ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን የምርምርና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅበታል
Dec 27, 2025 13
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያሳልጡ የምርምርና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ማጠናከር እንዳለበት ተገለጸ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የቀድሞ ተማሪዎች የቤተሰብ ቀን እየተከበረ ነው። በመርኃ-ግብሩ ላይ የቀድሞ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የዛሬዎች አንጋፋ ምሁራን፣ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የተጠናቀቀው የ2017 ዓ.ም እና የዘንድሮው ዓመት ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ነው። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በራስ ገዝነት ሂደት ወደ ፊት የሚያሻግሩ የለውጥ ስራዎች የተጀመሩበት ወቅት መሆኑን አንስተዋል። በዘንድሮው ዓመት በኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ ያበረከተውን አስተዋጽኦ የሚዘክርበትና አሻራውን የሚያሳይበት 75ኛ ዓመት በዓሉን እያከበሩ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች አቅጣጫ የተለሙና እየተለሙ ያሉ ዕውቅ ምሁራንን ያፈራ አንጋፋ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ውብ ህብረ-ቀለም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይንጸባረቃል ያሉት ሚኒስትሯ፤ ህብረ ቀለሙ አንድነት፣ ትብብርና አብሮነትን እንደሚያጠናክር ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው በዓለም ስመ-ጥር ምሁራንን ያፈራው በአንጋፋነቱ ብቻ ሳይሆን በአስተዳደር ብቃቱ ጭምር መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የለውጥ ሞተር የሆኑ ምሩቃንን ያፈራ መሆኑንም አንስተዋል። የዩኒቨርስቲው የቀድሞ ተማሪዎች የቤተሰብ ቀንም የጋራ ቤታችንን በማደስ በወደፊት አቅጣጫው ላይ አሻራችንን ማስቀመጥ ያግዛል ብለዋል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያዊነትን ያወቅንበት ትልቅ የህይወት ምዕራፍ ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ ለዛሬ ማንነታችን መሰረት የጣሉ አስደናቂ የሀገር ባለውለታ መምህራን ቁርጠኝነት የጎላ እንደነበር ተናግረዋል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልጽግና ጉዙ የሚያሳልጡ የምርምር፣ የማህበረሰብ አገልግሎትና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባው ገልጸው፤ ለዚህ ሁላችንም መደገፍ አለብን ብለዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ከ75 ዓመት በፊት በ50 ተማሪዎች ማስተማርን አሀዱ ብሎ የጀመረው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ75 ዓመት ጉዞው 300 ሺህ ተማሪዎችን አስመርቋል ብለዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አሻራ በሁሉም ዘርፍ ይታያል ያሉት ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ፤ በጥናትና ምርምር ሀገር አሻግረዋል በማስተማር ትውልድ ቀርጸዋል ብለዋል። ሀገር በመምራት ለውጥ አምጥተዋል፣ የንግድ ተቋማትን መርተው ባለጸጋ ሆነዋል፣ በህክምና ተሰማርተው ሚሊዮኖችን ፈውሰዋል ብለዋል። ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ በመወከል ብሔራዊ ጥቅሟን ያስከበሩ ዲፕሎማቶችን መፍጠሩንም ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሩቃን በኢትዮጵያ ለውጥ ታላቅ አሻራ አኑረዋል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ በዓለም ገናና ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ በጋራ እንስራ የሚል ጥሪ አስተላልፈዋል።
ልማት እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን- የምክር ቤት አባላት
Dec 27, 2025 20
ባሕርዳር ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት ልማት እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ገለጹ። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል ከሰሜን ጎንደር ዞን ድልይብዛ ምርጫ ክልል የተወከሉት አቶ ብርሃኑ ዘውዱ ፤ በክልሉ ሰላምን ለማዝለቅ የሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎና ድጋፍ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል። ችግር በውይይት እንጂ በግጭት እንደማይፈታ በመገንዘብ የቀሩ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተከትለው እንዲመለሱ መክረዋል። የክልሉን ሰላም በማዝለቅ ልማቱ ይበልጥ እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። ከደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ምርጫ ክልል በምክር ቤቱ የተወከሉት ወይዘሮ ፋጡማ ይማም በበኩላቸው፤ ሰላምን ለማዝለቅ የምክር ቤት አባላት ድርብ ኃላፊነት አለብን ብለዋል። አሁን በክልሉ የሰፈነውን ሰላም ለማዝለቅ ከሕዝቡ ጋር በመሆን ድጋፍና ክትትላቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል አቶ አሰፋ ይመር፤ የሰላም አማራጭን ተከትለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች እንደሚበረታቱና ይህም ሰላምን ለማፅናት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል። የቀሩ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ የተጀመረውን ስራ ለማጠናከር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲዳማ ቡናን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈ
Dec 27, 2025 26
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲዳማ ቡናን 5 ለ 0 ረትቷል። በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሸገር ከተማን አሸነፈ በአበበ በቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ንግስት በቀለ ሁለት ግቦችን ስታስቆጥር እሙሽ ዳንኤል፣ መሳይ ተመስገን እና ረድኤት አስረሳኸኝ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሊጉ 10ኛ ድሉን ያስመዘገበው የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ32 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ከሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ዝቅ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሲዳማ ቡና በ18 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። የቡድኖቹ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ በነበረው ተሳትፎ ምክንያት የተራዘመ ነው። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በያዝነው ሳምንት የመጀመሪያ ተስተካካይ ጨዋታውን ከሸገር ከተማ አድርጎ 2 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ዙር መርሃ ግብር መጠናቀቁ ይታወቃል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ ሊሰጠው ይገባል
Dec 27, 2025 23
አክሱም፤ ታህሳስ 18/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ ሊሰጠው ይገባል ሲሉ በአክሱም ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ። ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነቷን በውል ባልታወቀ ምክንያት እንዲታጣ ተደርጓል። የባህር በር ማጣት የብዙዎች ቁጭት ሆኖ ቆይቶ አሁን ላይ የትውልድ ጥያቄና የሀገር የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ እንዲያገኝ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ግልጽ የሆኑ ምክንያቶች ያሉት ሲሆን የሀገሪቱ የምጣኔ ሃብት እድገትና የህዝብ ቁጥር መጨመር፣ የጂኦ ፖለቲካዊ ሁኔታ፣ የታሪክና የህግ ምክንያቶችን መጥቀስ ይቻላል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ የኢዜአ ሪፖርተር ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ከመሰረታዊ አገልግሎቱ ባለፈ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል መምህር በረከት ሀይለ፤ ኢትዮጵያ ግዙፍ ኢኮኖሚ እና ብዙ ህዝብ ይዛ የባህር በር ልታጣ አይገባም ብለዋል። ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር በቅርብ ርቀት ላይ እያለች ሌሎች ከሩቅ መጥተው የሚጠቀሙበትን ባህር መንፈግ ከህግም ሆነ ከሞራል አንፃር ተቀባይነት የሌለው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት መሆን እንዳለባት ገልጸው ይህንንም ማሳካት የትውልዱ አደራ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ መምህርት ፍረወይኒ ፍስሃ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የመኖርና ያለመኖር ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል። የባህር በር ጥያቄው የታሪክ እውነታና የህግ ተቀባይነት ያለው፣ መልክዓ ምድርንና ፍትሃዊነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸው በሁሉም መመዘኛዎች የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት መብት ሊከበር ይገባል ብለዋል። በመሆኑም የትውልድ ጥያቄ የሆነው የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ምላሽ ማግኘት ያለበት የህዝብ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። በአክሱም ከተማ ነዋውና የህግ ባለሙያው አብራሃም አለማ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በህግም ይሁን በታሪክ ተቀባይነት ያለው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት ኢትዮጵያ በአቅራቢያዋ ባለው ቀይ ባህር የባህር በር ባለቤትነት መብቷ ሊከበር ግድ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ውድድሩ የከተማዋን ነዋሪዎች ማህበራዊ ትስስር ለማጎልበት ያግዛል
Dec 27, 2025 23
ነቀምቴ ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ በተካሄደው ስፖርት ለሰላም ውድድር የከተማዋ ነዋሪዎች ማህበራዊ ትስስራቸውን ለማጎልበት ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ማሳየታቸው ተገለጸ፡፡ በኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና በነቀምቴ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪነት የስፖርት ለሰላም የሩጫ ውድድር ዛሬ በነቀምቴ ከተማ ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ በኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ማርቆስ ገነቲ፣ የምሥራቅ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ወጋሪ ነገራ፣ የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሰረት ሀይሉ ፣ የወለጋ ዩኒቨርስቲ መምህራን እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። ሩጫውን ያስጀመረው የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ማርቆስ ገነቲ ባስተላለፈው መልዕክት፤ የሰላም ሩጫው የተካሄደው ሰላምን ለማፅናት በሚደረገው ጥረት የሕብረተሰቡን የጎላ ተሳትፎ ለማስገንዘብ ነው ብሏል። በሰላም ሩጫውም ነዋሪዎቹ ሰላምን ጠብቆ ለማዝለቅ፣ ልማትን ለማስቀጠልና ማህበራዊ ትስስራቸውን ለማጎልበት ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ማሳየታቸውን ተናግሯል። የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሰረት ሀይሉ በበኩላቸው፤ አስተዳደሩ የሕግ የበላይነት በማስከበር ሰላምን በማፅናት የሕብረተሰቡን የመሰረተ ልማት ፍላጎት ለማሟላት አበክሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ የተካሄደው የሰላም ሩጫም በአካባቢው ያለውን ሰላምና ልማትን አጉልቶ ያንጸባረቀ መሆኑን ገልጸዋል። ከተማዋ በፈጣን የእድገት ጎዳና ላይ ናት ያሉት ከንቲባው፤ ይህንን እውነታ ለማሳየት የሰላም ሩጫው የማይተካ ድርሻ አለው ብለዋል። የነቀምቴ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች በሰላም ሩጫው በመሳተፍ ከመንግስት ጋር በመቀናጀት ልማትና ሰላምን ለማፅናት ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋፍ ማረጋገጣቸውን አንስተዋል። 10 ኪሎ ሜትር በሸፈነው ሩጫ ላይ የተሳተፈችው ከኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ሳጅን አትሌት ጉተኒ ሻንቆ ፤ በወለጋ አካባቢ ያለውን ሰላምና ልማት በማድነቅ የሚበረታታ መሆኑን ተናግራለች። ዛሬ የተካሄደው ስፖርታዊ ውድድር የአካባቢውን ትክክለኛ ገጽታ ለማሳየት እንደሚያግዝም ጠቁማለች።
ፖለቲካ
ልማት እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን- የምክር ቤት አባላት
Dec 27, 2025 20
ባሕርዳር ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት ልማት እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ገለጹ። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል ከሰሜን ጎንደር ዞን ድልይብዛ ምርጫ ክልል የተወከሉት አቶ ብርሃኑ ዘውዱ ፤ በክልሉ ሰላምን ለማዝለቅ የሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎና ድጋፍ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል። ችግር በውይይት እንጂ በግጭት እንደማይፈታ በመገንዘብ የቀሩ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተከትለው እንዲመለሱ መክረዋል። የክልሉን ሰላም በማዝለቅ ልማቱ ይበልጥ እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። ከደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ምርጫ ክልል በምክር ቤቱ የተወከሉት ወይዘሮ ፋጡማ ይማም በበኩላቸው፤ ሰላምን ለማዝለቅ የምክር ቤት አባላት ድርብ ኃላፊነት አለብን ብለዋል። አሁን በክልሉ የሰፈነውን ሰላም ለማዝለቅ ከሕዝቡ ጋር በመሆን ድጋፍና ክትትላቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል አቶ አሰፋ ይመር፤ የሰላም አማራጭን ተከትለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች እንደሚበረታቱና ይህም ሰላምን ለማፅናት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል። የቀሩ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ የተጀመረውን ስራ ለማጠናከር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ለብሔራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላም ሁነኛ መፍትሄ በመሆኑ ለስኬቱ የበኩላችንን እንወጣለን--የካፋ ሀገር ሽማግሌዎች
Dec 27, 2025 77
ቦንጋ፤ ታህሳስ 18/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ለብሔራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላም ሁነኛ መፍትሄ በመሆኑ ለስኬቱ የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ የካፋ የሀገር ሽማግሌዎች ተናገሩ። በሀገሪቱ ለግጭትና አለመግባባት መንስኤ የሆኑ ችግሮችን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመፍታት የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ለመፍትሄው እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። ኮሚሽኑ ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች አካታችና አሳታፊ የሆነ ምክክር ለማካሄድ የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ በማከናወን ወደ መጨረሻው የውይይት ምዕራፍ ለመሸጋጋር ዝግጅት ላይ ነው። የምክክር ሂደቱን በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የካፋ የሀገር ሽማግሌዎች በምክክር የሀገርን ችግር መፍታት ትልቅ እድል መሆኑን አንስተዋል። የግጭት እንቅስቃሴ ከጉዳትና ውድመት በስተቀር ምንም ያመጣው ውጤት እንደሌለ ገልጸው የምክክር ሂደት ውጤቱ የሚያምርና ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደረግ ነው ብለዋል። የካፋ የሀገር ሽማግሌና ባህላዊ ንጉስ ኮላዎቾቺ ግርማ ኪዳኔ በምክክር አለመግባባ፣ ጠብና ቁርሾዎችን በእርቅ በመቋጨት ሰላምና አንድነትን ማጽናት እንደሚቻል ተናግረዋል። በዚህ ደግሞ ማንም ቢሆን ተጠቃሚ እንጂ የሚጎዳ አለመኖሩን አንስተው በምክክር ለዘላቂ ሰላም እንዘጋጅ በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ለኮሚሽኑ ሥራ ውጤታማነት የሁሉም አበርክቶ ወሳኝ በመሆኑ በተለይ ወጣቱ የአባቶችን ምክር መስማት፣ መከባበር እና መደማመጥን ባህል ማድረግ አለበት ብለዋል። ሌላኛው የካፋ የሀገር ሽማገሌ አድማሱ አቱሞ፤ ኢትዮጵያዊያን ችግሮችን በንግግርና በእርቅ የመፍታት የዳበረ ባህል ቢኖረንም እንደ ሀገር መክረን መፍትሄ በማምጣት ረገድ እስካሁን እድሉን አልተጠቀምንበትም ብለዋል። በመሆኑም በሀገር ጉዳይ ከጫፍ ጫፍ ያሉ ኢትዮጵያውያን ተሰባስበው የመምከር መልካም ዕድል በመሆኑ በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። የሀገር ሽማግሌ ጀማነህ ዘውዴ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ችግሮችን በንግግርና በውይይት መፍታት ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ጠንካራ ሀገር መገንባት በመሆኑ ለስኬቱ ሁላችንም የሚጠበቅብንን መወጣት አለብን ብለዋል። ሀገራዊ አንድነትና ሰላምን የማጽናት ጉዳይ የጋራ ሃላፊነት በመሆኑ ሁሉም በቅንነትና ታማኝነት መሳተፍ እንዳለበት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። የሀገር ሽማግሌዎቹ ለኮሚሽኑ ሥራ ውጤታማነት የሁሉም አስተዋፅኦ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረው፣ ምክክሩ ግቡን እስኪመታ ድረስ የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ
Dec 26, 2025 108
