልኩ የሚከናወንበትን ልምድና ክህሎት እንዳዳበሩ አክለዋል። ከቡኖ በደሌ የመጡት አቶ ደረጀ ረፌራም ስልጠናው ከዞናቸው ለመጡ ባለሙያዎች ስራውን በተያዘው ዕቅድ አፈፃፀምና አተገባበር ዙሪያ ውጤታማ ሊሆኑ የሚችሉበትን ግንዛቤ የጨበጡበት መሆኑን ጠቅሰዋል። በዞናቸው 68 ሚሊዮን የሻይ ተክል ችግኝ ለማዘጋጀት ዕቅድ መያዙን የጠቀሱት አቶ ደረጀ ከስምንት ወረዳዎች መጥተው በስለጠናው የተሳተፉት ባለሙያዎች ትልቅ የአቅም ግንባታ ያገኙበት መሆኑንም አክለዋል። የሻይ ልማት ግብርና በክልሉ መንግስት አቅጣጫ ተይዞባቸው ወደ ተግባር የተገባባቸው የግብርና ኢንሼቲቮች መካከል አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
የኢትዮ-ካናዳ የቢዝነስና ኢንቨስትመንት ፎረም በካናዳ ተካሄደ
Sep 22, 2023 68
አዲስ አበባ፤ መስከረም 11/2016(ኢዜአ)፦ የኢትዮ-ካናዳ የቢዝነስና ኢንቨስትመንት ፎረም በካናዳ ቶሮንቶ ተካሄዷል። በፎረሙ በርካታ የሁለቱም አገራት ባለሀብቶች የተሳተፉ ሲሆን በጋራ መስራት በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ መምከራቸውን ኢዜአ ካናዳ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የሁለትዮሽ ትብብርና የልምድ ልውውጥ በማድረግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጿል። የኢትዮጵያ ባለሀብቶች በካናዳ የንግድ ገበያ እድሎችንና አጋርነቶች እንዲያገኙ በር የሚከፍት ነው ተብሏል። የካናዳ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በግብርና፣ማኑፋክቸሪንግ እና ማዕድን ዘርፎች መዋለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ፎረሙ እድል ይፈጥራል ነው ያለው ኤምባሲው በመረጃው። በፎረሙ ከተገኙ የሁለቱ አገራት የንግድ ተቋማት መሪዎች ውስጥ የተወሰኑት በቀጣይ ይበልጥ ስለሚተዋወቁበት ሁኔታ ተከታታይ ውይይትና የመረጃ ልውውጥ ለማድረግ መስማማታቸው ተጠቁሟል። ፎረሙ በስኬት ተጠናቋል ያለው ኤምባሲው ሁነቱ የተሳካ እንዲሆን ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርቧል። እ.አ.አ በ2021 የኢትጵያና ካናዳ የንግድ ልውውጥ መጠን እ.አ.አ 164 ሚሊዮን ዶላር እንደነበር ተጠቅሷል። ከዚህ ውስጥ 112 ሚሊዮን ዶላሩ ካናዳ ወደ ኢትዮጵያ ከላከችው ምርቶች ያገኘችው ሲሆን 52 ሚሊዮን ዶላሩ ደግሞ ኢትዮጵያ ወደ ካናዳ ከላከችው ምርቶች የተገኘ ገቢ መሆኑ ተመላክቷል። የኢትዮጵያና ካናዳ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እ.አ.አ በ1965 እንደተጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አውደ-ርዕዩ በዘርፉ ያካበተ ልምድ ካላቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር ለመሥራት እድል ፈጥሯል - የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር
Sep 22, 2023 103
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 11/2016 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ለአንድ ወር የተካሄደው የውኃና ኢነርጂ አውደ-ርዕይ በዘርፉ ያካበተ ልምድ ካላቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር ለመሥራት እድል መፍጠሩን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለጸ። የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር "የውኃ ኃብታችን ለብልጽግናችን" በሚል መሪ ኃሳብ በሳይንስ ሙዚየም ለአንድ ወር ያካሄደው አውደ ርዕይ ትላንት ተጠናቋል። አውደ ርዕዩ ምን አስገኘ? የሚለውን ለማወቅ ኢዜአ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና በአውደ-ርዕዩ አገልግሎታቸውን ያቀረቡ ተቋማትን አነጋግሯል። በሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ጌትነት ጌጡ፤ በአውደ-ርዕዩ ዘርፉን ለማዘመን በትግበራ ላይ ያሉ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለዕይታ ቀርበዋል ብለዋል። ለአብነትም ኢትዮጵያ የውኃ መጠኗን በዲጂታል መተግበሪያ በመታገዝ እንዴት እንደምትከታተልና እንደምትቆጣጠር ማሳየት መቻሏን ጠቁመዋል። አውደ-ርዕዩን የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጨምሮ የዘርፉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች እንዲሁም አምባሳደሮች መጎብኘታቸውን ነው ያረጋገጡት። በመሆኑም አውደ-ርዕዩ አገሪቱ በዘርፉ የምታከናውነውን ሥራ ለማስገንዘብ እድል ሰጥቷል ነው ያሉት። ከዚህ በተጠማሪም አውደ-ርዕዩ በዘርፉ ከተለያዩ ተቋማት ጋር አዳዲስ አጋርነትና ትብብር ለመመሥረት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ገልጸዋል። በመድረኩ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ያቀረቡ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት በበኩላቸው አውደ-ርዕዩ የውኃና ኢነርጂ ዘርፍን በቴክኖሎጂ ለማዘመን የሠሯቸውን ሥራዎች ለሕዝብ ለማቅረብ እድል ሰጥቶናል ብለዋል። በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በመረጃና ክላይማቶሎጂ ክፍል ተመራማሪ የሆኑት ለታ በቀለ ተቋማቸው በአውደ-ርዕዩ በአገሪቱ ያለውን የአየር ፀባይ ሁኔታ ጥናት ለማካሄድ የሚጠቀምባቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶች ማቅረባቸውን ጠቅሰዋል። የተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አውደ-ርዕዩን መጎብኘታቸው ገልጸው ይህም በቀጣይ በሚቲዎሮሎጂ ዘርፍ አብረው መሥራት የሚችሉባቸውን ሁኔታዎች ለመለየት ዕድል መፍጠሩን ነው የገለጹት። የአነጋ ኢነርጃይዝ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የሽያጭ ባለሙያ እየሩሳሌም ደጀኔ በበኩሏ በአውደ-ርዕዩ ኅብረተሰቡ የሚጠቀምባቸውን ኃይል ቆጣቢ ምድጃዎች ማቅረባቸውን ተናግራለች። በዝግጅቱ ላይ መሳተፋቸው ኃይል ቆጣቢ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በቀላሉ ለማስተዋወቅ እንደረዳቸው በመግለፅ እንደ አገር መሰል አውደ-ርዕዮች በተለያዩ አካባቢዎች ሊስፋፉ እንደሚገባ ተናግራለች። በሐፍ አስመጪና አቅራቢ ድርጅት የኦፕሬሽን ማናጀር ሃበን ገብሩ በአውደ-ርዕዩ ምንም አይነት ኤሌክትሪክ ኃይልና የውኃ ማጣሪያ ኬሚካል ሳይጠቀም ውኃን ማጣራት የሚችል ቴክኖሎጂ ለኅብረተሰቡ በስፋት አሳይተናል ብለዋል።
የውሃ ሃብትን በአግባቡ ለመጠቀም በቴክኖሎጂ የታገዘ የመረጃ ማደራጀት ሥራ እየተከናወነ ነው- ዶክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ
Sep 21, 2023 70
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የውሃ ሃብት በአግባቡ ለመጠቀም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ የመረጃ ማደራጀት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ገለጹ። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ሃብታሙ፤ የውሃ ሃብት አጠቃቀምና በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን በማስመልከት ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም የኢትዮጵያን የውሃ ሃብት በአግባቡ ለመጠቀም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ የመረጃ ማደራጀት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል። የመረጃ ቴክኖሎጂው አጠቃላይ የውሃ ሃብትን ለማስተዳደር፣ የሃብቱን መገኛ አካባቢዎች በመለየት ለማልማትና የአጠቃቀም ስልቶችን የሚያመላክት መሆኑን ጠቁመዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያን የውሃ ሃብት በተደራጀና ዘመናዊ የመረጃ ሥርዓት በመሰነድ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ይቻላል ብለዋል። የውሃ ሃብት መረጃን በዘመናዊ የመረጃ ቋት በማስቀመጥ ከአካባቢው አገራት ጋር የጋራ ተጠቃሚነትን ለማጠናከርና የውሃ ዲፕሎማሲ (ሃይድሮ ዲፕሎማሲን) ለመገንባት ጠቃሚ መሆኑንም ሚኒስትሩ አብራርተዋል። የኢትዮጵያን የውሃ ሃብት በምርምር የተደገፈና በተጨባጭ መረጃ የተደራጀ በማድረግ ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። የውሃ ሃብትን በዘለቄታ በመጠቀም ሁለንተናዊ ልማትና የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልፀዋል። የውሃ ሃብትን በእውቀትና ምርምር ታግዞ ጥቅም ላይ ለማዋል የተቀናጀ ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ የሁሉም ጥረት እንዲታከልበት ጠይቀዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ከማይክሮሶፍት ኩባንያ የስራ ሃላፊዎች ጋር ተወያዩ
Sep 21, 2023 81
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶክተር በለጠ ሞላ በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው 78ኛው የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ ጎን ለጎን ከማይክሮሶፍት ኩባንያ የስራ ሃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ ማይክሮሶፍትና ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ በትብብር መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስለሚገኘው የቴክኖሎጂ መስፋፋት፣ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እንዲሁም ወጣቶችን በዲጂታል እውቀት ለማበልጸግ እየተደረገ ስለሚገኘው ጥረት ለሃላፊዎቹ ገለጻ አድርገዋል። ኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለማሳደግ እየሰራች ስለምትገኘው ስራ ያብራሩ ሲሆን ይህም ከኩባንያው ጋር በትብብር የሚሰራበት አንዱ ዘርፍ እንዲሚሆን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የዲጂታል መሰረተ-ልማትን ለማስፋት በተለይ በክላውድ አገልግሎት፣ ዳታ ማእከልና ሌሎች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ውጤቶች ከማይክሮሶፍት ጋር መስራት እንደምትፈልግም ገልጸዋል። በቴክኖሎጂ የስራ ፈጠራ ላይ ጀማሪዎችን ለማበረታታት ኩባንያው በገንዘብ፣ በስልጠናና አስፈላጊ ግብአቶችን በማቅረብ ኢትዮጵያን ሊያግዝ ስለሚችልባቸው ጉዳዮች ገለጻ አድርገዋል። የማይክሮሶፍት ኩባንያ የስራ ሃላፊዎች በበኩላቸው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ለጤና፣ ለግብርና እንዲሁም ሌሎች ዘርፎች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመን በሚደረገው ጥረት ድጋፍ ለማድረግ ፍላጎት እንዳለው ገልጸዋል። በተጨማሪም በአፍሪካ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ፕሮግራሙን ለማስፋፋት ኢትዮጵያን እንደ አማራጭ ለመጠቀም ፍላጎት እንዳለውም ሃላፊዎቹ ገልጸዋል።
ሀገራት በሳይበር ደህንነት ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ እንዲሠሩ የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር ጥሪ አቀረቡ
Sep 19, 2023 129
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 8/2016 (ኢዜአ)፦ ሀገራት በሳይበር ደህንነት ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ እንዲሠሩ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ ጥሪ አቀረቡ። አቶ ሰለሞን ሶካ "የመንግስታት፣ የሲቪል ማህበራት እና የንግድ ማህበረሰቦች ትብብር ዓለም አቀፍ የመረጃ ደህንነትን ለማረጋገጥ" በሚል መሪ ሀሳብ ከመስከረም 7-9 /2016 በሩሲያ እየተካሄደ በሚገኘው 17ኛው ዓለም አቀፍ ፎረም ላይ የቪዲዮ መልእክት አስተላልፈዋል። ዋና ዳይሬክተሩ በመልዕክታቸው በተለይም የሳይበር ቴክኖሎጂው በየጊዜው መራቀቅ የሰውን የአኗኗር ዘይቤ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ አስተሳሰቦችን ጭምር እየቀየራቸው እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡ የቴክኖሎጂው እያደገ መምጣት ለኢኮኖሚው፣ ለፖለቲካው፣ ለባህሉና ለማህበራዊ መስተጋብሩ አወንታዊ ተጽእኖ እንዳለው ሁሉ አሉታዊ ጎንም እንደሚኖረው አቶ ሰለሞን መጥቀሳቸውን አስተዳደሩ አስታውቋል፡፡ አቶ ሰለሞን አያይዘውም አሁን ላይ ሁሉም ሐገራት ተግባራቸውን ለማከናወንና ከሌላው ዓለም ለመገናኘት የዲጂታል ቴክኖሎጂን መጠቀም ግድ እያላቸው ከመምጣቱም በላይ አንድ ሐገር ደሴት ሆኖ ተገልሎ መኖር እንደማይችል ሁሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂው ያመጣቸውን መልካም አጋጣሚዎች እና የሚያስከትለውን የደህንነት ስጋት በጋራ መምከር አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡ ድንበር የለሽ እና ወስብስብ ተፈጥሮ ያለውን የሳይበር ደህንነት ጉዳይ ሐገራት በተናጠል በሚያደርጉት ጥረት ማረጋገጥ እንደማይችሉና ዓለም አቀፋዊ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ ገልጸው፤ ይኸውም ትብብር፤ እውቀታችንን፣ ልምዳችንን እና ሪሶርሳችንን በማስተባበር ደህንነቱ የተጠበቀ የሳይበር ዓለምን መፍጠር ያስችላል ሲሉ አቶ ሰለሞን አስረድተዋል፡፡ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች የምትገኘው ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት አጀንዳን ፈጽሞ ቸል እንደማትል የገለጹት አቶ ሰለሞን፤ ለዚህም በዋናነት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን ከማቋቋም አንስቶ፣ ፖሊሲዎችን መቅረጽ፣ የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅ መደንገግን እንዲሁም የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች ብለዋል፡፡ ይሁንና የሚገጥሙንን ተግዳሮቶች ለመፍታት በተናጠል ከምናደርገው ጥረት ይልቅ ከተለያዩ ሐገራት ጋር በትብብር የምንፈጥረው አቅም የተሻለ በመሆኑ መንግስታት በሳይበር ደህንነት ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ስፖርት
