ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የገበታ ለትውልድ ሥራ የመጀመሪያው መዳረሻ የሆነው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በይፋ ተመረቀ
Jan 18, 2026 38
አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2018 (ኢዜአ)፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገበታ ለትውልድ ሥራ የመጀመሪያው መዳረሻ የሆነው እና በ36.7 ሔክታር የጥብቅ ደን እና የተፈጥሮ ኃብት ስጦታ የተዘረጋው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በይፋ ተመርቋል። ኢኮ ሎጁ የሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍ ባለፉት ሰባት ዓመታት ዘላቂነትን፣ የቅርስ ሀብትን እና ለዘመናት የሚዘልቅ ዓለም አቀፍ ደረጃን የመጠበቅ ዕድል መፍጠርን በማዋሃድ ምን ያህል እንደተለወጠ ማሳያ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ገልጿል። የገበታ ለትውልድ ሥራ ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ መዳረሻዎችን በማልማት የሀገራችንን እምቅ አቅም ለማውጣት የሚደረገው የሰፊው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ስትራቴጂ አካል ነውም ብሏል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመረው ይኽ ሥራ በስኬት ከተተገበሩት የገበታ ለሸገር እና ገበታ ለሀገር መርሐ-ግብሮች የቀጠለ እና ሥራዎቹን ወደአዳዲስ አካባቢዎች የወሰደ ሲሆን የተፈጥሮ ውበትን፣ የባሕል ቅርስን እና ዘላቂ ልምድን በማቀናጀት የተከናወነም መሆኑ ተመላክቷል። እነዚህ ሥራዎች የከተማ እና ተፈጥሯዊ መዳረሻዎችን ወደ ሳቢ የቱሪዝም ማዕከልነት የለወጡ መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።
ተፈጥሯዊ ፀጋዎችን ተጠቅመን የዜጎቻችንን ኑሮ መቀየር ከቻልን የተሟላ ብልጽግና እናመጣለን- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jan 17, 2026 58
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡- በሀገር ደረጃ በየአካባቢው ያሉ ተፈጥሯዊ ፀጋዎችን ለይተን በመጠቀም የዜጎቻችንን ኑሮ መቀየር ከቻልን የተሟላ ብልጽግና እናመጣለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጉራፈርዳ ወረዳ የገጠር ኮሪደርን ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላም ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በሰጡት ገለጻ፤ ጉራፈርዳ ወረዳ በለምነቱ፣ በሚያመርተው ቡና፣ በልዩ ልዩ የግብርና ምርቶች እንደሚታወቅ እና ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ዜጎች በጋራ የሚኖሩበት መሆኑን አንስተዋል። በከተማ የጀመርነውን የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ገጠር እናምጣ ብለን እየሠራን ባለው ሥራ፤ በሁሉም ክልሎች አዳዲስ የተሻገሩ የገጠር መንደሮች እየተገነቡ ይገኛሉ ሲሉም አስታውቀዋል። በጉራፈርዳ ወረዳ በተሠራው የገጠር ኮሪደርም የጓሮ አትክልት፣ ዶሮ፣ የወተት ላሞችና ማርን ጨምሮ የሌማት ትሩፋት መመልከታቸውን ጠቅሰዋል። በእያንዳንዱ ጓሮ ይህ ካለ በአካባቢው ካሉ የእርሻ ውጤቶች ጋር ተደምረው በቂ ምግብ የሚያገኙበትን ዕድል ይፈጥራል ብለዋል። ስለዚህ በሀገር ደረጃ እንደየ አካባቢው ተፈጥሯዊ ፀጋዎችን ለይተን በመጠቀም የዜጎቻችንን ኑሮ መቀየር ከቻልን የተሟላ ብልጽግና ማምጣት እንችላለን ሲሉ አስገንዝበዋል። በወረዳው የተገነባው የገጠር ኮሪደር ልማት መዋዕለ-ሕጻናት ማካተቱ ከሌላው እንደሚለየውም ጠቁመዋል። በአጠቃላይ ብልጽግናን እናረጋግጥ ሲባል በቁጥር የሚታይ ዕድገት ብቻ ሳይሆን፤ በከተማም በገጠርም እያንዳንዱን ዜጋ መንካት አለበት ማለት ነው ብለዋል። ክልሉ ያለውን ጸጋ በመጠቀም የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል መሥራት እንደሚጠበቅበትም አመላክተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እስካሁን የተሠሩትና እየተሠሩ ያሉ የገጠር ኮሪደሮች ሞዴል መሆናቸውን ገልጸው፤ ክልሎች፣ ባለሃብቶች፣ ዞኖች እንዲሁም ነዋሪው በራሱ ወጪው ቀላል መሆኑን በመረዳት ማስፋትና ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል። በስንዴ፣ በቡና፣ በሌማት ትሩፋት ያገኘነው ውጤት የዜጎችን ኑሮ መቀየር አለበት በሚል የጀመርነው የገጠር ኮሪደር ሥራ ፍሬ እያፈራ ነው ብለዋል። ስለዚህ በቀጣይ በይበልጥ እንዲስፋፋ አሳስበው፤ ተባብረን በመሥራት የዜጎቻችንን ኑሮ እንድንቀይር አደራ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የግብር ከፋዩ ለሀገር ዕድገት ያለው ቁርጠኝነት ማደግ ስኬታማ ለውጥ እንዲመዘገብ አግዟል- ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሤ
Jan 17, 2026 54
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ ግብር ከፋዩ የሚከፍለው ግብር ለሀገር ዕድገት እንደሚውል ያለው ግንዛቤና ታክስ የመክፈል ቁርጠኝነት ማደግ ስኬታማ የታክስ አሰባሰብ እንዲኖር ማገዙን የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሤ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ''የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ'' በሚል ሐሳብ በተካሄደ ኮንፈረንስ ላይ የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሤ ገለጻ አድርገዋል። ሚኒስትሯ የታክስ አሥተዳደር ሪፎርም ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ቀጣይነት በሚል ርዕሰ ጉዳይ ባቀረቡት ገለጻ፤ የታክስ አሥተዳደር አገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻልና የማስፈጸም ዐቅምን ማጠናከር፣ ዘመናዊ የታክስ አሥተዳደር ሥርዓት መገንባት፣የታክስ ሕግ ተገዥነትን ማረጋገጥ እና ዘላቂ የገቢ ዕድገት ማረጋገጥ በሚሉት ዐበይት ጉዳዮች ላይ ሪፎርሙ መከናወኑን አንስተዋል። ከላይ በተገለጹት ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣትም በሪፎርሙ ወቅት የፖሊሲ እና የሕግ ማሻሻዎች መደረጋቸውን ጠቁመው፥ እነዚህን ለመፈጸምም የአሠራር ማሻሻያዎች ተደርገዋል ብለዋል። ቅርንጫፎች ማስፋፋትን ጨምሮ ከፌደራል እስከ ክልል ባሉ ባለድርሻ አካላት ዘንድ ስኬታማ ተግባራት ለማስመዝገብ እንዲቻል የዐቅም ግንባታ ሥራዎች መከናወናቸውንም ጠቅሰዋል። እንደ ሀገር የተጣጣመ የታክስ አሥተዳደር ሥርዓት እንዲኖር ጥረቶች መደረጋቸውንም አመላክተዋል። የዲጂታል ሥርዓቶችን በመዘርጋት ለግብር ከፋዮች ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር አንጻር ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተው፤ ለአብነትም መሠረታዊ የሚባሉ የዲጂታል ፕላት ፎርሞች መዘርጋታቸውን ጠቅሰዋል። በዚህም መሠረት ግብር ከፋዩ በየቢሮው መሄድ ሳይጠበቅበት ኢ-ፋይል እና ኢ-ፔይ የሚያደርግበትን ሥርዓት ዘርግተናል ነው ያሉት። በሌላ በኩል በኢንሳ አማካኝነት ለምቶ በቅርቡ ወደ ሥራ እያስገባነው ባለው የኤሌክትሮኒክ ኢንቮይሲንግ ሲስተም በትራንዛክሽን ደረጃ ወደ 291 ቢሊየን ብር ግብይት ተካሂዶበታል ብለዋል። ይህም ከሐሰተኛ ደረሠኝ፣ ከውሳኔ አሰጣጥ፣ ከመረጃ አጠቃቀም እና ተያያዥ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮችን የሚቀርፍ መሆኑን አስገንዝበዋል። ከጉምሩክ አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘም አሁን ላይ የወጪና ገቢ ንግድን ከማሳለጥ አንጻር በአንድ መስኮት አገልግሎት ከ80 በላይ ተቋማት በአንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። በሌላ በኩል ኢኮኖሚውን በዘላቂነት የሚደግፍ ወደ ሉዓላዊነት የሚወስደን ገቢ በሀገር ውስጥ መመንጨት አለበት በሚል የተከናወነው ሥራ የሪፎርሙን ስኬት አሳይቷል ነው ያሉት። በዚህም መሠረት በ2011 የበጀት ዓመት የፌደራል መንግሥት 198 ቢሊየን ብር ታክስ መሰብሰቡን አውስተው፤ በ2017 ደግሞ 900 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ገልጸዋል። በተያዘው ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ ደግሞ 907 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ገልጸው፤ ይህ አሃዝ ከዕቅዳችን አንጻር ወደ 68 ቢሊየን ብር ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንጻርም የ258 ቢሊየን ብር ብልጫ ማሳየቱን አንስተዋል። ይህም በየደረጃው ያሉ አካላት ድጋፍ፣ የግብር ከፋዮች ሀገርን ለመለወጥ ያለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ያላቸው ቁርጠኝነት ውጤት መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል። ከክልሎች አኳያም በ2011 የታክስ ገቢ 79 ቢሊየን ብር ብቻ እንደነበር አውስተው፤ በ2017 ደግሞ 543 ቢሊየን ብር መሰብሰባቸውን ተናግረዋል። በተያዘው የበጀት ዓመት እንደ ሀገር ከ2 ነጥብ 1 ትሪሊየን ብር በላይ ታክስ ለመሰብሰብ መታቀዱን እና ባለፉት ስድስት ወራት 1 ነጥብ 17 ትሪሊየን ብር ታክስ መሰብሰቡን አስታውቀዋል።
የኢኮኖሚ ሪፎርሙ በዘርፉ የጎላ ሚና ያላቸው ቁልፍ ተቋማትን ወልዷል- ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ
Jan 17, 2026 56
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ የለውጡ መንግሥት ያከናወነው የኢኮኖሚ ሪፎርም በኢኮኖሚ ረገድ ቁልፍ ሚና ያላቸው ተቋማት መውለዱንና የኢኮኖሚ ዕድገቱንም ማቃናቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ''የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ '' በሚል ሐሳብ በተካሄደ ኮንፈረንስ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ገለጻ አድርገዋል። በገለጻቸውም፤ከሰባት ዓመታት በፊት ኢኮኖሚውን የገጠሙት ዋና ዋና የማክሮ ፊሲካል ተግዳሮቶችን አንስተዋል። እነዚህ ተግዳሮቶችም፤ ከፍተኛ የዋጋ ንረት፣ የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ ዘላቂና አስተማማኝ የፊሲካል ቁመና አለመኖር፣ ከፍተኛ የዕዳ ጫና፣ የውጭ ምንዛሪ እጥረት እና የገበያ አለመረጋጋት መሆናቸውን አብራርተዋል። ስለዚህ ይህን የማክሮ ኢኮኖሚ ስብራት ለመጠገን ላለፉት ሰባት ዓመታት መንግሥት፤ በመጀመሪያው እና በሁለተኛው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ሊከሰት የነበረውን የማክሮ ፋይናንሻል ቀውስ አስቀርቷል ብለዋል። በዚህም ጠንካራ ዕድገትን አስመዝግቦ በሁሉም የማክሮ ኢኮኖሚ አመላካቾች (ኢንዲኬተሮች) ወደ ተሻለ ቁመና ለመሻገር ተችሏል ነው ያሉት ሚኒስትሩ። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት አንዷ ልትሆን ትችላለች ነው ያሉት። የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ጠንካራ ተቋማት የተፈጠሩበት መሆኑን በአጽንኦት ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ስለዚህ ከተቋማት ግንባታ አንጻርም በኢኮኖሚ ረገድ ቁልፍ ሚና ያላቸው ተቋማትን የወለደ ሪፎርም ነው ብለዋል። በተጨማሪም የኢኮኖሚ ዕድገቱን ያቃና ሪፎርም መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም በርካታ ውጤቶች መገኘታቸውን አረጋግጠዋል።
የሊጉ መሪ አርሰናል እና ኖቲንግሃም ፎረስት አቻ ተለያዩ
Jan 17, 2026 74
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ22ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ኖቲንግሃም ፎረስት እና አርሰናል ያደረጉት ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። ማምሻውን በሲቲ ግራውንድ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ብልጫ ወስዶ የተጫወተው አርሰናል ያገኛቸውን የግብ እድሎች አለመጠቀሙ ሶስት ነጥብ እንዳያገኝ አድርጎታል። በመጀመሪያው አጋማሽ ጋብርኤል ማርቲኔሊ የሳተው ግልጽ የግብ እድል ተጠቃሽ ነው። ተጋጣሚው ኖቲንግሃም ፎረስት ወደ ኋላ አፈግፍጎ የመከላከል እና የመልሶ ማጥቃት ስልት ይዞ በመግባት ግብ ሳይቆጠርበት ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ የሊጉ መሪ አርሰናል ነጥቡን ወደ 50 ከፍ አድርጓል። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሰባት ከፍ አድርጓል። አርሰናል ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ያላሸነፈ ሲሆን ግብም ማስቆጠር አልቻለም። ኖቲንግሃም ፎረስት በሊጉ በ22 ነጥብ 17ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ፖለቲካ
በአማራ ክልል በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን ዘረፋና እገታን የሃብት ምንጭ ያደረገ ነው
Jan 17, 2026 105
ባህር ዳር፤ ጥር 9/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን ዘረፋና እገታን የሃብት ምንጭ ያደረገ መሆኑን በቡድኑ አሻራ ሚዲያ ተብሎ የሚጠራው ሚዲያ ዋና ስራ አስኪያጅ የነበረው ኤሊያስ ደባሱ ተናገረ። ኤሊያስ በህዝብ ላይ ላደረሰው ጥፋት ይቅርታ በመጠየቅ የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የበደለውን ህዝብ ለመካስ መምጣቱን ገልጿል። በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን በህዝብ ላይ ግፍና በደል በመፈፀም በዘረፋ ሃብት ማካበት ላይ መሆኑን ተናግሯል። በዚህ የጥፋት ዓላማ በመሰለፍ በተለይም አመራር የሚሰጡ ግለሰቦች በገንዘብ ኪሳቸውን በማድለብ ሃብት እያካበቱ ይገኛሉ ብሏል። በተሳሳተ አረዳድ ለትግል በሚል ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በጫካ መቆየቱን አስታውሶ የጥፋት ቡድኑን አላማ በመረዳት ላደረሰው ጥፋትና በደል ይቅርታ በመጠየቅ መምጣቱን ገልጿል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ከክልሉ መንግስት ጋር ያደረገውን ስምምነት ተከትሎ በመምጣት የሰላም ስምምነቱ አካል መሆኑን ገልጿል። የሚዲያ ስራ ለመልካም ነገር ከዋለ ሀገር እንደሚገነባ የገለጸው ኤሊያስ ለጥፋት አላማ ጥቅም ላይ ከዋለ ደግሞ ጉዳቱ የከፋ መሆኑን አንስቶ በዚህ ረገድ ቡድኑ አሻራ ብሎ የሚጠራው ሚዲያ በክልሉ ህዝብ ላይ ጥፋት መፈፀሙን አስታውሷል። በሚዲያው “ያልደረስንበትን ከተማ ተቆጣጠርን፣ ያልተገደለን ሰው ተገደለ በማለት” የበዙ የፈጠራና የውሸት መረጃዎችን በማሰራጨት ሰዎችን አደናግረናል ያለው ኤሊያስ በዚህ ከባድ ጥፋት በመጸጸትም ይቅርታ ጠይቋል። በቀጣይ የሰላም አምባሳደርና የልማት አርበኛ በመሆን የበደልኩትን ህዝብ ለመካስ ተዘጋጅቻለሁ በማለት አሁንም በጫካ የሚገኙ ጊዜ ሳያባክኑ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እንዲመጡ መልእክቱን አስተላልፏል። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል።
ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍና ስኬታማ ሥራዎችን በማከናወን ወሳኝ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል-አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Jan 17, 2026 106