ባህር ዳር፤ ታህሳስ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ላለፉት ሁለት ቀናት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምምከር ሲካሄድ ቆይቷል። በዛሬው እለት ደግሞ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ የቀረቡ የተለያዩ ሹመቶችን መርምሮና ተወያይቶ አጽድቋል። ለምክር ቤቱ ቀርቦ ከፀደቀላቸው መካከል 4ቱ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዘርፍ አስተባባሪዎች ሲሆኑ 9ኙ ደግሞ የተለያዩ ቢሮ ኃላፊዎች ሲሆኑ በዚህም መሠረት፦ 1ኛ, አህመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር)፦ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ልማት ዘርፍ አሥተባባሪ 2ኛ, ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር)፦ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ልማት ዘርፍ አሥተባባሪ 3ኛ, ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር)፦ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የማኅበራዊ ዘርፍ አሥተባባሪ 4ኛ, አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የአሥተዳደር ዘርፍ አሥተባባሪ 5ኛ, መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ 6ኛ, አቶ ደረጀ ማንደፍሮ ፦ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ 7ኛ, አቶ ጥላሁን ወርቅነህ፦ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ 8ኛ, ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) የአማራ ክልል ከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ 9ኛ, ኢንጅነር ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር)፦ የአማራ ክልል ውኃና ኢነርጅ ቢሮ ኃላፊ 10ኛ, አቶ አታላይ ጥላሁን፦ የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ 11ኛ, ጋሻው ሙጨ (ዶ/ር) የአማራ ክልል እንስሳት እና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ 12ኛ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር) የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ 13ኛ, አቶ ዓባይ መንግሥቴ፦ የአማራ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ሆነው ሹመታቸው በምክር ቤቱ ጸድቋል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት በአቶ አለምአንተ አግደው የቀረቡ 174 የወረዳ ዳኞችን ሹመትም ተቀብሎ አፅድቋል። በአጠቃላይ ተሿሚዎቹ በአመራር ብቃታቸው፣ በትምህርት ዝግጅታቸው፣ የካበተ የስራ ልምዳቸውና በስነ-ምግባራቸው የተመሰገኑና የክልሉን ሰላም፣ ዕድገትና ልማት ወደፊት ለማሻገር ተግተው ይሰራሉ ተብሎ እምነት የተጣለባቸው እንደሆኑም ተገልጿል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ
Dec 26, 2025 115
ባሕርዳር፤ ታሕሳስ 17/2018(ኢዜአ)፡ - የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ የተሻሻለውን የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን ጨምሮ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ። የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጁ በፌዴራል ደረጃ ተሻሽሎ ከፀደቀው ጋር እንዲጣጣም ተደርጎ የወጣ መሆኑም ተመላክቷል። የክልሉ መሬት ቢሮ ኃላፊ ሲሳይ ዳምጤ ለምክር ቤቱ እንደገለጹት፤ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጁ የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ለማሳደግ የሚያስችል ነው። የገጠር መሬት ባለመብቶች መሬታቸውን ማከራየት፣ በዋስትና ማስያዝ፣ ከባለሃብቶች ጋር በጋራ ማልማትና በውርስ ወይም በስጦታ ለማስተላለፍ የሚፈቅድ እንደሆነ አስረድተዋል። አርሶ አደሩ የመሬት ይዞታ ዋስትና በመስጠት ያፈራውን ንብረት የመጠቀም መብትን ለማጠናከርና የገጠር መሬት ምዝገባ መረጃ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለማደራጀት የሚያስችል መሆኑንም አንስተዋል። እንዲሁም የሴቶችና ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን የመሬት ተጠቃሚነት በማረጋገጥ አካታች የመሬት አጠቃቀም ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችልም አመልክተዋል። የምክር ቤቱ የግብርናና አካባቢ ጥበቃና ውሃ ሃብት ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከፍያለው ሙላቴ በበኩላቸው፤ የአዋጁ መፅደቅ ከመሬት ጋር ተያይዞ ይነሱ የነበሩ ችግሮችን በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤቱ ጉባዔ በተጨማሪም የፕሮጀክት አስተዳደርና አመራር ስርዓት ፣ የኤክስሳይዝ ታክስን ለማሻሻል የወጣን አዋጅና የተሻሻለው የመንግስት ሰራተኞች አስተዳደርን ጨምሮ ሌሎች አዋጆች ላይ ተወያይቶ አፅድቋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ነው
Dec 25, 2025 211
ባሕርዳር ፤ ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ) ፡- የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ገለጹ። የአማራ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር፤ አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔ በባሕርዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፤ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በቅርቡ የተፈራረመው የዘላቂ ሰላም ስምምነት በክልሉ ሰላምን ለማፅናት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የክልሉ መንግስት ችግሮችን በውይይትና በንግግር መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሲያቀርብ የነበረው የሰላም አማራጭ ፍሬ ማፍራቱን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል። ግጭት ይብቃ ብለው የክልሉን መንግስት የሰላም ጥሪ ተቀብለው ለተመሰሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን ምክር ቤቱ ያመሰግናል ያሉት አፈ ጉባኤዋ ፤ ሌሎች በጫካ የቀሩ ታጣቂዎችም የሰላም ጥሪውን ተቀብለው እንዲመጡ ጠይቀዋል። የአማራ ክልል መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን ገልጸው ፤ አጠናክሮ እንዲቀጥል በምክር ቤቱ በኩል አስፈላጊው ድጋፍና ትብብር የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል። የምክር ቤት አባላት ለመልካም አስተዳደር መስፈን፣ ለዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበርና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተያዘው ዓመት የሚካሄደው 7ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተአማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅና ህዝቡ በምርጫው በንቃት እንዲሳተፍ የምክር ቤት አባላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። ምክር ቤቱ የክልሉን ትምህርት ቢሮ የ5 ወራት እቅድ አፈፃፀምና የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በተከናወኑ የፋይናንስ ህጋዊነትና ክዋኔ ኦዲት ግኝቶች ላይ እንደሚመክር ከመርሃ ግብሩ መረዳት ተችሏል። በጉባዔው ልዩ ልዩ አዋጆችና ሹመቶች እንደሚጸድቁም ይጠበቃል።
የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ ለውጦችን በሚያሳይ መልኩ ይከበራል
Dec 25, 2025 188
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡-የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በሚያሳይ መልኩ ከጥር 15 እስከ 19 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከበር በኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ ገለፁ። በበዓሉ ላይ "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በሚል የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብም ተመላክቷል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ-ገጽ ይፋ ሆነ የአየር ሀይል የተመሰረተበት 90ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት የአየር ላይ ትርኢት ይካሄዳል-ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ፤ የአየር ኃይሉን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል መሪ ሃሳብ ከጥር 15 እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ደማቅ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር አስታውቀዋል። በበዓሉ ከጥር 15 ቀን ጀምሮ በሚካሄደውና "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በተሰኘው መርሃ ግብር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብ አመላክተዋል። በዚህም የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ የሩሲያ የአየር ኃይል ትርኢት ቡድን፣ የሞሮኮ እና የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይሎች በጋራ በመሆን የጥቁር አንበሳ የአየር ትርኢት እንደሚያቀርቡ ጠቅሰዋል። "የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ የቻይና፣ ህንድ፣ አሜሪካ እና ደቡብ አፍሪካ ግዙፍ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ኤክስፖ እንደሚካሄድም ገልፀዋል። ከ25 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ የቴክኖሎጂ ተቋማት የደረሱበትን ደረጃ ለጉብኝት ክፍት የሚያደርጉበት "ስታቲክ ዲስፕለይ እና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2026" እንደሚካሄድም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የአቪዬሽን ማዕከል መሆኗን የምታረጋግጥበት "ፊውቸር አፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም" ለሶስተኛ ጊዜ እንደሚካሄድም ተናግረዋል። "የጋራ ስራዎቻችንን አጠናክረን የተረጋጋ ዓለም እንገንባ" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው መድረክ ላይ ከ38 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦችና ታላላቅ የአቪዬሽን ባለሙያዎች ይታደማሉ ነው ያሉት። የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አዛዦችና የመንግስት ባለስልጣናት "ሀገርን በማገልገል የሚገኝን ክብር መዘከር" በሚል ርዕስ ከህዝቡ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ጠቅሰዋል። በዓሉ የአየር ኃይሉን የ90 ዓመት የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በማሳየት ይከበራል ነው ያሉት። መላው የሀገሪቱ ህዝብ በዚህ ታሪካዊ በዓል ላይ በመገኘት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የደረሰበትን ዝግጁነት እንዲመለከት ጥሪ አቅርበዋል። የበዓሉ አካል የሆነና "ለአየር ኃይል እድገት በሙሉ አቅሜ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ሃሳብ ባሳለፍነው ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ የ10 ኪሎ ሜትር ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ሩጫ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይህ ውድድር በህዝብና በተቋሙ መካከል ያለውን ትስስር ያጠናከረና ለዋናው በዓል መሰረት የጣለ ታሪካዊ ኹነት ሆኖ ማለፉንም ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ
Dec 25, 2025 146
ባሕር ዳር፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔውን መካሄድ ጀምሯል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ የአምስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለጉባዔው ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል። በውይይቱ በትምህርት አጀማመርና በተከናወኑ ተግባራት ላይ በመምከር የቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ተጠቁሟል። እንዲሁም በክልሉ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የፋይናንስ ሕጋዊነትና የክዋኔ ኦዲት ግኝቶችንና የተሰጡ የማሻሻያ ሐሳቦችን የሚያሳይ የተጠቃለለ ሪፖርት ላይ እንደሚመክር ተመላክቷል። ጉባዔው ለሁለት ቀናት እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፤ በቆይታው ልዩ ልዩ ዐዋጆች እና ሹመቶችን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።
መንግሥት ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል-የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Dec 24, 2025 228
አዲስ አበባ፣ታኅሣስ 15/2018(ኢዜአ)፡-መንግሥት የሀገር ግንባታ ሂደቱን ለማጽናት እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል፡፡ እነዚህ ሦስቱ ምሰሶዎች ሀገራዊ አንድነትን፣ሰላምና ብልጽግናን፣ እንዲሁም ዜጎች በመተማመን እና በተጠያቂነት ላይ የተመሠረተ የጋራ ራዕይ እንዲኖራቸዉ የሚያደርጉ ቁልፍ መሰረቶች ናቸው፡፡ ዲሞክራሲን የመገንባት ሂደት ለአንድ ሀገር ወሳኝ ተግባር ሲሆን፣ በዋናነት ነፃ፣ ገለልተኛ እና ብቁ ተቋማትን ማቋቋም ላይ ትኩረት ያደረገ ነዉ፡፡ተቋማቱ የሚመሩባቸዉ ህጎችና የአሰራር ሥርዓቶች፣የተቋማቱ አወቃቀርና አደረጃጀት፣ እንዲሁም ለህዝብ ያላቸዉን ተዓማኒነትን መጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራበት ይገኛል፡፡ ጠንካራ የዲሞክራሲ ባህልና ሥርዓት የሚገነባው ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት ሲፈጠሩና ሲጠናከሩ መሆኑን መንግሥት በጽኑ የሚገነዘበው ጉዳይ ነዉ፡፡በዚህም ኢትዮጵያ ባለፉት 7 ዓመታት በዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ሂደት ውስጥ ሁለተናዊ ሪፎርም ሥራዎችን ስታከናውን ቆይታለች፡፡ እነዚህ ሪፎርሞች የሀገሪቱን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑትን የዲሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እና ጠንካራ አድርጎ ለመገንባት መንግሥት ምን ያህል ቁርጠኛ እንደሆነ ያሳየባቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ተቋማት መጠናከር በአንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም እና ልማት እንዲረጋገጥ እንደ ዋንኛ ምሰሶ የሚወሰድ ነው፡፡ በተለይም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በዲሞክራሲ ተቋማት ላይ የታዩ ተጨባጭ ለውጦች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ለመጠበቅ፣ እንዲሁም የሕዝቡን ዕምነት ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ መንግሥት በተለይ ተቋማዊ ዐቅምን በማሳደግ እና ነፃነትን በማረጋገጥ፣ የዲሞክራሲ ምህዳርን እንዲሰፋ ለማደረግ የሚጠበቅበት ግዴታ ብቻ ሳይሆን ዲሞክራሲ የሚያብብበትን አስቻይ ዐውድና ማዕቀፍ ለመፍጠር ዓለማው አድረጓል፡፡ ይሄንን ከግብ ለማድረስ በተለይ የፀጥታ፣ የፍትሕ፣ የሲቪልና የሚዲያ ተቋማት፣ እንዲሁም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕዝብን ማዕከል አድርገው እንዲሰሩ መንግሥት በቁርጠኝነት በመደገፉ እንደ ሀገር ገለልተኛ ተቋማት እንዲፈጠሩ በማደርረግ ተጨባጭ ዉጤቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል፡፡ ሌላው መንግስት በትኩረት እየሰራበት ያለው ጉዳይ እንደ ሀገር ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ነዉ፡፡ ይህ ሂደት ዋና ዓለማ ያደረገው መላዉ ሕዝብ፣ ተቋማት፣ አመራርና ሠራተኛዉ በሀገራዊ ራዕይ ላይ በተለያዩ ድምጾች የጋራ እድገትን በመገንባት ሀገራዊ ህለውና እና ብልጽግና እንዲረጋገጥ እንዲሁም በዜጎች መካከል መተማመን እና ሀገራዊ አንድነትን እንዲፈጠር ማድርግ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ የብዙሃን ድምጽ የሚሰማበት የፖለቲካ ዐዉድ ለመፍጠር አያሌ የፖለቲካ ማሻሻያዎችን አድርጋለች፡፡ በዚህም እስከዛሬ በነበሩ መንግሥታት ያለተሞከረውን ጫፍ ወጥተው የሚታዩ ተቃርኖ ሀሳቦችን ለማጥበብና ለማቀራረብ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም፣ ሀገራዊ የውይይት መድረክ እንዲፈጠር ተደርጓል፡፡ በዚህም ገና ከወዲሁ በርካታ ለዉጦች እየታዩ ሲሆን ውሳኔው ለምንመኛት የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን የማዕዘን ድንጋይ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ በአጠቃላይ መንግሥት መልአተ ሕዝቡን በማስተባበር ጠንካራና ብልጽግናዋን በልጆቿ ያረጋገጠች ኢትዮጵያን ለመፍጠር እያደረገ ባለው ዘርፈ ብዙ ጥረት ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን የመፍጠርን ጉዳይ በልዩ ትኩረት የሚሰራበት ዋንኛው አጀንዳው ሆኖ ይቀጠላል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ፖለቲካ
ልማት እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን- የምክር ቤት አባላት
Dec 27, 2025 20
ባሕርዳር ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል ሰላምን በማጽናት ልማት እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ገለጹ። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል ከሰሜን ጎንደር ዞን ድልይብዛ ምርጫ ክልል የተወከሉት አቶ ብርሃኑ ዘውዱ ፤ በክልሉ ሰላምን ለማዝለቅ የሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎና ድጋፍ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል። ችግር በውይይት እንጂ በግጭት እንደማይፈታ በመገንዘብ የቀሩ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተከትለው እንዲመለሱ መክረዋል። የክልሉን ሰላም በማዝለቅ ልማቱ ይበልጥ እንዲፋጠን ክትትልና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። ከደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ምርጫ ክልል በምክር ቤቱ የተወከሉት ወይዘሮ ፋጡማ ይማም በበኩላቸው፤ ሰላምን ለማዝለቅ የምክር ቤት አባላት ድርብ ኃላፊነት አለብን ብለዋል። አሁን በክልሉ የሰፈነውን ሰላም ለማዝለቅ ከሕዝቡ ጋር በመሆን ድጋፍና ክትትላቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል። ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል አቶ አሰፋ ይመር፤ የሰላም አማራጭን ተከትለው የተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች እንደሚበረታቱና ይህም ሰላምን ለማፅናት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል። የቀሩ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ የተጀመረውን ስራ ለማጠናከር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ለብሔራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላም ሁነኛ መፍትሄ በመሆኑ ለስኬቱ የበኩላችንን እንወጣለን--የካፋ ሀገር ሽማግሌዎች
Dec 27, 2025 77
ቦንጋ፤ ታህሳስ 18/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ምክክሩ ለብሔራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላም ሁነኛ መፍትሄ በመሆኑ ለስኬቱ የበኩላችንን እንወጣለን ሲሉ የካፋ የሀገር ሽማግሌዎች ተናገሩ። በሀገሪቱ ለግጭትና አለመግባባት መንስኤ የሆኑ ችግሮችን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመፍታት የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ለመፍትሄው እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። ኮሚሽኑ ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች አካታችና አሳታፊ የሆነ ምክክር ለማካሄድ የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ በማከናወን ወደ መጨረሻው የውይይት ምዕራፍ ለመሸጋጋር ዝግጅት ላይ ነው። የምክክር ሂደቱን በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የካፋ የሀገር ሽማግሌዎች በምክክር የሀገርን ችግር መፍታት ትልቅ እድል መሆኑን አንስተዋል። የግጭት እንቅስቃሴ ከጉዳትና ውድመት በስተቀር ምንም ያመጣው ውጤት እንደሌለ ገልጸው የምክክር ሂደት ውጤቱ የሚያምርና ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደረግ ነው ብለዋል። የካፋ የሀገር ሽማግሌና ባህላዊ ንጉስ ኮላዎቾቺ ግርማ ኪዳኔ በምክክር አለመግባባ፣ ጠብና ቁርሾዎችን በእርቅ በመቋጨት ሰላምና አንድነትን ማጽናት እንደሚቻል ተናግረዋል። በዚህ ደግሞ ማንም ቢሆን ተጠቃሚ እንጂ የሚጎዳ አለመኖሩን አንስተው በምክክር ለዘላቂ ሰላም እንዘጋጅ በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ለኮሚሽኑ ሥራ ውጤታማነት የሁሉም አበርክቶ ወሳኝ በመሆኑ በተለይ ወጣቱ የአባቶችን ምክር መስማት፣ መከባበር እና መደማመጥን ባህል ማድረግ አለበት ብለዋል። ሌላኛው የካፋ የሀገር ሽማገሌ አድማሱ አቱሞ፤ ኢትዮጵያዊያን ችግሮችን በንግግርና በእርቅ የመፍታት የዳበረ ባህል ቢኖረንም እንደ ሀገር መክረን መፍትሄ በማምጣት ረገድ እስካሁን እድሉን አልተጠቀምንበትም ብለዋል። በመሆኑም በሀገር ጉዳይ ከጫፍ ጫፍ ያሉ ኢትዮጵያውያን ተሰባስበው የመምከር መልካም ዕድል በመሆኑ በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። የሀገር ሽማግሌ ጀማነህ ዘውዴ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ችግሮችን በንግግርና በውይይት መፍታት ዘላቂ ሰላም የሰፈነባት ጠንካራ ሀገር መገንባት በመሆኑ ለስኬቱ ሁላችንም የሚጠበቅብንን መወጣት አለብን ብለዋል። ሀገራዊ አንድነትና ሰላምን የማጽናት ጉዳይ የጋራ ሃላፊነት በመሆኑ ሁሉም በቅንነትና ታማኝነት መሳተፍ እንዳለበት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። የሀገር ሽማግሌዎቹ ለኮሚሽኑ ሥራ ውጤታማነት የሁሉም አስተዋፅኦ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረው፣ ምክክሩ ግቡን እስኪመታ ድረስ የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ
Dec 26, 2025 108
ባህር ዳር፤ ታህሳስ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ላለፉት ሁለት ቀናት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምምከር ሲካሄድ ቆይቷል። በዛሬው እለት ደግሞ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ የቀረቡ የተለያዩ ሹመቶችን መርምሮና ተወያይቶ አጽድቋል። ለምክር ቤቱ ቀርቦ ከፀደቀላቸው መካከል 4ቱ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዘርፍ አስተባባሪዎች ሲሆኑ 9ኙ ደግሞ የተለያዩ ቢሮ ኃላፊዎች ሲሆኑ በዚህም መሠረት፦ 1ኛ, አህመዲን ሙሐመድ (ዶ/ር)፦ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ልማት ዘርፍ አሥተባባሪ 2ኛ, ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር)፦ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ልማት ዘርፍ አሥተባባሪ 3ኛ, ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር)፦ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የማኅበራዊ ዘርፍ አሥተባባሪ 4ኛ, አማኑኤል ፈረደ (ዶ/ር) በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የአሥተዳደር ዘርፍ አሥተባባሪ 5ኛ, መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ 6ኛ, አቶ ደረጀ ማንደፍሮ ፦ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ 7ኛ, አቶ ጥላሁን ወርቅነህ፦ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ 8ኛ, ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) የአማራ ክልል ከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ 9ኛ, ኢንጅነር ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር)፦ የአማራ ክልል ውኃና ኢነርጅ ቢሮ ኃላፊ 10ኛ, አቶ አታላይ ጥላሁን፦ የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ 11ኛ, ጋሻው ሙጨ (ዶ/ር) የአማራ ክልል እንስሳት እና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ 12ኛ እሸቱ የሱፍ (ዶ/ር) የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ 13ኛ, አቶ ዓባይ መንግሥቴ፦ የአማራ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ሆነው ሹመታቸው በምክር ቤቱ ጸድቋል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት በአቶ አለምአንተ አግደው የቀረቡ 174 የወረዳ ዳኞችን ሹመትም ተቀብሎ አፅድቋል። በአጠቃላይ ተሿሚዎቹ በአመራር ብቃታቸው፣ በትምህርት ዝግጅታቸው፣ የካበተ የስራ ልምዳቸውና በስነ-ምግባራቸው የተመሰገኑና የክልሉን ሰላም፣ ዕድገትና ልማት ወደፊት ለማሻገር ተግተው ይሰራሉ ተብሎ እምነት የተጣለባቸው እንደሆኑም ተገልጿል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት ጉባዔ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ
Dec 26, 2025 115
ባሕርዳር፤ ታሕሳስ 17/2018(ኢዜአ)፡ - የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ የተሻሻለውን የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን ጨምሮ የተለያዩ አዋጆችን አፀደቀ። የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጁ በፌዴራል ደረጃ ተሻሽሎ ከፀደቀው ጋር እንዲጣጣም ተደርጎ የወጣ መሆኑም ተመላክቷል። የክልሉ መሬት ቢሮ ኃላፊ ሲሳይ ዳምጤ ለምክር ቤቱ እንደገለጹት፤ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጁ የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ለማሳደግ የሚያስችል ነው። የገጠር መሬት ባለመብቶች መሬታቸውን ማከራየት፣ በዋስትና ማስያዝ፣ ከባለሃብቶች ጋር በጋራ ማልማትና በውርስ ወይም በስጦታ ለማስተላለፍ የሚፈቅድ እንደሆነ አስረድተዋል። አርሶ አደሩ የመሬት ይዞታ ዋስትና በመስጠት ያፈራውን ንብረት የመጠቀም መብትን ለማጠናከርና የገጠር መሬት ምዝገባ መረጃ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለማደራጀት የሚያስችል መሆኑንም አንስተዋል። እንዲሁም የሴቶችና ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን የመሬት ተጠቃሚነት በማረጋገጥ አካታች የመሬት አጠቃቀም ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችልም አመልክተዋል። የምክር ቤቱ የግብርናና አካባቢ ጥበቃና ውሃ ሃብት ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከፍያለው ሙላቴ በበኩላቸው፤ የአዋጁ መፅደቅ ከመሬት ጋር ተያይዞ ይነሱ የነበሩ ችግሮችን በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑን ገልጸዋል። የምክር ቤቱ ጉባዔ በተጨማሪም የፕሮጀክት አስተዳደርና አመራር ስርዓት ፣ የኤክስሳይዝ ታክስን ለማሻሻል የወጣን አዋጅና የተሻሻለው የመንግስት ሰራተኞች አስተዳደርን ጨምሮ ሌሎች አዋጆች ላይ ተወያይቶ አፅድቋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ነው
Dec 25, 2025 211
ባሕርዳር ፤ ታህሳስ 16/2018 (ኢዜአ) ፡- የክልሉ መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ገለጹ። የአማራ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር፤ አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔ በባሕርዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፤ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በቅርቡ የተፈራረመው የዘላቂ ሰላም ስምምነት በክልሉ ሰላምን ለማፅናት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የክልሉ መንግስት ችግሮችን በውይይትና በንግግር መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሲያቀርብ የነበረው የሰላም አማራጭ ፍሬ ማፍራቱን የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል። ግጭት ይብቃ ብለው የክልሉን መንግስት የሰላም ጥሪ ተቀብለው ለተመሰሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን ምክር ቤቱ ያመሰግናል ያሉት አፈ ጉባኤዋ ፤ ሌሎች በጫካ የቀሩ ታጣቂዎችም የሰላም ጥሪውን ተቀብለው እንዲመጡ ጠይቀዋል። የአማራ ክልል መንግስት ሰላምን በማፅናት ለልማት ስራዎች ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ መሆኑን ገልጸው ፤ አጠናክሮ እንዲቀጥል በምክር ቤቱ በኩል አስፈላጊው ድጋፍና ትብብር የሚደረግ መሆኑን አረጋግጠዋል። የምክር ቤት አባላት ለመልካም አስተዳደር መስፈን፣ ለዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበርና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ የሚያደርጉት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተያዘው ዓመት የሚካሄደው 7ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተአማኒነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅና ህዝቡ በምርጫው በንቃት እንዲሳተፍ የምክር ቤት አባላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። ምክር ቤቱ የክልሉን ትምህርት ቢሮ የ5 ወራት እቅድ አፈፃፀምና የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በተከናወኑ የፋይናንስ ህጋዊነትና ክዋኔ ኦዲት ግኝቶች ላይ እንደሚመክር ከመርሃ ግብሩ መረዳት ተችሏል። በጉባዔው ልዩ ልዩ አዋጆችና ሹመቶች እንደሚጸድቁም ይጠበቃል።
የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ ለውጦችን በሚያሳይ መልኩ ይከበራል
Dec 25, 2025 188
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡-የአየር ኃይል የምስረታ በዓል የተቋሙን የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በሚያሳይ መልኩ ከጥር 15 እስከ 19 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከበር በኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ ገለፁ። በበዓሉ ላይ "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በሚል የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብም ተመላክቷል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ ቀን አጠቃላይ እንቅስቃሴን የሚያሳይ ድረ-ገጽ ይፋ ሆነ የአየር ሀይል የተመሰረተበት 90ኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት የአየር ላይ ትርኢት ይካሄዳል-ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የአንደኛ አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ብሩክ ሰይፉ፤ የአየር ኃይሉን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል "የኢትዮጵያ አየር ኃይል የነፃነትና የአንድነት ምልክት" በሚል መሪ ሃሳብ ከጥር 15 እስከ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ደማቅ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር አስታውቀዋል። በበዓሉ ከጥር 15 ቀን ጀምሮ በሚካሄደውና "የአንበሶች ሰማይ! ኢትዮጵያ" በተሰኘው መርሃ ግብር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከሌሎች አጋር ሀገራት ጋር በመሆን አስደናቂ የአየር ላይ ትርኢት እንደሚያቀርብ አመላክተዋል። በዚህም የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ የሩሲያ የአየር ኃይል ትርኢት ቡድን፣ የሞሮኮ እና የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይሎች በጋራ በመሆን የጥቁር አንበሳ የአየር ትርኢት እንደሚያቀርቡ ጠቅሰዋል። "የወደፊቱን የአቪዬሽን አቅም በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ የቻይና፣ ህንድ፣ አሜሪካ እና ደቡብ አፍሪካ ግዙፍ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ኤክስፖ እንደሚካሄድም ገልፀዋል። ከ25 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ የቴክኖሎጂ ተቋማት የደረሱበትን ደረጃ ለጉብኝት ክፍት የሚያደርጉበት "ስታቲክ ዲስፕለይ እና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2026" እንደሚካሄድም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የአቪዬሽን ማዕከል መሆኗን የምታረጋግጥበት "ፊውቸር አፍሪካ አየር ኃይሎች ፎረም" ለሶስተኛ ጊዜ እንደሚካሄድም ተናግረዋል። "የጋራ ስራዎቻችንን አጠናክረን የተረጋጋ ዓለም እንገንባ" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው መድረክ ላይ ከ38 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል አዛዦችና ታላላቅ የአቪዬሽን ባለሙያዎች ይታደማሉ ነው ያሉት። የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አዛዦችና የመንግስት ባለስልጣናት "ሀገርን በማገልገል የሚገኝን ክብር መዘከር" በሚል ርዕስ ከህዝቡ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ጠቅሰዋል። በዓሉ የአየር ኃይሉን የ90 ዓመት የጀግንነት ጉዞ፣ የተከፈለውን መስዋዕትነትና የተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶችን በማሳየት ይከበራል ነው ያሉት። መላው የሀገሪቱ ህዝብ በዚህ ታሪካዊ በዓል ላይ በመገኘት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የደረሰበትን ዝግጁነት እንዲመለከት ጥሪ አቅርበዋል። የበዓሉ አካል የሆነና "ለአየር ኃይል እድገት በሙሉ አቅሜ እሮጣለሁ" በሚል መሪ ሃሳብ ባሳለፍነው ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ የ10 ኪሎ ሜትር ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ሩጫ መካሄዱን አስታውሰዋል። ይህ ውድድር በህዝብና በተቋሙ መካከል ያለውን ትስስር ያጠናከረና ለዋናው በዓል መሰረት የጣለ ታሪካዊ ኹነት ሆኖ ማለፉንም ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ
Dec 25, 2025 146
ባሕር ዳር፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔውን መካሄድ ጀምሯል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ የአምስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለጉባዔው ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል። በውይይቱ በትምህርት አጀማመርና በተከናወኑ ተግባራት ላይ በመምከር የቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ተጠቁሟል። እንዲሁም በክልሉ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የፋይናንስ ሕጋዊነትና የክዋኔ ኦዲት ግኝቶችንና የተሰጡ የማሻሻያ ሐሳቦችን የሚያሳይ የተጠቃለለ ሪፖርት ላይ እንደሚመክር ተመላክቷል። ጉባዔው ለሁለት ቀናት እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፤ በቆይታው ልዩ ልዩ ዐዋጆች እና ሹመቶችን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።
መንግሥት ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል-የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Dec 24, 2025 228
አዲስ አበባ፣ታኅሣስ 15/2018(ኢዜአ)፡-መንግሥት የሀገር ግንባታ ሂደቱን ለማጽናት እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል፡፡ እነዚህ ሦስቱ ምሰሶዎች ሀገራዊ አንድነትን፣ሰላምና ብልጽግናን፣ እንዲሁም ዜጎች በመተማመን እና በተጠያቂነት ላይ የተመሠረተ የጋራ ራዕይ እንዲኖራቸዉ የሚያደርጉ ቁልፍ መሰረቶች ናቸው፡፡ ዲሞክራሲን የመገንባት ሂደት ለአንድ ሀገር ወሳኝ ተግባር ሲሆን፣ በዋናነት ነፃ፣ ገለልተኛ እና ብቁ ተቋማትን ማቋቋም ላይ ትኩረት ያደረገ ነዉ፡፡ተቋማቱ የሚመሩባቸዉ ህጎችና የአሰራር ሥርዓቶች፣የተቋማቱ አወቃቀርና አደረጃጀት፣ እንዲሁም ለህዝብ ያላቸዉን ተዓማኒነትን መጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራበት ይገኛል፡፡ ጠንካራ የዲሞክራሲ ባህልና ሥርዓት የሚገነባው ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት ሲፈጠሩና ሲጠናከሩ መሆኑን መንግሥት በጽኑ የሚገነዘበው ጉዳይ ነዉ፡፡በዚህም ኢትዮጵያ ባለፉት 7 ዓመታት በዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ሂደት ውስጥ ሁለተናዊ ሪፎርም ሥራዎችን ስታከናውን ቆይታለች፡፡ እነዚህ ሪፎርሞች የሀገሪቱን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑትን የዲሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እና ጠንካራ አድርጎ ለመገንባት መንግሥት ምን ያህል ቁርጠኛ እንደሆነ ያሳየባቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ተቋማት መጠናከር በአንድ ሀገር ዘላቂ ሰላም እና ልማት እንዲረጋገጥ እንደ ዋንኛ ምሰሶ የሚወሰድ ነው፡፡ በተለይም ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በዲሞክራሲ ተቋማት ላይ የታዩ ተጨባጭ ለውጦች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ለመጠበቅ፣ እንዲሁም የሕዝቡን ዕምነት ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ መንግሥት በተለይ ተቋማዊ ዐቅምን በማሳደግ እና ነፃነትን በማረጋገጥ፣ የዲሞክራሲ ምህዳርን እንዲሰፋ ለማደረግ የሚጠበቅበት ግዴታ ብቻ ሳይሆን ዲሞክራሲ የሚያብብበትን አስቻይ ዐውድና ማዕቀፍ ለመፍጠር ዓለማው አድረጓል፡፡ ይሄንን ከግብ ለማድረስ በተለይ የፀጥታ፣ የፍትሕ፣ የሲቪልና የሚዲያ ተቋማት፣ እንዲሁም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕዝብን ማዕከል አድርገው እንዲሰሩ መንግሥት በቁርጠኝነት በመደገፉ እንደ ሀገር ገለልተኛ ተቋማት እንዲፈጠሩ በማደርረግ ተጨባጭ ዉጤቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል፡፡ ሌላው መንግስት በትኩረት እየሰራበት ያለው ጉዳይ እንደ ሀገር ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር ነዉ፡፡ ይህ ሂደት ዋና ዓለማ ያደረገው መላዉ ሕዝብ፣ ተቋማት፣ አመራርና ሠራተኛዉ በሀገራዊ ራዕይ ላይ በተለያዩ ድምጾች የጋራ እድገትን በመገንባት ሀገራዊ ህለውና እና ብልጽግና እንዲረጋገጥ እንዲሁም በዜጎች መካከል መተማመን እና ሀገራዊ አንድነትን እንዲፈጠር ማድርግ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ የብዙሃን ድምጽ የሚሰማበት የፖለቲካ ዐዉድ ለመፍጠር አያሌ የፖለቲካ ማሻሻያዎችን አድርጋለች፡፡ በዚህም እስከዛሬ በነበሩ መንግሥታት ያለተሞከረውን ጫፍ ወጥተው የሚታዩ ተቃርኖ ሀሳቦችን ለማጥበብና ለማቀራረብ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም፣ ሀገራዊ የውይይት መድረክ እንዲፈጠር ተደርጓል፡፡ በዚህም ገና ከወዲሁ በርካታ ለዉጦች እየታዩ ሲሆን ውሳኔው ለምንመኛት የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን መሆን የማዕዘን ድንጋይ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ በአጠቃላይ መንግሥት መልአተ ሕዝቡን በማስተባበር ጠንካራና ብልጽግናዋን በልጆቿ ያረጋገጠች ኢትዮጵያን ለመፍጠር እያደረገ ባለው ዘርፈ ብዙ ጥረት ዲሞክራሲን መገንባት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ብሔራዊ መግባባትን የመፍጠርን ጉዳይ በልዩ ትኩረት የሚሰራበት ዋንኛው አጀንዳው ሆኖ ይቀጠላል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ማህበራዊ
ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን የምርምርና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅበታል
Dec 27, 2025 13