ሉሲዎቹ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ዛሬ ያደርጋሉ
Sep 22, 2023 41
አዲስ አበባ፤ መስከረም 11/2016(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ማጣሪያ ጨዋታውን ዛሬ ከብሩንዲ አቻው ጋር በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ያካሂዳል ። እ.አ.አ 2024 በሞሮኮ አስተናጋጅነት የሚካሄደው 15ኛው የሴቶች ብሔራዊ ቡድን የማጣሪያ ጨዋታውን ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት ያካሂዳል። በአሰልጣኝ ፍሬው ኃይለገብርኤል የሚሰለጥነው ብሔራዊ ቡድኑ፤ 26 ተጨዋቾችን በመያዝ ዝግጅቱን ከጳጉሜን 3 ቀን 2015 ዓ.ም. አንስቶ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ሲያደርግ ቆይቷል። ከአገር ውስጥ ቡድኖች ጋርም የተለያዩ የአቋም መፈተሻ ጨዋታዎችን አድርጓል። ለዛሬው ጨዋታ የመጨረሻ ልምምዱን ትናንት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም አከናውኗል። በ38 ዓመቱ ብሩንዲያዊ ጉስታቭ ኒዮንኩሩ የሚሰለጥነው የብሩንዲ ብሔራዊ ቡድን ላለፉት ጥቂት ሳምንታት ዝግጅቱን ሲያደርግ ቆይቷል። በዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማኅበር(ፊፋ) ወርሃዊ በሴቶች የአገራት የእግር ኳስ ደረጃ ኢትዮጵያ 124ኛ እንዲሁም ብሩንዲ 175ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። ሴንያሴንግ ሴፌ ከቦትስዋና የሁለቱን ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመራሉ። በሁለቱ አገራት የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ስምምነት የቡድኖቹ የመልስ ጨዋታ መስከረም 15 ቀን 2016 ዓ.ም. በአበበ ቢቂላ ስታዲየም እንደሚከናወን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የመልሱ ጨዋታ በአዲስ አበባ የሚከናወነው ብሩንዲ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መስፈርቶች የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ማስተናገድ የሚችል ስታዲየም የሌለው እንደሆነ ገልጿል። በአንጻሩ የአበበ ቢቂላ ስታዲየም የካፍን መስፈርቶች ያሟላ መሆኑን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ሉሲዎቹ በደርሶ መልስ ጨዋታ ካሸነፉ በቀጣዩ ዙር ከዩጋንዳና አልጄሪያ አሸናፊ ጋር ይጫወታሉ። ሞሮኮ እ.አ.አ በ2024 በምታስተናግደው 15ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ 40 አገራት የማጣሪያ ጨዋታቸውን በማድረግ ላይ ይገኛሉ። የማጣሪያ ጨዋታዎቹ በሁለት ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታዎች የሚከናወን ሲሆን ከአስተናጋጇ አገር ሞሮኮ ውጭ 11 አገራት የተሳትፎ ቦታውን ለማግኘት ይፋለማሉ። በአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ላይ 12 አገራት እንደሚሳተፉ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን(ካፍ) አስታውቋል።
በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ሁለተኛ ዙር ቅድመ ማጣሪያ ባህር ዳር ከተማ አሸነፈ
Sep 17, 2023 160
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 6 /2016 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ሁለተኛ ዙር ቅድመ ማጣሪያ ባህር ዳር ከተማ ከቱኒዚያው ክለብ አፍሪካን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2 ለ 0 አሸንፏል። ጎሎቹን ሀብታሙ ታደሰ ከእረፍት በፊት እና በጨዋታው መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ አስቆጥሯል። የመልሱ ጨዋታ ከቀናት በኋላ የሚካሄድ ሲሆን፤ በደርሶ መልሱ ጨዋታ አሸናፊ የሚሆነው ቡድን በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ተሳታፊ ይሆናል። ባህር ዳር ከተማ በመጀመሪያው ዙር ቅድመ ማጣሪያ የታንዛኒያውን አዛም በደርሶ መልስ ጨዋታ ማሸነፉ ይታወሳል።
የአፍሪካ ስፔሻል ኦሊምፒክ ፌዴሬሽኖች የመሪዎችና የአመራር አካዳሚ ጉባኤ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
Sep 15, 2023 300
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 4/2016 (ኢዜአ) ፦ የአፍሪካ ስፔሻል ኦሊምፒክ ፌዴሬሽኖች የመሪዎችና የአመራር አካዳሚ ጉባኤ በሚቀጥለው ሣምንት በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው። ጉባኤው ከመስከረም 07/2016 ዓ.ም ጀምሮ ሦስት ተከታታይ ቀናት የሚሄድ ሲሆን ከ39 የአፍሪካ አገራት የተውጣጡ የዘርፉ ተዋናዮችና ሌሎች እንግዶች በጉባኤው ይሳተፋሉ ተብሏል። የአፍሪካ ስፔሻል ኦሊምፒክ ፌዴሬሽን ይህንን ጉባኤው የተሳካ ለማድረግና በቀጣይ በሌሎች ጉዳዮች በትብብር ለመሥራት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ዛሬ ሥምምነት ፈጽሟል። ሥምምነቱን በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተቀናጀ የማርኬቲንግ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ንጉሱ ወርቁና የአፍሪካ ስፔሻል ኦሊምፒክ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ቻርለስ ንያምቤ ፈርመውታል። የኢትዮጵያ ስፔሻል ኦሊምፒክ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ምህረት ንጉሴ የአፍሪካ ስፔሻል ኦሊምፒክ ፌዴሬሽኖች የአመራርና የአካዳሚ ጉባኤን ለማስተናገድ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል። በጉባኤውም በዓለም አቀፍ የስፔሻል ኦሊምፒክ ሕግጋት፣ አሰራሮችና በተካሄዱ ውድድሮች ላይ የነበሩ ጥንካሬን ድክመቶች ላይ በመምከር የቀጣይ ማሻሻያ ርምጃ እንደሚቀመጥ አንስተዋል። የኢትዮጵያ ስፔሻል ኦሊምፒክ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ፈሪድ መሃመድ፤ በጉባኤው የተገኙ አዳዲስ ልምዶች ላይ ምክክር በማድረግ የአዕምሮ ውስንነት ተጠቂ የሆኑ ዜጎችን ስፖርታዊ ተሳትፎ ማሳደግ የጉባኤው ዓላማ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተቀናጀ የማርኬቲንግ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ንጉሱ ወርቁ፤ ሥምምነቱ በአዲስ አበባ በሚካሄደው የአፍሪካ ስፔሻል ኦሊምፒክ ጉባኤ የሚታደሙ ተሳታፊዎችን ማጓጓዝ፣ የስካይ ላይት ሆቴል መስተንግዶና ሌሎች ቀጣይ ትብብሮችን ያካትታል ነው ያሉት። የአፍሪካ ስፔሻል ኦሊምፒክ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ቻርለስ ንያምቤ፤ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የተደረሰው ሥምምነት ጉባኤውን በስኬት ለማስተናገድ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። የስፔሻል ኦሊምፒክ ፌዴሬሽን እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1968 የተመሰረተው ሲሆን የአዕምሮ ውስንነት ያለባቸውን ዜጎች በስፖርታዊ ውድድሮች የሚያበረታታ ስፖርታዊ የውድድር አይነት ነው።
ሉሲዎቹ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከቡሩንዲ ጋር የሚያደረጉት የደርሶ መልስ ጨዋታ አዲስ አበባ ላይ ይካሄዳል
Sep 15, 2023 200
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 4/2016 (ኢዜአ) ፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ከቡሩንዲ ጋር የሚያደርገው የደርሶ መልስ ጨዋታ አዲስ አበባ ላይ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ። ኢትዮጵያ በሜዳዋ የምታደርገውን ጨዋታ በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም እንደምታከናውን ለካፍ ማሳወቋን ፌዴሬሽኑ ገልጿል፡፡ በሌላ በኩል ቡሩንዲ በሜዳዋ ልታደርግ የነበረውን ጨዋታ አዲስ አበባ ላይ ለማድረግ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በተደረገው ስምምነት መሰረት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም እንደሚካሄድም ነው የተገለጸው። የመጀመርያው ጨዋታ መስከረም 9/2016 ሲከናወን፤ ሁለተኛው ጨዋታ ደግሞ መስከረም 15/2016 እንደሚከናወን ፌዴሬሽኑ አስታውቋል።
አካባቢ ጥበቃ
የአየር ንብረት ለውጥ የሚያሳድራቸውን ተጽዕኖዎች ለመከላከል ዓለም አቀፍ ትብብርን ማጠናከር ያስፈልጋል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን
Sep 21, 2023 91
አዲስ አበባ፤ መስከረም 10/2016 (ኢዜአ)፦ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያሳድራቸውን ተጽዕኖዎች ለመከላከል ዓለም አቀፍ ቅንጅታዊ ትብብርን ማጎልበት እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ። 78ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ “ሰላም፣ብልጽግና፣ለውጥና ዘላቂነት” በሚል መሪ ሀሳብ በኒው ዮርክ እየተካሄደ ነው። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከጉባኤው ጎን ለጎን በተካሄደ የአየር ንብረት ለውጥን የተመለከተ ጉባኤ ላይ ተሳትፈዋል። አቶ ደመቀ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቋቋም በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከፍተኛ የሚባል መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል። በመርሐ-ግብሩ እስከ አሁን ከ32 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸውንና የተለያዩ ውጤቶች እየተገኙበት መሆኑንም አመልክተዋል። የአደጋዎች ስፋት፣ መጠንና የሚከሰቱበት የጊዜ ገደብ ታሳቢ በማድረግ ኢትዮጵያ ፖሊሲዎቿን በመለወጥ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓት የማጠናከር ስራ በማከናወን ላይ ነች ብለዋል። በዚህ ረገድም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉትዬሬዝ “ቅድመ ማስጠንቀቂያ ለሁሉም” በሚል የጀመሩትን ኢኒሺዬቲቭ አቶ ደመቀ አድንቀዋል። ዓለም አቀፍ ትብብር አስፈላጊውን ቅንጅትና ትስስር በመፍጠር የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ወሳኝ አስተዋጽኦ እንዳለውም ነው ያብራሩት። በአገር፣ በአህጉርና ዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ውጤታማ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓት ለመገንባት አስፈላጊው የፋይናንስ ድጋፍ እንዲደረግም ጥሪ አቅርበዋል።
ዓለም እያጋጠማት ለሚገኘው አሳሳቢ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ አፋጣኝ ምላሽ መስጠት ይገባል-የተመድ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ
Sep 19, 2023 158