አዲስ አበባ፤ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍና ስኬታማ ሥራዎችን በማከናወን ወሳኝ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ የሚታዩ መሰረታዊ የሀሳብ ልዩነቶችን እና አለመግባባቶችን ለመፍታት አካታች በሆነ መልኩ ምክክር ለማካሄድ በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቋቋመ ገለልተኛ ተቋም ነው፡፡ ኮሚሽኑ መሰረታዊ የሆኑ ሀገራዊ የሀሳብ ልዩነቶችንና አለመግባባቶችን አካታችና ሰፋፊ ህዝባዊ ምክክሮችን በማካሄድ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል፡፡ በዚህም ኮሚሽኑ ምክክር ማድረግ በሚቻልባቸው በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን በማከናወን ወደ መጨረሻው ምዕራፍ መድረሱ ይታወቃል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የኢትዮጵያ ጉዳይ ይገደናል ያሉ ኢትዮጵያውያን በንቃት የተሳተፉበት የምክክር ሂደት እያከናወነ ይገኛል፡፡ ኮሚሽኑ በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በውጭ ሀገር ጭምር አጀንዳ በመሰብሰብና የዋናው ምክክር ሂደት ተሳታፊዎችን በመለየት ስኬታማ ስራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ በምክክር ሂደቱ ብዙሃን ማህበራት፣ሲቪል ማህበራት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ይበጃል ያሉትን ሀሳብ ያዋጡበት በዓይነቱ ልዩ እና ስኬታማ የምክክር ሂደት መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ የማጠቃለያ የምክክር ምዕራፉን ሂደት ተግባራዊ ለማድረግና ለመምራት የሚያስችል ስነ ዘዴ መቀረጹን ገልጸው፤ ቀሪ ስራ በተጀመረበት ስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ በኢትዮጵያ ከታሪክ፣ከህግ፣ ከአሰራር መሰል ጉዳዮች ጋር ተያይዞ የሚነሱ ነገሮች በምክክር ዕልባት ማግኘት የሚችሉ መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለዚህ ደግሞ ሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ ዕድል ነው ብለዋል፡፡ የትግራይ ክልልን በሚመለከት በሀገራዊ ምክክሩ ሊመለሱ የሚገባቸው ጥያቄዎች በተለያዩ አደረጃጀቶች መቅረባቸውን ገልጸዋል። በውይይቱ ብዙሃን ማህበራት፣ ሲቪል ማህበራትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ክልሉን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ማንሳታቸውን ገልጸው፤ የፖለቲካ ሀይሎችም ጥያቄያቸውን በሰነድ አቅርበዋል ብለዋል። ስለሆነም በትግራይ ክልል ያሉ ባለድርሻ አካላት እየተጠናቀቀ ባለው የምክክር ሂደት በንቃት በመሳተፍ ለምክክሩ ስኬት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ትልቅ አቅምና ሀብት ያላት ሀገር ነች ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ በንግግር፣በውይይትና በመተሳሰብ ተዓምር መሥራት እንችላለን ብለዋል፡፡ በዚህም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግ ከማውጣትና ተቋም ከማቋቋም ጀምሮ ዕለታዊ ሥራዎችን እየተከታተለና እየደገፈ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከሀገራዊ ምክክሩ የሚገኘው ውጤት የህዝቡ ውሳኔ መሆኑን ያነሱት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ መንግሥት ውጤቱን ገቢራዊ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በምክክሩ ህዝብ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ተገቢውን አክብሮትና ምላሽ መስጠት ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የፍትሕ ዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ይቀጥላል
Jan 17, 2026 99
ጋምቤላ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡- የፍትሕ ዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል። በጋምቤላ ክልል የፍትሕ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አተገባበር ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋምቤላ ከተማ ውይይት ተካሂዷል። በፍትሕ ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴዔታ የሆኑት ኡሞድ ኡጁሉ፤ የፍትሕ ዘርፉን ለማሻሻል የሶስት ዓመት የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተዘጋጅቶ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አሥተዳደሮች ተግባራዊ መደረጉን ገልጸዋል። በዚህም የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ሰብዓዊ መብቶች ለማስከበር በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ስኬቶች እየተመዘገቡ ነው ብለዋል። የፍትሕ አገልግሎቱን ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ወጪ ቆጣቢ በማድረግ የሕዝቡን ርካታ ለማረጋገጥ የተሠሩ ሥራዎች ውጤታማ እንደነበሩም ጠቅሰዋል። በጋምቤላ ክልልም የፍትሕ ዘርፍ የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ተግባራዊ በማድረግ የፍትሕ አገልግሎትን ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አበረታች መሆኑን አንስተዋል። በተለይም የፍትሕ አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ እየተከናወነ ያለው ተግባር ውጤት የታየበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይም በይበልጥ መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል። የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ መሠረት ማቲዎስ በኩላቸው፤ የፍትሕ ተቋማት ዜጎች በፍትሕ ሥርዓቱ ያላቸውን ተጠቃሚነት የሚያጠናክሩ ተግባራት ላይ አተኩረው መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በተለይም ማኅበረሰብ አቀፍ የፍትሕ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ ያለው ተግባር ሊጠናክር ይገባል ብለዋል። በክልሉ ያለውን የፍትሕ ሥርዓት ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ ኡዶል ኡኩሪ ናቸው። በክልሉ ፀድቆ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የፍትሕ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ፍኖተ ካርታ የዜጎች ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ ከማድረግ አንፃር አበርክቶው የጎላ መሆኑንም አብራርተዋል።
ችግሮችን በምክክር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የፖለቲካ ፓርቲዎች በቁርጠኝነት መስራት ይገባናል
Jan 17, 2026 73
ደሴ፤ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የፖለቲካ ፓርቲዎች በላቀ ዝግጁነትና በቁርጠኝነት መስራት ይገባናል ሲሉ በደሴ ከተማ የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በኢትዮጵያ አካታች፣አሳታፊና ሁሉን አቀፍ ምክክር በማድረግ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት የመፍታት ዓላማ በመሰነቅ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ እየሰራ ይገኛል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በዴሴ ከተማና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የፖለቲካ ፓርቲዎች በላቀ ዝግጁነትና በቁርጠኝነት መስራት ይገባናል ብለዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የወሎ ዴሞክራቲክ ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ዳውድ መሀመድ፤ ፓርቲያቸው በምክክሩ እስካሁን ጠንካራ ተሳትፎ ማድረጉን አስታውሰው እስከ ፍፃሜው የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የምክክር ሂደቱ አካታችና አሳታፊ በመሆኑ የሀገርን መሰረታዊ ችግሮች በመፍታት ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት ጠንካራ ሃገረ መንግስት መገንባት የሚያስችል ይሆናል ብለዋል። በመሆኑም ለስኬታማነቱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉም አካላት የነቃ ተሳትፎና ትብብር ማድረግ ይጠበቅብናል ሲሉ ተናግረዋል። የምክክር ሂደትን በመግፋት ትጥቅ አንስተው በጫካ የሚገኙ ወገኖችም ለምክክር፣ ለዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ ለመስራት መምጣት አለባቸው ብለዋል። የኢዜማ ፓርቲ ደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጸሃፊ ብርሃነ አለም፤ በምክክሩ የእስካሁኑ ሂደት ነፃ፣ አሳታፊና አካታች በሆነ መልኩ እየተካሄደ በመሆኑ የተሳካ ውጤት እንደሚመጣ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የሚፈለገው ውጤት እንዲመጣ የሁላችንም ቀና ትብብርና ተሳትፎ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል። በበልጽግና ፓርቲ የደሴ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሸናፊ አለማየሁ፤ የምክክር ሂደቱ ለዚህ ትውልድ ታሪካዊ አጋጣሚ በመሆኑ እድሉን በመጠቀም ጠንካራ ሀገረ መንግስትና የበለጸገች ሀገር መገንባት ይገባናል ብለዋል። ለምክክር ሂደቱ መሳካት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በቅርበት እየሰራ መሆኑን ገልጸው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የምክክር ሂደቱ ችግሮችን በዘላቂነት መፍቻ በመሆኑ ዕድሉን በአግባቡ መጠቀም ይገባል
Jan 17, 2026 98
ሚዛን አማን፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡- የምክክር ሂደቱ ችግሮችን በዘላቂነት የመፍቻና የሰላም ዕሴት መሰረት ስለሆነ ዕድሉን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ የሚዛን አማን ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች አስገነዘቡ። ከሀገር ሽማግሌዎቹ መካከል ሙሴ አይነታ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የጥፋት አዙሪትን በመቋጨት ለቀጣዩ ትውልድ የምትመች ሀገር ለመገንባት በምክክር ችግሮቻችንን መፍታት ይገባል። የሀገሩን ሰርዶ በሀገሩ በሬ እንዳሚባለው የራሳችንን ችግሮች በራሳችን መፍታት ይኖርብናል ብለዋል። የትኛውንም የግጭትና የልዩነት ዕሳቤ በምክክር፣ ዕርቅና ይቅርታ ከመፍታት የሚሻል አማራጭ የለም ያሉት ደግሞ ሌላኛው የሀገር ሽማግሌ ምትኩ ሾሻ ናቸው። በሀገር ጉዳይ በመምከር መፍትሔ እናምጣ ብሎ መገናኘት መልካም ሐሳብ በመሆኑ ውጤት የሚያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛው የሀገር ሽማግሌ ተስፋዬ ዘካርያስ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ አንድነትን፣ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማረጋገጥ የሚቻለው ልዩነቶችን በምክክር እየፈቱ ለሰላም መትጋት ሲቻል መሆኑን ጠቁመዋል። ያልተጠቀምንባቸው የካበቱ ዕሴቶች ስላሉ ለሀገር ሰላምና ልማት እንጠቀምባቸው ብለዋል። ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካትም የሀገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት አባቶች ትልቅ ኃላፊነት እንዳለብን ተገንዝበን በዚህ ልክ መትጋት ይጠበቅብናል ነው ያሉት የሀገር ሽማግሌዎቹ።
ብልጽግና ፓርቲ በሁሉም ዘርፎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የጀመራቸውን ተግባራት ያጠናክራል - አቶ አደም ፋራህ
Jan 16, 2026 106
ሆሳዕና፤ ጥር 8/2018(ኢዜአ)፡- ብልጽግና ፓርቲ በየዘርፉ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የጀመራቸውን ተግባራት እንደሚያጠናክር የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ገለጹ። በሆሳዕና ከተማ ሲካሄድ የቆየው የፓርቲው የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም መድረክ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና ገበያን ለማረጋጋት የተሰሩ ሥራዎችን በመገምገም ተጠናቋል፡፡ አቶ አደም ፋራህ በመድረኩ እንደገለጹት፣ የብዝሀ ዘርፍ ኢኮኖሚ አቅጣጫን ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ተገኝቷል። ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ተግባራዊ በማድረግ የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማስፋት በተከናወኑ ተግባራት ባለፋት 6 ወራት ተስፋ ሰጪ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ የተገኙ ድሎችን ለማላቅ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግና የሥራ ዕድል የሚያስገኙ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ የሥራ አጥ ልየታን፣ ነባር ኢንተርፕራይዞችን የማጠናከርና የብቃት ምዘና ተቋማት ሥራ በጥራት እንዲከናወን በልዩ ትኩረት መምራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ገበያን ለማረጋጋት በተሰሩ ሥራዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎች እንዳሉ ገልጸው ይህን ለማጠናከር የምርት አቅርቦትን ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡ ለዚህም የግብይት ማዕከላትን የማስፋት፣ የምርት ጥራትን የማስጠበቅ፣ ህብረት ስራ ማህበራትን የመደገፍና የፓርቲው የአንድ ግብ የሆነውን ደረጃውን የጠበቀ ዘመናዊ የግብይት ማዕከል በአንድ ከተማ ግንባታ ስራን ማጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ በአጠቃላይ ብልጽግና ፓርቲ በተለያዩ ዘርፎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የጀመራቸውን ተግባራት ያጠናክራል ሲሉም ገልጸዋል። ለዚህም በየዘርፉ ባለፉት ስድስት ወራት የተገኙ ስኬቶችን በማላቅና ለሚገጥሙ ተግዳሮቶች የመፍትሔ አቅጣጫ በማስቀመጥ የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ የአመራሩ ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል። በመድረኩ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ኃላፊዎችና የወጣቶች ክንፍ አመራሮች ተሳትፈዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
አሰባሳቢና ገዢ ትርክት በማስረጽ ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚና መጎልበት አለበት
Jan 16, 2026 87
ሐረር ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል አሰባሳቢና ገዢ ትርክት በማስረጽ ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን ማጎልበት እንደሚገባቸው ተመለከተ። በሐረሪ ክልል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች እና የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ሚናቸውን ማጠናከር በሚቻሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄዷል። የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ፣ መልካም እሴቶች እንዲጎለብቱ እና ህዝቡ በክልሉ በሚከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የሚያደርገውን ተሳትፎ ለማሳደግ ያስቻሉ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል ብለዋል። በተለይም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ፅንፈኛ ሀይሎች በማህበረሰቡ መካከል የሚነዙትን የጥላቻና ሀሰተኛ መረጃዎችን በመከላከል አሰባሳቢና ገዢ ትርክቶች እንዲሰርጹ በማድረግ ረገድ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም አፍራሽ የሆኑ ፕሮፓጋንዳዎችን ቀድሞ በመከላከል የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅና ሕብረ ብሄራዊነት እንዲሰርፅና እንዲፀና በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ባለሙያዎች እና ማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች በክልሉ በሁሉም ዘርፎች ለተመዘገቡ ውጤቶች አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንም አንስተዋል። በተጨማሪም የህዝብ ሰላምና አንድነት እንዲጎለብትና የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አዎንታዊ ሚናቸውን እንዲያጠናክሩ አስገንዝበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ በበኩላቸው፤ የክልሉ ህዝብ የሚታወቅበት የሰላም፣ መቻቻልና አብሮነት እሴቶች እንዲጎለብቱ በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች ተግባራትን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል። የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በተለይም የጋራ የሚያደርጉ ሀገራዊ እሴቶችን በማጠናከርና ገዢ ትርክትን በመገንባት ሰላምና ልማት እንዲጠናከር እያበረከቱ የሚገኘው ተግባር ይበልጥ መጎልበት አለበት ብለዋል። የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎችም የሚያስተላለፉት መልዕክት ሀገርን የሚገነባ፣ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን የሚሰብክ እንዲሁም ህብረተሰቡ በልማት እንቅስቃሴው ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችሉ ሊሆኑ ይገባል ነው ያሉት።