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡-አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ የሚያሳልጡ የምርምርና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ማጠናከር እንዳለበት ተገለጸ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የቀድሞ ተማሪዎች የቤተሰብ ቀን እየተከበረ ነው። በመርኃ-ግብሩ ላይ የቀድሞ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የዛሬዎች አንጋፋ ምሁራን፣ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የተጠናቀቀው የ2017 ዓ.ም እና የዘንድሮው ዓመት ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ነው። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በራስ ገዝነት ሂደት ወደ ፊት የሚያሻግሩ የለውጥ ስራዎች የተጀመሩበት ወቅት መሆኑን አንስተዋል። በዘንድሮው ዓመት በኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ ያበረከተውን አስተዋጽኦ የሚዘክርበትና አሻራውን የሚያሳይበት 75ኛ ዓመት በዓሉን እያከበሩ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች አቅጣጫ የተለሙና እየተለሙ ያሉ ዕውቅ ምሁራንን ያፈራ አንጋፋ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ውብ ህብረ-ቀለም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይንጸባረቃል ያሉት ሚኒስትሯ፤ ህብረ ቀለሙ አንድነት፣ ትብብርና አብሮነትን እንደሚያጠናክር ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው በዓለም ስመ-ጥር ምሁራንን ያፈራው በአንጋፋነቱ ብቻ ሳይሆን በአስተዳደር ብቃቱ ጭምር መሆኑን ጠቁመው የኢትዮጵያ የለውጥ ሞተር የሆኑ ምሩቃንን ያፈራ መሆኑንም አንስተዋል። የዩኒቨርስቲው የቀድሞ ተማሪዎች የቤተሰብ ቀንም የጋራ ቤታችንን በማደስ በወደፊት አቅጣጫው ላይ አሻራችንን ማስቀመጥ ያግዛል ብለዋል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያዊነትን ያወቅንበት ትልቅ የህይወት ምዕራፍ ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ ለዛሬ ማንነታችን መሰረት የጣሉ አስደናቂ የሀገር ባለውለታ መምህራን ቁርጠኝነት የጎላ እንደነበር ተናግረዋል። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልጽግና ጉዙ የሚያሳልጡ የምርምር፣ የማህበረሰብ አገልግሎትና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባው ገልጸው፤ ለዚህ ሁላችንም መደገፍ አለብን ብለዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ከ75 ዓመት በፊት በ50 ተማሪዎች ማስተማርን አሀዱ ብሎ የጀመረው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ75 ዓመት ጉዞው 300 ሺህ ተማሪዎችን አስመርቋል ብለዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አሻራ በሁሉም ዘርፍ ይታያል ያሉት ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ፤ በጥናትና ምርምር ሀገር አሻግረዋል በማስተማር ትውልድ ቀርጸዋል ብለዋል። ሀገር በመምራት ለውጥ አምጥተዋል፣ የንግድ ተቋማትን መርተው ባለጸጋ ሆነዋል፣ በህክምና ተሰማርተው ሚሊዮኖችን ፈውሰዋል ብለዋል። ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ በመወከል ብሔራዊ ጥቅሟን ያስከበሩ ዲፕሎማቶችን መፍጠሩንም ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሩቃን በኢትዮጵያ ለውጥ ታላቅ አሻራ አኑረዋል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ በዓለም ገናና ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ በጋራ እንስራ የሚል ጥሪ አስተላልፈዋል።
የመንገድ መሠረተ ልማቱ ቀደም ሲል የነበሩ ችግሮችን ቀርፎልናል- የደጀን ወረዳ ነዋሪዎች
Dec 27, 2025 32
ደብረ ማርቆስ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡- የተገነባው የጠጠር መንገድ ትራንስፖርት ለማግኘትና ምርታቸውን በቀላሉ አጓጉዘው በተሻለ ዋጋ በመሸጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻሉን በደጀን ወረዳ የተለያዩ ቀበሌዎች ነዋሪዎች ተናገሩ። የመንገድ ተደራሽነትን በማሳደግ የሕብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የምሥራቅ ጎጃም ዞን መንገድ መምሪያ ኃላፊ ማናየ አዳነ ለኢዜአ ተናግረዋል። ባለፉት አምስት ወራትም ከ780 ኪሎ ሜትር በላይ የገጠር መንገድ አዲስ ግንባታና ጥገና በማካሄድ ለአገልግሎት መብቃቱን ጠቅሰው፤ ተንጠልጣይ ድልድይ መገንባቱንም አስታውቀዋል። በዚህም መሠረት ቀበሌን ከቀበሌ፣ ወረዳን ከወረዳና ዞን ማዕከላት ጋር ማስተሳሰር ተችሏል ብለዋል። በተሠራው ሥራ ትራንስፖርት በአቅራቢያቸው በማግኘታቸው ምርታቸውን በተሽከርካሪ አጓጉዘው በተሻለ ዋጋ በመሸጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻሉን በደጀን ወረዳ የሽንቡሪ ቀበሌ ነዋሪ ምንዋጋው ያዜ ተናግረዋል። ቀደም ሲል ትራንስፖርት ባለመኖሩ እናቶችና የጤና ችግር ያጋጠማቸውን ወደ ሕክምና ተቋም ለማድረስ እንቸገር ነበር፤ አሁን ግን መንገዱ በመገንባቱ የዘመናት ችግራችን ተቀርፏል ብለዋል። የበረቅ ወርቅ አምባ ቀበሌ ነዋሪ ፈጠነ ይደግ በበኩላቸው፤ የተገነባው ተንጠልጣይ ድልድይ ለዘመናት በጎርፍ ምክንያት በሰውና እንስሳት ላይ ይደርስ የነበረውን ችግር ማስቀረቱን አንስተዋል። የገጠር መንገድ ግንባታና ጥገናው የተከናወነው በመንግሥት፣ በሕብረተሰቡና ሌሎች አጋር አካላት ድጋፍ መሆኑንም ገልጸዋል።
የድሬዳዋ አሥተዳደር ያደረገልን አቀባበል አብሮነትን ያጎለብታል - የዓመታዊ የቁልቢ ገብርኤል ንግሥ በዓል ተጓዦች
Dec 26, 2025 72
ድሬዳዋ፤ ታኅሣስ 17/2018 (ኢዜአ)፡- የድሬዳዋ አሥተዳደር ያደረገልን አቀባበል አብሮነትን ያጎለብታል ሲሉ ዓመታዊውን የቁልቢ ገብርኤል የንግሥ በዓል ለማክበር ወደ ሥፍራው ያቀኑ ተጓዦች ተናገሩ። ከነገ በስቲያ ለሚከበረው ዓመታዊ የቁልቢ ገብርኤል የንግሥ በዓል ወደ ሥፍራው እያቀኑ ላሉ እንግዶች የድሬዳዋ አሥተዳደር አቀባበል አድርጓል። በዚሁ ወቅት ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ እንግዶች፤ የተደረገላቸው ደማቅ አቀባበልና መስተንግዶ ትስስርን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል። አክለውም አብሮነትን የሚገነባ በጎ ተግባር መሆኑን ነው ያስረዱት። በአሥተዳደሩ አመራሮችና ነዋሪዎች ለተደረገላቸው አቀባበል ምሥጋናቸውን አቅርበው ሁነቱን ሁልጊዜም እንደሚያስታውሱት ጠቅሰዋል። ዘመንን የተሻገረው የአንድነትና የአብሮነት ትስስር በኅብረ ብሔራዊ አንድነት ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ደግሞ የድሬዳዋ አሥተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ናቸው። ድሬዳዋ የፍቅር፣ የሰላምና የአንድነት መገለጫ ናት ያሉት ከንቲባው፤ ይህም በዓሉን ለማክበር እየመጡ የሚገኙ እንግዶችን በመቀበል መንፀባረቁን አስገንዝበዋል። በዓመት ሁለት ጊዜ በሚከበረው በዓል ላይ የሚከናወኑ ተግባራት ኅብረ ብሔራዊ አንድነትንና ትስስርን በማጠናከር የወል ትርክትን ለማነፅ ወሳኝ መሆናቸውንም አስረድተዋል። የአሥተዳደሩ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ በበኩላቸው፤ በዓሉን በድምቀት ለማክበርም ፖሊስና የፀጥታ አካላት ተቀናጅተው እየሠሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
የአካል ጉዳተኞችን የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ ቅንጅታዊ ሥራ ይጠናከራል
Dec 26, 2025 138
ጅማ ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦የአካል ጉዳተኞችን የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ በቅንጅት የሚሰራው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። ትምህርት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዲስአቢሊቲስ ኤንድ ዴቫሎፕመንት ድርጅት ጋር በትብብር ያዘጋጀውና የአካል ጉዳተኞችን የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ የምክክር መድረክ ዛሬ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል። በምክክር መድረኩ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የአካል ጉዳተኞችን የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ ለግብአት አቅርቦትና ለመሰረተ ልማት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አካል ጉዳተኞችን ያካተተ ትምህርት ስርአት እንዲኖራቸው ከማድረግ ጀምሮ ቴክኖሎጂን የማሟላት ሥራው ትኩረት ተሰጥቶት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን እና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከል ዲን ደሳለኝ በየነ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በዩኒቨርሲቲው የአካል ጉዳተኞችን የትምህርት አቀባበል ለማሳደግ ለግብአት አቅርቦትና ለመሰረተ ልማት ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል። አካታችና ሁሉን አቀፍ የትምህርት አሰጣጥ ለመተግበርም በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ሥርአት መዘርጋቱን ነው የገለጹት። አካል ጉዳተኞችን ያማከለ የትምህርት የመሰረተ ልማትና የቴክኖሎጂ አቅርቦትን ለመዘርጋት በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ ነው ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዲስአቢሊቲስ ኤንድ ዴቫሎፕመንት ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ጌታሁን ስምኦን (ዶ/ር) ናቸው። ለተግባራዊነቱም ተቋሙ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግና ግብአትን በማሟላት ለአካል ጉዳተኞች ምቹ የመማር ማስተማር ምህዳር እንዲፈጠር ሲሰራ መቆየቱን አስረድተዋል። አካታች የትምህርት ስርአትን በማጠናከር አካል ጉዳተኞች ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆኑንም ጠቁመዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉ አካል ጉዳተኞች በበኩላቸው፤ የአካል ጉዳት ያለባቸው ተማሪዎችን የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት በትብብር መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የጅማ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዓመት የህግ ተማሪ ዘለቀ ሽፈራው፣ ዩኒቨርሲቲው አካል ጉዳተኞች በትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የዘረጋው ቴክኖሎጂና መሰረተ ልማት የሚበረታታ መሆኑን ተናግሯል። የአካል ጉዳተኞችን ውጤታማነት ለማሳደግ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከሚሰራው ስራ በተጨማሪ በታችኛው የትምህርት እርከንም ጠንካራ ሥራ መስራት ይገባል ብሏል። አካል ጉዳተኞችን በማብቃቱ ሥራ ወላጆችና ማህበረሰቡ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸውም ተናግሯል። በመድረኩ ላይ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ እንግዶች፣ አካል ጉዳተኞችና የትምህርት ሚኒስቴር ተወካዮች ተገኝተዋል።
ኢኮኖሚ
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ ሊሰጠው ይገባል
Dec 27, 2025 23
አክሱም፤ ታህሳስ 18/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ ሊሰጠው ይገባል ሲሉ በአክሱም ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ። ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነቷን በውል ባልታወቀ ምክንያት እንዲታጣ ተደርጓል። የባህር በር ማጣት የብዙዎች ቁጭት ሆኖ ቆይቶ አሁን ላይ የትውልድ ጥያቄና የሀገር የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ምላሽ እንዲያገኝ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ግልጽ የሆኑ ምክንያቶች ያሉት ሲሆን የሀገሪቱ የምጣኔ ሃብት እድገትና የህዝብ ቁጥር መጨመር፣ የጂኦ ፖለቲካዊ ሁኔታ፣ የታሪክና የህግ ምክንያቶችን መጥቀስ ይቻላል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ የኢዜአ ሪፖርተር ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ከመሰረታዊ አገልግሎቱ ባለፈ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል መምህር በረከት ሀይለ፤ ኢትዮጵያ ግዙፍ ኢኮኖሚ እና ብዙ ህዝብ ይዛ የባህር በር ልታጣ አይገባም ብለዋል። ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር በቅርብ ርቀት ላይ እያለች ሌሎች ከሩቅ መጥተው የሚጠቀሙበትን ባህር መንፈግ ከህግም ሆነ ከሞራል አንፃር ተቀባይነት የሌለው መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት መሆን እንዳለባት ገልጸው ይህንንም ማሳካት የትውልዱ አደራ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ መምህርት ፍረወይኒ ፍስሃ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የመኖርና ያለመኖር ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል። የባህር በር ጥያቄው የታሪክ እውነታና የህግ ተቀባይነት ያለው፣ መልክዓ ምድርንና ፍትሃዊነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸው በሁሉም መመዘኛዎች የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት መብት ሊከበር ይገባል ብለዋል። በመሆኑም የትውልድ ጥያቄ የሆነው የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ምላሽ ማግኘት ያለበት የህዝብ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል። በአክሱም ከተማ ነዋውና የህግ ባለሙያው አብራሃም አለማ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ በህግም ይሁን በታሪክ ተቀባይነት ያለው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት ኢትዮጵያ በአቅራቢያዋ ባለው ቀይ ባህር የባህር በር ባለቤትነት መብቷ ሊከበር ግድ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጠ የቡና ዝርያዎች ለአልሚዎች ተላልፈዋል
Dec 27, 2025 23
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡- ሥነ-ምኅዳርን መሠረት በማድረግ ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጠ ከ42 በላይ የቡና ዝርያዎች ለአልሚዎች መተላለፋቸውን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን አስታወቀ። የቡናን ምርትና ምርታማነት ለመጨመር ከሚያስፈልጉ ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ ምርጥ ዘርን መጠቀም መሆኑን ባለሥልጣኑ አስገንዝቧል። በመረጣ እና በማዳቀል በጅማ ግብርና ምርምር ማዕከልና በሥሩ በሚገኙ ንዑስ የምርምር ማዕከላት አማካኝነት ሥነ-ምኅዳርን መሠረት ያደረጉ የቡና ዝርያዎች መለቀቃቸውን በባለሥልጣኑ የቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ደፈረስ ለኢዜአ ተናግረዋል። በዚህም መሠረት ለደጋ አካባቢ ተስማሚ የሆኑ 14 የቡና ዝርያዎች መለቀቃቸውን ጠቁመው፤ ምርታማነታቸውም በምርምር ማሳ ላይ በሔክታር ከ12 ነጥብ 2 እስከ 24 ነጥብ 41 ኩንታል መሆኑን አስረድተዋል። በተመሳሳይ ለወይና ደጋ አካባቢ ተስማሚ የሆኑ 16 የቡና ዝርያዎች መለቀቃቸውን የገለጹት አቶ ፍቃዱ፤ የእነዚህ ቡና ዝርያዎች ምርታማነት ከ14 ነጥብ 8 እስከ 24 ኩንታል በሔክታር መሆኑን ተናግረዋል። እንዲሁም ለሞቃታማ (ዝቅተኛ) አካባቢ ተስማሚ የሆኑ 12 የቡና ዝርያዎች መለቀቃቸውን ጠቅሰው፤ ከ13 ነጥብ 2 እስከ 25 ነጥብ 4 ኩንታል በሔክታር ምርት እንደሚያስገኙ አስታውቀዋል። በሌላ በኩል አካባቢ በቀል የሆኑ ለወለጋ አካባቢዎች አራት፣ ለምዕራብ ሐረርጌ አራት፣ ለይርጋ ጨፌ ስድስት እና ለሊሙ አንድ የቡና ዝርያዎች መለቀቃቸውን ነው የተናገሩት። የቡናን ምርታማነት በምርምር በማጎልበት ከዘርፉ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ቡና ዋና መዳረሻ እየሆነች የመጣችው ቻይና
Dec 27, 2025 52
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 18/2018(ኢዜአ)፦ ቻይና የኢትዮጵያን ቡና በብዛት እየገዙ ከሚገኙ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። የኢትዮጵያ ቡና በቻይናውያን ዘንድ ተወዳጅነቱ እየጨመረ መጥቷል። ቻይና የዛሬ አምስት አመት የኢትዮጵያን ቡና በመግዛት ከነበረችበት 33ኛ ደረጃ በተያዘው አመት ወደ 4ኛ ደረጃ ከፍ ብላለች። የኢትዮጵያ ቡናን በቻይና ገበያ የበለጠ ለማስተዋወቅ እና ኤክስፖርቱን ለማሳደግ ያለመ ኮንፍረንስ በቻይና ሁናን ግዛት እየተካሄደ ይገኛል። በቻይና ሁናን ግዛት ጁጆ ከተማ በተዘጋጀው ኮንፍረንስ ከ700ሺህ በላይ ሰዎች የኢትዮጵያን ባለ ልዩ ጣዕም ቡና ለማስቀመስ እቅድ ተይዟል። ቻይና የኢትዮጵያ ቡና ዋና መዳረሻ እየሆነች የመጣች ሲሆን የዛሬ አምስት አመት የኢትዮጵያን ቡና በመግዛት ከነበረችበት 33ኛ ደረጃ በተያዘው አመት ወደ 4ኛ ደረጃ ከፍ ብላለች። ኮንፍረንሱ ቻይና በኢትዮጵያ ቡና ያላትን ተደራሽነት የበለጠ ለማሳደግና ወደ ቻይና የሚላከውን የቡና መጠን ማሳደግ ያለመ መሆኑን ኢዜአ ከስፍራው ያገኘው ያመለክታል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጀው የኢትዮ ቻይና የወዳጅነት ኮሚቴ የተሰኘ ድርጅት ነው። የጁጆ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ የቻይና ከፍተኛ አመራሮች በሁነቱ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል። በኮንፍረንሱ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው፣ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢፋ ሙለታ(ዶ/ር)፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ፣ የቡና እና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ(ዶ/ር) እና ከተለያዩ ክልሎች የተውጣጡ አመራሮች ተገኝተዋል። ኢትዮጵያ በ2017 ዓ.ም ከ 35ሺህ ቶን በላይ ቡና ለቻይና ገበያ ማቅረቧ በመረጃው ተመላክቷል።
ግብርናን ማዘመን እና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የመንግስት ቁልፍ አጀንዳ ነው- ሚኒስትር አዲሱ አረጋ
Dec 27, 2025 38
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡- ግብርናን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመደገፍ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የመንግስት ቁልፍ አጀንዳ ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ ገለጹ። የግብርና ሜካናይዜሽንና የከተማ ግብርና ልማት ስትራቴጂዎች ላይ የባለድርሻ አካላት ምክክር እየተካሄደ ነው። የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ መንግስት የግብርናውን ዘርፍ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመደገፍ ውጤታማ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየሰራ ነው። መንግስት ዘርፉን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ብሎም በምግብ ራስን መቻልን ቁልፍ አጀንዳ አድርጎ እየሰራ ነው ብለዋል። የግብርና ሜካናይዜሽን ስትራቴጂ መዘጋጀቱ ግብርናው እንዲዘምንና የእሴት ሰንሰለቱን ከማሳጠር አኳያ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል። መንግስት ግብርናውን ለማዘመን የግብርና ሜካናይዜሽን ማሽነሪዎች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ ማድረጉንና ትራክተሮችን ጨምሮ በርካታ ኮምባይነሮች ለአርሶ አደሩ ማድረሱን ተናግረዋል። በዚህም ባለፉት ዓመታት ስድስት ነጥብ ሶስት ሚሊዮን ሄክታር መሬት በግብርና ሜካናይዜሽን ማልማት መቻሉን አመልክተዋል። ከማሽነሪ ብድር አቅርቦት ጋር በተያያዘ የሚታዩ ማነቆዎችን ለመፍታት የተለያዩ አማራጮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን አንስተዋል። የግብርና ሜካናይዜሽን ስትራቴጂ በአመለካከት ላይ ያለውን የተዛባ ግንዛቤ ለመፍታት እንዲሁም የማሽነሪ አጠቃቀም ላይ በቂ ስልጠና መስጠት ያስችላል ብለዋል። የከተማ ግብርና የግብርና ልማት ስትራቴጂም የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ከምናሳካባቸው ጉዳዮች አንዱ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ስትራቴጂው የከተማ መሬቶችን በአግባቡ ለመጠቀም ያስችላል ብለዋል። ባለፉት ጥቂት አመታት በከተማ ግብርና በተከናወኑ ተግባራት ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰው፣ ውጤቱ ቀጣይነት እንዲኖረው ወጥነት ባለውና ተቋማዊ በሆነ መልኩ መደገፍ ይገባል ብለዋል። በግብርና ትራንስፎርሜሽንና በከተማ ግብርና ልማት ስትራቴጂዎች ላይ ገለጻ እየተደረገ ሲሆን ባለድርሻ አካላት ግብዓት ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በውይይት መድረኩ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የፌዴራልና የክልል የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች፣ አጋር አካላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የዲጂታል ኢትዮጵያ ትግበራ የከተሞችን አገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን መሠረት ጥሏል