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 8/2016 (ኢዜአ) ፦ ዓለም በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት እያጋጠማት የሚገኘውን ተጽእኖ ለመዋጋት አፋጣኝ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አሳሰቡ። ዓለም አቀፍ ተቋማት የ21ኛው ክፍለ ዘመን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችንና ለውጦችን በሚመጥን መልኩ ራሳቸውን በማሻሻል ለሚታዩ ችግሮች የመፍትሄ አካል መሆን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። 78ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ በኒውዮርክ ተጀምሯል። በጉባኤው ከ140 በላይ የሀገራት መሪዎች እየተሳተፉ ሲሆን አሳሳቢ በሆኑና ምላሽ በሚሹ ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ እየመከሩ ይገኛሉ። የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ጉባኤውን ያስጀመሩት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ተናግረዋል። ዓለም በበርካታ የተፈጥሮ አደጋዎች እየተፈተነች ትገኛለች ያሉት ዋና ጸሐፊው የአየር ንብረት ለውጡ የከፋ ደረጃ ላይ ደርሶ የሰው ህይወት እየቀጠፈ እና ሰዎችን ከቀያቸው እያፈናቀለ ይገኛል ብለዋል። በአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ ምክንያት ዓለም ለችግር መጋለጧን ጠቅሰው ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖዎችን ለመዋጋት በትብብር መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። የአየር ንብረት ለውጡ በተለይ በታዳጊ ሀገራት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ ነው ያሉት ዋና ጸሀፊው ለዚህም ያደጉ ሀገራት የሚለቁትን የካርበን መጠን ለመቀነስ ከዚህ ቀደም የተደረሰውን ስምምነት ማክበር ይገባቸዋል ሲሉም ገልጸዋል። ሀገራት የሚለቁትን የካርበን መጠን ለመቀነስ ከነዳጅና የድንጋይ ከሰል ሀይል ፊታቸውን ወደ ታዳሽ ሀይል ማዞር እንዳለባቸው ጠቁመው የታዳሽ ሀይልን ማስፋፋት ዋነኛው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖ መቀነሻ መንገድ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ያደጉ ሀገራት የራሳቸውን የካርበን ልቀት ከመቀነስ ባለፈ ለታዳጊ ሀገራት የአረንጓዴ ልማትና የታዳሽ ሀይል መስፋፋት የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ የሰላምና የጸጥታ ሁኔታ በፍጥነት እየተቀየረ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ጸሀፊው የጸጥታው ምክር ቤትን ጨምሮ በርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት ማሻሻያ ሳያደርጉ ቆይተዋል ብለዋል። ለዚህም ዓለም አቀፍ ተቋማት የ21ኛው ክፍለ ዘመን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችንና ለውጦችን በሚመጥን መልኩ ራሳቸውን በማሻሻል ለሚታዩ ችግሮች የመፍትሄ አካል መሆን እንዳለባቸውም ነው የገለጹት። በመሆኑም እየተወሳሰበ የመጣውን ዓለም አቀፍ የሰላምና ጸጥታ ችግር ለመፍታት የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤትን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተቋማዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ እንደሚገባቸውም ዋና ጸሐፊው ያሳሰቡት። በተለይ የጸጥታው ምክር ቤት ዓለም አቀፍ የሰላምና የጸጥታ የፋይናንስ ስርዓቱን እንደገና መፈተሽ አለበት ሲሉም አሳስበዋል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓለምን እየቀየራት እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን ይህን መቆጣጠር የሚችል ዓለም አቀፍ ተቋም ማቋቋም እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። በዚህ ዙሪያም ለሚደረግ ምክክር የተባበሩት መንግስታት ድረጅተ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ሲሉም አስታውቀዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተመዘገበው ውጤት በትብብር ከተሰራ በሁሉም መስኮች ስኬታማ መሆን እንደሚቻል ሁነኛ ማሳያ ነው- ከንቲባዎች
Sep 18, 2023 145
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 7/2016 (ኢዜአ)፦ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ- ግብር የተመዘገበው ውጤት በትብብር ከተሰራ በሁሉም መስኮች ስኬታማ በመሆን የኢትዮጵያን ብልጽግና ማሳካት እንደሚቻል ሁነኛ ማሳያ መሆኑን የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ከንቲባዎች ተናገሩ። የሁለተኛው ምዕራፍ የመጀመሪያ ዓመት የአረንጓዴ አሻራ ማጠቃለያ መርሃ -ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ተካሂዷል። በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ጆጎ ተፋሰስ በተካሄደው የማጠቃለያ መርሃ- ግብር ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የሁሉም ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ከንቲባዎችና የግብርና ቢሮ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ በአዲስ አበባ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ከ17 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ከዕቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል ብለዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እንደ ሀገር የተከናወነው ስራና የተመዘገበው ውጤት በትብብር ከተሰራ በሁሉም መስክ ስኬታማ በመሆን የኢትዮጵያን ብልጽግና ማሳካት እንደሚቻል ሁነኛ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር፤ በድሬዳዋ በዘንደሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ - ግብር ከዕቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል ብለዋል። ከጎረቤት ሀገር ጅቡቲ ልዑካን ጋር ጭምር ችግኞች መተከላቸውን አስታውሰው የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራም እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ መተከል በጀመረው አረንጓዴ አሻራ ከተሞች በርሃማነትን መከላከል እና አየር ንብረት ልውጥን ከመቋቋም አኳያ የራሱ ሚና እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል። ሁለተኛውን ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ሃሳብ ሰኔ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፋር ክልል በመገኘት ማስጀመራቸው ይታወሳል። በሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ዘንድሮን ጨምሮ በአራት ዓመታት 25 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዷል። በእቅዱ መሰረት የሚተከሉት ችግኞች 60 በመቶ ለጥምር ደን እርሻ፣ 35 በመቶ ለደን እና 5 በመቶ ለከተማ ውበት የሚውሉ ይሆናሉ።
በህዝቦቿ የተባበረ ብርቱ ጥረት ጠንካራና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ እናስረክባለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ
Sep 18, 2023 148
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 7/2016 (ኢዜአ) ፦ በህዝቦቿ የተባበረ ብርቱ ጥረት ጠንካራና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ እናስረክባለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ። የሁለተኛው ምዕራፍ የመጀመሪያ ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ማጠቃለያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ተካሂዷል። በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሎሜ ወረዳ ጆጎ ተፋሰስ በተካሄደው የማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የሁሉም ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና የግብርና ቢሮ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአየር ንብረት ለውጥ እያደረሰ ስላለው ተፅዕኖ በርካታ ዓለም አቀፍ ውይይቶች መደረጋቸውን ገልጸዋል። ሆኖም ተፅዕኖውን ለመቋቋም ወደ ተግባር በመግባት በኩል ብዙ መጓዝ አለመቻሉን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን በማስጀመር ተፅዕኖውን ለመቋቋም ተምሳሌታዊ የተግባር እርምጃ ውስጥ መግባቷን ተናግረዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ እስካሁን በኢትዮጵያውያን የተባበረ ክንድ 32 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውንም ጠቅሰዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን በማንሳት፤ በሁለቱም ምዕራፎች የተተከሉ ችግኞች ብዛት 50 ቢሊዮን ለማድረስ እቅድ መያዙን ነው የገለጹት። ከአራት ዓመታት በፊት የጆጎ ተፋሰስ አካባቢ ምድረ በዳ እና ገላጣ ስፍራ እንደነበር ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፤ አሁን ላይ አካባቢው በአረንጓዴ ተሸፍኗል ብለዋል። ለዚህ ስኬት የአካባቢው ማህበረሰብ ትልቅ አበርክቶ እንዳለው ጠቅሰው የአረንጓዴ ልማቱን መሰረት በማድረግም ማህበረሰቡ የንብ ማነብ ስራ መጀመሩን ገልጸዋል። በአረንጓዴ ልማት የአፈር መሸርሸርን ማስቀረት፣ የዝናብ መጠንን መጨመርና ስርዓተ ምህዳርን ማስተካከል መቻሉን ገልጸው፤ ከዚህም ባለፈ ትልቅ የኢኮኖሚ ምንጭ እየሆነ መጥቷል ነው ያሉት። በቀጣይም የፍራፍሬ፣ የቡና፣ የሻይ እና ሌሎች ገበያ ተኮር የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላሳየው ብርቱ ጥረትና ላስመዘገበው ስኬት መንግስት ከፍተኛ ክብር እንደሚሰጥም ገልጸዋል። በቀጣይም በአረንጓዴ አሻራ፣ በህዳሴ ግድብ፣ በስንዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋት እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶችን በሁሉም ዘርፍ አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ነው ያሉት። የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ስኬት አይቀሬነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት በመንግስትና በህዝብ ትብብር እየተከናወኑ መሆናቸውንም ነው የገለጹት። የኢትዮጵያን የለውጥ ጉዞ የማፅናትና ብልፅግናዋን የማረጋገጥ ጉዞን የሚያስቆም አንዳችም ምድራዊ ሃይል አይኖርም ሲሉም በአፅንኦት ተናግረዋል። በህዝቦቿ የተባበረ ብርቱ ጥረት ጠንካራና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ እናስረክባለን ሲሉም ተናግረዋል። ሁለተኛውን ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ሃሳብ ሰኔ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፋር ክልል በመገኘት ማስጀመራቸው ይታወሳል። በሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ዘንድሮን ጨምሮ በአራት ተከታታይ ዓመታት 25 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዷል። በእቅዱ መሰረት የሚተከሉት ችግኞች 60 በመቶ ለጥምር ደን እርሻ፣ 35 በመቶ ለደን እና 5 በመቶ ለከተማ ውበት የሚውሉ ይሆናሉ።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአማርኛ ቋንቋ በሞስኮ ከተማ ትምህርት ቤቶች መሰጠት ተጀመረ
Sep 20, 2023 131
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 09/2016 (ኢዜአ)፦ የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በሩሲያ ሞስኮ ትምህርት ቤቶች መሰጠት ተጀምሯል። የሩሲያው ዜና አግልግሎት ስፑቲኒክ እንደዘገበው አማርኛን ጨምሮ የአፍሪካ ቋንቋዎችን በሩሲያ ትምህርት ቤቶች መሰጠት ተጀምሯል። የቋንቋዎቹ ትምህርት መጀመር በሩሲያ እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የሚኖረውን ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና ባሕላዊ መስኮች የነበሩ ትስስሮችን ይበለጥ ለማሳድግ ሚናው የጎላ መሆኑን የትምህርት ቤቶች ርዕሰ መምህራን ተናግረዋል። አማርኛ ቋንቋን በሁለተኛ ቋንቋነት መማር የጀመሩ ተማሪዎች ለስፑቲኒክ እንደተናገሩት፣ የአማርኛ ቋንቋ ከማወቅ ባሻገር ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የህዝቡን ባህልና አኗኗር የማወቅ ጉጉት አሳድሮባቸዋል። ሩሲያ በሞስኮ ትምህርት ቤቶች ከመስከረም ጀምሮ አማርኛ ቋንቋ ማስተማር እንደምትጀምር ባለፈው ዓመት ማስታወቋ ይታወሳል።
የቡድን 20 የመሪዎች ጉባዔ የአፍሪካ ኅብረትን አባል በማድረግ ተጠናቀቀ
Sep 10, 2023 280
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 5/2015(ኢዜአ)፦በሕንድ አስተናጋጅነት ኒውዴልሂ ከተማ ውስጥ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የቡድን 20 አባል አገራት የመሪዎች ጉባዔ የአፍሪካ ኅብረትን 21ኛ አባል በማድረግ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባዔው ማጠናቀቂያ ላይ የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ለብራዚሉ ፕሬዝዳንት ሉዊዝ ኢናሲዮ ዳ ሲልቫ የቡድን 20 ፕሬዝዳንትነት ቀጣይ መንበር አስረክበዋል። ሉላ ዳ ሲልቫ ማኅበራዊ አካታችነትን፣ ረሃብን መዋጋት፣ የኃይል ሽግግርን እና ዘላቂ ልማትን የቡድን 20 አገራት ቅድሚያ ትኩረት የሚሰጧቸው እንደሆነም ከወዲሁ ይፋ አድርገዋል። ጉባዔው 55 አባል አገራት ያቀፈውን የአፍሪካ ኅብረትን ታሪካዊ በተባለ ውሳኔ የቡድን 20 አባል አድርጎ ተቀብሏል። የአፍሪካ ኅብረት የቡድን 20 ሃያ አንደኛ አባል ሆኖ መቀላቀሉ የቡድኑን አካታችነት መርህ እንደሚያጎላው የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ተናግረዋል። ሕንድ ባስተናገደችው የቡድን 20 የመሪዎች ጉባዔ ላይ በተከፋፈሉ የዓለም ኃያላን መንግሥታት መካከል ስምምነትን መፍጠር ችላለች ተብሏል። ይህ ደግሞ ለአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ላቅ ያለ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት እንደሆነም ተገልጿል። ጉባዔው የኒውዴልሂ የጋራ መግለጫ ሰነድ ይፋ በማድረግ ሲጠናቀቅ ሁሉም የቡድን 20 አባላት አገራት በዓለም ዙሪያ ሰላም፣ ደህንነት እና ግጭት በማስወገድ አንድ ሆነው ለመስራት ተስማምተዋል። ሰነዱ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት በአገር አቀፍ ደረጃ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ገቢራዊ ለማድረግ እኤአ እስከ 2030 ድረስ ከ5 ነጥብ 8 እስከ 5 ነጥብ 9 ትሪሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልጋቸው አመልክቷል። እንዲሁም እስከ 2030 ድረስ ለታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂዎች 4 ትሪሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልጋቸውና ይህም እኤአ በ2050 የካርባን ልቀትን ዜሮ ለማድረስ እንደሚረዳቸው ግልጽ አድርጓል። በተጨማሪም አባል አገራት የኃይል እርምጃን ከመውሰድ እንዲቆጠቡ መግባባት ላይ ተደርሷል ነው የተባለው።