ከኢትዮጵያ ጋር ያለንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር እንሰራለን -አምባሳደሮች
Jan 15, 2026 126
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018 (ኢዜአ)፡ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ገለጹ። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙ የ 14 ሀገራት አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ ተቀብለዋል። የሹመት ደብዳቤያቸውን ለፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ያቀረቡትም የኪርጊስታን፣ ጣልያን፣ ሞሪሺየስ፣ ዛምቢያ፣ጀርመን፣ ጆርዳን፣ ኒውዝላንድ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቡሩኪና ፋሶ፣ ሞዛምቢክ፣ ኬንያ፣ቤላሩስ፣ ፊሊፒንስ፣ ላቲቪያ ሀገራት አምባሳደሮች ናቸው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በሰጡት ማብራሪያ የሹመት ደብዳቤያቸውን ካቀረቡ ሀገራት መካከል 11ዱ ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ መሆኑን ገልጸዋል። አምባሳደሮቹ ከፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ጋር ከፍተኛ ውጤት እየተመዘገበበት ባለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እንዲሁም በንግድ እና ኢንቨስትመንት በሚሰማሩባቸው መስኮች ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች በሚያስከብሩ ስራዎች ዙሪያ ምክክር ማድረጋቸውን ነው የተናገሩት። በውይይቱ አምባሳደሮቹ በኢትዮጵያ እየተመዘገበ ላለው ለውጥ አድናቆት መስጠታቸውን ጠቁመው፥ ሀገሮቻቸው ከኢትዮጵያ ልምድና ተሞክሮ መውሰድ እንደሚፈልጉ መናገራቸውን አንስተዋል። በኢትዮጵያና በሀገራቱ መካከል የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል ነው ያሉት። በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙት የጣልያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ በትምህርት፣ በክህሎት፣ በሳይንሳዊ እና በባህል ትብብር ዙሪያ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በሚኖራቸው ቆይታ ጣልያን ለኢትዮጵያ ጠንካራ ወዳጅ መሆን የምትችልባቸውን መንገዶች ለማየት እንደሚጥሩ ጠቁመዋል። አዲስ የተሾሙት የዛምቢያ አምባሳደር አልበርት ሙቻንጋ በበኩላቸው በግብርና ማለትም በተሻሻሉ የሰብል ዝሪያዎች ላይ ልምድ በመለዋወጥ እና በስፋት በመተግበር ምርታማነትን ለማሻሻል እንደሚሰሩ ገልፀዋል። የኬንያ አምባሳደር ጋልማ ሙክሄ በኢትዮጵያ እና በኬንያ መካከል ያለውን ታሪካዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር እና ለማሳደግ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ እና በሌሎች በርካታ ዘርፎች ላይ ይህን ግንኙነት ለማጠናከር በጋራ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ባክ ቫለንቲኖ የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ይህንንም በኢትዮጵያ ከሚገኙ ሌሎች አካላት ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ አመላክተዋል:: የፊሊፒንስ አምባሳደር ማሬ ቻርሎቴ በቀጣዩ አመት ሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበትን የምስረታ በአላቸውን እንደሚያከብሩም ተናግረዋል። በሁለቱ አገራት መካከል በፖለቲካ፣በኢኮኖሚ እና በህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ጠንካራ ትብብር ለመፍጠር እንደሚሰራ አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ፖለቲካ
በአማራ ክልል በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን ዘረፋና እገታን የሃብት ምንጭ ያደረገ ነው
Jan 17, 2026 105
ባህር ዳር፤ ጥር 9/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን ዘረፋና እገታን የሃብት ምንጭ ያደረገ መሆኑን በቡድኑ አሻራ ሚዲያ ተብሎ የሚጠራው ሚዲያ ዋና ስራ አስኪያጅ የነበረው ኤሊያስ ደባሱ ተናገረ። ኤሊያስ በህዝብ ላይ ላደረሰው ጥፋት ይቅርታ በመጠየቅ የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የበደለውን ህዝብ ለመካስ መምጣቱን ገልጿል። በጫካ የሚንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን በህዝብ ላይ ግፍና በደል በመፈፀም በዘረፋ ሃብት ማካበት ላይ መሆኑን ተናግሯል። በዚህ የጥፋት ዓላማ በመሰለፍ በተለይም አመራር የሚሰጡ ግለሰቦች በገንዘብ ኪሳቸውን በማድለብ ሃብት እያካበቱ ይገኛሉ ብሏል። በተሳሳተ አረዳድ ለትግል በሚል ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በጫካ መቆየቱን አስታውሶ የጥፋት ቡድኑን አላማ በመረዳት ላደረሰው ጥፋትና በደል ይቅርታ በመጠየቅ መምጣቱን ገልጿል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ከክልሉ መንግስት ጋር ያደረገውን ስምምነት ተከትሎ በመምጣት የሰላም ስምምነቱ አካል መሆኑን ገልጿል። የሚዲያ ስራ ለመልካም ነገር ከዋለ ሀገር እንደሚገነባ የገለጸው ኤሊያስ ለጥፋት አላማ ጥቅም ላይ ከዋለ ደግሞ ጉዳቱ የከፋ መሆኑን አንስቶ በዚህ ረገድ ቡድኑ አሻራ ብሎ የሚጠራው ሚዲያ በክልሉ ህዝብ ላይ ጥፋት መፈፀሙን አስታውሷል። በሚዲያው “ያልደረስንበትን ከተማ ተቆጣጠርን፣ ያልተገደለን ሰው ተገደለ በማለት” የበዙ የፈጠራና የውሸት መረጃዎችን በማሰራጨት ሰዎችን አደናግረናል ያለው ኤሊያስ በዚህ ከባድ ጥፋት በመጸጸትም ይቅርታ ጠይቋል። በቀጣይ የሰላም አምባሳደርና የልማት አርበኛ በመሆን የበደልኩትን ህዝብ ለመካስ ተዘጋጅቻለሁ በማለት አሁንም በጫካ የሚገኙ ጊዜ ሳያባክኑ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እንዲመጡ መልእክቱን አስተላልፏል። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል።
ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍና ስኬታማ ሥራዎችን በማከናወን ወሳኝ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል-አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Jan 17, 2026 106
አዲስ አበባ፤ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡-ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በማሳተፍና ስኬታማ ሥራዎችን በማከናወን ወሳኝ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ የሚታዩ መሰረታዊ የሀሳብ ልዩነቶችን እና አለመግባባቶችን ለመፍታት አካታች በሆነ መልኩ ምክክር ለማካሄድ በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቋቋመ ገለልተኛ ተቋም ነው፡፡ ኮሚሽኑ መሰረታዊ የሆኑ ሀገራዊ የሀሳብ ልዩነቶችንና አለመግባባቶችን አካታችና ሰፋፊ ህዝባዊ ምክክሮችን በማካሄድ ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል፡፡ በዚህም ኮሚሽኑ ምክክር ማድረግ በሚቻልባቸው በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን በማከናወን ወደ መጨረሻው ምዕራፍ መድረሱ ይታወቃል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የኢትዮጵያ ጉዳይ ይገደናል ያሉ ኢትዮጵያውያን በንቃት የተሳተፉበት የምክክር ሂደት እያከናወነ ይገኛል፡፡ ኮሚሽኑ በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በውጭ ሀገር ጭምር አጀንዳ በመሰብሰብና የዋናው ምክክር ሂደት ተሳታፊዎችን በመለየት ስኬታማ ስራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ በምክክር ሂደቱ ብዙሃን ማህበራት፣ሲቪል ማህበራት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ይበጃል ያሉትን ሀሳብ ያዋጡበት በዓይነቱ ልዩ እና ስኬታማ የምክክር ሂደት መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ የማጠቃለያ የምክክር ምዕራፉን ሂደት ተግባራዊ ለማድረግና ለመምራት የሚያስችል ስነ ዘዴ መቀረጹን ገልጸው፤ ቀሪ ስራ በተጀመረበት ስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ በኢትዮጵያ ከታሪክ፣ከህግ፣ ከአሰራር መሰል ጉዳዮች ጋር ተያይዞ የሚነሱ ነገሮች በምክክር ዕልባት ማግኘት የሚችሉ መሆናቸውን በመግለጽ፤ ለዚህ ደግሞ ሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ ዕድል ነው ብለዋል፡፡ የትግራይ ክልልን በሚመለከት በሀገራዊ ምክክሩ ሊመለሱ የሚገባቸው ጥያቄዎች በተለያዩ አደረጃጀቶች መቅረባቸውን ገልጸዋል። በውይይቱ ብዙሃን ማህበራት፣ ሲቪል ማህበራትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ክልሉን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ማንሳታቸውን ገልጸው፤ የፖለቲካ ሀይሎችም ጥያቄያቸውን በሰነድ አቅርበዋል ብለዋል። ስለሆነም በትግራይ ክልል ያሉ ባለድርሻ አካላት እየተጠናቀቀ ባለው የምክክር ሂደት በንቃት በመሳተፍ ለምክክሩ ስኬት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ትልቅ አቅምና ሀብት ያላት ሀገር ነች ያሉት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ በንግግር፣በውይይትና በመተሳሰብ ተዓምር መሥራት እንችላለን ብለዋል፡፡ በዚህም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግ ከማውጣትና ተቋም ከማቋቋም ጀምሮ ዕለታዊ ሥራዎችን እየተከታተለና እየደገፈ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከሀገራዊ ምክክሩ የሚገኘው ውጤት የህዝቡ ውሳኔ መሆኑን ያነሱት አፈ ጉባኤ ታገሰ፤ መንግሥት ውጤቱን ገቢራዊ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በምክክሩ ህዝብ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ተገቢውን አክብሮትና ምላሽ መስጠት ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የፍትሕ ዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ይቀጥላል
Jan 17, 2026 99
ጋምቤላ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡- የፍትሕ ዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል። በጋምቤላ ክልል የፍትሕ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አተገባበር ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋምቤላ ከተማ ውይይት ተካሂዷል። በፍትሕ ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴዔታ የሆኑት ኡሞድ ኡጁሉ፤ የፍትሕ ዘርፉን ለማሻሻል የሶስት ዓመት የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተዘጋጅቶ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አሥተዳደሮች ተግባራዊ መደረጉን ገልጸዋል። በዚህም የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዜጎችን ሰብዓዊ መብቶች ለማስከበር በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ስኬቶች እየተመዘገቡ ነው ብለዋል። የፍትሕ አገልግሎቱን ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ወጪ ቆጣቢ በማድረግ የሕዝቡን ርካታ ለማረጋገጥ የተሠሩ ሥራዎች ውጤታማ እንደነበሩም ጠቅሰዋል። በጋምቤላ ክልልም የፍትሕ ዘርፍ የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ተግባራዊ በማድረግ የፍትሕ አገልግሎትን ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት አበረታች መሆኑን አንስተዋል። በተለይም የፍትሕ አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ እየተከናወነ ያለው ተግባር ውጤት የታየበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይም በይበልጥ መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል። የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ መሠረት ማቲዎስ በኩላቸው፤ የፍትሕ ተቋማት ዜጎች በፍትሕ ሥርዓቱ ያላቸውን ተጠቃሚነት የሚያጠናክሩ ተግባራት ላይ አተኩረው መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በተለይም ማኅበረሰብ አቀፍ የፍትሕ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ ያለው ተግባር ሊጠናክር ይገባል ብለዋል። በክልሉ ያለውን የፍትሕ ሥርዓት ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ ኡዶል ኡኩሪ ናቸው። በክልሉ ፀድቆ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የፍትሕ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ፍኖተ ካርታ የዜጎች ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ ከማድረግ አንፃር አበርክቶው የጎላ መሆኑንም አብራርተዋል።
ችግሮችን በምክክር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የፖለቲካ ፓርቲዎች በቁርጠኝነት መስራት ይገባናል
Jan 17, 2026 73
ደሴ፤ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የፖለቲካ ፓርቲዎች በላቀ ዝግጁነትና በቁርጠኝነት መስራት ይገባናል ሲሉ በደሴ ከተማ የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። በኢትዮጵያ አካታች፣አሳታፊና ሁሉን አቀፍ ምክክር በማድረግ ሀገራዊ ችግሮችን በዘላቂነት የመፍታት ዓላማ በመሰነቅ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ እየሰራ ይገኛል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በዴሴ ከተማና አካባቢው የሚንቀሳቀሱ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች የቆዩ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የፖለቲካ ፓርቲዎች በላቀ ዝግጁነትና በቁርጠኝነት መስራት ይገባናል ብለዋል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል የወሎ ዴሞክራቲክ ፓርቲ የደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ዳውድ መሀመድ፤ ፓርቲያቸው በምክክሩ እስካሁን ጠንካራ ተሳትፎ ማድረጉን አስታውሰው እስከ ፍፃሜው የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የምክክር ሂደቱ አካታችና አሳታፊ በመሆኑ የሀገርን መሰረታዊ ችግሮች በመፍታት ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት ጠንካራ ሃገረ መንግስት መገንባት የሚያስችል ይሆናል ብለዋል። በመሆኑም ለስኬታማነቱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሁሉም አካላት የነቃ ተሳትፎና ትብብር ማድረግ ይጠበቅብናል ሲሉ ተናግረዋል። የምክክር ሂደትን በመግፋት ትጥቅ አንስተው በጫካ የሚገኙ ወገኖችም ለምክክር፣ ለዘላቂ ሰላምና ልማት በጋራ ለመስራት መምጣት አለባቸው ብለዋል። የኢዜማ ፓርቲ ደሴ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጸሃፊ ብርሃነ አለም፤ በምክክሩ የእስካሁኑ ሂደት ነፃ፣ አሳታፊና አካታች በሆነ መልኩ እየተካሄደ በመሆኑ የተሳካ ውጤት እንደሚመጣ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። በመሆኑም በምክክር ሂደቱ የሚፈለገው ውጤት እንዲመጣ የሁላችንም ቀና ትብብርና ተሳትፎ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል። በበልጽግና ፓርቲ የደሴ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሸናፊ አለማየሁ፤ የምክክር ሂደቱ ለዚህ ትውልድ ታሪካዊ አጋጣሚ በመሆኑ እድሉን በመጠቀም ጠንካራ ሀገረ መንግስትና የበለጸገች ሀገር መገንባት ይገባናል ብለዋል። ለምክክር ሂደቱ መሳካት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በቅርበት እየሰራ መሆኑን ገልጸው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የምክክር ሂደቱ ችግሮችን በዘላቂነት መፍቻ በመሆኑ ዕድሉን በአግባቡ መጠቀም ይገባል
Jan 17, 2026 98