Dec 27, 2025 44
ጎንደር፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡- የዲጂታል ኢትዮጵያ ትግብራ የከተሞችን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን መሠረት መጣሉን የጎንደር ከተማ አስተዳደር የስማርት ሲቲ ዳይሬክተር ይልቃል ሙሉአለም (ዶ/ር) ገለጹ። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 መጠናቀቅን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በቅርቡ ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል። ኢዜአ ያነጋገራቸው የጎንደር ከተማ አስተዳደር የስማርት ሲቲ ዳይሬክተር ይልቃል ሙሉአለም (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ ከተሞችን በቴክኖሎጂ በማደራጀት ለተገልጋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል። ስማርት ሲቲን በመፍጠር የከተሞችን ምጣኔ ሀብታዊና ማህበራዊ አገልግሎቶች እንዲቀላጠፉ የራሱን ሚና እንደሚጫወትም ነው የገለጹት፡፡ በተለይም ዲጂታል ፋይናንስን ለማቀላጠፍና ወንጀልን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዲጂታል ኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ለማሳካትና ወጥ የሆነ የመረጃ አያያዝን በማጠናከር ለሀገራዊ እድገት ጉልህ ድርሻ እያበረከተ መሆኑንም ነው የገለጹት። የአርተፊሻል ኢንተለጀንስና የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መጀመር ዲጂታል ኢትዮጵያን ስኬታማ ለማድረግ ተጨማሪ አቅም እንደሚሆንም አስረድተዋል። የመንግስት አገልግሎት በቴክኖሎጂ ታግዞ መሰጠቱ ተጠያቂነትንና ግልጸኝነትን በማስፈን ሲስተዋሉ የነበሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ እንደ ይልቃል (ዶ/ር) ገለጻ፤ ኢትዮጵያ እስከ 2030 የሚዘልቅ የዲጂታል ስትራቴጂ መንደፏ ዓለም አቀፍ ተቀባይነትና ተወዳዳሪነቷን የሚያሳድግ ነው። ከአማራ ክልል ከተሞች መካከል ጎንደር በስማርት ሲቲ ቴክኖሎጂ የመጀመሪያና ፈር ቀዳጅ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ይህም የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማነቃቃት ያስችላል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በቅርቡ በይፋ ማስጀመራቸው የሚታወስ ነው፡፡
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የከተሞችን ዘመናዊነት ለማሳደግ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው
Dec 27, 2025 48
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡- የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በቴክኖሎጂ የዘመኑ ከተሞችን ለመፍጠርና የዜጎችን የአኗኗር ሁኔታ ለማሻሻል ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል ዕድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት የስትራቴጂው ቁልፍ ትልሞች መሆናቸውን መግለጻቸው ይታወቃል። እነዚህን ትልሞች ለማሳካት የሕዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማትን ማስፋፋት ቁልፍ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው ይህም ቴክኖሎጂን ሰው ተኮር በማድረግ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ ለማሻሻል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የመደመር መንግሥት ከተሞች የፈጠራ፣ የቴክኖሎጂ እና የብልጽግና ማሳያ እንዲሆኑ እየሰራ ነው። የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ከተሞችን ስሉጥ (ስማርት ሲቲ) ለማድረግ የሚያስችል ጠንካራ መሠረት መጣሉን ተናግረዋል፡፡ ይህም ከተሞች ከዕቅድ ዝግጅት ጀምሮ በዲጂታል መንገድ እንዲመሩ በማስቻል እና የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። በዚህም ለነዋሪዎች ምቹ ከተማ፣ የኤሌክትሮኒክ ግብይት እንዲሁም ለዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት የተቻለበት እንደነበረ አንስተዋል። በዚህም የሚታይ ውጤት እና ለከተሞች እድገት ትልቅ መሰረት ጥሎ በስኬት መጠናቀቁን ገልፀዋል። አዲሱ 2030 ዲጂታል ስትራቴጂ ከተሞች ከስማርት ከተማነት ባለፈ በቴክኖሎጂ የዘመኑ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። አዲሱ የከተማ ልማት ፖሊሲም ከስትራቴጂው ጋር በቀጥታ የሚዛመድ ሲሆን፤ የኃይል አጠቃቀምን፣ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን፣ የአገልግሎት አሰጣጥን እንዲሁም በሰዎች እንቅስቃሴ ውስጥ ብልህነትን የሚያሰርጽ መሆኑን አስረድተዋል። ዲጂታላይዜሽን በዜጎችና በመንግሥት እንዲሁም በአገልግሎት ሰጭና ተቀባይ መካከል መተማመንን የሚፈጥር መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡ የመረጃ ደኅንነትን በማረጋገጥ መረጃዎችን ለሀገር ዕድገት የመጠቀም ልምድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ መምጣቱንም በአብነት ጠቅሰዋል። የመደመር መንግሥት ከተሞች የፈጠራ፣ የቴክኖሎጂ እና የብልጽግና ማሳያ እንዲሆኑ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑንና ዲጂታላይዜሽን ለዚህ ስኬት ዋነኛው የመስፈንጠሪያ አቅም መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ፖሊሲ ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ተጣጣሚ በሆነ መልኩ የተዘጋጀ ነው
Dec 26, 2025 109
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ፖሊሲ ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ተጣጣሚ በሆነ መልኩ መዘጋጀቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፥ የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ረቂቅ ፖሊሲን አስመልክቶ ከዲጂታል ካውንስል አባላት ጋር በበይነ መረብ ውይይት አካሂደዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በሁሉም መስክ የሥራ ፈጠራ ባህልን በማስረጽ ቀጣይነት ያለው እና ፈጣን ዕድገትን ዕውን ለማድረግ ኢንተርፕረነርሽፕ ቁልፍ መሳሪያ ነው ብለዋል። ፖሊሲው በዋናነት ሁሉን አቀፍ እና አካታች ሀገራዊ የኢንተርፕረነርሽፕ ንቅናቄን በማቀጣጠል በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ተጣጣሚ በሆነ መልኩ የዲጂታል ሥራ ፈጠራንና ተወዳዳሪነትን የሚያበረታታና የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል። የፖሊሲ ማዕቀፉ ችግር ፈች ማህበረሰብን ለመገንባት፣ የፈጠራ ባህልን ለማጎልበት፣ እሴትን ለመጨመር እንዲሁም ምቹ ስነምህዳርን ለመገንባት የሚያስችል የኢኮኖሚ ዕድገት ማዕቀፍ እንደሆነም ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያን የኢንተርፕረነርሽፕ ስነ-ምህዳርና የስራ ፈጠራ ውጥኖችን አቅጣጫ በመስጠት የመምራት ቁልፍ ሚና አለው ነው ያሉት። በተለይ የኢንተርፕረነርሽፕ ስነ-ምህዳሩን ሊያሻሽሉ የሚችሉ የጋራ አመለካከቶችን፣ እምነቶችንንና ባህሪያትን ለማጎልበት በእጅጉ እንደሚያግዝ አብራርተዋል። በውይይቱ የልማት ፖሊሲው የታለመለትን ውጤት ማምጣት እንዲችል በፖሊሲው ትግበራ ወቅት የሚታዩ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖችን በመለየት በየደረጃው ወጥና ጠንካራ የክትትል ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ከዲጂታል ካውንስሉ ጋር መግባባት መፈጠሩን ገልጸዋል። በኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ እና ግብዓቶችን በመጨመር የልማት ፖሊሲ ሰነዱ ወደ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ተልኮ እንዲፀድቅ መወሰኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
የዲላ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ ዲጂታል አገልግሎት ተገልጋዮች ፈጣን መስተንግዶ እንዲያገኙ አስችሏል
Dec 26, 2025 82
ዲላ፤ ታህሳስ 17/2018(ኢዜአ)፦የዲላ ከተማ ማዘጋጃቤታዊ አገልግሎት ዲጂታል መደረጉን ተከትሎ ፈጣን አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። አገልግሎቱን በማዘመን ከወረቀት ንክኪ ነጻ መደረጉ ለተጠቃሚዎች ፈጣን አገልግሎት ለመስጠትና ገቢን ለማሳደግ ከማስቻሉ ባለፈ የተቋሙን የመፈጸም አቅም ማሳደጉም ተመላክቷል። የከተማው ነዋሪዎች ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ዲጂታል መደረጉን ተከትሎ ፈጣንና የተሻለ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን አንስተዋል። ከዚህ ቀደም በማዘጋጃ ቤቱ አንድ ጉዳይ ለማስጨረስ በቀጠሮ የሚያጠፉት ጊዜና ጉልበትን ከማስቀረቱ ባለፈ ለብልሹ አሰራር የነበረባቸውን ተጋላጭነትም በእጅጉ መቀነሱን ተናግረዋል። ኢዜአ ካነጋገራቸው ነዋሪዎች መካከል አቶ ከበደ ወራሳ፤ በወረቀት ያለውን የካዳስተር ይዞታቸውን ወደ ዲጂታል ለመቀየር እንደመጡ ገልጸው፣ በአንድ ቀን ጉዳያቸውን ጨርሰው በመመለሳቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል። ይህም ከዚህ ቀደም አንድ ጉዳይ ለማስጨረስ ለበርካታ ቀናት ሲደርስባቸው የነበረውን እንግልትና ምልልስ በማስቀረት የጊዜና የገንዝብ ብክነትን እንዳስቀረላቸው አንስተዋል። በመንደራቸው ከረጅም ጊዜ በፊት ተለክቶ ያልተሰራ መንገድ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ላይ ጫና በመፍጠሩ ይህን የህዝብ ቅሬታ ይዘው እንደመጡ የገለጹት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ክፍሌ ሎላ ናቸው። በማዘጋጃ ቤቱ በተጀመረው የፊት ለፊት አገልግሎት የልማት ጥያቄያቸው ለሚመለከተው የሥራ ሃላፊ ቀርቦ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ማግኘታቸውን ተናግረዋል። በማዘጋጃ ቤቱ የተጀመረው ዘመናዊ አገልግሎት ከዚህ ቀደም አንድ ጉዳይ ለማስጨረስ ከቢሮ ቢሮ የቀጠሮ ምልልስ ነበረው፤ በዚህም ጊዜና ጉልበት ይባክን ነበር ብለዋል። ማዘጋጃ ቤቱ አገልግሎቱን ማዘመኑ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማስቻሉ ባለፈ ለብልሹ አሰራር የነበራቸውን ተጋላጭነት በእጅጉ መቀነሱን አስረድተዋል። የመኖሪያ ቤት ጥያቄያቸውን ይዘው ለረጅም ጊዜ ምላሽ ሳያገኙ ተቸግረው መቆየታቸውን የተናገሩት ወይዘሮ ሃያሌ ሠራዊት የተባሉ ነዋሪ በበኩላቸው፣ ማዘጋጃ ቤቱ አገልግሎቱን ማዘመኑን ተከትሎ ጥያቄያቸው ሰሚ አግኝቶ በሚመለከተው የሥራ ክፍል እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። ዲጂታል አገልግሎቱ በማዘጋጃ ቤቱ ከዚህ በፊት የሚነሳውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግር የቀረፈ ነው ብለዋል። ተቋሙ ከተያዘው በጀት ዓመት ጀምሮ አሰራሩን በማዘመን የግንባታ፣ መሬት አስተዳደር፣ የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢን ጨምሮ 71 አገልግሎቶችን ዲጂታል ማድረጉን ያነሱት ደግሞ የዲላ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሃብታሙ ተፈሪ ናቸው። በዚህም አገልግሎቶች ከወረቀት ንክኪ ነጻ በሆነ መንገድ እየተሰጡ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ይህም ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን ማህበረሰብ ጊዜና ጉልበት ለመቆጠብ ማስቻሉን ጠቁመዋል። በቴክኖሎጂ ታግዞ የሚሰራው ሥራ የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ከመፍታት ባለፈ የተቋሙን የእለት ገቢና የመፈጸም አቅም አሳድጎታል ብለዋል።
ስፖርት
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲዳማ ቡናን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈ
Dec 27, 2025 26
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲዳማ ቡናን 5 ለ 0 ረትቷል። በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሸገር ከተማን አሸነፈ በአበበ በቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ንግስት በቀለ ሁለት ግቦችን ስታስቆጥር እሙሽ ዳንኤል፣ መሳይ ተመስገን እና ረድኤት አስረሳኸኝ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሊጉ 10ኛ ድሉን ያስመዘገበው የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ32 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። ከሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ዝቅ አድርጓል። በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ሲዳማ ቡና በ18 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል። የቡድኖቹ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ በነበረው ተሳትፎ ምክንያት የተራዘመ ነው። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በያዝነው ሳምንት የመጀመሪያ ተስተካካይ ጨዋታውን ከሸገር ከተማ አድርጎ 2 ለ 1 ማሸነፉ የሚታወስ ነው። የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ዙር መርሃ ግብር መጠናቀቁ ይታወቃል።
ውድድሩ የከተማዋን ነዋሪዎች ማህበራዊ ትስስር ለማጎልበት ያግዛል
Dec 27, 2025 23
ነቀምቴ ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ በተካሄደው ስፖርት ለሰላም ውድድር የከተማዋ ነዋሪዎች ማህበራዊ ትስስራቸውን ለማጎልበት ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ማሳየታቸው ተገለጸ፡፡ በኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና በነቀምቴ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪነት የስፖርት ለሰላም የሩጫ ውድድር ዛሬ በነቀምቴ ከተማ ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ በኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ማርቆስ ገነቲ፣ የምሥራቅ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ወጋሪ ነገራ፣ የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሰረት ሀይሉ ፣ የወለጋ ዩኒቨርስቲ መምህራን እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። ሩጫውን ያስጀመረው የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ማርቆስ ገነቲ ባስተላለፈው መልዕክት፤ የሰላም ሩጫው የተካሄደው ሰላምን ለማፅናት በሚደረገው ጥረት የሕብረተሰቡን የጎላ ተሳትፎ ለማስገንዘብ ነው ብሏል። በሰላም ሩጫውም ነዋሪዎቹ ሰላምን ጠብቆ ለማዝለቅ፣ ልማትን ለማስቀጠልና ማህበራዊ ትስስራቸውን ለማጎልበት ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ማሳየታቸውን ተናግሯል። የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሰረት ሀይሉ በበኩላቸው፤ አስተዳደሩ የሕግ የበላይነት በማስከበር ሰላምን በማፅናት የሕብረተሰቡን የመሰረተ ልማት ፍላጎት ለማሟላት አበክሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ዛሬ የተካሄደው የሰላም ሩጫም በአካባቢው ያለውን ሰላምና ልማትን አጉልቶ ያንጸባረቀ መሆኑን ገልጸዋል። ከተማዋ በፈጣን የእድገት ጎዳና ላይ ናት ያሉት ከንቲባው፤ ይህንን እውነታ ለማሳየት የሰላም ሩጫው የማይተካ ድርሻ አለው ብለዋል። የነቀምቴ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች በሰላም ሩጫው በመሳተፍ ከመንግስት ጋር በመቀናጀት ልማትና ሰላምን ለማፅናት ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋፍ ማረጋገጣቸውን አንስተዋል። 10 ኪሎ ሜትር በሸፈነው ሩጫ ላይ የተሳተፈችው ከኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ሳጅን አትሌት ጉተኒ ሻንቆ ፤ በወለጋ አካባቢ ያለውን ሰላምና ልማት በማድነቅ የሚበረታታ መሆኑን ተናግራለች። ዛሬ የተካሄደው ስፖርታዊ ውድድር የአካባቢውን ትክክለኛ ገጽታ ለማሳየት እንደሚያግዝም ጠቁማለች።
የሊጉ መሪ አርሰናል ከብራይተን ጋር ይጫወታል
Dec 27, 2025 59
አዲስ አበባ፤ታህሳስ 18/2018(ኢዜአ):- በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ውሎ ሰባት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በ"ቦክሲንግ ደይ" መርሃ ግብ ማንችስተር ዩናይትድ ኒውካስትል ዩናይትድን አሸነፈ በአፍሪካ ዋንጫ ናይጄሪያ ከቱኒዚያ ሴኔጋል ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ ምሽት 12 ሰዓት ላይ አርሰናል ብራይተንን በኤምሬትስ ስታዲየም ያስተናግዳል። አርሰናል ሊጉን በ39 ነጥብ እየመራ ነው። ብራይተን በ24 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ከቀኑ 9 ሰዓት ከ30 ላይ ኖቲንግሃም ፎረስት ከማንችስተር ሲቲ በሲቲ ግራውንድ ስታዲየም ይጫወታሉ። ኖቲንግሃም ፎረስት በ18 ነጥብ 17ኛ ደረጃን ይዟል። ማንችስተር ሲቲ በ37 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች በተመልካቾች ትኩረትን አግኝተዋል። ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ ቼልሲ ከአስቶንቪላ በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታም ይጠበቃል። ቼልሲ በ29 ነጥብ አራተኛ እና አስቶንቪላ በ36 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። በሌሎች መርሃ ግብሮች ሊቨርፑል ከዎልቭስ፣ ዌስትሃም ዩናይትድ ከፉልሃም፣ ብሬንትፎርድ ከቦርንማውዝ እና በርንሌይ ከኤቨርተን በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በአፍሪካ ዋንጫ ናይጄሪያ ከቱኒዚያ ሴኔጋል ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ
Dec 27, 2025 44