በቴል አቪቭ የሚኖሩ ኤርትራዊያን ከፖሊስ ጋር በፈጠሩት ግጭት 160 ሰዎች መቁሰላቸው ተገለጸ
Sep 2, 2023 433
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 27/2015 (ኢዜአ) ፦ በእስራኤል ቴል አቪቭ የሚኖሩ ጥገኝነት ጠያቂ ኤርትራዊያን ከፖሊስ ጋር በፈጠሩት ግጭት ፖሊሶችን ጨምሮ 160 ሰዎች መቁሰላቸው ተገለጸ። እንደ እየሩሳሌም ፖስት ዘገባ የኤርትራ ኤምባሲ በቴል አቪቭ ያቀረበውን የባህል ዝግጅት ኤርትራዊያኑ ስደተኞች በመቃወማቸው ምክንያት በተነሳ ብጥብጥ ብዙዎቹ ጉዳት ደርሶባቸዋል። በተቃውሞው ላይ በነበራቸው ተሳትፎ ከቆሰሉት ጥገኝነት ጠያቂ ኤርትራዊያን መካከል ስምንቱ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ናቸው። እየሩሳሌም ፖስት የሆስፒታልና የፖሊስ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ከቆሰሉት መካከል 13ቱ መጠነኛ እንዲሁም 93 የሚሆኑት ደግሞ ቀላል ጉዳት ያጋጠማቸው ናቸው። ዛሬ ከቀትር በኋላ በቴል አቪቭ የኤርትራ ኤምባሲ ባሰናዳው ዝግጅት ላይ በተነሳው የተቃውሞ ብጥብጥ 50 የሚሆኑ ፖሊሶች መቁሰላቸውን ጨምሮ በንብረት ላይም ጉዳት መድረሱ ተዘግቧል። ኤርትራዊያኑ ስደተኞች የሃገራቸውን መንግስት በመቃወም በተነሳው ብጥብጥ የሱቆችን መስኮቶች፣ የፖሊስ ተሽርካሪዎችን የሰባበሩ ሲሆን ፖሊስም ሁኔታውን ለመቆጣጠር አስለቃሽ ጭስና ሌሎችንም አማራጮች መጠቀሙ ተዘግቧል።
የኢትዮጵያ የብሪክስ አባልነት የአፍሪካን አጀንዳና ጥቅሞችን ለማስጠበቅ የሚረዳ ነው- በአልጀዚራ የጥናት ማዕከል የምርምር ግንኙነት ኃላፊ ቴምቢሳ ፋኩዴ
Aug 26, 2023 637
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 2015 (ኢዜአ) ኢትዮጵያ የብሪክስ ቡድን አባል አገር መሆኗ የአፍሪካን ድምጽ ከማሰማት አልፋ አሕጉራዊ ጥቅሞችን ታስጠብቃለች የሚል እምነት እንዳላቸው በአልጀዚራ የጥናት ማዕከል የምርምር ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት ቴምቢሳ ፋኩዴ ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በብዙ ዓለም አቀፍ መድረኮች ያላቸው ላቅ ያለ ተቀባይነት የአፍሪካን አጀንዳ ያሳከሉ የሚል እምነት እንዳላቸውም ተናግረዋል። በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ ከሚዘግበው ኢ-ኒውስ ቻናል አፍሪካ ቴሌቪዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት የኢትዮጵያ የብሪክስ አባልነት የአፍሪካን ጥቅሞች ለማስጠበቅ የሚረዳ ነው። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን በብሪክስ አባል አገራት በሚነሱ ጉዳዮች ላይ የአፍሪካ አጀንዳን በማንሳት አሕጉራዊ ጥቅሞች እንዲጠበቁ የማድረግ ብቃት እንዳላት ተናግረዋል። ቴምቤሳ ፋኩዴ አክለውም ኢትዮጵያ የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤዎችን በማቀንቀን አፍሪካዊ አንድነት እንዲጠናከር የምትሰራ አገር መሆኗ ለአባልነት ይበልጥ ተመራጭ አድርጓታል ብለዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ጠንካራ የመከላከያ ኃይል የገነባች አገር መሆኗ ደግሞ በብሪክስ አባል አገራት ተመራጭ እንድትሆን አድርጓታል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ካለፉት ሃያ ዓመታት ወዲህ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ማስመዝገብ የቻለች ብቻ ሳይሆን በቀጣይም ይህን ዕድገት ማስቀጠል የምትችል አገር መሆኗ ለመመረጧ በዋቢነት አንስተዋል። በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 15ኛው የብሪክስ አባል አገራት የመሪዎች ጉባዔ ኢትዮጵያን ጨምሮ 6 አገራት በአባልነት መቀበሉ የሚታወቅ ነው።
ሐተታዎች
የአባቱን የጀግንነት ፈለግ የተከተለው ዳግም ኤቢሳ
Sep 19, 2023 129
በኢትዮጵያ የሺህ ዘመናት ታሪክ ለሀገር ክብር፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነትን ጠብቆ ለማቆየት የተዋደቁ፣ ጀግንነትን የተዋረሱ እና መስዋዕትነት የከፈሉ ቤተሰቦች ማግኘት የተለመደ ነው። በየዘመኑ ለአገር ሉዓላዊነት፣ ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ዘብ የቆሙ ወታደሮች ጀግንነታችውን ለልጆቻቸው አውርሰዋል፤ ልጆችም የአባትና አያቶቻቸውን ፈለግ በመከተል የራሳቸውን የጀግንነት አሻራ ያሳርፋሉ። ለእናት አገር ዘብ መቆምን በትውልድ ቅብብሎሽ ካስቀጠሉ ቤተሰቦች መካከል የወይዘሮ እሙዬ ፈለቀ ባለቤት ኮሎኔል ኤቢሳ ታይሳ እና ልጃቸው ዳግም ኤቢሳ ይገኙበታል። "እኛ የመከላከያ ሰራዊት ቤተሰብ ነን" የሚሉት ወይዘሮ እሙዬ ፈለቀ፣ ባለቤታቸው ኮሎኔል ኤቢሳ በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ አገልግሎ ለሀገሩ ክብር በጀግንነት መሰዋቱን ያነሳሉ። የጀግና አባቱን ገድል እየሰማ ያደገውና የሀገር ፍቅርን የወረሰው ልጃቸው ዳግም ኤቢሳ ደግሞ በጦላይ ከፍተኛ ባለሌላ ማዕረግተኛ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በመሰረታዊ ወታደርነት ተመርቋል። ከአዲስ አበባ ተነስተው ወደ ጦላይ በመሄድ በልጃቸው ምርቃት ላይ ያገኘናቸው ወይዘሮ እሙዬ ፈለቀ፣ "ልጄ የአባቱን የኮሎኔል ኤቢሳ ታይሳ ጀግንነትና የሀገር ፍቅር ለመከተል ከፍተኛ ስሜት ነበረው" ይላሉ። "የጀግና ልጅ ጀግና ነውና ልጄም ሰራዊትን በመቀላቀል ጀግንነቱን በተግባር አረጋግጧል" ሲሉም ይናገራሉ። ባለቤታቸው እና ልጃቸው ለሀገር ክብር ዘብ በመሆናቸውም የላቀ ክብርና ኩራት እንደሚሰማቸው የሚያነሱት ወይዘሮ እሙዬ፤ ልጃቸውን "እንደ አባትህ ጀግና ሁን" እያሉ ጀግንነትን እንዲላበስ ማድረጋቸውንም ይገልጻሉ። "ልጄ የአባቱን ወታደራዊ የደንብ ልብስ ለብሶ በማየቴ ከፍተኛ ኩራት ተሰምቶኛል" ያሉት እናት፣ ሀገርን በቅንነትና ታማኝነት በማገልገል የአባቱን የጀግንነት ታሪክ እንዲያስቀጥል መምከራቸውንም አንስተዋል። ባለቤታቸው ለከፈለው መስዋዕትነትም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለቤተሰቡ ተገቢውን ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑን ጠቅሰዋል። መሰረታዊ ወታደር ዳግም ኤቢሳ በበኩሉ በማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ወታደራዊ ትምህርትና ስልጠና ወስዶ ከጓዶቹ ጋር በመመረቁ ተደስቷል። "የእናት ሀገሬን ሉዓላዊነት አንድነት በመጠበቅ የአባቴን አሻራ ለማስቀጠል ዝግጁ ነኝ" ብሏል። ወታደራዊ ግዳጅን በብቃት መወጣት የሚያስችል ትምህርትና ስልጠና መውሰዱን የሚናገረው ዳግም ኤቢሳ፣ እንደ አባቱ እስከ ሕይወት መስዋዕትነት ከፍሎ ሀገሩን ለማገልገል ያለውን ወኔና ቁርጠኝነትም ገልጿል።
ችግር ፈቺ ፈጠራ
Sep 9, 2023 287
ባስልኤል የእንጨትና ብረታ ብረት ማህበር በጅንካ ከተማ በክላስተር ማዕከል ውስጥ ከተደራጁ 8 ማህበራት አንዱ ነው ። የማህበሩ ሰብሳቢ አቶ ጌታቸው ሙሐመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ማህበሩ ከኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ባገኘው 450 ሺህ ብር የብድር ድጋፍ በ2007 ዓ.ም ወደ ስራ መግባቱን አስታውሰዋል። ከብድር አቅርቦቱ በተጨማሪ በመንግስት የማሽነሪ እና የማምረቻ ሼድ ድጋፍ እንደተደረገላቸውም ተናግረዋል። ማህበሩ ከሚያመርታቸው የእንጨትና ብረታ ብረት ውጤቶች በተጨማሪ ከውጪ በከፍተኛ የዶላር ምንዛሪ የሚገቡ የተለያዩ ማሽነሪዎችን ያመርታል። ማህበሩ ካመረታቸው አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች አንዱ የጥልቅ ጉድጓድ መቆፈሪያ ማሽን ይጠቀሳል። ቀደም ሲል ማሽኑን ለመግዛት እስከ 2 ሚሊዮን ብር ይፈጅ እንደነበር የገለፁት የማህበሩ ሰብሳቢ ፤ ይህንኑ ማሽን በተሻለ ጥራት ማምረት በመቻላችን ለማሽኑ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ ማዳን ችለናል ብለዋል። የጉድጓድ መቆፈሪያ ማሽኑንም በጅንካ ከተማ ለሚገኙ ለተለያዩ ተቋማት በተመጣጣኝ ዋጋ የጥልቅ ጉድጓድ በመቆፈር የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግራቸውን መቅረፉንም ነው አቶ ጌታቸው የሚናገሩት። በተጨማሪ ኃይል ቆጣቢ የእህል ወፍጮ፣ ኃይል ቆጣቢ ምድጃ፣ በሰአት እስከ 10 ኪሎ ግራም ቡና የሚቆላ ማሽን፣የገብስ መፈተጊያና የአተር መቁያ ማሽን በአገልግሎት ላይ ከሚገኙ የማህበሩ የፈጠራ ውጤቶች ይጠቀሳሉ። ከተጠቀሱት ምርቶች ባለፈም ማህበሩ በሚሰራቸው የብረት ማቅለጫና ቅርፅ ማውጫ ማሽኖች የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎችንም ያመርታል። የማህበሩ የረጅም አመታት ደንበኛ እንደሆኑ የሚገልጹት የጅንካ ከተማ ነዋሪ አቶ አወቀ አይኬ፤ ''ማህበሩ የሚሰራቸው አዳዲስ የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች የማህበረሰቡን ችግር በእጅጉ እያቃለሉ ናቸው'' ብለዋል። ከዚህ ቀደም የተሽከርካሪ የመለዋወጫ ዕቃዎችን ለማግኘት 730 ኪሎ ሜትር በመጓዝ ወደ አዲስ አበባ እንደሚሄዱ አስታውሰው አሁን ማህበሩ የምንፈልገውን ብሎንም ሆነ ሌሎች የመለዋወጫ ዕቃዎችን በፈለግነው ዲዛይን እዚሁ አምርቶ በማቅረቡ ወደ አዲስ አበባ በመሄድ የምናባክነውን ጊዜና ገንዘብ እንድንቆጥብ አስችሎናል ብለዋል። በተለይ የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ መቆፈሪያ ማሽኑ በከተማዋ የሚስተዋለውን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር ከማቃለል አኳያ ትልቅ ሚና እየተወጣ እንዳለም ተናግረዋል። ወይዘሮ ትዕግስት አባይነህ የተባሉ የጅንካ ከተማ ነዋሪ በበኩላቸው ማህበሩ የፈጠራቸው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በተለይ የሴቶችን ድካም በእጅጉ እንዳቃለለ ተናግረዋል። ቀደም ሲል ገብስ ለመፈተግ፣አተር ለመቁላት እና ሌሎች ቅመማ ቅመሞችን ለማዘጋጀት ብዙ ውጣ ውረዶች እንደነበር ገልፀው ይህም ከቢሮ የስራ ሰአት ውጪ ባለው ትርፍ ጊዜ ለማከናወን አስቸጋሪ እንደነበር ገልጸዋል ። በተለይ በቤት ውስጥ የበአልና ሌሎች ፕሮግራሞች ሲኖሩ እነኚህን ስራዎች መስራት አድካሚ እንደሆነ ገልፀው አሁን ማህበሩ በፈጠራቸው ዘመናዊ ማሽኖች አድካሚ ስራዎችን ግማሽ ሰአት ባልሞላ ጊዜ እንደሚያጠናቅቁ ተናግረዋል ። ማህበሩ የሰራቸው ወጪ ቆጣቢ ምድጃዎችም በቤት ውስጥ ምግብ ለማዘጋጀት አመቺና ጥራታቸውም ወደር እንደሌለው የገለፁት ወይዘሮ ትዕግስት እነዚህ ምርቶች በእጅጉ የማህበረሰቡን ችግር የሚቀርፉና ህይወትን ቀለል የሚያደደርጉ በመሆናቸው እንዲህ ያለ የፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ግለሰቦች ሊበረታቱ እንደሚገባም ተናግረዋል ። የባስልኤል የእንጨትና ብረታ ብረት ስራ ማህበር ከማህበሩ አባላት በተጨማሪ ለ8 ሰራተኞች ቋሚ የስራ እድል ፈጥሯል፤ ቀደም ሲል በማህበሩ ይሰሩ የነበሩ አባላትም ከማህበሩ በቀሰሙት ዕውቀትና ልምድ የግል ድርጅት በመክፈት የራሳቸውን ገቢ እያመነጩ ለሌሎችም የሥራ ዕድልን ፈጥረዋል። በማህበሩ ተቀጥረው ከሚሰሩ ባለሙያዎች አንዱ አቶ ደረጀ ሙሐመድ ሲሆኑ በማህበሩ ውስጥ በመስራታቸው ተጠቀሚነታቸው የደሞዝ ብቻ እንዳልሆነና የዕውቀት ሽግግር ዕድልን ተጠቃሚ እንደሆኑ ያነሳሉ። ታዲያ የነዚህ የፈጠራ ሀሳቦች ባለቤት የሆነውና የማህበሩ መስራች አቶ ጌታቸው ሙሐመድ ይህን የፈጠራ ሀሳብ በማፍለቅ እውን የሚያደርገው እንደ ሙሉ ጤነኛ ሰው በእግሩ እንደ ልቡ እየተንቀሳቀሰ ሳይሆን በዊልቸር እየተገፋ ነው። አቶ ጌታቸው በ1990 ዓመተ ምህረት በድሬዳዋ ከተማ በስራ ላይ ባጋጠመው የኤሌክትሪክ አደጋ ከፎቅ ላይ በመውደቁ በእግሮቹ ላይ ጉዳት ሊደርስበት መቻሉን ተናግሯል። አደጋው ካጋጠመው ጊዜ አንስቶ በበርካታ ውጣ ውረዶች ውስጥ ማለፉን አስታውሶ ለፈተናዎች እጅ ባለመስጠቱ ለዚህ ስኬት መብቃቱን ይናገራል። ''ያጋጠመኝን የተሽከርካሪ ችግር ለመቅረፍ የወዳደቁ ሞተር ሳይክሎች በመጠገን ለራሴ እንድትመቸኝ አድርጌ የሰራኋት ተሽከርካሪ እዚህ ደረጃ ላይ እንድደርስ አድርጋኛለች'' ብለዋል። ማህበሩ አሁን ላይ ከቋሚ ንብረቶች በተጨማሪ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ ሃብትእያንቀሳቀሰ እንደሚገኝ አቶ ጌታቸው ገልጿል። በቀጣይም እንደ አገር በተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በውድ ዋጋ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን በተሻለ ዲዛይን በማምረት የውጭ ምንዛሪውን ለማስቀረትና የማህበረሰቡንም ችግር ለማቃለል ማህበሩ በትጋት እንደሚሰራም ተናግረዋል። የአምራችነት ቀን '' ከሸማችነት ወደ አምራችነት'' በሚል መሪ ሃሳብ እየተከበረ በሚገኝበት በዛሬው ዕለት የመሰል ማህበራት ተሞክሮ የሚያስተምረው ነገር ብዙ ነው።
በጎነት ለሌሎች መኖር ነው- ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ
Sep 8, 2023 289