ሚዛን አማን፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡- የምክክር ሂደቱ ችግሮችን በዘላቂነት የመፍቻና የሰላም ዕሴት መሰረት ስለሆነ ዕድሉን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ የሚዛን አማን ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች አስገነዘቡ። ከሀገር ሽማግሌዎቹ መካከል ሙሴ አይነታ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የጥፋት አዙሪትን በመቋጨት ለቀጣዩ ትውልድ የምትመች ሀገር ለመገንባት በምክክር ችግሮቻችንን መፍታት ይገባል። የሀገሩን ሰርዶ በሀገሩ በሬ እንዳሚባለው የራሳችንን ችግሮች በራሳችን መፍታት ይኖርብናል ብለዋል። የትኛውንም የግጭትና የልዩነት ዕሳቤ በምክክር፣ ዕርቅና ይቅርታ ከመፍታት የሚሻል አማራጭ የለም ያሉት ደግሞ ሌላኛው የሀገር ሽማግሌ ምትኩ ሾሻ ናቸው። በሀገር ጉዳይ በመምከር መፍትሔ እናምጣ ብሎ መገናኘት መልካም ሐሳብ በመሆኑ ውጤት የሚያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛው የሀገር ሽማግሌ ተስፋዬ ዘካርያስ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ አንድነትን፣ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማረጋገጥ የሚቻለው ልዩነቶችን በምክክር እየፈቱ ለሰላም መትጋት ሲቻል መሆኑን ጠቁመዋል። ያልተጠቀምንባቸው የካበቱ ዕሴቶች ስላሉ ለሀገር ሰላምና ልማት እንጠቀምባቸው ብለዋል። ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካትም የሀገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት አባቶች ትልቅ ኃላፊነት እንዳለብን ተገንዝበን በዚህ ልክ መትጋት ይጠበቅብናል ነው ያሉት የሀገር ሽማግሌዎቹ።
ብልጽግና ፓርቲ በሁሉም ዘርፎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የጀመራቸውን ተግባራት ያጠናክራል - አቶ አደም ፋራህ
Jan 16, 2026 106
ሆሳዕና፤ ጥር 8/2018(ኢዜአ)፡- ብልጽግና ፓርቲ በየዘርፉ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የጀመራቸውን ተግባራት እንደሚያጠናክር የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ገለጹ። በሆሳዕና ከተማ ሲካሄድ የቆየው የፓርቲው የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም መድረክ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና ገበያን ለማረጋጋት የተሰሩ ሥራዎችን በመገምገም ተጠናቋል፡፡ አቶ አደም ፋራህ በመድረኩ እንደገለጹት፣ የብዝሀ ዘርፍ ኢኮኖሚ አቅጣጫን ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ተገኝቷል። ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ተግባራዊ በማድረግ የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማስፋት በተከናወኑ ተግባራት ባለፋት 6 ወራት ተስፋ ሰጪ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ የተገኙ ድሎችን ለማላቅ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግና የሥራ ዕድል የሚያስገኙ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ የሥራ አጥ ልየታን፣ ነባር ኢንተርፕራይዞችን የማጠናከርና የብቃት ምዘና ተቋማት ሥራ በጥራት እንዲከናወን በልዩ ትኩረት መምራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ገበያን ለማረጋጋት በተሰሩ ሥራዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎች እንዳሉ ገልጸው ይህን ለማጠናከር የምርት አቅርቦትን ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡ ለዚህም የግብይት ማዕከላትን የማስፋት፣ የምርት ጥራትን የማስጠበቅ፣ ህብረት ስራ ማህበራትን የመደገፍና የፓርቲው የአንድ ግብ የሆነውን ደረጃውን የጠበቀ ዘመናዊ የግብይት ማዕከል በአንድ ከተማ ግንባታ ስራን ማጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ በአጠቃላይ ብልጽግና ፓርቲ በተለያዩ ዘርፎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የጀመራቸውን ተግባራት ያጠናክራል ሲሉም ገልጸዋል። ለዚህም በየዘርፉ ባለፉት ስድስት ወራት የተገኙ ስኬቶችን በማላቅና ለሚገጥሙ ተግዳሮቶች የመፍትሔ አቅጣጫ በማስቀመጥ የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ የአመራሩ ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል። በመድረኩ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ኃላፊዎችና የወጣቶች ክንፍ አመራሮች ተሳትፈዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
አሰባሳቢና ገዢ ትርክት በማስረጽ ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚና መጎልበት አለበት
Jan 16, 2026 87
ሐረር ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል አሰባሳቢና ገዢ ትርክት በማስረጽ ረገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን ማጎልበት እንደሚገባቸው ተመለከተ። በሐረሪ ክልል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች እና የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ሚናቸውን ማጠናከር በሚቻሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄዷል። የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ፣ መልካም እሴቶች እንዲጎለብቱ እና ህዝቡ በክልሉ በሚከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የሚያደርገውን ተሳትፎ ለማሳደግ ያስቻሉ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል ብለዋል። በተለይም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ፅንፈኛ ሀይሎች በማህበረሰቡ መካከል የሚነዙትን የጥላቻና ሀሰተኛ መረጃዎችን በመከላከል አሰባሳቢና ገዢ ትርክቶች እንዲሰርጹ በማድረግ ረገድ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በተለይም አፍራሽ የሆኑ ፕሮፓጋንዳዎችን ቀድሞ በመከላከል የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅና ሕብረ ብሄራዊነት እንዲሰርፅና እንዲፀና በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ባለሙያዎች እና ማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች በክልሉ በሁሉም ዘርፎች ለተመዘገቡ ውጤቶች አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንም አንስተዋል። በተጨማሪም የህዝብ ሰላምና አንድነት እንዲጎለብትና የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አዎንታዊ ሚናቸውን እንዲያጠናክሩ አስገንዝበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ በበኩላቸው፤ የክልሉ ህዝብ የሚታወቅበት የሰላም፣ መቻቻልና አብሮነት እሴቶች እንዲጎለብቱ በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች ተግባራትን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል። የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በተለይም የጋራ የሚያደርጉ ሀገራዊ እሴቶችን በማጠናከርና ገዢ ትርክትን በመገንባት ሰላምና ልማት እንዲጠናከር እያበረከቱ የሚገኘው ተግባር ይበልጥ መጎልበት አለበት ብለዋል። የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎችም የሚያስተላለፉት መልዕክት ሀገርን የሚገነባ፣ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን የሚሰብክ እንዲሁም ህብረተሰቡ በልማት እንቅስቃሴው ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችሉ ሊሆኑ ይገባል ነው ያሉት።
ከኢትዮጵያ ጋር ያለንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር እንሰራለን -አምባሳደሮች
Jan 15, 2026 126
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018 (ኢዜአ)፡ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ገለጹ። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙ የ 14 ሀገራት አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ ተቀብለዋል። የሹመት ደብዳቤያቸውን ለፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ያቀረቡትም የኪርጊስታን፣ ጣልያን፣ ሞሪሺየስ፣ ዛምቢያ፣ጀርመን፣ ጆርዳን፣ ኒውዝላንድ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቡሩኪና ፋሶ፣ ሞዛምቢክ፣ ኬንያ፣ቤላሩስ፣ ፊሊፒንስ፣ ላቲቪያ ሀገራት አምባሳደሮች ናቸው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በሰጡት ማብራሪያ የሹመት ደብዳቤያቸውን ካቀረቡ ሀገራት መካከል 11ዱ ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ መሆኑን ገልጸዋል። አምባሳደሮቹ ከፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ጋር ከፍተኛ ውጤት እየተመዘገበበት ባለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እንዲሁም በንግድ እና ኢንቨስትመንት በሚሰማሩባቸው መስኮች ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች በሚያስከብሩ ስራዎች ዙሪያ ምክክር ማድረጋቸውን ነው የተናገሩት። በውይይቱ አምባሳደሮቹ በኢትዮጵያ እየተመዘገበ ላለው ለውጥ አድናቆት መስጠታቸውን ጠቁመው፥ ሀገሮቻቸው ከኢትዮጵያ ልምድና ተሞክሮ መውሰድ እንደሚፈልጉ መናገራቸውን አንስተዋል። በኢትዮጵያና በሀገራቱ መካከል የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል ነው ያሉት። በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙት የጣልያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ በትምህርት፣ በክህሎት፣ በሳይንሳዊ እና በባህል ትብብር ዙሪያ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በሚኖራቸው ቆይታ ጣልያን ለኢትዮጵያ ጠንካራ ወዳጅ መሆን የምትችልባቸውን መንገዶች ለማየት እንደሚጥሩ ጠቁመዋል። አዲስ የተሾሙት የዛምቢያ አምባሳደር አልበርት ሙቻንጋ በበኩላቸው በግብርና ማለትም በተሻሻሉ የሰብል ዝሪያዎች ላይ ልምድ በመለዋወጥ እና በስፋት በመተግበር ምርታማነትን ለማሻሻል እንደሚሰሩ ገልፀዋል። የኬንያ አምባሳደር ጋልማ ሙክሄ በኢትዮጵያ እና በኬንያ መካከል ያለውን ታሪካዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር እና ለማሳደግ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመከላከያ እና በሌሎች በርካታ ዘርፎች ላይ ይህን ግንኙነት ለማጠናከር በጋራ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ባክ ቫለንቲኖ የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። ይህንንም በኢትዮጵያ ከሚገኙ ሌሎች አካላት ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ አመላክተዋል:: የፊሊፒንስ አምባሳደር ማሬ ቻርሎቴ በቀጣዩ አመት ሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበትን የምስረታ በአላቸውን እንደሚያከብሩም ተናግረዋል። በሁለቱ አገራት መካከል በፖለቲካ፣በኢኮኖሚ እና በህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ጠንካራ ትብብር ለመፍጠር እንደሚሰራ አመላክተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ማህበራዊ
ተፈጥሯዊ ፀጋዎችን ተጠቅመን የዜጎቻችንን ኑሮ መቀየር ከቻልን የተሟላ ብልጽግና እናመጣለን- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Jan 17, 2026 58
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡- በሀገር ደረጃ በየአካባቢው ያሉ ተፈጥሯዊ ፀጋዎችን ለይተን በመጠቀም የዜጎቻችንን ኑሮ መቀየር ከቻልን የተሟላ ብልጽግና እናመጣለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጉራፈርዳ ወረዳ የገጠር ኮሪደርን ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላም ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በሰጡት ገለጻ፤ ጉራፈርዳ ወረዳ በለምነቱ፣ በሚያመርተው ቡና፣ በልዩ ልዩ የግብርና ምርቶች እንደሚታወቅ እና ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ዜጎች በጋራ የሚኖሩበት መሆኑን አንስተዋል። በከተማ የጀመርነውን የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ገጠር እናምጣ ብለን እየሠራን ባለው ሥራ፤ በሁሉም ክልሎች አዳዲስ የተሻገሩ የገጠር መንደሮች እየተገነቡ ይገኛሉ ሲሉም አስታውቀዋል። በጉራፈርዳ ወረዳ በተሠራው የገጠር ኮሪደርም የጓሮ አትክልት፣ ዶሮ፣ የወተት ላሞችና ማርን ጨምሮ የሌማት ትሩፋት መመልከታቸውን ጠቅሰዋል። በእያንዳንዱ ጓሮ ይህ ካለ በአካባቢው ካሉ የእርሻ ውጤቶች ጋር ተደምረው በቂ ምግብ የሚያገኙበትን ዕድል ይፈጥራል ብለዋል። ስለዚህ በሀገር ደረጃ እንደየ አካባቢው ተፈጥሯዊ ፀጋዎችን ለይተን በመጠቀም የዜጎቻችንን ኑሮ መቀየር ከቻልን የተሟላ ብልጽግና ማምጣት እንችላለን ሲሉ አስገንዝበዋል። በወረዳው የተገነባው የገጠር ኮሪደር ልማት መዋዕለ-ሕጻናት ማካተቱ ከሌላው እንደሚለየውም ጠቁመዋል። በአጠቃላይ ብልጽግናን እናረጋግጥ ሲባል በቁጥር የሚታይ ዕድገት ብቻ ሳይሆን፤ በከተማም በገጠርም እያንዳንዱን ዜጋ መንካት አለበት ማለት ነው ብለዋል። ክልሉ ያለውን ጸጋ በመጠቀም የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል መሥራት እንደሚጠበቅበትም አመላክተዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እስካሁን የተሠሩትና እየተሠሩ ያሉ የገጠር ኮሪደሮች ሞዴል መሆናቸውን ገልጸው፤ ክልሎች፣ ባለሃብቶች፣ ዞኖች እንዲሁም ነዋሪው በራሱ ወጪው ቀላል መሆኑን በመረዳት ማስፋትና ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል። በስንዴ፣ በቡና፣ በሌማት ትሩፋት ያገኘነው ውጤት የዜጎችን ኑሮ መቀየር አለበት በሚል የጀመርነው የገጠር ኮሪደር ሥራ ፍሬ እያፈራ ነው ብለዋል። ስለዚህ በቀጣይ በይበልጥ እንዲስፋፋ አሳስበው፤ ተባብረን በመሥራት የዜጎቻችንን ኑሮ እንድንቀይር አደራ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የዋግ ልማት ማህበር የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያከናውነውን ተግባር አጠናክሮ ይቀጥላል
Jan 17, 2026 119
ሰቆጣ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፡-የዋግ ልማት ማህበር በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል የልማት ማህበሩ አስታወቀ። የዋግ ልማት ማህበር 13ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን በሰቆጣ ከተማ እያካሄደ ነው። የልማት ማህበሩ ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ መልሰው ተፈራ (ዶ/ር) በጉባኤው እንዳሉት ልማት ማህበሩ ባለፉት ዓመታት በብሔረሰብ አስተዳደሩ መንግስት ከሚያከናውናቸው ተግባራት በተጨማሪ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን አከናውኗል። ደረጃቸውን ያልጠበቁ መማሪያ ክፍሎችን በአዲስ መልክ አሻሽሎ ከመስራት ባለፈ የጤና ተቋም ተደራሽ ባልሆኑባቸው አካባቢዎች የጤና ተቋማት ግንባታ ማከናወኑን በማሳያነት ጠቅሰዋል። ልማት ማህበሩ በብሔረሰብ አስተዳደሩ የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት ሲያከናውን የቆያቸውን ተግባራት በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል መልሰው (ዶ/ር) ገልፀዋል። የብሔረሰብ አስተዳደሩ ምክትል አስተዳዳሪና የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ሹመት ጥላሁን እንዳሉት ልማት ማህበሩ በአስተዳደሩ በኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፍ የሚስተዋሉትን የልማት ክፍተቶች ለመሙላት የተለያዩ የልማት ስራዎችን ማከናወኑን ጠቁመዋል። የልማት ማህበሩ ህብረተሰቡን በማስተባበር በተለይ በትምህርት፣ በጤና እና በሰብዓዊ ድጋፎች ያከናወናቸው ተግባራት የህብረተሰቡን ችግር እያቃለሉ መሆናቸውንም ተናግረዋል። በዚህ ረገድ የልማት ማህበሩ እያደረገ ያለው አስተዋጾን ማጠናከር በራስ አቅም የመረዳዳት ባህልን ለማሳደግ ትልቅ አቅም ይሆናል ሲሉም አቶ ሹመት ገልፀዋል። ልማት ማህበሩ የዋግ ህዝብ ሃብት በመሆኑ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ማህበሩን በተለያየ መንገድ በማገዝ የልማት ክፍተቶችን ለመድፈን የሚደረገውን ጥረት ማገዝ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል። ጉባኤው የልማት ማህበሩ ያለፉት ሦስት ዓመታት ተግባራት አፈፃፀምና የኦዲት ሪፖርትን ከመገምገም ባለፈ የልማት ማህበሩ መመሪያ እና የቦርድ አባላት ምርጫን በተመለከተ የሚቀርቡ አጀንዳዎችን ገምግሞ እንደሚያጸድቅ ተመላክቷል።