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሰባተኛ ቀን ውሎ የምድብ ሶስት እና አራት ሁለተኛ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ። በምድብ ሶስት ናይጄሪያ ከቱኒዚያ ምሽት አምስት ላይ በፌዝ ስታዲየም ይጫወታሉ። በምድቡ የመጀመሪያ ጨዋታዎች ናይጄሪያ ታንዛንያን 2 ለ 1 እና ቱኒዚያ ዩጋንዳን 3 ለ 1 አሸንፈዋል። ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ ዋንጫ ሲገናኙ የአሁኑ ለሰባተኛ ጊዜ ነው። የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ግንኙነታቸው ጋና እ.አ.አ በ1978 ባዘጋጀችው 11ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ነበር። ቡድኖቹ በደረጃ ጨዋታ ተገናኝተው ናይጄሪያ በባባ ኦቱ መሐመድ ግቦች 2 ለ 0 በማሸነፍ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ሀገራቱ በአህጉራዊው መድረክ ለመጨረሻ ጊዜ እርስ በእርሳቸው የተጫወቱት ካሜሮን እ.አ.አ በ2022 ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ነው። በጥሎ ማለፍ ላይ ተገናኝተው ቱኒዚያ በዩሱፍ ምሳክኒ ጎል 1 ለ 0 በማሸነፍ ለሩብ ፍጻሜ አልፋለች። ናይጄሪያ እና ቱኒዚያ በአፍሪካ ዋንጫው ባደረጓቸው ስድስት ጨዋታዎች ናይጄሪያ አራት ጊዜ ስታሸንፍ ቱኒዚያ ሁለት ጊዜ ድል ቀንቶታል። የሚያሸንፈው ቡድን ወደ ጥሎ ማለፍ መግባቱን ያረጋግጣል። ናይጄሪያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ፣ ቱኒዚያ አንድ ጊዜ አሸንፈዋል። በምድብ አንድ ሌላኛው መርሃ ግብር ዩጋንዳ ከታንዛንያ ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ በአል መዲና ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ብሄራዊ ቡድኖቹ በመጀመሪያ ጨዋታ ካስተናገዱት ሸንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታሉ። በተያያዘም የምድብ አራት ጨዋታዎችም ዛሬ ይደረጋሉ። ሴኔጋል ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በታንጀር ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። በምድቡ የመጀመሪያ መርሃ ግብር ሴኔጋል ቦትስዋናን 3 ለ 0፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ቤኒን 1 ለ 0 አሸንፈዋል። ሀገራቱ ከዚህ ቀደም በአፍሪካ ዋንጫ ሁለት ጨዋታዎችን እርስ በእርስ አድርገዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1968 ባዘጋጀችው ስድስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ ተገናኝተው ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 2 ለ 1 አሸንፋለች። ማሊ እ.አ.አ በ2002 ባዘጋጀችው 23ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሩብ ፍጻሜው ተገናኝተው ሴኔጋል 2 ለ 0 በማሸነፍ ለግማሽ ፍጻሜ አልፋለች። አሸናፊው ቡድን ጥሎ ማለፉን ይቀላቀላል። ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫን አንድ ጊዜ ያነሳች ሲሆን ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሁለት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ ሆናለች። በዚሁ ምድብ ቤኒን ከቦትስዋና ከቀኑ 9 ሰዓት ከ30 በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ሁለቱ ሀገራት የመጀመሪያ ድላቸውን ለማግኘት ይፋለማሉ።
አካባቢ ጥበቃ
የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራው ምርታማነትን ጨምሮልናል- አርሶ አደሮች
Dec 26, 2025 122
ሰቆጣ፤ ታኅሣስ 17/2018 (ኢዜአ)፡- ቀደም ሲል የሠራነው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ የሰብልና የእንስሳት መኖ ምርታማነትን ጨምሮልናል ሲሉ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር የፃግብጅ ወረዳ አርሶ አደሮች ተናገሩ። የአሥተዳደሩ የ2018 ዓ.ም የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ በፃግብጅ ወረዳ 01 ቀበሌ ማላባ ተፋሰስ ዛሬ ተጀምሯል። በዚሁ ወቅት አርሶ አደር ግርማይ ብዙ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ በየዓመቱ ሲያከናውኑት የቆየው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል። አካባቢያችን ዝናብ አጠር በመሆኑ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራን በልዩ ትኩረት አጠናክረን ቀጥለናል ብለዋል። የሠራናቸው እርከኖች የአፈር ለምነትና እርጥበት የመያዝ ዐቅም እንዲጨምር በማድረግ ምርታማነታችን እንዲያድግ አስችለዋል ሲሉም ገልጸዋል። የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራን በማጠናከራቸው የተጎዳው መሬታቸው ማጋገሙን ብሎም ከጎርፍ ስጋት ነጻ መሆኑንና የእንስሳት መኖ ምርታማነትም መጨመሩን የገለጹት ደግሞ አርሶ አደር ግርማይ ጌታሁን ናቸው። በዚህም መሠረት እየተገኙ ያሉ ጥቅሞችን አስፋፍቶ ለማስቀጠል በዘንድሮው የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራ በንቃት መሣተፍ መጀመራቸውን ተናግረዋል። አርሶ አደር ደሳለኝ መኮንን በበኩላቸው፤ ጠፍተው የነበሩ ምንጮች በተከናወኑ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራዎች ምክንያት ጎልብተው ለመስኖ ልማት መዋላቸውን እና በዚህም ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። በሌላ በኩል ዘንድሮ በ366 ተፋሰሶች የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ሥራ እንደሚከናወን የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ግብርና መምሪያ ኃላፊ አዲስ ወልዴ ጠቁመዋል። የተፋሰሶች ኅብረት ሥራ ማኅበራት በማቋቋም ሕብረተሰቡም እንዲጠብቅና እንዲንከባከብ በማድረግ ዘላቂ ተጠቃሚነቱን እንዲያረጋግጥ እየተሠራ ነው ብለዋል። የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ሥራ ዝናብ አጠር ለሆኑ ለአካባቢዎች ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም አስገንዝበዋል። ባለፉት ዓመታት የለሙ ተፋሰሶች ምርታማነትን ከማሳደግ በተጨማሪ ለንብ ማነብ ሥራ ምቹ ሁኔታ መፍጠራቸውንም አስረድተዋል። ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋጋጥ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራን በይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ የተናገሩት ደግሞ የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ምክትል አሥተዳዳሪ፣ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ሹመት ጥላሁን ናቸው። በአሥተዳደሩ በዘንድሮው በጋ ከ138 ሺህ በላይ ሰዎችን በማሳተፍ በሚካሄደው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ሥራ ከ2 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት እንደሚሸፈን ተገልጿል።
የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ አርሶ አደሮች ምርታማነታቸው እንዲያድግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Dec 24, 2025 155
ባሕርዳር ፤ ታህሳስ 15/2018 (ኢዜአ)፡ - ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የተጎዳው መሬታቸው አገግሞ ምርታማነታቸው እንዲያድግ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው በባሕርዳር አስተዳደር የዘንዘልማ ቀበሌ አርሶ አደሮች ተናገሩ። የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ዛሬ በዘንዘልማ ቀበሌ በንቅናቄ አስጀምሯል። በማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢው አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል። ከተሳታፊ አርሶ አደሮች ውስጥ የዘንዘልማ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ሙላት መኮንን ፤ ለዓመታት ያከናወንነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የልፋታችንን ዋጋ መልሶ እየከፈለን ነው ሲሉ ለኢዜአ ገልጸዋል። በዚህም ሰብልን ማብቀል ወደ ማቆም ተቃርቦ የነበረው መሬታቸው ለምነቱ እንዲጨምር በማድረጉ የሰብል ምርታማነታቸው እንዲያድግ ብሎም በቂ የእንስሳት መኖ እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸው ተናግረዋል። በተጨማሪም በማሳቸው አካባቢ የተከሏቸው የማንጎና ሌሎች የፍራፍሬ ተክሎች ለውጤት በቅተው ተጠቃሚ እንደሆኑ አንስተው፤ዛሬ በተጀመረው ስራ ያለምንም ቀስቃሽ በንቃት መሳተፋቸውንና እንደሚቀጥሉበትም ገልጸዋል። አርሶ አደር ደስታው ማንዴ በበኩላቸው፤ ተጠቃሚነታችንን እያረጋገጠልን ያለው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ በመጀመሩ ተደስቼያለሁ ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወነው ስራ ምርታማነታቸው ማደጉን ገልጸው፤ ያገኘሁትን ጥቅም ለማሳደግም ዛሬ በተጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ያለማንም ቀስቃሽ ወጥተን እየሰራን ነው ሲሉ ገልጸዋል። በባሕር ዳር ከተማ ዛሬ በተጀመረው የተፋሰስ ልማት ስራ በጥራትና በውጤታማነት ተምሳሌት እንዲሆን አስፈላጊው እገዛ እንደሚደረግ የገለጹት ደግሞ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ መሰሉ ብርሃኑ ናቸው። ባለፉት ዓመታት የተራቆቱ አካባቢዎችን በመለየት የአፈርና ውሃ እቀባ ስራ በመሰራቱና ከእንስሳት ንክኪ ነጻ በመደረጉ የአየር ንብረቱ እንዲስተካከልና የዝናብ መጠኑ እየጨመረ እንዲመጣ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል። በሚለሙ ተፋሰሶች ላይ አርሶ አደሩ የፍራፍሬና የመኖ ችግኞችን እንዲተክል በማድረግ ዘላቂ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱን እንዲያረጋግጥ የተጀመረው ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ፤ የዘንድሮው የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ልማት ስራ በአስተዳደሩ ስር በሚገኙ በ12 የገጠር ቀበሌዎች በጥራት እንደሚካሄድ ገልጸዋል። በተለዩ ተፋሰሶች ከ1ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለማከናወን ዛሬ የተጀመረው ተግባር በቀጣይ ለ30 ቀናት እንደሚቆይ ተናግረዋል።
በመገጭ ግድብ አዋሳኝ በሆኑ ተፋሰሶች የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ማከናወን ተጀመረ
Dec 24, 2025 186
ጎንደር፣ ታኅሣስ 15/2018 (ኢዜአ)፡- የመገጭ የመስኖና የመጠጥ ውኃ ግድብን ከደለል ለመጠበቅ የሚያስችል ሕብረተሰቡን ያሳተፈ የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ዛሬ ተጀምሯል። የዘንድሮው የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት በጎንደር ከተማ አሥተዳደር ድባ ደፈጫ ቀበሌ ተካሂዷል፡፡ በዚሁ ወቅት የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው እንዳሉት፤ የዘንድሮው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራ የመገጭ ግድብ አዋሳኝ በሆኑ 18 ተፋሰሶች ላይ ይካሄዳል። በዚህም መሠረት የማሳ እርከንና ክትር ሥራ እንደሚሠራና ሀገር በቀል ችግኞችም እንደሚተከሉ ጠቁመዋል። የጎንደር ከተማን ሕዝብ የረጅም ዓመታት የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ጥያቄ በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ እየተገነባ ያለውን ግድብ በደለል እንዳይሞላ ከወዲሁ መጠበቅ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ አርሶ አደሮች ምርታማነታቸው እንዲያድግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል በክልሉ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ ለማጠናከር ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል በዞኑ በአንድ ሺህ 52 ተፋሰሶች ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ እየተከናወነ ነው በአሥተዳደሩ ሥር በሚገኙ 11 የገጠር ቀበሌዎች 847 ሔክታር የሚሸፍን የእርከንና ክትር ሥራ በግድቡ ተፋሰሶች ይከናወናል ያሉት ደግሞ የከተማ አሥተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አበራ አደባ ናቸው፡፡ ለአንድ ወር በሚቆየው የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ከ8 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል። ቀደም ሲል በሕብረተሰቡ ተሳትፎ የተከናወኑ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራዎች የአፈር ለምነትን በመጨመር የሰብል ምርታማነት እንዲያድግ ማስቻላቸውንም አንስተዋል። በለሙ ተፋሰሶች በእንስሳት ማድለብ፣ በንብ ማነብ፣ በወተት ሀብትና በፍራፍሬ ልማት ዘርፍ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እየጨመረ መምጣቱንም አመላክተዋል። በሥራው የተሳተፉ አርሶ አደሮች በበኩላቸው፤ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ሥራ በአነስተኛ መሬት ብዙ ምርት እንድናገኝና ለእንስሳት በቂ የመኖ እንድናቀርብ አስችሎናል ብለዋል፡፡ የአፈርና ውኃ ዕቀባ ሥራ ምንጮች ጎልብተው መስኖ እንዲጠቀሙ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸውም ጠቅሰዋል።
በክልሉ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ ለማጠናከር ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል
Dec 24, 2025 131
ባሕርዳር፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሁሉም ሰው የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተመላከተ። የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ በዘንዘልማ ቀበሌ ዛሬ ተጀምሯል። በመርሃ ግብሩ የተገኙት የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ መሰሉ ብርሃኑ እንዳሉት፤ የተጎዳ አካባቢን ወደ ነበረበት ለመመለስ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ማጠናከር ያስፈልጋል። ከተያዘው ወር መግቢያ ጀምሮ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በተለዩ ተፋሰሶች የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ዘንዘልማ ቀበሌ የተጀመረው የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራ ጣናን ከደለል የሚታደግ እንደሆነም ገልጸዋል። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የተጀመረው የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራን በውጤታማነት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሁሉም ሰው የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባም አመልክተዋል። የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤ ከዛሬ ጀምሮ ለ30 ቀናት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራው በ12 ቀበሌዎች በተለዩ 24 ተፋሰሶች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ስራው ጥራቱን በጠበቀና ዘላቂነት ባለው መልኩ በማከናወን ወደ ጣና ኃይቅ የሚገባውን ደለል መከላከል በሚያስችል አግባብ እንዲከናወን ክትትል እንደሚደረግ ተናግረዋል። በዘንዘልማ ቀበሌ በተጀመረው የበጋ ወራት የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ መርሃ ግብር የክልልና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎችና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት፤ የአፍሪካ ህብረት የ2026 መሪ ሀሳብ ዋና የትኩረት አጀንዳ
Dec 26, 2025 139
39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ነው። መሪ ሀሳቡን ያረቀቀው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የግብርና፣ ገጠር ልማት፣ ብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ ከባቢ አየር ኮሚሽን ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የዘንድሮው መሪ ቃል ከአጀንዳ 2063 ጋር የተቆራኘ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት ዘላቂ ልማት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ከአጀንዳ 2063 ግቦች ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። ሁሉም አፍሪካዊ ንጹህ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና በቂ ውሃ ለመጠጥ፣ ለግብርና፣ ለኢንዱስትሪ እና ለሌሎች ፍላጎቶቹ እንዲያገኝ የማድረግ ራዕይን ለማስተዋወቅ እድል እንደሚፈጥርም ታምኖበታል። ህብረቱ የውሃ ደህንነት እንደ አህጉር የተያዙ ስትራቴጂካዊ ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን በማዕቀፎቹ አስቀምጧል። ውሃ እና ንጽህና የኢኮኖሚ እድሎችን በማስፋት፣ የስራ አጥነት ምጣኔን በመቀነስ፣ የስደቶችና ተፈናቃዮችን ጫና ለማቃለል እንዲሁም ለሰላምና ደህንነት መስፈን አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተመላክቷል። የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ህብረቱ ውሃ እና ንጽህና ለጤና፣ ለኢኮኖሚ እድገት፣ የምግብ ዋስትና መረጋገጥና ዘላቂ የአካባቢ ምህዳር ለመፍጠር መሰረት መሆኑን የበለጠ እውቅና እንደተሰጠው አመልክቷል። ሁሉን አቀፍ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይገበር የውሃ ደህንነትን የማረጋገጥ አላማ ካለው የአፍሪካ የውሃ ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነው። የዘንድሮው መሪ ቃል የአፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ጥረቶችን ያስተሳሰረ ድልድይ ሆኗል። በዘላቂ ልማት ግቦች ውስጥ ያለው ግብ ስድስት ከውሃ እና ንጽህና ጋር የተያያዘ ነው። ይህ ግብ እ.አ.አ በ2030 ለሁሌም ዜጋ ደህንነቱ የተረጋገጠ ውሃ አቅርቦትና የንጽህና አጠባበቅን ተደራሽ የማድረግ አላማ አለው። የአየር ንብረት ለውጥ፣ የህዝብ እድገት፣ የከተሜነት በፍጥነት መስፋፋትና ውሃ በአግባቡ አለመጠቀም የውሃ ደህንነት እና ዘላቂ አቅርቦት ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። የንጽህና አጠባበቅ የአፍሪካ አንዱ ፈተና ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች መሰረታዊ የሚባል የንጽህና መጠበቂያ መሰረተ ልማቶችን አያገኙም። ይህም እንደ ኮሌራ ላሉ የውሃ ወለድ በሽታዎች መስፋፋት ምክንያት ሆኗል። የተቀናጀ የውሃ አስተዳደር ስርዓት፣ ድንበር ተሻጋሪ ትብብር፣ ለዘላቂ መሰረተ ልማት የሚፈሰወን መዋዕለ ንዋይን ማሳደግ፣ ውሃ በድጋሚ አጣርቶ መጠቀም፣ የውሃ ሀብቶችን መጠበቅ፣ ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር እና ለውሃ ደህንነት ትኩረት የሚሰጡ ፖሊሲዎችና ማዕቀፎችን በውጤታማነት መተግበር ያሉትን እድሎች በዘላቂነት ለመፍታትና ፈተናዎችን ለመቅረፍ ያስችላል። ደህንነቱ የተረጋገጠ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ላይ ያለፈውን ኢንቨስትመንት ማሳደግ፣ የቆሸሸ ውሃ በአግባቡ ማከም፣ የንጽህና አጠባበቅ ማስፋትና የግንዛቤ ፈጠራ ስራን በስፋት ማከናወን፣ ማህበረሰብ መር የንጽህና አጠባበቅ ኢኒሼቲቮችን ትግበራ ማስፋት፣ ጠንካራ የፖሊሲ ማዕቀፎችና ሀገር በቀል አቅምን መገንባት ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓትን መፍጠር ያስችላል። “ዘላቂ የውሃ አቅርቦት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ቃል ለአፍሪካ ዘላቂ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና ጤናማ ማህበረሰብ ግንባታ ያላቸውን ቁልፍ ሚና የሚያሳይ ነው። የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ማድረግ መሰረታዊ መብቶች እንዲጠበቁ ከማድረግ ባለፈ ለማህበረሰብ ደህንነትና የተሻለ የኑሮ ዘይቤ፣ ለአካባቢ ጥበቃና ለአፍሪካ ብልጽግና መረጋገጥ ስትራቴካዊ አቅም ናቸው። 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ በሚካሄድበት ወቅት በመሪ ሀሳቡ በጥልቀት በመምከር የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦች ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል። ከመሪዎቹ ጉባኤ አስቀድሞ 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም እና 51ኛው የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኞች ስብሰባ ከጥር 4 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳሉ። ኢትዮጵያ 39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና የአፍሪካ ጣሊያን ስብሰባን ለማዘጋጀት ብሄራዊ የዝግጅት ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቀን ነው - የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
Dec 24, 2025 207