"በጎነት ለሌሎች መኖር ነው" ሲሉ የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ተናገሩ። በኢትዮጵያ የጳጉሜን ቀናት የተለያየ ስያሜ በመስጠት በጎነትን ፣አብሮነትን ፣መተሳሰብንና መስዋዕትነትን የሚያንጸባርቁ ሃሳቦችን በመስጠት መከበር ከጀመረ ቆይቷል። በዚህም የዛሬዋ ጳጉሜን 3 ቀን “በጎነት ለሀገር” በሚል ሀሳብ በጎ ተግባራትን በሚያንጸባርቁ የተለያዩ መርሐ-ግብሮች እየተከበረ ነው። ቀኑን ምክንያት በማድረግ ኢዜአ የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ሲስተር ዘቢደርን አነጋግሯል። "የኢትዮጵያውያን እርስ በርስ የመደጋገፍ ባህል እየጎለበተ መምጣቱን" የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ በዚሁ ወቅት ተናግረዋል። ከተመሰረተ 29ኛ ዓመቱን የያዘው ድርጅቱ ከ11 ሺህ ያላነሱ ጧሪና ደጋፊ ያጡ አረጋዊያንን በመንከባከብና የተሻለ ኑሮ እንዲኖሩ የማድረግ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች ለችግር የተጋለጡ ከ39 ሺህ በላይ ሕፃናትን ደግፎና አስተምሮ ለቁምነገር ማብቃት መቻሉንም ጠቅሰዋል፡፡ በተለይ ላለፉት 17 ዓመታት "ኢትዮጵያዊያን ለኢትዮጵያዊያን" በሚል መርህ በሀገር ልጆች ሀብት ላይ ተመስርቶ በሶስት ክልሎች በ 24 ከተሞችና 112 ወረዳዎች ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ በዚህም በትምህርት፣ጤና፣ የሕጻናት ጥበቃና የኢኮኖሚ አቅምን ማጎልበትና አረጋውያንን የመንከባከብ ስራዎችን በስፋት ሲያከናወን መቆየቱን ይጠቀሳሉ። በጎነት ለሌሎች መኖር ነው የሚሉት ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ፤ በጎነት ሕይወትንና ስኬትን ሙሉ የሚያደርግ እሳቤ መሆኑን ገልጸዋል። በጎነት ለግለሰብም ሆነ ለማህበረሰብ ብሎም ለአገር የሚጠቅም በጎ ተግባር እንደሆነ ተናግረዋል። በጎነት ለሁሉም ሰው የተሰጠ ነው የሚሉት ሲስተር ዘቢደር ልዩነቱ በጎነትን መለማመድ መሆኑን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያውያን በመተባበር ለአገርና ለወገን ትልቅ ስራ ማከናወን ይቻላሉ ብለዋል። በመስጠት ብዙ መቀበል እንደሚቻልና በጎነት የሕይወት አካል ማድረግ እንደሚገባም ነው ሲስተር ዘቢደር የገለጹት። ሜሪጆይ በ1986 ዓ.ም የተቋቋመ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ሲሆን በተቀናጀ የልማት መርሐ-ግብሮች ለችግር የተጋለጡና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ዋና ትኩረቱን አድርጎ እየሰራ ይገኛል።
ምስጉንና ትጉህ የጤና ባለሙያ አርጃ ቲሎ
Sep 6, 2023 476
የጤና መኮንን ባለሙያው አርጃ ቲሎ በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ምስጉን እና ታታሪ ሠራተኛ ናቸው። በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል የተቀናጀ ድንገተኛ የማህፀን ፅንስና አጠቃላይ ቀዶ ህክምና ባለሙያው ከ35 ዓመታት በላይ በተለያዩ ተቋማትና አካባቢዎች ሀገራቸውን አገልግለዋል። ካገለገሉባቸውም አካባቢዎች በጋሞ፣ወላይታና ደቡብ ኦሞ ዞኖችን ጨምሮ ሀዋሳና ጂንካ ተጠቃሽ ናቸው። የህክምና ትምህርታቸውን በሀገር ውሰጥና በውጭ ሃገር በመከታተል ሙያቸውን አሻሽለዋል። የጤና መኮንን ባለሙያው አርጃ ቲሎ በበዓላትና በእረፍት ቀናት ጭምር ከቤተሰብ ይልቅ ለታካሚዎቻቸው ቅድሚያ በመስጠታቸው ምስጋናን ተችረዋል ። ከሌሎች ሰራተኞች ከመግባታቸው በፊት ቀድመው ቢሮ መግባታቸውና ታታሪነታቸው ለሽልማት አብቅተቸዋል፡፡ ባለሙያው አርጃ ቲሎ ባለፈው አመት ከደቡብ ኦሞ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ የዋንጫና የወርቅ ሜዳሊያ ሽልማትን ተቀብለዋል። በ35 ዓመታት የስራ ቆይታቸው ብዙ ነገሮችን ያሳለፉት ባለሙያው አርጃ ቲሎ ታዲያ አንዴ ያጋጠማቸውን ከባድ ፈተና መቼም እንደማይረሱት ይናገራሉ ። በጂንካ ሆስፒታል በማገልገል ላይ እያሉ አንዲት ነፍሰ ጡር እናት በወሊድ ወቅት ባጋጠማት የተራዘመ ምጥ በሞትና በህይወት መካከል ነበረች ሲሉ ያስታውሳሉ። ይቀጥሉናም በወቅቱ በሆስፒታሉ የደም አቅርቦት እና በዘርፉ የሰለጠኑ ስፔሻሊስት ሀኪሞች ባለመኖራቸው ለዚህች እናት ህክምና መስጠት አልተቻለም ነበር ። ስፔሻሊስቱ ለተሻለ ህክምና ወደ አርባ ምንጭ ሆስፒታል ሪፈር መፃፍ ቢጠበቅባቸውም ታካሚዋ እስከ አርባ ምንጭ በህይወት ስለመድረሷ ይጠራጠራሉ ሲሉ ትውስታቸውን ይተርካሉ። ይህን የተገነዘቡት የጤና መኮንኑ ታዲያ አንድ ነገር ለማድረግ ወሰኑ፡፡ ወደ አርባ ምንጭ ልከው ነፍሰ ጡሯ መንገድ ላይ ህይወቷ ከሚያልፍ አቅማቸው የፈቀደውን አድርገው የመጣውን ለመቀበል ወሰኑ። ውሳኔውም ህክምናውን ሳያደርጉ ሞቷን ከመጠባበቅ እንደሚሻል በማመን ከህመምተኛዋ ቤተሰቦች ባገኙት ደም የተሳካ የቀዶ ጥገና በማድረግ ወላዷን እናት ከሞት ሊታደጉ መቻላቸውን በኩራት ይተርካሉ። 'የፈጣሪ እርዳታ ታክሎበት ቀዶ ጥገናውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቅቄያለሁ' ታካሚዋም በህይወት ቆይታ ጤናማ ህይወት ስትመራ በማየታቸው ቃላት ሊገልፁት የማይችሉት ደስታ ይሰማቸዋል። በመሆኑም ማንኛውም ሀኪም ቁሳቁስ አልተሟላም እጥረት አለ በማለት ከማማረርና ባለው አቅም ተገልጋዩን በማገልገል ኃላፊነቱን ይወጣ ሲሉም ምክራቸውን ይለግሳሉ። የረጅም አመታት የስራ ባልደረባ አቶ ኢያሱ ታንቱ የአርጃን ከሰራተኛው ጋር ተግባቢነት ፣ደከመኝ ሰለቸኝ የማያውቁ፣ለስራቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው ክብር ያላቸው ፣ታካሚውን በርህራሄ የሚያገለግሉ፣ ለሌሎች ተምሳሌት የሚሆኑ ሲሉም ይገልጿቸዋል። በጅንካ አጠቃላይ ሆስፒታል በቀዶ ህክምና ክፍል የነርሶች አስተባባሪ አቶ አማኑኤል ካሳ የባልደረባቸውነ ምስክርነት ይጋራሉ። የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር አይፎክሩ ግዛቸው በበኩላቸው አቶ አርጄ በሆስፒታሉ ስፔሻሊስት ሀኪሞች ከመመደባቸው አስቀድሞ ስፔሻሊስት ሀኪሞች እጥረት በነበረበት ወቅት በአጠቃላይ ቀዶ ህክምናና ነፍሰ ጡር እናቶችን በቀዶ ህክምና በማዋለድ ትልቅ ሙያዊ ኃላፊነት ሲወጡ የነበሩ ትጉህ ሰራተኛና የሀገር ባለውለታ ናቸው ሲሉ ይመሰክራሉ። ወይዘሮ ዘላለም ሰኢድ የጅንካ ከተማ ነዋሪ ናቸው፤ የአርጃ ቲሎ የህክምና ሙያ ከጎበኟቸው ተገልጋዮች አንዷ ሲሆኑ የሀኪሙን መልካምነት ይመሰክራሉ፡፡ እንዲ ሲሉ የህክምና ሙያን ከመልካም ስነምግባር ጋር የያዙ።
ትንታኔዎች
ያሆዴ- የአዲስ ተስፋና ልምላሜ ምልክት
Sep 22, 2023 53
(በማሙሽ ጋረደው ከሆሳዕና) ያሆዴ የሃድያ ብሔር የአዲስ ዘመን መሸጋገሪያ በዓል ነው። በዓሉ ሲከበር ቂምና ቁርሾ ተወግዶ ያለፈው ዓመት መልካምና በጎ ያልሆነ ሁኔታ ታይቶ ለቀጣይ ስኬት አዲስ ተስፋና ልምላሜ ሰንቆ የሚሻገሩበት በዓልም እንደሆነ ይነገራል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የሃድያ ዞን አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ አቶ ታምሬ ኤርሚያስ እንዳሉት ሃድያ የራሱ የሆነ የጊዜ አቆጣጠር ባህል፤ ልማድ፤ ወግና ስርዓት አለው። ለዚህም እንደ ማሳያ በብሔሩ ዘንድ በከፍተኛ ድምቀት የሚከበረውን የያሆዴ ክብረ በዓል ለአብነት ጠቅሰዋል። በዓሉ የአዲስ ተስፋና ልምላሜ ምልክት ተደርጎ እንደሚወሰድ የተገለጸ ሲሆን በተለይም የሚመጣው ዘመን የስኬት እንዲሆን እያንዳንዱ ካለፈው ዓመት ስኬትና ውድቀት ልምድ እየቀመረ ሃገር ሰላም እንዲሆን ተመራርቀው በደስታ እየተበላ፤ እየተጠጣ የሚከበር በዓል መሆኑንም ተናግረዋል። በብሔሩ ዘንድ ልዩ ቦታ የሚሰጠው የያሆዴ ክብረ በዓል አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበትም ነው። በዓሉ ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ በተለያዩ ክዋኔዎች የሚከበር ሲሆን በዓሉ መቅረቡን ታዳጊ ልጆች በተለያዩ ገላጭ በሆኑ ድርጊቶች እንደሚያበስሩ አቶ ታምሬ ተናግረዋል። በተለይም ታዳጊዎቹ ያሆዴ መድረሱን ለማብሰር ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ እስከ ጳጉሜ መጨረሻ ድረስ በብሔሩ አጠራር ገምባቡያ ወይም (ዋሽንት) በመጠቀም የተለያዩ ጥዑመ ዜማዎችን በማሰማት በዓሉ መቅረቡን ያበስራሉ። በሃድያ ብሔር ዘንድ የአዲስ ዘመን ብስራት “ያሆዴ" የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት ተደርጎ የሚወሰድ በዓል መሆኑንም አመልክተዋል። ይህም የሆነበት ምክንያት በመስከረም ሰውና እንስሳ ከዶፍ ዝናብ፣ ከውርጭ፣ ከጤዛና ከጭቃ፣ ከጉም፤ ከጭጋግና ጽልመት ነጻ ይሆናሉ። ምድሩ በሃምራዊ ቀለም ደምቆ ያሸበርቃል። ፀሐይ ሙሉ ገላዋን ገልጣ ጸዳሏን ትሰጣለች። በመሆኑም በስራ የደከመ ሰውነት ዘና፣ የታመመ ቀና ይልበታል፣ ልጅ አዋቂ የደስታ ነጋሪቱን ይጎስማል፣ የፍቅር ጽዋ ይጠጣል፣ የአእምሮ እርካታ ይነግሳል፣ በሁሉም ነገር ደስታ ይሰፍናል ወርሃ መስከረም በጥጋብና ደስታ ይጀመራል ። በዓሉ ከመግባቱ በፊት የራሱ የሆነ የሥራ ክፍፍል ኖሮት ቅድመ ዝግጅት የሚደረግበት መሆኑን ያነሱት ሃላፊው የቤተሰብ አባላት ሁሉም በየድርሻቸው ሃላፊነታቸውን እየተወጡ እንደሚጠብቁት ተናግረዋል። ለአብነትም ለበዓሉ መድመቅ በዓሉ ከመድረሱ ሦስትና አራት ወራት በፊት በአንድ ቤት ውስጥ የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት የሚወጡት ድርሻ አላቸው። የሃድያ አባቶች የያሆዴን የዘመን መለወጫ በዓል የሚያከብሩት በቅንጅት አማካኝነት ከአራት እስከ ስድስት ሰው በመሆን ተቀናጅተው ሰንጋ በመግዛት ነው። ለበዓሉ ሰንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ ማስቀመጥ የሚጀምሩትም ቀደም ብለው ነው ። እናቶች በዓሉ ከመቃረቡ ከሦስትና እና አራት ወራት በፊት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ለማጠራቀም በሚገቡት (ዊጆ) በተሰኘ ዕቁብ ቅቤ ማከማቸት ይጀምራሉ። በተጨማሪም ለስጋ መብያና ለአተካና መስሪያ የሚሆን እንሰት በመለየትና በመፋቅ፣ ቆጮ፣ ሜሬሮና፣ ቡላን ጨምሮ የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት የድርሻቸውን ይወጣሉ። የደረሱ ልጃገረዶች የቤቱን ወለል ቆፍረው ይደለድላሉ፣ የተለያዩ ውበት የሚሠጡ ቀለማትንና የተለያዩ ኖራዎችን በመጠቀም የቤቱን የውስጥና የውጭ ግርግዳን በመቀባት ያስውባሉ። ወጣቶች ከነሐሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚመርጡላቸውን ዛፍ፣ ግንድ ቆርጠው ለምግብ ማብሰያና ለደመራ የሚሆን ችቦ የማዘጋጀት ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ይቆያሉ። ከመስከረም መግቢያ ጀምሮ ያሉ የቅዳሜ ገበያዎች ስያሜ (መቻል ሜራ ) የእብድ ገበያ በመባል ይጠራሉ።እነዚህ የግብይት ቀናት ከዚህ ቀደም እንደነበሩ የግብይት ቀናት በተረጋጋ መንገድ የሚተገበሩ ባለመሆኑና በጠዋት ቆሞ በጊዜ የሚበተን ገበያ በመሆኑ (መቻል ሜራ) የእብድ ገቢያ የሚል ስያሜ አሰጥቶታል ነው ያሉት አባቶች ሰንጋ ገዝተው ለመብላት ባደራጁት (ቱታ) ቅንጃ አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ ወደ መቻል ሜራ (እብድ ገበያ) በመሔድ የሚፈልጉትን ሰንጋ ገዝተው ይመለሳሉ። ገንዘብ ያላስቀመጡና በወቅቱ ማግኘት የማይችሉ አባወራዎች በዓሉን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተደስተው እንዲያሳልፉ ሌላኛው አማራጭ (ሃባ) በመባል የሚታወቅና ምንም ገንዘብ የሌላቸው ሰዎች ለበዓሉ የሚሆን ሰንጋ በብድር የሚወስዱበት በብሔሩ ተወላጆች ዘንድ የኖረ የመተጋገዝና የመተሳሰብ እሴት አንዱ ነው። የሚፈልጉትን ሰንጋ ከመረጡ በኋላ እህል በሚደርስበት በታህሳስና በጥር ለመክፈል በዱቤ ይወስዳሉ። የበሬ ነጋዴውም ያለ ማንገራገር ሰንጋውን በመስጠት ወቅቱ ሲደርስ ገንዘቡን ለመውሰድ ተስማምቶ ይሰጥና ወቅቱን ጠብቆ ገንዘቡን ይወስዳል። በትውስት ተወስዶ ገንዘብ ያልከፈለ አባወራ ለቀጣይ የዘመን መለወጫ አይደርስም ተብሎ በብሔሩ ዘንድ ስለሚታመን በተስማሙበት ወቅት ገንዘቡን የመስጠት ግዴታቸው የተጠበቀ ነው። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ የመምሪያው ባለሙያ አቶ ይዲድያ ተስፋሁን እንዳሉት በዓሉ ያለው ለሌለው አካፍሎ በጋራ የሚበላበትና ወደ አዲስ ዘመን በጠንካራ አብሮነት የሚሻገሩበት ነው። በመሆኑም የያሆዴ በዓል በዜጎች መካከል ጠንካራ አንድነትና አብሮነትን መሰረት ያደረጉ ዕሴቶች ያሉበት መሆኑን አንስተው ለትውልድ ግንባታ የሚሆኑ ዕሴቶችን አጎልብቶ መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል ። ለበዓሉ ዋዜማ ከሚዘጋጁ ሁነቶች መካከል አተካና ልዩ ቦታ የሚሰጠው ነው። አተካና በተለይም ለዚህ በዓል ከዚህ ባሻገር ለትልልቅ እንግዶች ከሚዘጋጁ ምግቦች መካከል አንዱ ነው። አተካና ከወተት፣ ከቅቤ፣ አይብና ቡላ የሚዘጋጅና በበዓሉ የምግብ ፍላጎትን የሚከፍት ተበልቶ የማይጠገብ በእናቶች የሚዘጋጅ ጣፋጭ ምግብ ነው። የበዓሉ ዋዜማ አተካን ሂሞ (የአተካና ምሽት) የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን በዓሉን ለማክበር ከሩቅም ከቅርብም የተሰበሰበ ቤተሰብና እንግዶች በናፍቆት የሚመገቡት ምግብ ነው። በዚሁ ዕለት በአካባቢው ትልቅ የሚባል አባወራ (አዛውንት) ቤት ችቦ (ሳቴ ) ተዘጋጅቶ ማምሻውን አባቶች ወይም የሃገር ሽማግሌዎች የማቀጣጠያ (ጦምቦራ) ደመራ ማቀጣጠያ ይዘው ይወጣሉ። ከዚያም የአካባቢው ማህበረሰብም የሃገር ባህል ልብስ ለብሰው እንዲሁም ወጣቶች ተሰብስበው ያሆዴ ይጨፍራሉ። የሃገር ሽማግሌዎች ይመርቃሉ፤ ከዚያም የተዘጋጀውን ችቦ በእሳት ለኩሰው ያበራሉ። ይህም አዲስ ዘመን መግባቱን ማብሰርና ዓመቱ የብርሃን ዓመት እንዲሆን መልካም ምኞት የሚገለፅበት ነው። ደመራው ከተቀጣጠለ በኃላ ወጣቶች ያሆዴ (ኦሌ) ጭፈራ ሲጫወቱ ያነጋሉ። ይህ ጭፈራ ከያሆዴ በዓል ውጭ አይጨፈርም። ወጣት ደመቀ አባቴ የሆሳዕና ከተማ ነዋሪ ሲሆን ስለ በዓሉ አስተያየቱን ሲሰጥ ''በአባቶች ደመራው ከተቀጣጠለ በኃላ እኛ ወጣቶች ያሆዴ ....ያህዴ....ሆያ ሆ... /ኦሌ/ ጭፈራ እየተጫወትን እናነጋለን፤'' ይህ ጭፈራ ከያሆዴ በዓል ውጭ ስለማይጨፈር በዓሉን ቀን በጉጉት እንደሚጠብቁት ተናግሯል። ተራርቀው የቆየ ወዳጅ ዘመድ ተሰብስቦ ያለምንም ልዩነት ችግርም ካለ በዕርቅና ሰላምን በማውረድ የሚመጣው ዘመን የልምላሜና የስኬት እንዲሆን ተመራርቀው የሚለያዩበት በዓል በመሆኑ በተስፋ የሚጠብቁት እንደሆነ ነው ወጣቱ የሚናገረው። የበዓሉ እለት ለዕርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኃላ የባህል ሽማግሌዎች (ጋቢማ ) ሥርዓት ያከናውናሉ። ክዋኔውም የበሬውን ሻኛ በለጋ ቅቤና በሠርዶ ሳር በመቀባትና ወተት በማፍሰስ ይከናወናል። ይህም በሚከናወንበት ወቅትም ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሃገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን በማለት (ፋቴ) ዳግም ምርቃት ፈጽመው በሬው ይጣልና የዕርድ ሥርዓት ይካሔዳል። በዕለቱም ከታረደው ሥጋ ቅምሻ በጋራ ይበሉና ቀሪውን ለማህበሩ (ለቱታ) አባላት ክፍፍል ይፈፀማል። ከእርድ ሥርዓቱ በኃላ በማግስቱ ልጆች ወደ ወላጆቻቸው ዘራሮ የሚባል አበባ ይዘው እየጨፈሩ ያስማሉ -ይመረቃሉ የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባባላሉ፤ ከስጋውም ፣ከቦርዴውም ፣ ከአተካናውም የሚመገቡበት ክዋኔ (ሚክራ) በመባል ይታወቃል። ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ስጋና (ዘራሮ) አደይ አበባ ጭምር ይዘው የሚሔዱበት እንዲሁም ያላገቡ ወጣቶች ለትዳር የሚሆናቸውን አጋር የሚፈልጉበትና የሚያጩበት ባህልም ያለው ነው ያሆዴ ክብረ በዓል። ከእርድ ስነ ስርዓቱ በኋላ ከሶስት ሳምንታት እስከ ወር ለሚሆን ጊዜ የመጠያየቂያና የመረዳጃ ወቅት ይሆናል። የያሆዴ በዓል ያሉ ዕሴቶች ለህዝብ ትስስር፣ ጠንካራ የስራ ባህልና ዘላቂ ሰላም ግንባታ ያላቸውን ሚና ለማላቅ በልዩ ትኩረት ሊሰራ እንደምገባ የሚያነሱት በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ የህዝብ ግንኙነትና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የአቶ ዳንኤል ገዴ በዚህ ላይ በአከባቢው ያሉ የማህበረሰብ ልምዶችና ወጎች ለትውልድ እንዲሸጋገሩ መስራትና የሃገር በቀል ዕውቀትን ማጠናከር እንደምገበባ ተናግረዋል። በዚህ ረገድ የዋቸሞ ዩኒቨረሲቲ የሃድያን ብሔር የዘመን አቆጣጠር ታሪክ : ባህልና ቋንቋ እንዲሁም ሌሎች ዕሴቶች ተሰንደው እንዲቀመጡና ለማስተማሪያነት እንዲውሉ ለማስቻል በጥናትና ምርምርና የተደገፈ ስራ በመስራት ላይ መሆኑን አመላክተዋል። በተጨማሪም ባህሉ ይበልጥ እንዲታወቅና በዩኔስኮ ተመዝግቦ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚገባውን ጥቅም እንዲያመጣና ከቱሪዝም አንጻር ሚናውን እንዲጫወት ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የመኔ ሸድዬ ባሮ - የጠንካራ የስራ ባህል፣ የአብሮነትና የሰላም ተምሳሌት
Sep 20, 2023 511
በሽመልስ ጌታነህ (ኢዜአ) የመኔ ሸድዬ ባሮ የካፈቾ ብሄር ከአሮጌው ዘመን ወደ አዲሱ የሚሸጋገሩበት፣ የአዲስ ዘመን ብስራትና የዘመን መለወጫ በዓል ነው። በዓሉ የጠንካራ የስራ ባህል፣ የአብሮነትና የሰላም ተምሳሌት በዓል እንደሆነ ይነገርለታል። በዚህም የካፋ ብሄር ለዘመናት የገነባውና ጠንካራ የስራ ባህል፤ ተፈጥሮን የመጠበቅና የመንከባከብ እንዲሁም ከተለያዩ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ጋር ተቻችሎና ተፈቃቅሮ የሚኖር ሲሆን ቱባ ዕሴቱ ዛሬም ላለው ትውልድ መሰረት መሆኑን ያምኑበታል። የተለያዩ የታሪክ ድርሳናት እንደሚያሳዩት ከሆነ የካፋ ህዝብ ጠንካራ ንጉሳዊ ሥርዓት የነበረው፤ የታሪክና የቱባ ባህል ባለቤትም ነው። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የታሪክ ባለሙያና የሀገር ሽማግሌ አቶ አሰፋ ገብረማሪያም የካፈቾ ብሄር ዘመን መለወጫ በሃገሬው አጠራር ''የመኔ ሸድዬ ባሮ'' በዓል የካፋ ህዝብ ከሚያከብራቸው በርካታ በዓላት ውስጥ ትልቅ ሥፍራ የሚሰጠው መሆኑን አፅንኦት ሰጥተው ይናገራሉ። በዓሉ ያለውን ግዝፈት ሲያመለክቱ በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በውጭ ፀሐፍት ጭምር “ታላቁ በዓል ወይም (ግሬት ፌስቲቫል)” ተብሎ እንደሚጠራም ተናግረዋል። በዓሉ ታሪካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ዳራ ያለው ሲሆን ከጥንት ካፋ ንጉስ ጀምሮ በየአመቱ በድምቀት የሚከበር በዓል እንደሆነም ጠቁመዋል። የካፋ ህዝብ ከ14ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ከጎሳ መሪነት አንስቶ ጠንካራ የመንግስት መዋቅር የነበረው ታላቅ ህዝብ እንደሆነ ያነሱት አቶ አሰፋ፣ በዚህም በዓሉ በዘመኑ የነበሩ መንግስታት በዓል እንደነበረም አብራርተዋል። ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም የሚገመገምበት ጥሩ የሠራና የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገበ የሚሸለምበትና ለበለጠ ሥልጣን የሚታጭበት፤ ሰነፉ ደግሞ የሚወቀስበትና ስልጣኑ የሚነጠቅበት ታላቅ በዓልም ነው ብለዋል። ይህም በብሄሩ ዘንድ ለዘመናት የተሻገረ የጠንካራ የሥራ ባህል ግንባታ መሰረት ሆኖ የቆየ መሆኑን አንስተዋል። ይህ ሁሉ ሲከናወን በማህበረሰባዊ የህግ ተገዥነት መሰረት መሆኑ የተለየ እንደሚያደርገው ገልጸው ከሁሉ በፊት ሰላምን በማስቀደም መንግስትንና ህግን ማክበር እንዲሁም ህግ የሚመራው ህዝብ የበላይ መሆኑን አመላካች ሥርዓት መሆኑን አንስተዋል። በዓሉ ከአዝመራ ጋር የተያያዘ የዘመን አቆጣጠርን ተከትሎ እንደሚከበርም የታሪክ ባለሙያው አቶ አሰፋ ይገልጻሉ። እንደ ታሪክ ተመራማሪው ገለጻ የካፋ ህዝብ አብዛኛው አርሶ አደር አልፎም አርብቶ አደር ሲሆን ለአዝመራ የተለየ ትኩረት ይሰጣል፤ በዓሉ ሊከበር 77 ቀናት ሲቀሩት ህዝቡ የአዲስ ዘመን መለወጫ ብሎ ሃምሌ አንድ አዝመራውን እንደሚጀምርም ጠቁመዋል። የአዝመራ ወቅት ሊገባደድ 25 ቀናት ሲቀሩት (ከሼ ዋጦ) ብሎ አዝመራውን ያጠናቅቃል። ወቅቱም ጨለማው አልፎ በብርሃን የሚተካበት፤ ክረምቱ ለበጋ ቦታውን የሚለቅበት በመሆኑ አዲስ አመት መድረሱን ያሳውቃል። ያን ጊዜ በጥንት የካፋ ምክርቤት ከሚገኙ ሰባት የሚክረቾ አባላት ውስጥ አንዱ የሆነው አዲዬ ራሾ ፤ የንጉሱ መቀመጫ በሆነው ቦንጌ ሸምበቶ በዓሉን ለማክበር ከየአቅጣጫው ለሚመጣው ህዝብ መንገዶችን በማፅዳት እና ለወንዞች ድልድይ በማበጀት በዓሉ መድረሱን ያበስራል። ያን ጊዜ በዓሉን ለማክበር ህዝብ ከያለበት አቅጣጫ ወደ ቦንጌ ሸምበቶ ይተማል። ህዝቡ በቦንጌ ሸምበቶ ከተሰበሰበ በኋላም ንጉሱ በተገኙበት የእያንዳንዱ ወራፌ ራሾ ሥራ ይገመገማል፤ ጥሩ ሥራ የሠራ ጠንካራ መሪ ይሸለማል፤ ለበለጠ ስልጣንም ይታጫል፤ ሀላፊነቱን በተገቢ ሁኔታ ያልተወጣው ደግሞ ይመከራል፣ ይወቀሳል አልፎም ስልጣኑን ይነጠቃል። ዛሬም ሀገራችን ይህ አይነቱን ጠንካራ የሥራ ባህል አብዝታ ትሻለች፤ እንዲህ አይነት ሀገር በቀል ዕውቀቶች ትውልዱን በጠንካራ ሥነ-ምግባርና የሥራ ባህል ለመገንባት ትልቅ ድርሻ አላቸው። በተጨማሪም በዓሉ ቅሬታዎችን ለመፍታትና ሰላምን ለማጠናከር ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ፤ ቂምና ጥላቻን ይዞ ወደ ንጉሱ ፊት መቆምም ይሁን ወደ አዲሱ ዓመት መሻገር ነውር ተደርጎ የሚወሰድ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ወደ በዓሉ ከመምጣቱ አስቀድሞም ይሁን በበዓሉ ወቅት የተጣላ ይታረቃል፤ ጥላቻም በፍቅር ይተካል ብለዋል የታሪክ ተመራማሪው። እንዲህ አይነቱ ሀገር በቀል ዕውቀት ጠንካራ ባህል ለመገንባት፤ ቅራኔዎችን በሰላም ለመፍታትና ማህበራዊ ግኑኝነቶችን ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ ስላላቸው በትምህርት ሥርዓት ውስጥ አካቶ ማስተማርና ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ ይገባል ሲሉም ሃሳባቸውን አካፍለዋል። ሌላኛው የሀገር ሽማግሌና የካፋ፣ጫራ እና ናኦ የባህል ምክርቤት አባል አቶ ፀጋዬ ገብረማሪያም እንደሚሉት የካፋቾ ''የመኔ ሸድዬ ባሮ'' በዓል ማህበራዊ ግንኙነትን በማጠናከሩ ረገድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው በዓል ነው። ምክንያቱ ደግሞ፣ በዓሉን ለማክበር በአካባቢው ያሉ፣ በሌሎች የሃገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ እንዲሁም ባህር ማዶ የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆች የሚሰበሰቡበት ታላቅ በዓል ስለሆነ ነው ብለዋል። በዚህም የተራረቀ የሚገናኝበት፤ የተጠፋፋ የሚጠያየቅበት ሲሆን ህዝቡ በአንድ ላይ ተሰብስቦ በንጉሱ ተመርቆ፣ በልቶ ጠጥቶ እንዲሁም ተጫውቶ ወደ ቀጣዩ አመት በደስታና በታላቅ ተስፋ የሚሸጋገርበት እንደሆነም አብራርተዋል። ይህ ባህል በተለያዩ ምክንያቶች ከ120 ዓመታት በላይ ሳይከበር እንደቆየ የገለፁት አቶ ፀጋዬ ገብረማሪያም ዳግም መከበር ከጀመረበት ስምንት ዓመታት ወዲህ የነበረውን ታሪክና ባህል በሚያስቀጥል መልኩ በየዓመት በድምቀት እየተከበረ መሆኑንም አንስተዋል። ወጣቱ ትውልድ ባህሉንና ታሪኩን አውቆ እንዲኖርና እንዲያስቀጥል ግንዛቤ የመፍጠርና የማስተማር ሥራ በሰፊው እየተሠራ እንደሆነም ገልፀዋል። ከዚህ ባለፈም ባህሉንና ታሪኩን ለማስቀጠል የባህል ምክር ቤቱ የወረዳ የባህል ምክር ቤቶችን የማጠናከር፣ ታሪካዊ ቅርሶችን የመሰብሰብና የማደራጀት ሥራ እየሠራ ነውም ብለዋል። በዓሉ አንድነትን የሚያጠናክር፣ ጠንካራ የሥራ ባህልን የሚያበረታታ እና የተፈጥሮ ጥበቃን የሚያጠናክር በመሆኑ ከካፋ ብሔረሰብ በዓልነቱ ባለፈ የሀገርና የአለም ቅርስና ሀብት እንዲሆን ሰፊ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባም አቶ ፀጋዬ አሳስበዋል። የካፋቾ ዘመን መለወጫ በዓል (የመኔ ሸድዬ ባሮ) መሠረቱን ሳይለቅ ለትውልድ እንዲተላለፍ በዞን ደረጃ እየተሠራ መሆኑን የገለፁት የካፋ ዞን ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሃላፊ አቶ ተሾመ አምቦ ዘንድሮም ለዘጠነኛ ጊዜ በአደባባይ ለማክበር ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል። በዓሉ በሁሉም የካፋ ህዝብ በጋራ ያለምንም ልዩነት የሚከበር ታሪካዊ በዓል ሲሆን አለም አቀፋዊ እውቅና አግኝቶ በዩኔስኮ እንዲመዘገብ ለማስቻል ከተለያዩ ምሁራንና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመሆን የተለያዩ ጥናቶች እየተሠሩ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በበዓሉ ንጉሱ የተራቡትን የሚመግቡበት (ጮንጎ) የተሰኘ ስርዓት የሚፈፀምበትና የተጣሉ የሚታረቁበት ስርዓት እንደሚፈፀም የገለፁት አቶ ተሾመ አሁንም በዓሉ በየዓመቱ ሲከበር ይህ ሥርዓት ይከወናል ብለዋል። ቀጣይ ይህን በዓል በሰፊው አስተዋውቆ ወደ ቱሪዝም በማሳደግ ህዝቡ ከዘርፉ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችሉ ሥራዎች እንደተጀመሩም ሃላፊው ገልፀዋል። የዘንድሮው የ2016 ዓ.ም የካፊቾ ዘመን መለወጫ በዓል በቦንጋ ከተማ ከመስከረም 12 እስከ መስከረም 13/2016 ዓ.ም በፓናል ውይይትና በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበርም ጠቁመዋል።
አማራጭ ወደብ - የሎጅስቲክስ ዘርፍ ማነቆዎች ማቃለያ አማራጭ
Sep 17, 2023 169
አማራጭ ወደብ - የሎጅስቲክስ ዘርፍ ማነቆዎች ማቃለያ አማራጭ በሰለሞን ተሰራ የሎጂስቲክስ ምንነት ‘ሎጂስቲክስ’ የሚለው ቃል የመጣው "ሎጎስ" ከሚለው የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጓሜውም ረጅም መንገድ ማለት ነው። ሎጂስቲክስ በጥቅሉ ሲታይ የንግዱ ዓለም ኩባንያዎች የምርት አቅርቦት ሰንሰለት በትክክለኛው ጊዜ፣ መጠንና ቦታ ሂደቱን የማሳለጥ እንዲሁም ገበያና ገበያተኛን የማስተሳሰር ፅንሠ ሃሳብ ነው። የአንድን ምርትና አገልግሎት ከመነሻ እስከ መድረሻ ያለውን ውስብስብ ዑደት የሚያጠቃልል ሲሆን ንግድን አፋጥኖ እና አቀላጥፎ የማሳለጥና ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ጉዳይ እንደሆነም ይገለጻል። ሎጂስቲክስ ከምርት እስከ ስርጭት ሂደትን ያቀፈ ሲሆን ከትራንስፖርት (መጓጓዝ) ጋርም ቁርኝት አለው። ከአገር የወጪና ገቢ ምርቶች ፍሰትና መጓጓዝ ጋር የተሳሰረው ሎጂስቲክስ የአቅርቦት ሰንሰለት ፍጥነት፣ የምርትና ዕቃዎች ተገኝነትን፣ የአቅርቦት ዋስትና እና ሂደቶች አቅፎ ይዟል። አገራት በዓለም አቀፍ ንግድ ብቁና ተወዳዳሪ ለመሆን የሎጂስቲክስ አቅማቸው አይተኬ ሚና ይጫወታል። አገራትም ከግል ዘርፉ ይልቅ በብዛት በሎጂስቲክስ ዘርፉ የልማት ድርጅቶችን መስርተው በኃላፊነት የሚንቀሳቀሱትም ለዚህ ይመስላል። አያሌ ተዋናዮች ያሉበት ይህ ዘርፍ በመሰረተ ልማት ዝርጋታና የሎጂስቲክስ አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ታግዞ ለምርት ደህንነት መጠበቅና በተፈለገው ጊዜና ቦታ እንዲደርስ ለማድረግ ያስችላል። በሎጂስቲክስ እሴት ሰንሰለት ውስጥ የተዋዋዮች (ደንበኛና አገልግሎት ሰጭ) ውል፣ የምርት ምንጭና መጋዘን ቆይታ፣ የትራንስፖርት፣ የወደብ፣ የጉምሩክ፣ የዕቃዎች ክትትልና አተገባበር ተጠቃሽ አንኳር ጉዳዮች ናቸው። ሎጂስቲክስ ደንበኞች ፈጣንና ውጤታማ አገልግሎት አሰጣጥን ታሳቢ ያደረጉ የራሱ የአፈጻጸም መለኪያዎች አሉት። በዚህም የአገራት የሎጂስቲክስ ስርዓት በዓለም አቀፍ መለኪያዎች ተመዝኖ የአፈጻጸም ደረጃው ደካማነትና ጠንካራነት ይቀመጣል። የኢትዮጵያ ሎጂስቲክስ መልኮች የአንድን አገር ማህበረ ኢኮኖሚ ችግሮች ለመቅረፍ ብቁ እና ውጤታማ ሎጂስቲክስ ስርዓት መገንባት ያሻል። የወጪና ገቢ ንግድ ለማሳለጥ ቀልጣፋና ውጤታማ ሎጂስቲክስ ወሳኝ ነው። የባህር በር የሌላት ኢትዮጵያ በሎጂስቲክስ ዘርፍ አፈጻጸሟ ዝቅተኛ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ ናት። የሎጂስቲክስ ስርዓቷ ደካማ የአመራር ስርዓት ያለው፣ ቅንጅታዊ አሰራር የሚጎድለው፣ በሎጂስቲክስ መሰረተ ልማትና የማጓጓዝ አቅም ረገድ ደካማ እንደሆነ የተለያዩ ጥናቶች ያሳያሉ። ለአብነትም ከቀዳሚ ዓለም አቀፍ መስፈርቶች መካከል ከጊዜና ወጪ አንጻር ሲመዘን ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ይህም ከባሕር ወደብ አለመኖር ጋር ተዳምሮ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን እና አገራዊ ምጣኔ ሀብታዊ እምርታ ለማምጣት የራሱ አሉታዊ ተግዳሮት እንደሚያሳድር እሙን ነው። ከትራንዚት ጊዜ፣ ከመርከቦችና የዕቃዎች ወደብ ላይ ቆይታ እንዲሁም ጭነት ከማንሳት አቅምና መሰል የአፈጻጸም መለኪያዎች አኳያ ብዙ የቤት ስራ መኖሩን መረጃዎች ያሳያሉ። ይህም ዘርፉ ተወዳዳሪ እንዳይሆን ያደረገው ሲሆን ከዚህም ባሻገር ከአቅራቢዎች፣ የመርከብ ባለቤቶችና ሌሎች የንግድ አጋሮች ጋር በሚኖረው ግንኙነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳድራል። ኢትዮጵያ ከሕዝብ ብዛት ባሻገር በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ፈጣንና ግዙፍ ኢኮኖሚ ቢኖራትም የወጪና ገቢ ንግዷ በዋናነት በጅቡቲ ወደብ በኩል ይከናወናል፤ ይህም እያደገ ከመጣው የተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ አገልግሎት ፍላጎት አንጻር ትልቅ ማነቆ ሆኗል። በጥቅሉ የኢትዮጵያ የሎጂስቲክስስ ዘርፍ በሚፈለገው ደረጃ ያላደገ፣ የትራንስፖርት አገልግሎቱ ውጤታማነት ያነሰ በመሆኑ የሎጂስቲክስ ስርዓቱን ማዘመን ይጠይቃል። ሎጂስቲክስን ማዘመን የዓለማችን ሉላዊነት የአገራትን ብርቱ ውድድር አንሮታል። በዓለም ገበያ ተወዳዳሪና ተደራሽ የሆነ ምርትና አገልግሎት ለመስጠት የሎጂስቲክስ ዘርፉን ማዘመን አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ስርዓቷን ለማዘመን በጥልቅ ጥናት ላይ የተመሰረተ ብሔራዊ የሎጂስቲክስ ስትራቴጂክ ሰነድ አዘጋጅታለች። ይህም የተጠናከረ ሎጂስቲክስ ዕሴት ሰንሰለት በመዘርጋት ከመነሻው እስከ መድረሻ ያለውን የዕቃዎችን የማጓጓዝ ፍሰት በማቀላጠፍ ደንበኞች ምርታቸውን በቀላሉ እንዲከታተሉ ያስችላል። የዘርፉ ባለሙያዎች እንደሚሉት የሎጂስቲክስ ዘርፉን መለካት ካልተቻለ መቆጣጠር አይቻልም። መቆጣጠር ካልተቻለ ደግሞ ማስተዳደር አዳጋች ይሆናል። ኢትዮጵያ የባሕር በር ስለሌላት 90 በመቶ የሚሆነውን የንግድ እንቅስቃሴዋን በየብስ ትራንስፖርት ታከናውናለች። የኢትዮጵያ የሎጂስቲክስና ትራንስፖርት አገልግሎት ውጤታማነቱ በቂ ተርሚናል አገልግሎት የሌለው ነው። የዕቃዎች የወደብ ላይ ቆይታ ጊዜ መራዘም አንዱ ቁልፍ ችግር ነው። መርከቦች ጭነታቸውን ሳያራግፉ ባሕር ላይ ይቆያሉ። ይህ ደግሞ ከሎጂስቲክስ ጊዜና ወጪ አኳያ ኢኮኖሚያዊ ተጽእኖ አለው። በ2010 ዓ.