የክልሉን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የወጣቱን እውቀት፣ ጉልበትና ፈጠራ ለመጠቀም ትኩረት ተደርጓል
Jan 17, 2026 55
ባህርዳር ጥር 9/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የወጣቱን እውቀት፣ ጉልበትና ፈጠራ ለመጠቀም ትኩረት መደረጉን የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው በክልሉ የ25 ዓመት የአሻጋሪ እቅድ ላይ በክልሉ የሚገኙ ወጣት የመንግስት ሰራተኞችን ያሳተፈ መድረክ ዛሬ በባህርዳር ከተማ አካሂዷል። በቢሮው የወጣቶች ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ዘላለም አረጋ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት የክልሉን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የወጣቱን እውቀት፣ ጉልበትና ፈጠራ ለመጠቀም የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ ነው። አሁን የሚስተዋሉ ችግሮችን በማስወገድ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ልማትን ለማፋጠን በሁሉም መልኩ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው የክልሉ ወጣት የ25 ዓመት የአሻጋሪ የልማት እቅድ ላይ ግንዛቤ በመያዝ፣ ለአተገባበሩ አቅሙን መጠቀም እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተለይም የክልሉን ህዝብ ከድህነት ለማላቀቅ የተያዘውን የአሻጋሪ እቅድ ለማሳካት ወጣቶች ሙሉ አቅማቸውን ተጠቅመው መረባረብ አለባቸው ብለዋል። ዛሬ የተካሄደው መድረክም ይሄን አላማ ለማሳካት መሆኑን አመልክተው በቀጣይም እስከ ቀበሌ ድረስ እቅዱን በማውረድ መግባባት በመፍጠር የተቀናጀና የተናበበ አተገባበር እንዲኖር ይሰራል ነው ያሉት። በቢሮው የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና የወጣቶች ንቅናቄ ተሳትፎ ዳይሬክተር አቶ አወቀ መንግስቴ ባቀረፉት የውይይት መነሻ ጽሁፍ እንደገለጹት የ25 ዓመቱ አሻጋሪ እቅድ የክልሉን ህዝብ ወደ መካከለኛ ገቢ ለማሸጋገር የሚያስችል ነው። እቅዱ ከመነሻ ጀምሮ እስከ አተገባበር ድረስ ለወጣቶች ተሳትፎ፣ ተጠቃሚነትና ፈጻሚነት ልዩ ትኩረት የሰጠ መሆኑን ጠቁመው በተለይም ወጣት የመንግስት ሰራተኞች ለእቅዱ መሳካት የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል። የአሻጋሪ እቅዱ በሁሉም ዘርፍ ምርታማነትን ማሳደግ፣ ሰላምና ፍትህን ማረጋገጥ፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂን ማበልጸግ፣ ክልልዊ ባህልና እሴትን ማጎልበትና ሌሎች መሰረታዊ አቅጣጫዎችን ያስቀመጠ መሆኑን አስረድተዋል። ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የመጡት ጽሁፍ አቅራቢ የሻምበል አግማስ (ዶ/ር)፣ ወጣቱ አቅሙን፣ ጉልበቱንና እውቀቱን ለአገር ልማትና እድገት ማዋል እንዳለበት አመልክተዋል። በመድረኩ ላይ ከክልል ቢሮዎች፣ ወጣት አደረጃጀቶችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል።
ዩኒቨርሲቲው ብቁ ባለሙያዎችን በማፍራት አህጉራዊ የአቪዬሽን ትስስርን የማጎልበት ሚናውን እየተወጣ ነው
Jan 17, 2026 88
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በዘርፉ ብቁ ባለሙያዎችን በማፍራት አህጉራዊ የአቪዬሽን ትስስርን የማጎልበት ሚናውን እየተወጣ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ከ12 ሀገራት የተውጣጡ 457 የአቪዬሽን ባለሙያዎችን ዛሬ አስመርቋል። ተመራቂዎቹ 58 ፓይለቶች፣ 115 የአውሮፕላን ጥገና ቴክኒሻኖች እና 284 የበረራ አስተናጋጆች ናቸው፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል ኢትዮጵያ፣ የጣሊያን፣ የካሜሮን፣ ቻድ፣ ጋቦን፣ ማዳጋስካር፣ ማላዊ፣ ናይጄሪያ፣ ሴኔጋል፣ ታንዛኒያ፣ ኡጋንዳና የመን ዜጎች ይገኙበታል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው፥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ግንባር ቀደም አየር መንገድ እንዲሆን ያስቻሉ በርካታ ምክንያቶች መኖራቸውን ተናግረዋል። ከነዚህ መካከል ዋነኛው ከፍተኛ ችሎታ እና ተነሳሽነት ያለው የሰው ሃይል የመመልመል፣ የማሰልጠን እና የማቆየት ችሎታ ነው ብለዋል። በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ለበርካታ አስርት ዓመታት ቁልፍ የአቪዬሽን ባለሙያዎችን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በማቅረብ ወሳኝ ሚና መጫወቱን ጠቅሰዋል። የዛሬዎቹ ተመራቂዎች ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ መሆናቸውን በመጠቆም ይህም አህጉራዊ የአቪዬሽን ትስስርን ለማጎልበት ሚናው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ለአፍሪካ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ እድገት ያበረከተውን አስተዋፅኦ የሚያሳይ ግልጽ ምስክርነት ነው ሲሉ ዋና ስራ አስፈፃሚው አጽንኦት ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለስኬቱ ብቁ የአቪዬሽን ባለሙያዎችን ማፍራት አስፈላጊ መሆኑን በመገንዘብ የዩኒቨርሲቲውን አቅም የበለጠ ለማሳደግ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በመመደብ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ላዕከ ታደሰ በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የአቪዬሽን ስልጠና ለመስጠት በቁርጠኛነት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። ዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያ አየር መንገድን የሚያገለግሉ ባለሙያዎችን እያስተማርን ብቻ አይደለም፣ ነገር ግን በአፍሪካ በአቪዬሽን ዘርፍ የሚሰማሩ ባለራዕይ መሪዎችን እያነጽን ነው ሲሉ ተናግረዋል። እንደ እውነተኛ የፓን አፍሪካ ተቋም የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ተልዕኮ አህጉሪቱ በዘርፉ ያላትን ደረጃ ከፍ አድርጎ ማውጣት ነው ብለዋል፡፡
ኢኮኖሚ
የገበታ ለትውልድ ሥራ የመጀመሪያው መዳረሻ የሆነው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በይፋ ተመረቀ
Jan 18, 2026 38
አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2018 (ኢዜአ)፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገበታ ለትውልድ ሥራ የመጀመሪያው መዳረሻ የሆነው እና በ36.7 ሔክታር የጥብቅ ደን እና የተፈጥሮ ኃብት ስጦታ የተዘረጋው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በይፋ ተመርቋል። ኢኮ ሎጁ የሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍ ባለፉት ሰባት ዓመታት ዘላቂነትን፣ የቅርስ ሀብትን እና ለዘመናት የሚዘልቅ ዓለም አቀፍ ደረጃን የመጠበቅ ዕድል መፍጠርን በማዋሃድ ምን ያህል እንደተለወጠ ማሳያ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ገልጿል። የገበታ ለትውልድ ሥራ ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ መዳረሻዎችን በማልማት የሀገራችንን እምቅ አቅም ለማውጣት የሚደረገው የሰፊው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ስትራቴጂ አካል ነውም ብሏል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመረው ይኽ ሥራ በስኬት ከተተገበሩት የገበታ ለሸገር እና ገበታ ለሀገር መርሐ-ግብሮች የቀጠለ እና ሥራዎቹን ወደአዳዲስ አካባቢዎች የወሰደ ሲሆን የተፈጥሮ ውበትን፣ የባሕል ቅርስን እና ዘላቂ ልምድን በማቀናጀት የተከናወነም መሆኑ ተመላክቷል። እነዚህ ሥራዎች የከተማ እና ተፈጥሯዊ መዳረሻዎችን ወደ ሳቢ የቱሪዝም ማዕከልነት የለወጡ መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።
የግብር ከፋዩ ለሀገር ዕድገት ያለው ቁርጠኝነት ማደግ ስኬታማ ለውጥ እንዲመዘገብ አግዟል- ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሤ
Jan 17, 2026 54
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ ግብር ከፋዩ የሚከፍለው ግብር ለሀገር ዕድገት እንደሚውል ያለው ግንዛቤና ታክስ የመክፈል ቁርጠኝነት ማደግ ስኬታማ የታክስ አሰባሰብ እንዲኖር ማገዙን የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሤ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ''የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ'' በሚል ሐሳብ በተካሄደ ኮንፈረንስ ላይ የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሤ ገለጻ አድርገዋል። ሚኒስትሯ የታክስ አሥተዳደር ሪፎርም ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ቀጣይነት በሚል ርዕሰ ጉዳይ ባቀረቡት ገለጻ፤ የታክስ አሥተዳደር አገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻልና የማስፈጸም ዐቅምን ማጠናከር፣ ዘመናዊ የታክስ አሥተዳደር ሥርዓት መገንባት፣የታክስ ሕግ ተገዥነትን ማረጋገጥ እና ዘላቂ የገቢ ዕድገት ማረጋገጥ በሚሉት ዐበይት ጉዳዮች ላይ ሪፎርሙ መከናወኑን አንስተዋል። ከላይ በተገለጹት ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣትም በሪፎርሙ ወቅት የፖሊሲ እና የሕግ ማሻሻዎች መደረጋቸውን ጠቁመው፥ እነዚህን ለመፈጸምም የአሠራር ማሻሻያዎች ተደርገዋል ብለዋል። ቅርንጫፎች ማስፋፋትን ጨምሮ ከፌደራል እስከ ክልል ባሉ ባለድርሻ አካላት ዘንድ ስኬታማ ተግባራት ለማስመዝገብ እንዲቻል የዐቅም ግንባታ ሥራዎች መከናወናቸውንም ጠቅሰዋል። እንደ ሀገር የተጣጣመ የታክስ አሥተዳደር ሥርዓት እንዲኖር ጥረቶች መደረጋቸውንም አመላክተዋል። የዲጂታል ሥርዓቶችን በመዘርጋት ለግብር ከፋዮች ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር አንጻር ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተው፤ ለአብነትም መሠረታዊ የሚባሉ የዲጂታል ፕላት ፎርሞች መዘርጋታቸውን ጠቅሰዋል። በዚህም መሠረት ግብር ከፋዩ በየቢሮው መሄድ ሳይጠበቅበት ኢ-ፋይል እና ኢ-ፔይ የሚያደርግበትን ሥርዓት ዘርግተናል ነው ያሉት። በሌላ በኩል በኢንሳ አማካኝነት ለምቶ በቅርቡ ወደ ሥራ እያስገባነው ባለው የኤሌክትሮኒክ ኢንቮይሲንግ ሲስተም በትራንዛክሽን ደረጃ ወደ 291 ቢሊየን ብር ግብይት ተካሂዶበታል ብለዋል። ይህም ከሐሰተኛ ደረሠኝ፣ ከውሳኔ አሰጣጥ፣ ከመረጃ አጠቃቀም እና ተያያዥ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮችን የሚቀርፍ መሆኑን አስገንዝበዋል። ከጉምሩክ አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘም አሁን ላይ የወጪና ገቢ ንግድን ከማሳለጥ አንጻር በአንድ መስኮት አገልግሎት ከ80 በላይ ተቋማት በአንድ ማዕከል አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። በሌላ በኩል ኢኮኖሚውን በዘላቂነት የሚደግፍ ወደ ሉዓላዊነት የሚወስደን ገቢ በሀገር ውስጥ መመንጨት አለበት በሚል የተከናወነው ሥራ የሪፎርሙን ስኬት አሳይቷል ነው ያሉት። በዚህም መሠረት በ2011 የበጀት ዓመት የፌደራል መንግሥት 198 ቢሊየን ብር ታክስ መሰብሰቡን አውስተው፤ በ2017 ደግሞ 900 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ገልጸዋል። በተያዘው ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ ደግሞ 907 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ገልጸው፤ ይህ አሃዝ ከዕቅዳችን አንጻር ወደ 68 ቢሊየን ብር ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንጻርም የ258 ቢሊየን ብር ብልጫ ማሳየቱን አንስተዋል። ይህም በየደረጃው ያሉ አካላት ድጋፍ፣ የግብር ከፋዮች ሀገርን ለመለወጥ ያለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ያላቸው ቁርጠኝነት ውጤት መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል። ከክልሎች አኳያም በ2011 የታክስ ገቢ 79 ቢሊየን ብር ብቻ እንደነበር አውስተው፤ በ2017 ደግሞ 543 ቢሊየን ብር መሰብሰባቸውን ተናግረዋል። በተያዘው የበጀት ዓመት እንደ ሀገር ከ2 ነጥብ 1 ትሪሊየን ብር በላይ ታክስ ለመሰብሰብ መታቀዱን እና ባለፉት ስድስት ወራት 1 ነጥብ 17 ትሪሊየን ብር ታክስ መሰብሰቡን አስታውቀዋል።
የኢኮኖሚ ሪፎርሙ በዘርፉ የጎላ ሚና ያላቸው ቁልፍ ተቋማትን ወልዷል- ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ
Jan 17, 2026 56
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ የለውጡ መንግሥት ያከናወነው የኢኮኖሚ ሪፎርም በኢኮኖሚ ረገድ ቁልፍ ሚና ያላቸው ተቋማት መውለዱንና የኢኮኖሚ ዕድገቱንም ማቃናቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ አስገነዘቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ''የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ '' በሚል ሐሳብ በተካሄደ ኮንፈረንስ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ገለጻ አድርገዋል። በገለጻቸውም፤ከሰባት ዓመታት በፊት ኢኮኖሚውን የገጠሙት ዋና ዋና የማክሮ ፊሲካል ተግዳሮቶችን አንስተዋል። እነዚህ ተግዳሮቶችም፤ ከፍተኛ የዋጋ ንረት፣ የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ ዘላቂና አስተማማኝ የፊሲካል ቁመና አለመኖር፣ ከፍተኛ የዕዳ ጫና፣ የውጭ ምንዛሪ እጥረት እና የገበያ አለመረጋጋት መሆናቸውን አብራርተዋል። ስለዚህ ይህን የማክሮ ኢኮኖሚ ስብራት ለመጠገን ላለፉት ሰባት ዓመታት መንግሥት፤ በመጀመሪያው እና በሁለተኛው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም ሊከሰት የነበረውን የማክሮ ፋይናንሻል ቀውስ አስቀርቷል ብለዋል። በዚህም ጠንካራ ዕድገትን አስመዝግቦ በሁሉም የማክሮ ኢኮኖሚ አመላካቾች (ኢንዲኬተሮች) ወደ ተሻለ ቁመና ለመሻገር ተችሏል ነው ያሉት ሚኒስትሩ። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት አንዷ ልትሆን ትችላለች ነው ያሉት። የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ጠንካራ ተቋማት የተፈጠሩበት መሆኑን በአጽንኦት ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ስለዚህ ከተቋማት ግንባታ አንጻርም በኢኮኖሚ ረገድ ቁልፍ ሚና ያላቸው ተቋማትን የወለደ ሪፎርም ነው ብለዋል። በተጨማሪም የኢኮኖሚ ዕድገቱን ያቃና ሪፎርም መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም በርካታ ውጤቶች መገኘታቸውን አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በዲጂታል አማራጭ በመላ ሀገሪቱ ተደራሽነቱን እያሰፋ ነው
Jan 17, 2026 62