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15/2018(ኢዜአ)፦ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰብን ላለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶችና የዘር ማጥፋት ወንጀል በተመለከተ ለአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን ላቀረብነው ክስ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው ሲል የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ገለጸ። የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በኤርትራ መንግሥት አገዛዝ ደረሰብን ያለውን መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ጋምቢያ(ባንጁል) የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ላቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን አድንቋል። በኤርትራ መንግስት ላይ የቀረቡትን ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክስ ተቀብሎ በመዝገብ ቁጥር 868/25 መመዝገቡን፣ የክሱ ፍሬ ነገር እና ይዘት ተቀባይነት ያለው መሆኑን እውቅና በመስጠት የኤርትራ መንግስት እንዲመልስ ክሱን መላኩን ኮሚሽኑ ማስታወቁን ገልጿል። የድርጅቱ ሊቀ-መንበር ኢብራሂም ሀሩን በመግለጫቸው እንደተናገሩት፤ የኤርትራው መንግሥት በደናክል አካባቢ በቀይ ባህር አፋር ህዝቦች እየፈፀመ ያለው መጠነ ሰፊ፣ ስልታዊ፣ መንግስታዊ መር እና ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። በአሁኑ ወቅት እየደረሱ ነው ካሏቸው የመብት ጥሰቶች መካከልም ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ግድያዎች እና ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ማካሄድ፣ ያለ ፍርድ ማሰር እና ማሰቃየት፣ በሺዎች የሚቆጠሩትን መሰወር፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ማከናወን መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰው፤ በተለይም ከ300ሺህ በላይ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማፈናቀል እና ፆታዊ ጥቃትን የአገዛዙ የአፈና መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም ከሀገሪቱ ፖለቲካዊ አስተዳደር ማግለል፣ የቀይ ባህር አፋር ህዝብን ማንነትና ባህል ማጥፋትና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን መጣስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዚህም ድርጅቱ የአፍሪካ የሰብዓዊ እና የህዝቦች መብቶች ኮሚሽን ከ1993 ጀምሮ በኤርትራ መንግሥት እየደረሰባቸው ያለውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ክስ ማቅረባቸውን ገልጸዋል። እኤአ ጁን 04 ቀን 2025 በ122 ገጽ የተደራጀ ክስ ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ኮሚሽኑ የኤርትራ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ ክሱን መላኩን እንደገለጸላቸው ጠቁመዋል። ለክሱም ከተጠቀሙት ማስረጃዎች መካከል በድርጅቱ የተከናወነ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ግኝት፣ በተባበሩት መንግስታት እና በአፍሪካ የሰብዓዊና ሕዝባዊ መብቶች በኤርትራ ላይ የተደረጉ ምርመራዎች፣ ግኝቶችና ማስረጃዎች፣ የመብት ጥሰት የደረሰባቸው የቀይ ባሕር አፋር ተጎጂ ወገኖች እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የተገኙ የሰብዓዊ መብት ምርመራዎችን መቅረቡን ተናግረዋል። ድርጅቱ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት መከራ ለማዳን፣ የዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ድምፅ እንዲሆኑት፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት ትኩረት እንዲሰጡንና የኢሳያስ መንግስት ላይ ህጋዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ሰብዓዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንዲሁም ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጸንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው-ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
Dec 23, 2025 177
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 14/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እና ለረጅም ጊዜ ፀንቶ የቆየ አጋርነት አላቸው ሲሉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ኃላፊ አምባሳደር ኮንስታንሲያ አዴሊና ጋስፓራስ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አቅርበዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት (ዋይት ሃውስ) በተካሄደ ስነ ስርዓት የአምባሳደር ኮንስታንሲያን ሹመት በይፋ ተቀብለዋል። አምባሳደሯ በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው በአሜሪካ የአፍሪካ ህብረት ልዑክ ቢሮ ስራቸውን በይፋ ጀምረዋል። ዶናልድ ትራምፕ የአምባሳደር ኮንስታንሲያ የልዑኩ መሪ ሆኖ መመረጥ በጋራ የኢኮኖሚ እድሎች፣ በሉዓላዊ አመራር ሰጪነት እንዲሁም በሰላም እና ደህንነት ላይ የተመሰረተውን የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ጽኑ አጋርነት የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት እና አሜሪካ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በአፍሪካ ሰላም፣ ብልጽግና እና መረጋጋትን ማረጋገጥን ዋና ማዕከል ያደረገ ጠንካራ የአጋርነት ስራ እያከናወኑ እንደሚገኝ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት የማጠናከር ፍላጎት አላት -ተሰናባቹ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና
Dec 20, 2025 238
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ሽብርተኝነትን መዋጋትን ጨምሮ በቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ያላትን አጋርነት ለማጎልበት በጋራ መስራቷን እንደምትቀጥል ተሰናባቹ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና ገለጹ። አምባሳደር ጆርጅ ኦሪና የኢትዮጵያ እና ኬንያ የሁለትዮሽ ትብብር ጥልቅ የታሪክ ትስስር ያለው መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል። ሀገራቱ የኬንያው የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት እና መስራች አባት ጆሞ ኬንያታ እና ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ጊዜ አንስቶ ወዳጅነት እንደነበራቸው አውስተው ትብብሩ በከፍተኛ ደረጃ በሚደረጉ ጉብኝቶች እና ውይይቶች እየተጠናከረ መምጣቱን አመልክተዋል። በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ጠንካራ አጋርነት ፈጥረው እየሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ጨምሮ በቀጣናው ሽብርተኝነትን በመዋጋት እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ሰላም እና ደህንነት ለቀጣናው ዘላቂ ልማት ጠንካራ መሰረቶች ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ እና የኬንያ የንግድ ትብብር እያደገ መምጣቱን የገለጹት ተሰናባቹ አምባሳደር የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የሀገራቱን የኢኮኖሚ ትብብሩን አድማስ የበለጠ እንደሚያሰፋው ነው የተናገሩት። ቱሪዝም እና ንግድ የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲጎለብት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል። በቀጣይም የሁለቱ ሀገራት ቀጣናዊ ትስስር እንዲጎለብት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ፣ ኬንያንና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት የሚያስተሳስረው የ"ላፕሴት ፕሮጀክት" እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ጨምሮ በሌሎች መሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ቀጣናዊ ትስስሩን የሚያሳልጡ ትልቅ አቅም መሆናቸውን ተናግረዋል። አምባሳደር ጆርጅ ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በማስመረቋ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ግድቡ በቀጣናው ሽግግርን የሚፈጥር ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እና ኬንያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1963 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ቀጣናዊ መረጋጋት እና ደህንነት ፣ ንግድ እና የመሰረት ልማት ትስስር የሀገራቱ ዋንጫ የትብብር መስኮች ናቸው።
ሐተታዎች
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 375
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 558
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ለቀጣናዊ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ልህቀት እውቅና የሚሰጠው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት
Nov 28, 2025 881
የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተጀመረው በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) አማካኝነት ነው። ሽልማቱ የኢጋድ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ እና ተቋማዊ አቅምን የማጠናከር ጥረቶች አካል ነው። በኢጋድ ቀጣና በጋዜጠኝነት የላቀ ስራ ላከናወኑ የሚዲያ ባለሙያዎች በሽልማቱ እውቅና ይሳጣቸዋል። ሽልማቱ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ እና ሌሎችም ተጓዳኝ መድረኮችን የሚሸፍን ነው። የሚዲያ ስራው በቀጣናው በተለይም የድርቅ አይበገሬነት፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና ልማት ያሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆን ይኖርበታል። ዓመታዊው የኢጋድ ሽልማት የቀጣናዊ ተቋሙ አባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ በግላቸው የሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች እና የፎቶ ጋዜጠኞች ጨምሮ አጠቃላይ የሚዲያ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ነው። በተጨማሪም የቀጣናውን ጉዳይ የሚሸፍኑ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችም ይሳተፉበታል። በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስራቸውን በእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በኢጋድ አባል ሀገራት በሚገኙ ቋንቋዎች ያቀርባሉ። ከተለያዩ ሙያዎች የተወጣጡ የውሳኔ ሰጪ ወይም ገምጋሚ ቡድን ተቋቁሙ ስራዎቹን በመመዘን አሸናፊዎችን ይለያል። የመጀመሪያው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2023 በጅቡቲ ነበር። “የድርቅ ተጽእኖዎችን መቋቋም የሚያስችል ትብብር መፍጠር” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። መሪ ሀሳቡ በድርቅ፣ አይበገሬ አቅም መገንባት፣ የውሃ አስተዳደር እና ቀጣናዊ ትብብር ያተኮረ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመንት፣ ጦማር (ብሎግ) እና የፎቶ ጋዜጠኝነት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። በመጀመሪያው ሽልማት ላይ ከቀጣናው 105 ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን 14 ባለሙያዎች በዘርፎቹ ተመርጠው ተሸልመዋል። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ተቋሙ ሚዲያን ለግንዛቤ መፍጠር እና ቀጣናዊ ትብብር እንደ መሳሪያ ለመጠቀም ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ በወቅቱ ገልጾ ነበር። በድርቅ እና በምግብ ዋስትና ላይ ያሉ የጋራ ፈተናዎችን ለመፍታት የሚዲያ ሚና ወሳኝ እንደሆነም አመልክቷል። ሁለተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት የተካሄደው እ.አ.አ በ2024 በኬንያ ናይሮቢ ነው። “የተስፋ ትርክቶች፤ የቀጣናውን መጻኢ ጊዜ ሰላማዊ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና ሁሉን አቃፊ ማድረግ” የሽልማቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሽልማቱ በሰላም፣ ደህንነት፣ ሁሉን አሳታፊ የሆነ መጻኢ ጊዜን መፍጠር፣ ቀጣናዊ ትብብር እና መረጋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው። ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ህትመት፣ ፎቶግራፍ፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የእድሜ ዘመን ተሻላሚ ከሽልማት ዘርፎቹ ውስጥ ናቸው። ለ2024ቱ ሽልማት 318 የሚዲያ ባለሙያዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን 18 የሚዲያ ባለሙያዎች በዘርፎቹ ሽልማት አግኝተዋል። ሁለተኛው ሽልማት ከመጀመሪያው በዘርፎች እና በተሳታፊዎች ብዛት መሻሻል የታየበት ነበር። ይህም ሚዲያ በቀጣናዊ ሰላም፣ ደህንነት እና ቀጣናዊ ትስስር ላይ ያላቸውን ሚና የሚያሳይ ነው። ሶስተኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መጥቷል። ሽልማቱ ነገ ህዳር 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ “ ውጤታማ የአየር ንብረት ዘገባ ደህንነቱ ለተረጋገጠ፣ ጠንካራ እና የተረጋጋ ቀጣና” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከናወን ነው። ኢጋድ ቀጣናዊ ሁነቱን ያዘጋጀው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ነው። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያና የአፍሪካ ኢምፖርት እና ኤክስፖርት ባንክ (አፍሪኤግዚም ባንክ) ለፕሮግራሙ ድጋፍ እንደሚያደርጉም አስታውቋል። የዚህ ዓመት ሽልማት በአፍሪካ ቀንድ ውጤታማ የአየር ንብረት ትርክትን ለቀረጹ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች እውቅና የሚሰጥ ነው። የሁለት ቀን ሁነቱ የአየር ንብረት ጠንካራ ዘገባዎች እና ሀሳቦች የሚቀርቡበት እንዲሁም ቀጣናዊ ትብብር ጎልቶ የሚታይበት መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። የ2025 የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በ10 ዘርፎች የሚከናወን ነው። የህትመት ጋዜጠኝነት፣ የሬዲዮ ጋዜጠኝነት፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት፣ ዲጂታል ሚዲያ፣ ፎቶግራፈር፣ ሀገር በቀል ዘገባ፣ የዓመቱ ተጽእኖ ፈጣሪ/ የይዘት ቀራጭ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎች እና የእድሜ ዘመን ሽልማት የሽልማት ዘርፎቹ ናቸው። 400 የሚሆኑ የኢጋድ አባል ሀገራት ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ማስገባታቸውን ጠቁመው፤ ከዚህ ውስጥ 94 የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መሆናቸውን ኢጋድ አስታውቋል። ሽልማቱ በቀጣናው ገንቢ ሚና ያለው ጋዜጠኝነት እንዲጎለብት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አመልክቷል። ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የሚዲያ አዋርድ ማስተናገዷም ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬቶች ዕውቅና የሚሰጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚዲያ ሽልማት ውድድሩ ላይ በርካታ የኢጋድ አባል ሀገራት የመገናኛ ብዙሃን ሙያተኞች እንደሚሳተፉም ገልጿል። የሽልማት ሥነ-ስርዓቱ በአዲስ አበባ መካሄዱም በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም ነው ሚኒስቴሩ ያመለከተው። የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለሚሰሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ሙያዊ ደረጃውን የጠበቁ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ዘገባዎች እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር፣ የማህበረሰብን ግንዛቤ ለማሳደግ፣ ብዝሃ ድምጾች እንዲሰሙ በማድረግ፣ ለዴሞክራሲ እሴቶች መጎልበት እና ዘላቂ ልማት የበኩሉን ሚና ይወጣል።
የኢትዮጵያ የኮፕ 32 አዘጋጅነት
Nov 14, 2025 1081
ለረጅም አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ምሰሶ ሆና ቆማለች። በሀገራት መካከል የግንኙነት ድልድል እና የአንድነት መልዕክተኛ መሆን ችለላች። ከምስረታው አንስቶ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ናት። የአፍሪካ መዲና በመባል የምትጠራው አዲስ አበባ በርካታ ድርድሮች፣ የሰላም ውይይቶች እና አህጉራዊ ውሳኔዎች የተላለፈባቸው ሁነቶች ተስተናግደውባታል። ውሳኔዎቹ የአፍሪካ ቀጣና ፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ናቸው። የኢትዮጵያ የመሪነት ሚና ከዲፕሎማሲውም የተሻገረ ነው። ሀገሪቷ የገባችውን ቃል ከተግባር ጋር በማጣጣም በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ በመውሰድ የሚለኩ ውጤቶችን እያስመዘገብች ትገኛለች። የተራቆቱ መሬቶች ወደ ነባር ይዞታቸው እንዲመለሱ በማድረግ እና የታዳሽ ኃይል አማራጮቿን በማስፋት ለአረንጓዴ ልማት እና እድገት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይታለች። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው አረንጓዴ አሻራ ሚሊዮኖችን ከዳር እስከ ዳር በማነቃነቅ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ከችግር ተናገሪነት ወደ ተጨባጭ መፍትሄ አመንጪነት ሽግግር በማድረግ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ምሳሌ የሚሆን ተግባር አከናውናለች። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም ደረጃ ያላትን ተአማኒነት እና ተቀባይነት እንዲያድግ አድርጎታል። ኢትዮጵያ በከባቢ አየር ጥበቃ ቁርጠኝነት እና አቅምን በማጣመር ለውጥ አምጥታለች። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያገኘችው እምነት እና የመሪነት ሚና ውጤት የሚያሳይ ተጨማሪ ሃላፊነት ከሰሞኑ ከብራዚል የደን ከተማ ቤለም ተሰምቷል። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በቤለም እየተካሄደ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በአንገብጋቢ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳዮች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል። በጉባኤው ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ለማስተናገድ ይፋዊ ጥያቄ አቅርባለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ዓለም ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የገቡትን ቃል በተግባር ለመቀየር ቁርጠኝነት ባነሳቸው ወቅት ኢትዮጵያ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ተግባር መፈጸሟን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳላት ገልጸው የዳበረ የትራንስፖርት አገልግሎት ከብዙ የዲፕሎማሲ ተቋማት መቀመጫነት ጋር ሲደመር የዝግጁነት አቅሟን በላቀ ሁኔታ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል። ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ልምዱም አቅሙም እንዳላት ገልጸው፣ ሀገራት ድጋፍ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ናይጄሪያም ጉባኤውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርባ ነበር። የኢትዮጵያ የኮፕ 32 የማስተናገድ ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል። የወቅቱ የአፍሪካ የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር የሆነችው ታንዛንያ የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልጻለች። የአፍሪካውያን ውሳኔ ከቃል ባሻገር ኢትዮጵያ የአህጉሪቷን የአየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረቶች የማራመድ እና የመወከል አቅም አላት ብለው ይሁንታ የሰጡበት ነው። ይህ ጠንካራ እምነት ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ሁሉን አፍሪካውያን ያሳተፈ ውይይት እንዲደረግ እና አህጉሪቷን ያማከለ ውሳኔዎች በዓለም መድረክ እንዲተላለፍ እያደረገች ያለውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግም ነው። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ አፍሪካውያን ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስናግድ ድጋፍ በመስጠታቸው አመስግነው፤ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ አበክራ እንደምትሰራ ተናግረዋል። በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ መሰል አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን በብቃት ማስተናገድ እንደምትችል የሚያመላክት ነው ብለዋል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የኮፕ 32ን ለማስተናገድ መመረጧ በድንገት የመጣ ጉዳይ አይደለም። በተግባር የተረጋገጥ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የመሪነት ሚና፣ አረንጓዴ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያከናወነች ያለቻቸው ስራዎች እና የፖለቲካ ቁርጠኝነቷ፣ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ድምጽ እና ምልክት መሆኗ ከቃል ባለፈ በተጨበጠ ስራ መታየቱ፣ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን የማስተናገድ ውጤታማነቷ እና የዲፕሎማሲ ተሰሚነቷ ድምር ውጤቶች እንጂ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን እንድታስተናግድ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠን ክብር ይሰማናል ብለዋል። አፍሪካ በ2025 በተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በብራዚል በአንድ ድምጽ ተናግራለች፤ ዓለምም አዳምጧል ብለዋል። እንዲሁም ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2027 በአዲስ አበባ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ለደገፉ የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች ምሥጋና አቅርበዋል። በሰው ልጆች ኑሮ በጣም አንገብጋቢ ከሆኑት ተግዳሮቶች መካከል አንዱን ለመቅረፍ እንዲቻል የጋራ ጥረቶችን ለመምራት ዕድሉን ስላገኘንም አመሥጋኞች ነን ብለዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ትልቅ ኃላፊነት ስለሰጠንም ክብር ይሰማናል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ላይ ያላትን ቁርጠኛ ርምጃ፣ አመራር ብሎም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ የዳበረ ዐቅም ያሳያል ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ በምታስተናግደው የኮፕ 32 መድረክ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የጋራ ርምጃን የሚያበረታታ ጠንካራ እና ትርጉም ያለው ውጤት ለማምጣት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማዘጋጀቷ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ መድረኮች ኢትዮጵያ ያላትን የአየር ንብረት የመሪነት ሚና የበለጠ ያሳድጋል። የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ የሚያስፈልጋትን ፋይናንስ ለማግኘት እና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ለማጠናከር መልካም አጋጣሚን ይፈጥርላታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ የጉባኤው ተሳታፊዎች የቱሪዝም መስህቧቿንና መዳረሻዎቿን ሲጎበኙ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ ያድጋል ይህም ኢኮኖሚውን በመደገፍ ቁልፍ ሚና ይጫወታል። በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ ያላትን ተጽእኖ ፈጣሪን ጉባኤው በማስተናገድ በኩል ጉልህ አበርክቶ የሚኖረው ሲሆን ዘላቂ የሆነ የከባቢ አየር ትብብርን ለመፍጠር ያስችላል። ለኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ማስተናገድ ከክብር ባሻገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ሰው ለሚኖርባት ምድር ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር የምታሳይበት ይሆናል። ኢትዮጵያ ጠንካራ የከባቢ አየር ጥበቃ ኢኒሼቲቮች፣ የማይበገር ዲፕሎማሲ እና የነገ አረንጓዴ እድገት ህልሟ ከጉባኤው ጋር ተዳምረው የተፈጥሮ ጠበቃነቷን እና የዓለም ትብብር ተምሳሌትና መሪነቷን የበለጠ ያሳድጉታል። ኢትዮጵያ እና ህዝቧቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአየር ንብረት የረጅም ጊዜ ፈተናዎች እንዲፈቱ ከአፍሪካ ብሎም ከመላው ዓለም ጋር ለመፍታት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ እና ቁርጠኛ ናት።
ትንታኔዎች
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 726
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3143
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 3075
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3975
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 2584
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1660
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7475
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5963
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ እና የህንድ ዘመን አይሽሬ እና ድንበር ተሻጋሪ ወዳጅነት
Dec 16, 2025 484
በሙሴ መለስ (ኢዜአ) ኢትዮጵያ እና ህንድ ረጅም ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት አላቸው። በዚህም የስልጣኔ እሴቶችን ይጋራሉ። ሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ከፈጠሩ ከ2000 ዓመታት በላይ እንዳስቆጠሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። የኢትዮጵያ እና ህንድ ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መሰረት የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳሽነት እንደሆነም ይወሳል። ኢትዮጵያ እና ህንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1948 ነው። እ.አ.አ በ1950 ሳርዳት ሳንት ሲንግ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የህንድ አምባሳደር በመሆን ተሹመዋል። በወቅቱ ኢትዮጵያ እና ህንድ በየሀገራቱ ኤምባሲ በመክፈት የዲፕሎማሲ ትብብሩን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ገልጸዋል። ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ እ.አ.አ በ1956 እና በ1958 በህንድ ያደረጓቸው ጉብኝቶች ከኢትዮጵያ መሪዎች ጉብኝቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። እ.አ.አ 1960 ዎቹ ማብቂያ እና 1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ የህንድ ፕሬዝዳንቶች የነበሩት ሳርቬፓሊ ራድሃክሪሽናን እና ዛኪር ሁሴን በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝቶችን አድርገዋል። እ.አ.አ በ2011 ከአንድ ዓመት በፊት ህይታቸው ያለፈው የቀድሞው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንሞሃን ሲንግ በኢትዮጵያ ያደረጉት የስራ ጉብኝትም ተጠቃሽ ነው። የቀድሞው የህንድ ፕሬዝዳንት ራም ናት ኮቪንድ እ.አ.አ በ2017 የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በወቅቱ በጉብኝታቸው ህንድ እና ኢትዮጵያ በንግድ፣ ኮሙኒኬሽን እና የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር የሚያስችሉ የጋራ መግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 15ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። የሀገራቱ መሪዎች በወቅቱ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ የወጣቶች ክህሎት ማጎልበት እና በሕዝብ ለሕዝብ ልውውጥ ዙሪያ ትብብርን በማጠናከር ዙሪያ ተወያይተዋል። በወቅቱ ህንድ ባዘጋጀችው የሁለተኛው “Voice of Global South Summit” በተሰኘው ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተሳትፎ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲ በህንድ አጠቃላይ ምርጫ ለሶስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈውም ነበር። የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንደራ ሞዲም የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን የደስታ መግለጫ መልዕክት በመቀበል በአዲሱ የስልጣን ዘመናቸው ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት አጋርነት እንደሚያድግ መግለጻቸውም ይታወሳል። ህንድ እና ኢትዮጵያ በአፍሪካና በደቡብ ደቡብ ትብብር ያላቸውን አጋርነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል። በዚህም ህንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ትብብር ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥም ነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ያስታወቁት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 20ኛው የቡድን 20 አባላት ሀገራት ጉባኤ ከነበራቸው ተሳትፎ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ትርጉም ያለው እና ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል። ህንድ የቡድን 20 አባል ሀገር መሆኗ የሀገራቱን የባለብዙ ወገን ትብብር የበለጠ የሚያጠናክር ነው። ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2024 ባለው ጊዜ ውስጥ ሀገራቱ የሁለትዮሽ እና የባለዙወገን ትብብራቸውን የሚያጠናክሩ ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል። በወቅቱ የህንድ የትምህርት፣ ንግድ፣ ልማት፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የሀገራቱ ግንኙነት የበለጠ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ናቸው። ህንድ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል እንድትሆን ድጋፍ ያደረገች ሲሆን በብዝሃ ወገን ማዕቀፉ ሁለቱ ሀገራት በትብብር እየሰሩም ይገኛሉ። ኢትዮጵያ እና ህንድ በተለያዩ ጊዜያት በአየር ትራንስፖርት፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ መከላከያ፣ ተደራራቢ ታክስን የማስቀረት፣ ንግድ፣ ኮሙኒኬሽን ሳይንስ፣ባህል፣ ትምህርት እና የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች መስራት የሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 2025 ኢትዮጵያ እና ህንድ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ የተፈራረሙት የሁለትዮሽ ስምምነት ቁልፍ የሚባል ነው። እ.አ.አ በ2023/24 በወጣ መረጃ የኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ምጣኔ 271 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። ኢትዮጵያ አተር፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቆዳ ውጤቶች እና የከበሩ ድንጋዮችን ወደ ህንድ ትልካለች። ከህንድ ደግሞ ማሽነሪዎች፣ የመድኃኒትት ምርቶች እና የብረታ ብረት ውጤቶችን በዋናነት ታስገባለች። ህንድ የኢትዮጵያ ዋንኛ የኢንቨስትመንት አጋር ከሚባሉ ሀገራት መካከል ትጠቀሳለች። ከ500 በላይ የህንድ ኩባንያዎች በጨርቃ ጨርቅ፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አገልግሎት ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ። ህንድ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አቅርቦት ታደርጋለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ ጤና እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከሁለቱ ሀገራት አበይት የትብብር መስኮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሞዲ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ከማንሞሃን ሲንግ በኋላ ኢትዮጵያን የጎበኙ ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ህንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን የልማት አጋርነት ማሳደግን ያለመ ነው። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ከሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በፓርላማ ተገኝተው ንግግር እንደሚያደርጉ የጉብኝታቸው መርሃ ግብር ያሳያል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶች እና የጉብኝት ልውውጦች የኢትዮጵያ እና የህንድን ግንኙነት የበለጠ የሚያጸኑ ናቸው። ኢትዮጵያ እና ህንድ በታዳሽ ኃይል፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ግብርና ማቀነባበሪያን ጨምሮ በአዳዲስ መስኮች ትብብራቸውን የማጠናከር ጽኑ ፍላጎት አላቸው። የሁለቱ ሀገራት ትብብር ከእርስ በእርስ ግንኙነት ባለፈ የአፍሪካ እና ህንድ እንዲሁም የደቡብ ደቡብ ትብብር ማሳያ ሆኖ የሚጠቀስ ነው። ከ2000 ዓመት በፊት የተጀመረው የሀገራቱ ወዳጅነት ወደ ጠንካራ እና ጽኑ ትብብር ተቀይሯል። በማይናወጥ መሰረት ላይም ቆሟል። የበለጠ ጥልቀቱ እየጨመረ የመጣው የሀገራቱ ግንኙነት በጋራ ብልጽግና፣ ስትራቴጂካዊ ትስስር፣ ዘላቂ ልማት እና የሀገራቱን ዜጎች ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ አጠናክሮ ለመቀጠል የጋራ ቁርጠኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል።
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ
Dec 3, 2025 990
በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው - የቤንቾች ቀዬ (በቀደሰ ተክሌ) -ከሚዛን ቅርንጫፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ ቤንቾች ነፋሻማ አየር እየማጉ የመኖር ልምድን ያጎናጸፋቸው ይኸው አፈር ቆፍረው ዘር ተክለው ያበቀሉትና የተንከባከቡት አረንጓዴ ሀብት ነው። ከአንድ አርሶ አደር ማሳ እንሰት፣ ሙዝ፣ ጎደሬ፣ ፓፓያ፣ አቮካዶ፣ ብርቱካን እና ሌሎች ፍራፍሬዎች ማየት የተለመደ ነው። እግር ጥሎት ወደ ቀዬያቸው ያመራ እንግዳ ከፍራፍሬዎቹ የደረሰ ካለ ተቆርጦ ይሰጠዋል። በተጨማሪም ከብቶች፣ በጎችና ዶሮዎች የገቢ ምንጮቻቸው ናቸው። ወደ ቤታቸው ዘልቆ የገባ ሰው "ኪዥ" የተሰኘና የቤንች እናቶች ከወተት የሚያዘጋጁትን ''ጎደሬ'' ተብሎ ከሚጠራ የስራ ስር ምግብ ጋር ያጣጥማል። ቤንቾች በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን ያለማሉ። ማር፣ ቡና፣ ኮረሪማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ቅመማ ቅመሞችም ቤንቾች ከገበያ ገዝተው የሚያመጡት ሳይሆን ከማሳቸው የሚያፈሩት ነው። የተቀናጀ እርሻን ባህል ያደረጉት ብርቱ የቤንች አርሶ አደሮች ወደ ገበያ አውጥተው የሚሸጡት እንጂ የሚገዙት የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። የፋብሪካ ውጤቶችን ለመግዛትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግም ከጓዳቸው ሞልቶ የተረፈውን ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገበያን ያረጋጋሉ። በጠንካራ የእርሻ ባህላቸውም ምክንያት ልጆቻቸው የበሰለ ምግብን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ፍራፍሬዎችንም ከጓሮና ከጫካ ቆርጠው ስለሚመገቡ ረሀብን አያውቁም። የቤንቾች ቤት ዙሪያ ውብና ጽዱ ነው። ለዚህ ደግሞ ሴቶቹ የቤታቸውን ግድግዳ በተፈጥሮ ቀለም ከማስዋብ ጀምሮ ይጠበቡበታል። በቤንቾች ዘንድ የአንድ አርሶ አደር ጉብዝና የሚለካው በቤቱ ነው። ይህም የቤቱ ዙሪያ ያለው ውበትና የቤቱ ጥንካሬ ብቻም ሳይሆን ገላጣ መሆን አለመሆኑም ጭምር ከግምት ውስጥ ይገባል። አባዎራው በማሳው ላይ የሰብል ስራውን ያከናውናል። ልጆችና እማውራዋ ደግሞ ይኮተኩታሉ ያርማሉ። ከዚህም በተጨማሪ የቤንች እናት ጎደሬና ሌሎች የጓሮ አትክልቶችን የማልማት ኃላፊነት አለባት። የቤታቸው ዙሪያና ቀዬው በሙሉ በአረንጓዴ ልምላሜ አጊጦ የሚታይበት ምስጢሩ ይሄው ነው። ከርቀት ደን መስሎ የሚታየው አረንጓዴው ቀዬአቸው የገቢ ምንጭም በመሆኑ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ነውም ማለት ይቻላል። የሌማት ትሩፋት እሳቤ ቀድሞ የገባቸው ቤንቾች ማር አይገዙም፤ ለእንቁላል ሸመታም ገበያ አይወጡም። ወተት ቢያምራቸው በትኩሱ፤ ከዛም አለፍ ሲል በባህላዊ መንገድ እርሾ ጨምረው የሚያዘጋጁት "ኪዥ" የተሰኘ የወተት ውጤትን እንደ አይብም እንደ እርጎም አደርገው ይጠቀሙታል። የትኛውንም መልክዓ ምድር በሚስማማው የሰብል ዓይነት መሸፈን ያውቁበታል። መሬቱ ረግረጋማ ከሆነ ለጎደሬ፤ ዳገታማ ሆኖ ለማረስ የሚያስቸግር ከሆነ ደግሞ ለሙዝ ልማት ያውሉታል። የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ለማረጋገጥ ሥራ የሚሠራው በጓሮ ነው። ይህም ሁሉን ከአንድ ጓሮ ለማግኘት በመጣር የሚመጣ ነው። ይህም ካልሆነ ደግሞ አስተማማኝና ቋሚ ምርት ማሳ ላይ አልያም ጎተራው ላይ ማኖር ያስፈልጋል። እንደ ቤንቾች በቤተሰብ ደረጃ ምግብን በራስ አቅም ለመቻል የሚደረገው ጥረት እንደሀገር ሲጠናከር ለውጡ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይፋጠናን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ቁጥር አብዛኛው አርሶ አደር ነው። ይሁን እንጂ ጾሙን የሚያድር ሰፊ መሬት እንዳለ መረጃዎች ያመለከታሉ። አንድም መሬት ጾም እንዳያድር በየአካባቢው ስራዎች ቢጀመረም ውጤቱ ቀሪ ሥራዎችን የሚጠይቅ ነው። ዛሬም በምርት እጥረት የኑሮ ውድነትና መሰል ችግሮች ይስተዋላሉ። በእነዚህ መሬቶች ላይ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ ከተማ ቁጭ ማለትን የሚሻ ትውልድ ማየት የተለመደ ነው። የቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች እጃቸው ብርቱ በመሆኑ እነዚህ ችግሮች በስራ አሽንፈዋል። ይህም በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ በኢኮኖሚም እንዲረጋጉ አድርጓቸዋል። ለሀብት ምንጭ የሆነን ማሳ ለቆ ከተማ በመዋል የሚገኝ ነገር አይኖርም። በከተማም ሆነ በገጠር ለመለወጥ እንደ ቤንቾች ብርቱ እጆች ያስፈልጋሉ። ካልተሰራ ገቢ ሳይሆን ወጪ እያደገ ወዳልተገባ መንገድ ለመሄድ ምክንያት ይሆናል። ለችግርም ሆነ ሰርቶ የመለወጥ ዕድሉ የሚወሰነው በምርጫችንና ለሥራችን በምንሰጠው ትኩረት ነው። እንደ ቤንች ሸኮ ዞን አርሶ አደሮች ሰርቶ ለመለወጥና ራስን ለመቻል በየአካባቢው ያለን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ልማት ለመቀየር ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ። ሰላም!