ም የታተመው ብሔራዊ የሎጂስቲክስ ስትራቴጂክ ሰነድ እንደሚያመለክተው የኢትዮጵያ የገቢ ዕቃዎች ዓመታዊ መጠን ከ15 ሚሊዮን ቶን በላይ ደርሷል፡፡ በመንግስት አስመጪዎች ብቻ ወደ አገር ውስጥ የሚገባ ደረቅ ብትን ጭነት (የአፈር ማዳበሪያ፣ እህል፣ ከሰልና ስኳር) በዓመት በአማካይ ከ4 እስከ 8 ሚሊዮን ቶን ይገመታል። በወቅቱ ሸቀጦችን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ለጭነት ትራንስፖርት ብቻ (የባሕር፣ የወደብ አገልግሎትና የመንገድ) በዓመት በአማካይ 8 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ ይደረጋል፡፡ የሎጂስቲክስ ወጪ እና ብክነት እየጨመረ በመምጣቱ አላሰፈላጊ ወጪና የሀብት ብክነት መቀነስ ግድ ይላል። የሎጂስቲክስ ወጪ በአማካይ የአንድን አገር ጂዲፒ (የሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት ዕድገት) ከ14 በመቶ እስከ 35 በመቶ የሚሸፍን ነው። የኢትዮጵያ ወጪ ግን ከዚህም የላቀ ነው። ይህ የሆነበት ምክንያት የሎጂስቲክስ ስርዓቱን ፈጣንና ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ መምራት ባለመቻሉ እንደሆነ ይገለጻል። በዚህም ለትራንስፖርት፣ ለወደብና የመጋዘን ኪራይ፣ ለኮንቴይነር፣ ለግብይትና ሽያጭ፣ ለተለያዩ እቃዎችና ምርቶች እንዲሁም ለሌሎች የሎጅስቲክስ ወጪዎች ከፍተኛ ገንዘብ ታወጣለች። ይህ በየጊዜው እየናረ የመጣው የሎጂስቲክስ ዋጋ ዓለም አቀፍ የንግድ ተዋናዮችን ወጪ በመጨመር በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነትታቸው እንዲቀንስ ያደርጋል። የአገር እድገትንም ወደ ኋላ ይጎትታል። ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በሎጂስቲክስ ሰንሰለት የሚደረጉ ወጪዎች በምርቶች የመጨረሻ ዋጋ ላይ ከ20 እስከ 27 በመቶ ጭማሪ እንዲደረግ ምክንያት ይሆናሉ። በኢትዮጵያም የዕቃዎች የማጓጓዝ እና የጭነት ወጪ ከጎረቤት አገራት ጋር ሲነጻጸር የ60 በመቶ ብልጫ አለው። አማራጭ ወደቦችን ማማተር ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም ላይ 44 ሀገራት ወደብ የላቸውም። እነዚህ አገራት እንደየነባራዊ ሁኔታቸው የሎጂስቲክስ ስርዓት ዘርግተው ይንቀሳቀሳሉ። በተለይም የተሸጋጋሪ (የትራንዚት) ትራንስፖርት ስርዓት ዋንኛው አማራጭ አድርገው ይጠቀማሉ። ኢትዮጵያ የባሕር በር ካላቸው ጎረቤት አገራት ጋር የትራንዚት ትራንስፖርት ስርዓት ዘርግታ ትገለገላለች። ባቡርን ጨምሮ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ-ልማቶች ግንባታ አድርጋለች። ከጎረቤት አገራት ጋር የብዝሃ ወደብ አጠቃቀም ስምምነቶች ለማድረግም ጥሩ ትስስር እየፈጠረች ነው። የኢትዮጰያ የወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴ ወጪ መናር አማራጭ ወደቦችን መጠቀም አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንዲሆን አድርጎታል። ይህም የሎጂስቲክስ ስርዓቷን የማዘመንና የማሻሻል ግቧን ለማሳካት ያግዛል። በተለይም የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የንግድ ዕቃዎች መተላለፊያ ኮሪደሮችን በማስተሳሰር በኢኮኖሚ መስክ እምርታ ለማምጣት ያግዛሉ። የአማራጭ ወደቦች መኖር የባሕር ትራንስፖርትና ብዝሃ (Multimodal) የትራንስፖርት አገልግሎትን በማዘመን የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማሳጠር፣ የጊዜና ሀብት ብክነትን ለመቀነስ ያግዛል። በኢኮኖሚ ኮሪደሮች እና በአማራጭ የባሕር ወደቦች የሚደረግ ኢንቨስትመንት የኢትዮጵያን የወጪና ገቢ ንግድ በመጠንና በአይነት ለማሳለጥ ዋነኛው አማራጭ ተደርጎ እየተሰራ ይገኛል። በውስን ወደቦች ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ ብቻ ሳይሆን ከአገራት ጋር በሚደረጉ የንግድ ስምምነቶች ጠንካራ ትስስር ለመፍጠር ከማገዝ ባለፈ የመደራደር አቅሟንም ይጨምራል። ይህም የአገሪቱን ዘላቂ ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ሁነኛ ሚና ይኖረዋል። የኢትዮጵያ የገቢና ወጪ ንግድ በጅቡቲ ወደብ ላይ የተንጠለጠለ ነው። ይህ ደግሞ እየጨመረ የመጣውን ፍላጎት በቅጡ ለማስተናገድ አዳጋች ሆኗል። ስለሆነም የቀጣናው አገራትን ወደቦች በጋራ ተጠቃሚነት መርህ የማልማትና የመጠቀም እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል። የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ በቅርቡ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለውን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የሚሸከም የተቀላጠፈ የወጪና ገቢ ንግድ ሎጂስቲክስ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ አማራጭ ወደቦችን መጠቀም የሚያስችሉ ስራዎች እየከናወነች መሆኑንና ኢትዮጵያን የቀጣናው ሎጂስቲክስ ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አማራጭ ወደቦች የጅቡቲ ወደብን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቅረፍ እና ወጪንም ለማቃለል ዕድል ይፈጥራል። ከአማራጭ ወደቦችን መካከል የላሙ፣ ሞምባሳ እና በርበራ ይጠቀሳሉ። ኢትዮጵያ አማራጭ ወደቦች መጠቀሟ ከኬንያና ደቡብ ሱዳን ጋር በትራንስፖርት የሚያስተሳስረው 'ላፕሴት' ለተሰኘው ፕሮጀክት መሳለጥ ጉልህ ፋይዳ ይኖረዋል። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ብልፅግናዋን ለማረጋገጥና እያደገ የመጣውን ኢኮኖሚ ለማስተናገድ የሎጂስቲክስ ስርዓትን ማዘመንና ማስፋት ላይ በትኩረት እየሰራች መሆኑን አቶ ደንጌ ቦሩ ገልጸው ነበር። የብዝሀ ወደብ አጠቃቀም ለማስፋትም ቀጣይ ዲፕሎማሲያዊ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። በጎረቤት አገራት በኩል የሚገነቡ መሰረተ ልማቶች ሲጠናቀቁ በጋራ የመበልፀግ፣ አፍሪካን ለማስተሳሰር እንዲሁም ለኢትዮጵያ ትልቅ የገበያ ዕድል ለመፍጠር ሁነኛ ፋይዳ እንዳላቸውም ነው ያነሱት። የባቡርና የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታን ጨምሮ በላፕሴት ሰባት ፕሮጀክቶች አሉ። ኢትዮጵያ እስከ ሞያሌ ያለውን ፈጣን መንገድ ጨምሮ የበኩሏን ሃላፊነት ፈጽማለች። የላፕሴት ፕሮጀክት አማራጭ የወደብ አጠቃቀም ከማሳለጥ በተጨማሪ አፍሪካን እርስ በርስ በንግድ ለማስተሳሰር ግብ ይዞ ወደ ትግበራ ለገባው የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና ስኬት ጉልህ ሚና አለው። የሞጆ ደረቅ ወደብ ማስፋፊያን ጨምሮ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማትን በመዘርጋት ኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ማዕከል እንድትሆን እየተሰራ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። የሎጂስቲክስ አስተላላፊዎች የሎጂስቲክ ዘርፍ በርካታ ተዋናዮችንና ተቋማትን ያካተተ ሲሆን የባሕር፣ የየብስና የአየር ትራንስፖርት፣ ወደቦች፣ ጉምሩኮች፣ የፋይናንስ እና የንግዱ ዘርፍ ተቋማትን ለአብነት መጥቀስ ይቻላል። በኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ አስተላላፊዎች ዘርፉን ለማሻሻል በርካታ ስራዎች እንደተጀመሩ ይነሳል። ነገር ግን ከመሰረተ ልማት፣ ዓለም አቀፍ የማጓጓዝ ልምድ፣ የሎጂስቲክስ ተወዳዳሪነት፣ የዕቃዎች ክትትልና ቁጥጥር እና በጊዜ ውጤታማነት ሲመዘኑ የሎጅስቲክስ አገልግሎት ሰጪዎች ያላቸው ዓለም አቀፍ ልምድ በቂ የሚባል አይደለም። መንግስት ችግሩን ለመቅረፍ ሪፎርሞች እያካሄደ ይገኛል። ከሪፎርም ስራዎች መካከል የግል ባለሀብቶች በሎጂስቲክስ ዘርፉ በስፋት ማሳተፍ፣ ወቅቱን ታሳቢ ያደረጉና ተወዳዳሪነትን የሚጨምሩ ዓለም አቀፍ አሰራሮችን ተግባራዊ ማድረግ የሚሉት ይጠቀሳሉ። የሎጅስቲክስ ዘርፉን ለማዘመን መፍትሄ ተብው ከተቀመጡ አማራጮች መካከል የውጭ አገር አገልግሎት ሰጪዎች ከአገር ውስጥ ባለሀብቶች ጋር 49 በመቶ ድርሻ በመግዛት በጭነትና አስተላላፊነት ዘርፍ በጥምረት እንዲሰሩ ፈቃድ መስጠት የሚለው በጉልህ ይጠቀሳል። ይህም ደረጃውን የጠበቀና ዘመናዊ አስተዳደር ያለው የሎጂስቲክስ አገልግሎት ለመስጠትና የእውቀት ሽግግር ለማምጣት ይረዳል። ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሚገኙ የቴክኒክና የአቅም ግንባታ ድጋፎችን በመጠቀም የጉምሩክ ክሊራንስ መሰረተ ልማቶችን መገንባት እና የማስፋፊያ ስራዎችን ማከናወን ቀጣዩ የቤት ስራ ይሆናል። በሀገራችን የሎጂስቲክስ አገልግሎት ዙሪያ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች፣ የችግሮቹ መገለጫዎች፣ የችግሮቹ መንስኤዎችና እያስከተሉት ያለው ጉዳት ከሎጂስቲክስ ሥርዓቱ ጋር በቀጥታ የሚቆራኙ መሆኑ እሙን ነው። በመሆኑም የበርካታ ጉዳዮች ስብስብና ትስስር የሆነውን የሎጂስቲክስ ሥርዓት በሁለንተናዊ መልኩ ማዘመን ያስፈልጋል። በሎጂስቲክስ ሥርዓቱ ውስጥ ዘርፉ የሚመራበት ህግና ፖሊሲ፣ የተዘረጋው መሠረተ ልማት፣ ዘርፉን የሚመሩና የሚቆጣጠሩ ተቋማት አሠራር፣ የሎጂስቲክስ አገልግሎት ሰጪዎች፣ የሎጅስቲክስ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ብቃት፣ ዓቅምና መሰል ሁኔታዎች በልዩ ትኩረት ሊታዩና ሊሰራባቸው ይገባል። ይህን ማሳካት ሲቻልና አማራጭ ወደቦችን የማማተር ጉዳይ ሲታከልበት ፈጣን ልማትን ማረጋገጥና ከልማቱም ህዝቡ በየደረጃው ተጠቃሚ እንዲሆን በማድረግ አገራዊ ግቦችን ዕውን ማድረግ ይቻላል፡፡
“በጎነት ህይወት ነው፤ ለሰው መኖርን ብቻ ነው የሚጠይቀው" - ወጣት ተስፋ አለባቸው
Sep 8, 2023 331
ሐረር የአገር ልጅ የበጎ አድራጎት ማህበር በ2008 ዓ.ም በጎዳና ላይ የነበሩ 40 ልጆችን ከጎዳና ህይወት አንስቶ በመንከባከብ ነው ሥራውን የጀመረው። የማህበሩ መስራችና ሥራ አስኪያጅ ወጣት ተስፋ አለባቸው እንደገለጸው፣ በአሁኑ ወቅት ማህበሩ 166 ህጻናትን ተንከባክቦ እያስተማረና እያሳደገ ይገኛል። በጎነት "ህይወት ነው፤ መኖርን ብቻ ነው የሚጠይቀው” የሚለው ይህ ወጣት፣ "እየኖሩ ይህን ማድረግ ደግሞ መንፈስን ያድሳል፤ ህይወትም ይሰጣል" ይላል። "ለእኔ ፈጣሪ ካሟላልኝ እኔ ደግሞ ለሌሎች ማድረግ አለብኝ" የሚለው ወጣት ተስፋ፣ ማንኛውም ሰው ከራሱ ባለፈ ለሌላው የሚችለውን ማድረግ እንዳለበት ነው የገለጸው። ወጣት ተስፋ እንዳለው ማህበሩ በስምንት ዓመት የበጎ አድራጎት ሥራው ተንከባክቦ ያሳደጋቸውን ልጆች ለቁም ነገርም አብቅቷል። በክለብ ደረጃ አንድ የእግር ኳስ ተጫዋች እና ሁለት የመጀመሪያ ዲግሪ ምሩቃንን ያፈራ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ያሉ ልጆች መኖራቸውን ተናግሯል። ከዚህ በተጨማሪ ማህበሩ 208 ህጻናትን ከወላጆቻቸውና ከቤተሰቦቻቸው ጋር በማገናኘት ህጻናቱ የተስተካከለ ህይወት እንዲኖሩ ማድረጉን ነው የገለጸው። ማህበሩ በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጭ ካሉ በጎ ፍቃደኞች ጋር በመተባበር እንደሚሰራ የጠቀሰው ወጣት ተስፋ፣ በዚህም ለህጻናቱ የሚያስፈልጋቸውን በማሟላት እየተንከባከበ መሆኑን ተናግሯል። ማህበሩ እያከናወናቸው ባሉ በጎ ተግባራት ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዲሁም ከክልሉ ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት በቅርቡ ድጋፍ ማግኘቱንም ነው ወጣቱ የገለጸው። ማህበሩ በቅርቡ በከፈተው ሁለተኛ ቅርንጫፉም ታዳጊ ህጻናትን ከሱስ ነጻ በማድረግ መልሶ ከቤተሰብ ጋር የማገናኘት ሥራም እያከናወነ ይገኛል። "ህጻናትን ለመታደግ በማከናውነው ሥራ ደስተኛ ብሆንም የሰራሁት ስራ የሚያኩራራ አይደለም" የሚለው ወጣት ተስፋ፣ በቀጣይ ድጋፍ የሚያደርግላቸው ልጆች ሥራ መያዝ እንዲችሉ የሞያ ማሰልጠኛ ተቋም ለመክፈት አቅዶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ተናግሯል። ወደ ተቋሙ ከመጣሁ ስድስት ዓመት ሆኖኛል ያለው ወጣት ሃምዲ አልይ በበኩሉ፣ በአሁኑ ወቅት 12ኛ ክፍል መድረሱንና ለቤተሰቦቹም ተስፋን ሰንቆ እየተማረ መሆኑን ነው የገለጸው። "በጎነት በፈጣሪም የሚያስመሰግን ተግባር በመሆኑ ተስፋ የጀመረውን የበጎ አድራጎት ስራ ሳድግ ለማስቀጠል ራዕይ ይዤ ተነስቻለሁ" ብሏል። ወደማህበሩ ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ ደስተኛ ህይወት እየመሩ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ ተማሪ አይሻ አብዱላሂ እና ሳሙኤል እስራኤል ናቸው። በአሁኑ ወቅት የ8ኛ ክፍል ተማሪ እንደሆነች የገለጸችው ተማሪ አይሻ ወደማህበሩ ከመጣች በኋላ የደረጃ ተማሪ መሆኗን ተናግራለች። መልካምነት መልሶ ለራስ የሚደርስ ተግባር በመሆኑ ወደፊት በበጎ አድራጎት ሥራ ላይ ለመሰማራት መነሳሳቷን ጠቁማለች። በበጎ አድራጎት ሲኖር ደስተኛ መሆኑን የተናገረው ህጻን ሳሙኤል እስራኤል በበኩሉ የምፈልገውን ነገር ከማህበሩ እያገኘሁ ነው ብሏል። በቀጣይ ውጤታማ ተማሪ ሆኖ የተሻለ ደረጃ ላይ ለመድረስ ትምህርቱን በአግባቡ እየተከታተለ መሆኑን ተናግሯል። ከአንድ ወር በፊት ለሐረር የአገር ልጅ የበጎ አድራጎት ማህበር የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ያደረጉት የባህልና ስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ቀጀላ መርዳሳ በወቅቱ እንዳሉት የበጎ ፈቃድ ሥራ በራስ ጥረት ተነሳስቶ ሌላውን የማገዝ ተግባር ነው። በጎነት ለሰው ልጅ ህይወት መራራትና ማሰብ በመሆኑ እንደ ሐረር የአገር ልጅ በጎ አድራጎት ያሉ ማህበራት ሊጠናከሩ ይገባል ሲሉም አመልክተዋል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 4858