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በዲጂታል አማራጭ በመላ ሀገሪቱ ተደራሽነቱን እያሰፋ መሆኑን አገልግሎቱ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ሙሉጌታ ታደሰ ገለጹ። በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ የተደረገው 60 ሚሊየን ብር ተሸላሚ የሚያደርገው ዲጂታል ሎተሪ ዕጣ በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት እድል አዳራሸ ወጥቷል። በእጣ አወጣጥ ስነ ሰርዓቱ ላይ የመንግስት ተቋማት ሀላፊዎች፣ ባለድርሻ አካላትና ታዛቢዎች ተገኝተዋል። የ60 ሚሊየን ብር ዕጣው 6361547፤ 20 ሚሊየን ብር ተሸላሚ የሚያደርገው እጣ 5681025 እንዲሁም 10 ሚሊየን ብር ተሸላሚ የሚያደርገው ዕጣ 7699884 እንዲሁም ማስተዛዘኛ ቁጥር 4 ሆኖ ወጥቷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ እንደተናገሩት፤ የ60 ሚሊየን ብር ዲጂታል ሎተሪ በሽልማት ከፍተኛው መሆኑና ለመጀመሪያ ጊዜ በዲጂታል ብቻ መቅረቡ ልዩ ያደርገዋል። ደንበኞች በየትኛውም ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ በፖዝ ማሽን፣ በድረ ገጽና በተለያዩ የዲጂታል አማራጮች መሳተፍ መቻላቸውን ገልጸዋል። ይህም የሎተሪን ስራ ወጪ ቆጣቢ ፈጣንና ተደራሽ ማድረጉን ገልጸው፤ ደንበኞች በፍጥነትና በቀላሉ እንዲሳተፉ አስችሏል ብለዋል። በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ቴድሮስ ነዋይ በበኩላቸው፤ ዲጂታል ሎተሪ ሙሉ ለመሉ በዲጂታል መከናወኑ አገልግሎቱን ቀልጣፋ ማድረግ መቻሉን ጠቁመው፤ አሰራሩም ለደንበኞች ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንና ተሸላሚዎችን በቀላሉ ለማግኘት መቻሉን ተናግረዋል። በታምኮል ሶፍትዌር ሶልዩሽንስ የሳይበር ደህነነት ክፍል ሀላፊ አንማው ቃሬ የሎተሪ አገልግሎትን ለማዘመንና ዲጂታላይዝ ለማድረግ በጋራ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም የሎተሪ አገልግሎትን ከዝግጅት ጀምሮ እስከ ሽልማት ማውጣትና ደንበኞችን መለየት ደረጃ ድረስ በዲጂታል ለማከናወን አስችሏል ብለዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
በባህር ዳር ከተማ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ዘመናዊ የህዝብ ማጓጓዣ አውቶቡሶች ሥራ ጀመሩ
Jan 17, 2026 67
ባህር ዳር፣ጥር 9/2018(ኢዜአ)፦የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር በከተማዋ የሚስተዋለውን የትራንስፖርት ችግር ለማቃለል በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ዘመናዊ የህዝብ ማጓጓዣ አውቶቡሶችን ሥራ አስጀመረ። ዛሬ የአውቶቡሶቹ ርክክብ ሥነ ስርአት የተካሄደው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፣የምስራቅ እዝ ዋና አዛዥና የቀጠናው የፀጥታ ግብረ ሃይል ሰብሳቢ ሌተናል ጄነራል መሀመድ ተሰማና ሌሎች ሥራ ሃላፊዎች በተገኙበት ነው። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው በዚህ ወቅት እንደገለጹት፦ የከተማዋን ዘመናዊነት ከሚያረጋግጡ ተግባራት መካከል ዘመናዊና የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት አንዱ ነው። በዚህም ከተማ አስተዳደሩ ዘመኑን የዋጁና በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አስር አውቶብሶችን በመግዛት ዛሬ ሥራ ማስጀመሩን ገልፀዋል። ይህም የከተማዋን ህዝብ የትራንስፖርት ችግር ከመፍታት ባለፈ የቱሪዝም ማዕከልና የኢንቨስትመንት ተመራጭ ከተማ ለማድረግ የተጀመረውን ሥራ እንደሚያጠናክር አስረድተዋል። በተለይም አውቶቡሶቹ በከተማዋ በኮሪደር ልማት ከተገነባው ሰፊ የአስፋልት መንገድ ጋር የተጣጣመ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ዘመኑን የሚመጥንና በአነስተኛ ክፍያ ለህብረተሰቡ የትራንስፖርት አገልግሎት ማቅረብ ወሳኝና የከተማ እድገት መገለጫ እንደሆኑም አመልክተዋል። በከተማዋ ከዚህ ቀደም ከ20 በላይ አውቶብሶች ለህብረተሰቡ አገልግሎት ሲሰጡ እንደነበር ጠቁመው፣ የኤሌክትሪክ አውቶብሶች መጨመር የባህር ዳርን ስማርት ከተማነት ለማረጋገጥ የተያዘው ግብ ለማሳካት ያግዛል ብለዋል። የቢኬጅ (በላይነህ ክንዴ ግሩፕ) ባለቤትና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ በላይነህ ክንዴ በእለቱ እንደገለጹት፥ ቢኬጅ እንደሀገር በተለያዩ የልማት ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ያለ ድርጅት ነው ። በሀገር አቀፍ ደረጃ ትኩረት የተሰጠውን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለማሳካትም አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማስገባት ጭስ አልባና ለብዙ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ አውቶቡሶችን በመገጣጠም እያከፋፈለ ይገኛል ብለዋል። አውቶቡሶቹ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ እንደመሆናቸው መጠን ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ መሳካት ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸው ገልጸው፣ በሀገር ውስጥ መመረታቸው መለዋወጫ በቀላሉ ለማግኘት እንደሚያስችል ተናግረዋል። በአውቶቡሶቹ ርክክብ ላይ የተገኙት አማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በኤሌክትሪክ የሚሰሩትን አውቶብሶች ሥራ አስጀምረዋል። በሥነ-ስርዓቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች አመራሮችና የከተማዋ ነዋሪዎችም ተገኝተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
የኢንስቲትዩት የቴክኖሎጂ ፈጠራ በወሳኝ ጥቂት የሕክምና ዘርፎች የሚታየውን የሰው ኃይል እጥረት ለመሙላት ከፍተኛ ሚና አለው
Jan 17, 2026 109
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የቴክኖሎጂ ፈጠራ በወሳኝ ጥቂት የሕክምና ዘርፎች የሚታየውን የሰው ሃይል እጥረት ለመሙላት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ ገለፁ። የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አድርገዋል። ዋና ሥራ አስፈጻሚው በጉብኝታቸው በኢንስቲትዩቱ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች አስደናቂ መሆናቸውን መመልከታቸውን ገልጸዋል። በተለይም በጤናው ዘርፍ ለተግባራዊ አገልግሎት የሚውሉ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎች ላይ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል። የጤና እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ባለሙያዎች በቅንጅት መስራት የሚቻልበት ሁኔታ መኖሩ ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረባቸው ገልፀዋል። ይህም በሀገሪቱ የሰው ኃይል እጥረት ባለባቸው የሕክምና ዘርፎች ላይ የሚታየውን ክፍተት ለመሙላት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል። በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ሰፊ ዓለም አቀፍ የትብብር ዕድሎች መኖራቸውን ዶክተር ከሰተብርሃን ጠቁመዋል፡፡ በቦርድ አባልነት የሚያገለግሉበት ሴፒ የተሰኘው ዓለም አቀፍ ድርጅት ወረርሽኝ ሊያስከትሉ የሚችሉ ቫይረሶችን ቀድሞ በመለየት በ100 ቀናት ውስጥ ክትባቶችን ለማምረት እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ተቋሙ በአፍሪካ ውስጥ አብረውት ሊሰሩ የሚችሉ ማዕከሎችን በመፈለግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው፤ ጉብኝታቸው በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና በሴፒ መካከል ጠንካራ የሥራ ግንኙነት ለመፍጠር ዕድል እንደሚኖረው ገልጸዋል። ይህም የኢትዮጵያ የጤና ምርምር ተቋማት ሴፒ የሚያዘጋጃቸውን የኤ አይ ኢንጂኖች (AI Engines) በስፋት መጠቀም የሚችሉበትን መንገድ እንደሚያመቻች አመልክተዋል።
የግብርና ምርምር ውጤቶች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የጎላ ሚና እያበረከቱ ነው
Jan 16, 2026 64
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2018(ኢዜአ)፦ በምርምር የታገዙ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ በማቅረብ በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እንዲሁም የምግብና ሥርዓተ-ምግብ ሁኔታን ማሻሻል መቻሉን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ (ፎረም) ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ንጉሴ ደቻሳ (ፕ/ር) እንደገለጹት፤ ተቋሙ የምርት ማነቆ የሆኑ ችግሮችን በመለየት በሽታን የሚቋቋሙና ምርታማነትን የሚጨምሩ ዝርያዎችንና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የማፍለቅና የማስተዋወቅ ሥራዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ይህም ከምግብ ዋስትና ባለፈ ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ለማሳደግ እንዲሁም የገቢ ምርቶችን ለመተካት አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢንስቲትዩቱ ምርምሮችን ከሥነ-ምህዳርና ከማህበራዊ ተቀባይነት ጋር በማጣጣም የአፈር ለምነትን፣ የውኃ አጠቃቀምንና የባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ማድረጉንም ኃላፊው አብራርተዋል። በስዊዘርላንድ የበርን ዩኒቨርሲቲ ቡድን መሪ የሆኑት ዘሪሁን ታደለ (ፕ/ር)፤ በጤፍ ምርምር ዘርፍ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በመሆን ለአርሶ አደሩ ያቀረቧቸው የተሻሻሉ ዝርያዎች በተለያዩ ሥነ-ምህዳሮች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል። በአሜሪካ የሄልዝ ሜድና ፋርም ቢዝ ሥራ አስኪያጅ ሙሉ አየለ (ዶ/ር)፤ ግብርናውን ለማዘመን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ያለውን ፋይዳ በመጥቀስ በኢትዮጵያ የተጀመሩ ሥራዎች መጠናከር እንዳለባቸው አመልክተዋል። በናይጄሪያ ዓለም አቀፍ የትሮፒካል ግብርና ተመራማሪ መላኩ አየለ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በባዮቴክኖሎጂና በሥራስር ተክሎች ላይ የሚከናወኑ ምርምሮችን በኢትዮጵያ ለመተግበር ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ በስንዴ ምርት የታየው ስኬታማ ሥራ በሌሎችም ሰብሎች ሊደገም እንደሚገባ ጠቁመዋል። የሶር አፍሪካ ፋርም ሥራ አስኪያጅ ወጣት አንገፉ ባናታ፤ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ከተረፈ ምርቶች የዶሮ ምግብና የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ በማምረት ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን ተናግሯል፡፡ ሌሎች ወጣቶችን በማሰልጠን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ መሆኑን አክሏል፡፡ በመድረኩ ማጠቃለያ የግብርና ተዋናዮች በቅንጅት በመሥራትና የመረጃ ልውውጥን በማሳለጥ ለዘርፉ እመርታዊ ለውጥ እንዲመጣ መሥራት እንደሚገባ ተመላክቷል።
ማዕከሉ የኢትዮጵያና ኮሪያ ሪፐብሊክን ግንኙነት ከማጠናከር ባለፈ ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መሳካት ጉልህ ሚና ይኖረዋል
Jan 16, 2026 83
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እና ኮሪያ ሪፐብሊክ ትብብር እውን የሆነው የኢንፎርሜሽን ተደራሽነት ማዕከል ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሳካት ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ። በኢትዮጵያ የኮሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ካንግ ጁንግ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ውጤታማ እንዲሆን ኮሪያ ሪፐብሊክ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደምታደርግ አረጋግጠዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኮሪያ ሪፐብሊክ የቴክኖሎጂና አይ ሲ ቲ ሚኒስቴር እንዲሁም ከኮሪያ ሪፐብሊክ ብሄራዊ የኢንፎርሜሽን ማህበረሰብ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ያቋቋመውን የኢንፎርሜሽን ተደራሽነት ማዕከል በይፋ አስመርቋል። ማዕከሉ ዲጂታል ክህሎትን የሚያሳድጉ ስልጠናዎችን መስጠት እና በኮምፒውተር ሳይንስና አይ ሲቲ ዙሪያ የሚማሩ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተግባር ልምምድ እንዲያደርጉ እንደሚያስችልም ተመላክቷል። ማዕከሉ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት ማዕከልን ያካተተ ሲሆን በዘርፉ ጥናትና ምርምር የሚያካሄዱ የደህረ ምረቃ ተማሪዎች ምርምራቸውን እንዲያካሂዱ ምቹ አውድ የፈጠረ መሆኑም ተጠቅሷል። ማዕከሉ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያሉ ስታርታፖች የፈጠራ ሀሳባቸውን ወደ መሬት ማውረድ የሚችሉበት ድጋፍ የሚያገኙበት ሲሆን ጥናትና ምርምሮችን እንዲሁም ፈጠራን ማበረታታት ማዕከሉ ከተቋቋመባቸው ዓላማዎች መካከል ይገኙበታል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ አካታች የዲጂታል ስርዓት ለመገንባት ሀገራዊ ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው። ግቡን ለማሳካት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ወደ ስራ መግባቱን ጠቅሰው፥ ለስትራቴጂው ስኬት በዘርፉ የአቅም ግንባታ፣ ፈጠራና የዲጂታል ክህሎቱ ያደገ የሰው ኃይል ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል። ለዚህ ደግሞ በኢትዮጵያ እና ኮሪያ ሪፐብሊክ ትብብር ዛሬ ለምረቃ የበቃው ማዕከል ለዲጂታል 2030 ስትራቴጂ መሳካት የላቀ ሚና አለው ብለዋል። ማዕከሉ ኢትዮጵያና ኮሪያ ሪፐብሊክ ያላቸው ጠንካራ ትብብር መገለጫ መሆኑንም ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የኮሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ካንግ ጁንግ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የዲጂታል ኢኮኖሚ በመገንባት የዜጎችን ህይወት ለመለወጥ የጀመረው ጉዞ የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሪያ ሪፐብሊክ በዲጂታል ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ዝግጁ ናት ያሉት አምባሳደሩ በመስኩ ያለንን ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ዝግጁ ነን ብለዋል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ቤተልሔም ላቀው(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ዲጂታል ሥርዓት ግንባታ ውስጥ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል። በዚህ ረገድ የማዕከሉ ወደ ስራ መግባት የዲጂታል ክህሎቱ የዳበረ ትውልድ ለማፍራት አዎንታዊ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል። በመስኩ የሚከናወኑ ተግበራት ውጤት እንዲያመጡ በሕግ የማስደገፉ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም አብራርተዋል። የኮሪያ ሪፐብሊክ የብሔራዊ ኢንፎርሜሽን ማህበረሰብ ኤጀንሲ ፕሬዝዳንት ጆንግ ሱንግ ህዋንግ በበኩላቸው፤ ኤጀንሲው በተለይ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በአፍሪካ እንዲስፋፋ የአቅም ግንባታን ጨምሮ የተለያዩ ድጋፎችን ተደራሽ ለማድረግ ወጥኖ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ተመራጭ ከሆኑ የቴክኖሎጂ መዳረሻዎች መካከል አንዷ ናት ያሉት ፕሬዝዳንቱ ኤጀንሲው በዚህ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ስፖርት
የሊጉ መሪ አርሰናል እና ኖቲንግሃም ፎረስት አቻ ተለያዩ
Jan 17, 2026 74
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ22ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ኖቲንግሃም ፎረስት እና አርሰናል ያደረጉት ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። ማምሻውን በሲቲ ግራውንድ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ብልጫ ወስዶ የተጫወተው አርሰናል ያገኛቸውን የግብ እድሎች አለመጠቀሙ ሶስት ነጥብ እንዳያገኝ አድርጎታል። በመጀመሪያው አጋማሽ ጋብርኤል ማርቲኔሊ የሳተው ግልጽ የግብ እድል ተጠቃሽ ነው። ተጋጣሚው ኖቲንግሃም ፎረስት ወደ ኋላ አፈግፍጎ የመከላከል እና የመልሶ ማጥቃት ስልት ይዞ በመግባት ግብ ሳይቆጠርበት ወጥቷል። ውጤቱን ተከትሎ የሊጉ መሪ አርሰናል ነጥቡን ወደ 50 ከፍ አድርጓል። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሰባት ከፍ አድርጓል። አርሰናል ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ያላሸነፈ ሲሆን ግብም ማስቆጠር አልቻለም። ኖቲንግሃም ፎረስት በሊጉ በ22 ነጥብ 17ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ናይጄሪያ ግብጽን በማሸነፍ በአፍሪካ ዋንጫው ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች
Jan 17, 2026 62
አዲስ አበባ፤ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የደረጃ ጨዋታ ናይጄሪያ ግብጽን በመለያ ምት አሸንፋለች። ማምሻውን በመሐመድ አምስተኛ ስታዲየም የተደረገው ጨዋታ በመደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል። ጨዋታው ቀጥታ ወደ መለያ ምት አምርቷል።በዚህም ናይጄሪያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የነሐስ ሜዳሊያም አግኝታለች። ግብጽ አራተኛ በመሆን ጨርሳለች። በጨዋታው ናይጄሪያ የግብ እድል በመፍጠር፣ ግብጽ በኳስ ቁጥጥር የተሻሉ ነበሩ። ናይጄሪያ ሶስት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አንስታለች። ግብጽ ውድድሩን ሰባት ጊዜ በማሸነፍ ስኬታማዋ ሀገር ናት።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከአዳማ ከተማ ጋር አቻ ተለያየ
Jan 17, 2026 68
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት መርሐ- ግብር ሲዳማ ቡና እና አዳማ ከተማ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። ማምሻውን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ መስፍን ታፈሰ ለሲዳማ ቡና ግቦቹን አስቆጥሯል። አቡበከር ሳኒ እና ሙጂብ ቃሲም ለአዳማ ከተማ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ነጥቡን ወደ 30 ከፍ አድርጓል። ከተከታዩ ነገሌ አርሲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት የማስፋት እድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል። አዳማ ከተማ በ23 ነጥብ 7ኛ ደረጃን ይዟል። ጨዋታውን ተከትሎ የ15ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል። የ16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከጥር 12 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ እንደሚካሄዱ የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል።
በፕሪሚየር ሊጉ ቼልሲ ድል ሲቀናው ሊቨርፑል ነጥብ ጥሏል
Jan 17, 2026 61
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 22ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማምሻውን አምስት ጨዋታዎች ተደርገዋል። በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቼልሲ ብሬንትፎርድን 2 ለ 0 አሸንፏል። ጆአኦ ፔድሮ በጨዋታ እና ኮል ፓልመር በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ውጤቱን ተከትሎ ቼልሲ በ34 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃን ይዟል። ብሬንትፎርድ በ33 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ሊቨርፑል ከበርንሌይ አንድ አቻ ተለያይቷል። በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፍሎሪያን ዊትዝ ለሊቨርፑል፣ ማርከስ ኤድዋርድስ ለበርንሌይ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ሊቨርፑል በጨዋታው ላይ ያገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት አማካዩ ዶምኒክ ስቦዝላይ ሳይጠቀምበት ቀርቷል። ሊቨርፑል በ36 ነጥብ አራተኛ ደረጃን ሲይዝ በርንሌይ በ14 ነጥብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል። በሌሎች መርሃ ግብሮች ሰንደርላንድ ክሪስታል ፓላስን ፣ ዌስትሃም ዩናይትድ ቶተንሃም ሆትስፐርስን በተመሳሳይ 2 ለ 1 አሸንፈዋል። ሊድስ ዩናይትድ ፉልሃምን 1 ለ 0 ረቷል። በአሁኑ ሰዓት የሊጉ መሪ አርሰናል ከኖቲንግሃም ፎረስት ጋር ጨዋታውን እያደረገ ይገኛል።
አካባቢ ጥበቃ
በብሔረሰብ አሥተዳደሩ በሞዴል መንደሮች የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራ ይከናወናል
Jan 16, 2026 85
ሰቆጣ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር በሰባት ሞዴል መንደሮች የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታወቀ። በአሥተዳደሩ የገጠር ኮሪደር ልማትን ለማሳካት ያለመ የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በሰቆጣ ከተማ ተካሂዷል። የብሔረሰብ አሥተዳደሩ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የመንገድ መምሪያ ኃላፊ ፀጋው እሸቴ በዚሁ ወቅት፤ ከዚህ ወር መጨረሻ ጀምሮ ወደ ተግባር የሚገባው የገጠር ኮሪደር ልማት በሕዝብ ተሳትፎ ታጅቦ ይከናወናል ብለዋል። በሁሉም ወረዳዎች ሰባት ሞዴል መንደሮችን በመለየት የገጠር ኮሪደር ልማት እንደሚከናወን የገለጹት ደግሞ የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አዲስ ወልዴ ናቸው። በገጠር ኮሪደር ልማት ቅንጅታዊ አሠራርን በመከተል የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል እንደሚሠራ ጠቁመዋል።
በአስተዳደሩ የተከናወነው የተፋሰስ ልማት ስራ አርሶ አደሮች ከተረጂነት እንዲወጡ አስችሏል
Jan 16, 2026 78
ድሬዳዋ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በድሬዳዋ አስተዳደር ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ከተረጂነት ለመውጣት እንዳስቻላቸው አርሶአደሮች ተናገሩ። በተፋሰሱ እና በሌሎች የገጠር ልማቶች በተከናወነው ስራ በመታገዝ ዘንድሮ ከ38 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ከተረጂነት ወደ አምራችነት እንደሚሸጋገሩ አስተዳደሩ አስታውቋል ። ባለፉት ዓመታት የተሰሩት ልማቶች የተፈጥሮ ሃብት ይዞታን በመመለስ፣ የጎርፍ ችግርን በመከላከልና ምንጮችን በመመለስ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻሉን ዘንድሮ በተጀመረው የተፋሰስ ልማት እየተሳተፉ የሚገኙ አርሶአደሮች ለኢዜአ ገልጸዋል። ከአርሶ አደሮቹ መካከል የገንደ ሪጌ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ሱልጣን ፈጃል እንደገለፁት፤ ተፋሰሱ ተጨማሪ የእርሻ መሬትና ውሃን እንዲጠቀሙ በማስቻሉ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተው ህይወታቸውን ለመለወጥ አስችሏቸዋል። ቀደም ብለው ዓልምተው የነበረው ብርቱካን ባለፈው ሳምንት ተሰብስቦ ከ900 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን እንደአብነት አንስተዋል። ከብርቱካን በተጨማሪ ሽንኩርት፣ ሃባብና ሎሚ እያመረቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። .የኡሉል ሞጆ ቀበሌ አርሶአደር ወይዘሮ ሐሊማ መሐመድ በበኩላቸው፣የተፋሰስ ልማቱ ለግብርና ስራ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ አርሶአደሩ በምንጭና በዝናብ ውሃ በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ እያመረተ መሆኑን ተናግረዋል። ይሄን የመሰለ የተፈጥሮ ፀጋና ጉልበት እያለን ለልመና እጅ አንዘረጋም ያሉት አርሶአደር ሐሊማ፤ ከራሳችን አልፈን ለተቸገሩ ለመርዳት ጠንክረን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል። በተፋሰስ ልማትና በሌማት ትሩፋት በተፈጠሩላቸው እድሎችና ድጋፎች በመታገዝ ከተረጂነት ወደ አምራችነት በመሸጋገር ከልማታዊ ሴፍትኔት መውጣታቸውን የገለፁት ደግሞ ሌላው የኡሉል ሞጆ ቀበሌ አርሶአደር ኡስማን መሐመድ ናቸው። የቀበሌው ህብረተሰብ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የመሸጋገርን መርህ ለማሳካት በተፋሰስ ልማትንም ሆነ በሌሎች ስራዎች እየተጋ መሆኑን አንስተዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ግብርና፣ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ፤ ባለፉት ዓመታት በድሬዳዋ የገጠር ቀበሌዎች በሚገኙ 57 ሺህ ሄክታር የተራቆቱ ተፋሰሶች ላይ የተለያዩ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በተከናወኑት ተግባራት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በአነስተኛ መስኖ ልማት በመሰማራት አበረታች ውጤት መገኘቱን የገንደ ሪጌ ገጠርን በአብነት ጠቅሰው አስረድተዋል። እንደ ኃላፊው አቶ ኑረዲን ገለፃ እየተከናወኑ የሚገኙ አበረታች የገጠር ልማቶች ከተረጂነት ወደ አምራችነት የመሸጋገሩን ጉዞ ስኬታማ ያደርጉታል። በዘንድሮ በጀት አመት 38 ሺህ በልማታዊ ሴፍትኔት የታቀፉ አርሶአደሮችና አርብቶአደሮች ወደ አምራችነት ይሸጋገራሉ ብለዋል።
በዞኑ የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ በ631 ተፋሰሶች ላይ እየተካሄደ ነው
Jan 16, 2026 73
ወልዲያ ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በሰሜን ወሎ ዞን የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ በ631 ተፋሰሶች ላይ እየተካሄደ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የተፈጥሮ ሃብት ባለሙያ አቶ ጋሻው አለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ባለፉት አመታት የተከናወነው የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ደርቀው የነበሩ ምንጮች እንደገና በመፍለቃቸውና የከርሰ ምድርና ገጸ-ምድር የውሃ አቅም በመጨመሩ አርሶ አደሩ በስራው በንቃት እንዲሳተፍ አድርጓል። የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የአፈር ለምነትን በማሳደጉና የውሀ አማራጮች መስፋታቸው ለመስኖ ልማት ስራው ስኬት ተጨማሪ አቅም መፍጠራቸውን ገልጸዋል። ስራዎቹ ተራቁተው የነበሩ ተራሮችን ወደ ልምላሜ በመመለሳቸው አርሶ አደሩ በመኖ ልማትና በንብ ማነብ ስራ በመሰማራት ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እንዳስቻለው ተናግረዋል። በዘንድሮው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ 380 ሺህ 493 አርሶ አደሮች 631 ተፋሰሶችን እያለሙ መሆኑን አስረድተዋል። በዘንድሮው የአፈርና ውሃ እቀባ ልማት ስራም 443 ሺህ 77 ሄክታር መሬት ላይ የማሳና የተራራ ላይ እርከንና ሌሎች ስነ አካላዊ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዞኑ የመቄት ወረዳ የ029 ቀበሌ ነዋሪ አቶ አባቡ ዋለልኝ፣ ባለፉት ዓመታት ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ ያገኘናቸውን ጥቅሞች ዘንድሮም ለማስቀጠል በትጋት እየሠራን ነው ብለዋል። ባለፉት ዓመታት የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች አካባቢዎች አገግመው ለእንስሳት መኖ፣ ንብ ማነብና ሌሎች ስራዎች ጥቅም በመስጠታቸው ዘንድሮ በራሳቸው ተነሳሽነት ለስራ መውጣታቸውን ተናግረዋል። ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት ባከናወኗቸው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ዘርፈ-ብዙ ጥቅሞችን አግኝተንበታል ያሉን ደግሞ በላስታ ወረዳ የጠልፈጢት ቀበሌ ነዋሪ አቶ ታደሰ ዳምጤ ናቸው። በዚህም በጓሮአቸው በአነስተኛ መስኖ አትክልት በማልማት፣ መኖ በማጨድ በእንስሳት እርባታና ማድለብ ስራ በመሰማራት ተጨማሪ ሃብት ለማፍራት እንዳስቻላቸው አስረድተዋል። በዞኑ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተሰራው የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ የዞኑን የደን ሽፋን ከ20 በመቶ በላይ ማድረሱን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በአካባቢ ጥበቃ ልማት የተሠሩ ሥራዎች ጤናማ ትውልድ ለማፍራት ከፍተኛ ፋይዳ አላቸው
Jan 16, 2026 75
አዲስ አበባ፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት የተሠሩ ሥራዎች ጤናማ ትውልድ ለማፍራት የጎላ ፋይዳ እንዳላቸው በዓለም አቀፍ የጤና ተቋማት የሚሠሩ የጤና ባለሙያዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ የሕጻናት ሄማቶሎጂና ኦንኮሎጂ ማኅበር የምሥረታ መርሐ-ግብር በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በመርሐ-ግብሩ የተሳተፉ የጤና ባለሙያዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የተከናወኑ የአካባቢ ጥበቃና የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ጤናን ለመጠበቅ፣ ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ እና ለማኅበራዊ ግንኙነቶች ያላቸው ፋይዳ ከፍተኛ ነው። በአውስትራሊያ የጤና ባለሙያ የሆኑት ብሮንዊን ማክናማራ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ከተማ በአካባቢ ንጽህና፣ አረንጓዴ ቦታዎችና ፓርኮችን በማስፋፋት ረገድ ከዚህ ቀደም ከሚያውቁት የተለየ ለውጥ ማየታቸውን ተናግረዋል። የፕላስቲክና የኬሚካል ውጤቶች የጤና ጉዳት የሚያስከትሉ በመሆኑ ብክለትን ለመከላከል እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችንም አድንቀዋል። የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ለጤና አጠባበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ያስረዱት ደግሞ የቶሮንቶ ዩንቨርሲቲ ፕሮፌሰር ሺላ ዋይትዝማን ናቸው። አረንጓዴና ንጹህ አካባቢ ጤናን ለመጠበቅ ከሚያስችሉ ጉዳዮች አንዱ መሆኑን ገልጸው፤ በሽታን አስቀድሞ መከላከል ከማከም የተሻለ ነው ብለዋል። በ’ፒውር ኧርዝ’ የምሥራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ፍሬው ከፍያለው በአካባቢ ጥበቃ ተሟጋችነትና ወጣቶችን በማሳተፍ የጽዳት ሥራዎች ላይ ለበርካታ ዓመታት እየሠሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ትብብራቸውን ለማጽናት ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Jan 14, 2026 118
አዲስ አበባ፤ ጥር 6/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን በባለብዙ ወገን መድረኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አያኖ ኩኒሚትሱ ጋር በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ትብብር እንዳላቸው አውስተው በጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም (ቲካድ) ማዕቀፍ ያላቸውን ግንኙነት አንስተዋል። በዮካሃማ በነሃሔ ወር 2017 ዓ.ም የተካሄደው ዘጠነኛው የጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም(ቲካድ) በሁለቱ ወገኖች አጋርነት ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው መሆኑን አመልክተዋል። ውይይቱ የሁለትዮሽ ትብብሩን የበለጠ ማጠናከርን ያለመ ነው። ጃፓን ለአፍሪካ የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (African CDC) እያደረገች ያለው ድጋፍ እንዲሁም የአፍሪካ ዘላቂ እድገት እና ትስስር ለሚደግፉ የመሰረተ ልማት ስራዎች እያፈሰሰች ያለው መዋዕለ ንዋይ እያደገ መምጣቱ ተመላክቷል። የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አያኖ ኩኒሚትሱ ዘጠነኛው የጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም (ቲካድ) በስኬት መካሄዱን አድንቀዋል። 10ኛው ቲካድ በአፍሪካ እንዲካሄድ ጃፓን ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ጋር በቅርበት ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን አመልክተዋል። ሀገራቸው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና (AfCFTA) እና የአፍሪካ የመሠረተ ልማት ማስፋፊያ ፕሮግራም (ፒዳ) ጨምሮ የአፍሪካ ህብረት ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ቁልፍ ኢኒሼቲቮች መደገፏን እንደምትቀጥል ገልጸዋል። በሌላ በኩል ሚኒስትር ዴኤታዋ በዓለም አስተዳደር ውስጥ እያደገ የመጣውን የአፍሪካ ሚና በማንሳት የአፍሪካ ህብረት በቡድን 20 ቋሚ አባል መሆኗ ትልቅ ሽግግር መሆኑን ተነግረዋል። ባለስልጣናቱ በአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን የከፍተኛ ደረጃ የምክክር መድረክ እና ቲካድ አማካኝነት ትብብራቸውን የበለጠ ለማጠናከር እና የባለብዙወገን ዲፕሎማሲ እንዲጸና በጋራ እንደሚሰሩ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን እ.አ.አ በ1993 አጋርነት መመስረታቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ። ሰላም እና ደህንነት፣ ኢኮኖሚ፣ ልማት፣ ንግድ፣ ጤና ፣ ግብርና፣ ቴክኖሎጂ እና የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ከሁለቱ ወገኖች የትብብር መስኮች መካከል ይጠቀሳሉ።