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 9849
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት። እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 3393
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል። “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 4176
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
መጣጥፍ
የዕልፍ ሕጻናትን ዕጣ ፈንታ ከሞት ወደ ሕይወት የለወጠው ወጣት ላሌ ላቡኮ
Sep 8, 2023 454
በሀገራችን በርካታ አካባቢዎች የታዳጊዎችን ተስፋና ህልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የሚገዳደሩ ከባህላዊ እምነት ጋር የተቆራኙ አይነተ ብዙ ጎጂ ባህላዊና ልማዳዊ ድርጊቶች እና ክዋኔዎች አሉ። ለአብነትም ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የተለመደው እና ከህጻናት ጥርስ አበቃቅል ጋር የተያያዘው ’ሚንጊ' የሚሰኘው ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ይጠቀሳል። በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣቸዋል። ከዚህ ጋር በማገናኘትም የሚወለዱ ህጻናት የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ከሆነ እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥመዋል። ይህ ልማድ “ሚንጊ” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን አያሌ ህጻናትን ቀጥፏል። ይህ ብቻም ሳይሆን የማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። ሚንጊ ተብለው የተፈረጁ ህጻናት በማህበረሰቡ ዘንድ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… እንደሚያመጡ ስለሚቆጠር ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል ዕጣ ይገጥማቸዋል። ሚንጊንና መሰል በየማህበረሰቡ ዘንድ ለዘመናት የተለመዱ ጎጂ ድርጊቶችን ለማስቀረት እና ማህበረሰብ አቀፍ ለውጥ ለማምጣት ግን ውስብስብ እና ጊዜ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው። ላሌ ላቡኮና መሰል ብርቱና አርቆ አሳቢ ሰዎች ግን ባደጉበት ብርቱ ጥረት የማህብረሰብን አስተሳስብ በመለወጥ ለዘመናት ለሚከወኑ ውስብስብ ችግሮችን መፍትኤ መስጠት ችለዋል። ላሌ ላቡኮ በተወለደበት ቀዬ እና አባል በሆነበት ደመ ከልብ ሆነው የሚቀሩ ህጻናትን ዕጣ ፈንታ ከወንዝ፣ ከገደልና ከጫካ ከመጣል ተርፈው ለወግና ማዕረግ እንዲበቁ አስችላል። በአጉል ባህል ሕይወታቸውን የሚነጠቁ ዕልፍ አዕላፍ ህጻናት ነፍስ እንዲዘሩ በማድረግ ትውልድ ያሻገረ፣ ማህበረሰብን የለወጠ አርበኛ ነው። ላሌ ላቡኮ ይህን ነባር ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ለመቃወምና መፍትሄ ለማምጣት ያነሳሳው ሁለት እህቶቹን ጨምሮ ምንም ነፍስ ያላወቁ ሕጻናት በሚንጊነት ተፈርጀው ሲቀጠፉ በማየቱና በመስማቱ እንደሆነ ይናገራል። ከ17 ዓመታት በፊት ‘ኦሞ ቻይልድ’ በሚል ባቋቋመው ድርጅት 'ሚንጊ' የተባሉ 58 ሕፃናትን ከገዳዮች ፈልቅቆ ከሕልፈት ወደ ሕይወት ለውጧል፣ ለቁም ነገር ለማብቃትም እያስተማራቸው ይገኛል። እህቶቹን ጨምሮ የትውልድ መንደሩ ሕጻናትን ሕይወት ለመቀጠፍ የዳረጋቸው የሚንጊ ድርጊት የሚፈጸመው፣ በማህበረሰቡ ዕውቀት ማነስ ነው ብሎ ያምናል። በዚህም ይህን አስከፊ ድርጊት እና አስተሳሰብ ለመቀየር ቆርጦ በመነሳቱ ቤተሰቡን ጨምሮ ከማህበረሰቡ መገለል እስከ ማስፈራሪያ ጥቃቶች አስተናግዷል። እርሱ ግን ፈተናዎች ሳይበግሩት በዓላማው ጸንቶ፣ ትዕግስትና ብልሃት ተላብሶ ሸውራራ ማህበረሰብ አቀፍ አመለካከቶችን መስበር ችሏል። የሚንጊ ባህል አሁንም ሙሉ ለሙሉ እንዳልተቀረፈ የሚናገረው ላሌ፣ ስር ነቀል የአስተሳስብ ለውጥ ለማምጣት ለህብረተሰቡ አሁንም ብርቱ ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎች እንደሚገቡ ገልጿል። ላሌ በመሰረተው ድርጅት ከሚማሩ ሕጻናት ባሻገር ከ300 በላይ ህጻናት ከቤተሰባቸው ዘንድ ሆነው ለመማር እንዲችለኩ ማድረጉንም ይናገራል። ሕፃናቱን ከሞት አፋፍ ታድጎ ከራሳቸው ሕልውና ባለፈ ለቁም ነገር እንዲበቁና ለሀገርና ለወገን የሚበጁ ሰዎች እንዲሆኑ በመስራቱ አዕምራዊ እርካታ እንደሚሰማው ይገልጻል። ላሌ የሚንጊን ጎጂ ድርጊት ከመታደጉ በተጨማሪ በደቡብ ኦሞ ትምህርት ቤት ገንብቶ ከ700 በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል። ናሽናል ጂኦግራፊ፣ ቴድ ቶክ፣ የሰብዓዊ መብቶች ተቋም እና የበጎ ሰው ሽልማት ድርጅት የላሌን ትውልድ የመታደግ ተግባር ዕውቅና ከሰጡት ወስጥ ይጠቀሳሉ።
የ19ኛ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዎና ደጋሹ የቡዳፔስት ስታዲየም
Aug 22, 2023 957
የቡዳፔስቱ ናሽናል አትሌቲክስ ሴንተር ስታዲየም 700 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በሚጠጋ ገንዘብ ተገንብቶ ዝግጅቱን አሟልቶ እንዲያስተናግድ በሚያስችል ቁመና ላይ የደረሰው ከ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዎና መጀመር ቀደም ብሎ ነው። የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከኦሊምፒክ ጨዋታዎች ቀጥሎ የሚጠቀስ ግዙፍ የሆነ ዓለም አቀፍ የስፖርት ሁነት ነው። “የስፖርቶች ንጉስ” የሆነ ውድድር ነው የሚሉትም አልጠፉም። አገራት ለሻምፒዮናው ከሚያደርጉት ሽር ጉድ ባለፈ እንደዚህ ዓይነት ስፖርታዊ ውድድሮችን ለማዘጋጀት የሚያደርጉት ፉክክር ቀላል የሚባል አይደለም። ዓለም አቀፍ የስፖርት ሁነቶችን ለማዘጋጀት ሚሊዮኖችን አለፍ ካለም ቢሊዮኖችን ወጪ ያደርጋሉ። አገራት ውድድሩን ከማስተናገድ ባለፈ ታሪካቸውንና ባህላቸውን ጨምሮ ያላቸውን መልካም ገጽታ ለመገንባት ይጠቀሙበታል ። 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከቀናት በፊት በማዕከላዊ አውሮፓዊቷ አገር ሃንጋሪ ተጀምሯል። በሻምፒዮናው ላይ ከ200 አገራት በላይ የተወጣጡ ከሁለት ሺህ በላይ አትሌቶች እየሳተፋ ይገኛሉ። ሻምፒዮናው ቡዳፔስት በሚገኘው ናሽናል አትሌቲክስ ሴንተር ስታዲየም በመካሄድ ላይ ይገኛል። ነሐሴ 13/2015 የሻምፒዮናው ደማቅ የመክፈቻ ስነ ስርዓት በዚሁ ስታዲየም ተከናውኗል። በመክፈቻ ስነ ስርዓቱ ላይ የሀንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን፣የሀንጋሪ ፕሬዝዳንት ካታሊን ኖቫክ፣ የተርኪዬ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ታይብ ኤርዶጋን፣ የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዝዳንት ሰባስቲያን ኮ፣የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ፕሬዝዳንት አሌክሳንዳር ሴፈሪንና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች መገኘታቸው ይትወሳል። እኛም ሻምፒዮናው እየተካሄደበት ስላለው ስታዲየም መረጃዎችን ልናካፍላችሁ ወደናል። ናሽናል አትሌቲክስ ሴንተር ስታዲየም የግንባታ መሰረት ድንጋይ እ.አ.አ በ2020 ተጥሎ ግንባታው የተጀመረው እ.አ.አ 2021 መግቢያ ላይ ነበር። ስታዲየሙ ግንባታው ከመጀመሩ በፊት 40 ሺህ ተመልካች እንደሚያስተናግድ ይፋ ተደርጎም ነበር። ይሁንና የግንባታው ስራ ሲጀመር በሚይዘው የተመልካች ብዛት ላይ ክለሳ ተደርጎ ስታዲየሙ 36 ሺህ ተመልካች በሚያስተናግድ መልኩ ግንባታው እንደሚቀጥል ተገለጸ። በዚሁ መሰረት የላይኛው የስታዲየም ክፍል 22 ሺህ እንዲሁም የታችኛው ክፍል 14 ሺህ ተመልካች እንዲደሚይዝ የሃንጋሪ መንግስት አስታወቀ። የስታዲየሙ ግንባታ ከእ.አ.አ 2022 አጋማሽ ዓመት በኋላ ተጠናቆ በዛው ዓመት ማብቂያ ለዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናው የትኬት ሽያጭ መከናወን ጀመረ። ስታዲየሙ እ.አ.አ ሰኔ 16/2023 የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዝዳንት ሰባስቲያን ኮን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተመርቆ በይፋ ስራ ጀመረ። አጠቃላይ ለስታዲየሙ ግንባታ 700 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚጠጋ ወጪ መደረጉንና ይህም ሀንጋሪ ለስፖርት መሰረተ ልማት ግንባታ ያወጣችው ትልቁ ገንዘብ ሆኖ ተመዝግቧል። ከዚህ ቀደም ሀንጋሪ ለስፖርት መሰረተ ልማት ያወጣችው ትልቁ ወጪ ከ67 ሺህ በላይ ተመልካች ለሚያስተናግደው ፑሽካሽ አሬና ስታዲየም ሲሆን ለስታዲየሙ ግንባታ 600 ሚሊዮን ዶላር ፈሰስ እንደተደረገበት መረጃዎች ያመለክታሉ። የውድድሩ መሮጫ መም “The Crown of the Queen of Sports” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን ስያሜው የመነጨው አትሌቲክስ የሁሉ ስፖርቶች ቁንጮ ነው ከሚል እሳቤ መሆኑን ተገልጿል። ናሽናል አትሌቲክስ ሴንተር ስታዲየምን የገነቡት ‘ዛኤቭ ኢፕቶይፓሪ ዜድአርቲ’ (ZÁÉV Építőipari Zrt) ‘ማግያር ኢፒቶ ዜድአርቲ’ (Magyar Építő Zrt) የተሰኙ ተቋራጮች ናቸው። ስታዲየሙ የሚገኘው በደቡብ ማዕካላዊ ቡዳፔስት እና በአውሮፓ በትልቅነቱ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው የዳኑብ ወንዝ ምስራቃዊ አቅጣጫ ነው። ከዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናው በኋላ የስታዲየሙ የመያዝ አቅም ወደ 14 ሺህ ዝቅ እንደሚልና በተመልካቾች በኩል ያሉ ጊዜያዊ የስታዲየሙ የላይኛው ክፍል መሰረተ ልማቶች እንደሚነቀሉም ተገልጿል። የዓለም የአትሌቲክስ አፍቃሪያን በስታዲየሙ በቀጣይ ቀናት በሚካሄዱ የአትሌቲክስና የሜዳ ተግባራት ውድድሮችን በጉጉት መከታተላቸውን ይቀጥላሉ። የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናው እስከ ነሐሴ 21/2015 ይቆያል። በሃንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ በሚገኘው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የአራተኛ ቀን ውሎ የኢትዮጵያ አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ይካሄዳሉ። ከምሽቱ 4 ሰአት ከ30 የ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች አትሌት ብርቄ ኃየሎም እና አትሌት ድርቤ ወልተጂ ይሳተፋሉ። አትሌት ብርቄ 3 ደቂቃ ከ54 ሴኮንድ ከ94 ማይክሮ ሴኮንድ እና አትሌት 3 ደቂቃ ከ55 ሴኮንድ ከ8 ማይክሮ ሴኮንድ በርቀቱ ያላቸው የግል ምርጥ ሰዓት ነው። በ3 ደቂቃ ከ49 ሴኮንድ ከ11 ማይክሮ ሴኮንድ የርቀቱ የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት የሆነችው የ29 ዓመቷ ኬንያዊ አትሌት ፌዝ ኪፕዬጎን ውድድሩን የማሸነፍ የቅድሚያ ግምት አግኝታለች። አትሌቷ የ1 ማይል እና የ5 ሺህ ሜትር የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤትም ናት። በዚህ ውድድር ላይ በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት ኔዘርላንዳዊ የሆነችው አትሌት ሲፋን ሀሰን ትወዳደራለች። ከምሽቱ 4 ሰዓት ከ42 ደቂቃ በ3 ሜትር መሰናክል ወንዶች ፍጻሜ የርቀቱ የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት አትሌት ለሜቻ ግርማና አትሌት ጌትነት ዋለ ይወዳደራሉ። አትሌት ለሜቻ በሰኔ ወር 2015 በፓሪስ በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል 7 ደቂቃ ከ52 ሴኮንድ ከ11 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት በኳታሩ አትሌት ሳይፍ ሰኢድ ሻሂን ለ19ኝ ተይዞ የነበረውን የርቀቱን ክብረ ወሰን በ1 ሴኮንድ ከ52 ማይክሮ ሴኮንድ ማሻሻሉ ይታወቃል። አትሌት ጌትነት 8 ደቂቃ ከ5 ሴኮንድ ከ15 ማይክሮ ሴኮንድ በርቀቱ ይግል ምርጥ ሰአቱ ነው። በውድድሩ አትሌት ለሜቻ እና የሞሮኮው አትሌት ሶፊያን ኤል ባካሊ የሚያደርጉት ፉክክር በስፖርት ቤተሰቡ ከወዲሁ በጉጉት ይጠበቃል። ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው እስከ አሁን 1 የወርቅ፣1 የብር እና 2 የነሐስ በአጠቃላይ አራት ሜዳሊያዎችን በማግኘት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።