ውኃ ለአፍሪካ የኅልውና ጉዳይ ነው - መሐሙድ አሊ ዩሱፍ
Jan 12, 2026 212
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ ውኃ ሁሉንም ዘርፍ የሚነካ አህጉራዊ የኅልውና ጉዳይ መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የሕብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። ስብሰባው"ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሐሳብ የሚደረግ ነው። በስብሰባው ላይ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ፣ የአፍሪካ ሕብረትና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የሕብረቱ አባል ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት ትኩረቱን ያደረገው በውኃ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። ውኃ በሁሉም አይነት እጅጉን ወሳኝ የሆነ ሀብት እና የኅልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ አህጉራዊ ግቦቹን ለማሳካት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አስገንዝበዋል። በብራዚል ቤለም የተካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) ትኩረት ከተሰጣቸው አጀንዳዎች መካከል አንዱ መሆኑንም አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በምታዘጋጀው 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) ውኃ አንዱ አጀንዳ እንደሚሆንም ተናግረዋል። ሊቀ መንበሩ ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማዘጋጀት በመመረጧ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ያሉ ሲሆን፤ ለጉባኤው ስኬታማነት ሕብረቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ሰላም እና ደኅንነት የአፍሪካ አንገብጋቢ አጀንዳ መሆኑን የገለጹት ሊቀ መንበሩ ሱዳን፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሊቢያን በማሳያነት ጠቅሰዋል። ኢ-ሕገመንግሥታዊ ለውጦች አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቅሰው፤ ሀገራት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንዲያከብሩ አሳስበዋል። የአፍሪካ ሕብረት ተቋማዊ ሪፎርም እና ኢኮኖሚያዊ ትሥሥርን ጨምሮ ለአህጉራዊ አጀንዳዎች እየሠራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል። አህጉራችን ፈተናዎች ቢኖሩባትም በጋራ ከቆምን እናልፋቸዋለን ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል። የዛሬው ስብስባ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን፤ የኮሚቴው መደበኛ ስብስባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብስባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል ሀገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ መሆኑ ይታወቃል።
51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ይጀመራል
Jan 12, 2026 243
አዲስ አበባ፤ ጥር 4/2018 (ኢዜአ)፦ 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚደረግ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና አጠባበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በስብሰባው ላይ የአፍሪካ ሕብረትና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች፣የሕብረቱ አባል አገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች እንደሚሳተፉበት ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ስብስባው የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ እንዲሁም የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚከናወነው 39ኛው የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ኮሚቴው በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚገኙ የተለያዩ ተቋማትን የአፈጻጸም እንዲሁም ሕብረቱ እ.አ.አ በ2025 ያካሄዳቸውን ስብሰባዎች የተመለከቱ ሪፖርቶችን ያደምጣል። ሰላም እና ደህንነት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ጨምሮ የኢኮኖሚ ትስስር፣ የተቋማዊ ሪፎርሞች እና የበጀት እቅዶችን የተመለከቱ የቴክኒክ ሰነዶችንም ያዘጋጃል። ኮሚቴው በ2026 የአፍሪካ ህብረት መሪ ሀሳብ ላይ ምክረ ሀሳቦችን ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የኮሚቴው መደበኛ ስብስባ ለዋናው ጉባኤ እንደ ይፋዊ የዝግጅት ስብስባ የሚያገለግል ነው። የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ የሕብረቱን ቋሚ ተወካዮችና የአባል አገራቱን አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ያቀፈ ነው።
የቻይና አፍሪካ ትብብር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል
Jan 8, 2026 218
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማሕሙድ አሊ ዩሱፍ ከቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ጋር ውይይት አካሄዱ። ውይይቱ እያደገ የመጣው የቻይና አፍሪካ ትብብርን ማጠናከር ላይ ያለመ ነው ተብሏል። ቻይና የአፍሪካ እውነተኛ አጋር መሆኗን የገለፁት የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ያተኮረው ፖሊሲ ጠንካራ ወዳጅነት እንዲፈጠር ማድረጉን ገልፀዋል። የቻይና አፍሪካ ግንኙነት በተለያዩ የትብብር ማዕቀፎች እያደገ መምጣቱንም ተናግረዋል። ከውይይቱ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ፤ ሁለቱ ወገኖች የዓለም ደቡባዊ ቀጣና (Global South) ሀገራትን መብትና ጥቅም ለማስከበር፣ የሉዓላዊነትን ክብር ለመጠበቅ እና ዓለም አቀፍ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በጋራ ለመሥራት መስማታቸውን አስታውቀዋል። በውይይቱ ወቅት የቻይናን የአምስት ዓመት የልማት ዕቅድ ከአፍሪካ ኅብረት የ2063 አጀንዳ ሁለተኛው የዐሥር ዓመት ትግበራ ጋር በማጣጣም ዘመናዊነትን ለማምጣት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ምክክር መደረጉ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ስምምነቶችን ጨምሮ፣ ቻይና ያቀረበቻቸውን ዓለም አቀፍ የደኅንነትና የልማት ተነሳሽነቶች በጋራ ለመደገፍ ከስምምነት መድረሳቸውን ኢቢሲ ዘግቧል። በተጨማሪም የተፈረሙ የትብብር ስምምነቶችን በተግባር በመተርጎም እና የንግድ ልውውጥን በማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት በጋራ መግለጫቸው አረጋግጠዋል።
ሐተታዎች
እኩል አጋርነትን መፍጠር፤ አዲሱ የአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር ምዕራፍ
Dec 30, 2025 572
የአፍሪካ እና ጣልያን ግንኙነት የጀመረው በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። ጣልያን እ.አ.አ በ1947 የተፈራረመቻቸው የሰላም ስምምነቶች ቅኝት ግዛት እና የአንድ አካል የፖለቲካ የበላይነት እንዲያከትም አድርጓል። በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ከቅኝ አገዛዝ የሁለትዮሽ ትስስር ወደ የኢኮኖሚ ትብብር ተሸጋግሯል። ወቅቱ አፍሪካውያን ሉዓላዊነታቸውን የበለጠ ያረጋገጡበትና ጣልያን ከአፍሪካ ጋር በአዲስ መልክ አጋርነቷን ያደሰችበት ነበር። ከቅኝ ግዛት በኋላ የአፍሪካ እና የጣልያን ትብብር በባህል መስክ ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የንግድ እና የቴክኒክ ትብብሩ ውስን ነበር። እ.አ.አ ከ1990ዎቹ መግቢያ አንስቶ የአፍሪካ እና ጣልያን ስትራቴጂክ አጋርነት እያበበ የመጣበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል። የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች እና የንግድ ቢሮዎች መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ትብብር አድማስ መስፋት የትብብሩ መገለጫ ሆኗል። ዘመናዊው የአፍሪካ እና ጣልያን አጋርነት ከእርዳታ ወደ የጋራ እድገት ምዕራፍ መሸጋገር ችሏል። የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው የሁለቱን ወገኖች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብር አጠናክሯል። የልማት ትብብሩ እርዳታን ከመለገስ ወጥቶ እድገት ተኮር ሆኗል። ከደህንነት ጋር በተያያዘም የፍልሰት አስተዳደር እና ሽብርተኝነት መዋጋት አንዱ የትብብር መገለጫ ነው። የጣልያን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የአፍሪካ እና ጣልያን የባለፈው ጊዜ የነበሩ ፈተናዎች እውቅና በመስጠት አሁን ላይ የሁለቱን ወገኖች የጋራ ፍላጎት ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። የፖሊሲው ሰነድ “ ዋጋ እና ክብርን ማዕከል ያደረገ” ዲፕሎማሲ በሚልው እሳቤው ከአፍሪካ ጋር ላለው ወዳጅነት ከፍተኛ ግምት እንደሚሰጥ አስቀምጧል። እ.አ.አ በ2024 በሮም የተካሄደው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ በቅርብ ጊዜያት ከነበሩ ከፍተኛ መድረኮች መካከል ይጠቀሳል። በጉባኤው ላይ የ45 የአፍሪካ ሀገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የልማት አጋሮች ተሳትፈዋል። ጉባኤው የተካሄደበት ዓመት ጣልያን የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ሊቀ መንበር የነበረችበት ወቅት ሲሆን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ አንኳር ትኩረት ሆኗል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በወቅቱ ጉባኤውን የአፍሪካ እና ጣልያን ትብብርን በአዲስ መልክ የበየነና ትብብሩ እኩል በቆሙ ወገኖች መካከል ያለ ትስስር እንደሆነ አንስተዋል። ሜሎኒ የሰጪ እና ተቀባይ ዘመን እንዳበቃና የጋራ እድገት እና የጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ ግንኙነት አዲሱ የትብብር ምዕራፍ እንደሆነም ተናግረዋል። በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋቂ ማህማት የጣልያንን አዲሱን የፖሊሲ ለውጥ ያደነቁ ሲሆን አፍሪካ ከቃል ባለፈ እውነተኛ አጋርነትን ትፈልጋለች ብለዋል። የፖሊሲ ሽግግሩ ፍትሃዊነትን ያረጋገጠ እና እኩልነትን መሰረት ያደረገ ዓለም መፍጠርን ያማከለ መሆን እንዳለበትም አንስተዋል። ጣልያን የገባቻቸውን ቃሎች ወደ ተግባር መቀየር አለባት ሲሉም ማህማት ተናግረው ነበር። በጉባኤው ላይ ይፋ ከተደረጉ ቁልፍ ማዕቀፎች አንዱ የማቴይ እቅድ (The Mattei Plan) ይገኝበታል። የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ይፋ ያደረጉት የማቴይ ፕላን ጣልያን ከአፍሪካ ጋር ያላት የኢኮኖሚ እና የልማት ትብብር ማጠናክርን ያለመ ነው። የ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ የስትራቴጂክ ማዕቀፉ በጣልያኑ የብሄራዊ የዘይት እና ነዳጅ ኩባንያ መስራች ኤነሪኮ ማቴይ የተሰየመ ነው። ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር ከአጭር ጊዜ እርዳታ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ትብብርን በማስቀደም እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። የአፍሪካን የኢኮኖሚ እድገት መደገፍ፣ የስራ እድሎችን ማስፋት፣ አፍሪካን የአውሮፓ የኢነርጂ አቅራቢ አጋር የማድረግ ስራን ማስተዋወቅ፣ ለአፍሪካውያን የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሄ በመስጠት ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ከምንጩ ማድረቅ እንዲሁም ከበጎ አድራጎት የተላቀቀ የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መፍጠር የእቅዱ አበይት አላማዎች ናቸው ። ለአራት ዓመታት የሚቆየው የማቴይ እቅድ በአፍሪካውያን በበጎ መልኩ የታየ ሲሆን እቅዱ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር ጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ተነስቷል። እ.አ.አ በ2023 የአፍሪካ እና የጣልያን የንግድ ልውውጥ 59 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ መድረሱን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የንግድ ልውውጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል። የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት የተፈጥሮ ጋዝ፣ ድፍድፍ ነዳጅ፣ የብረታ ብረት እና ማዕድናት ምርቶች እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ምርቶች የሆኑ ጥሬ እቃዎችን ወደ ጣልያን ይልካሉ። ጣልያን የኢንዱስትሪ ማሽን እና መሳሪያ፣ እሴት የተጨመረባቸው እቃዎች እና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ እቃዎች ወደ አፍሪካ ከምትላካቸው ምርቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። አጠቃላይ የንግድ ምጣኔው ሲታይ ጣልያን በገቢ አብዛኛውን ድርሻ ትይዛለች። ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ተፈጥሮ ሀብት፣ ኢነርጂ፣ መሰረተ ልማት፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት፣ ምርምር፣ ጤና፣ ቴክኖሎጂ፣ የፍልሰት አስተዳደር፣ ደህንነት እና አስተዳደር ከአፍሪካ እና ጣልያን የትብብር መስኮች መካከል ይገኙበታል። የ2026 የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ በየካቲት ወር አጋማሽ 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ እና የአህጉሪቷ መዲና ናት። ይህም ጉባኤውን የአፍሪካ ዋንኛ የዲፕሎማሲ አጀንዳ ያደርገዋል። ኢትዮጵያ በታሪክ በፓን አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና ያላት ሀገር ናት። በአሁኑ ሰዓትም በርካታ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እያዘጋጀች ትገኛለች። የሁለቱን ወገኖች አጋርነት የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል። የማቴይ እቅድ ትግበራ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብር፣ የአፍሪካን ተሰሚነት መጨመር፣ ፍልሰትን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ አቋም መያዝ፣ የአጋርነት እና የመግባቢያ ስምምነቶች የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤው ውጤቶች ናቸው። የአፍሪካ-ጣልያን ጉባኤ ካለፈው ታሪካዊ ግንኙነቶች ፣ እያደገ ከመጣው የኢኮኖሚ ትብብር እና የጋራ ፈተናዎችን የመፍታት ቁርጠኝነት አኳያ በአፍሪካ እና በጣልያን መካከል አዲስ የትብብር ምዕራፍ የሚከፍት እንደሆነ ታምኖበታል። የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚደረገው ጉባኤ አፍሪካ መር አጋርነት ለመፍጠር እና የአፍሪካን ተሰማኒነት ለመጨመር መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው።
አፍሪካውያን ሀገር በቀል አሰልጣኞች ጎልተው የታዩበት የአፍሪካ ዋንጫ !
Dec 28, 2025 506
35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።24 ሀገራት በስድስት ምድቦች ተከፍለው ጨዋታቸውን እያደረጉ ነው። በውድድሩ ላይ ከሚሳተፉ 24 ሀገራት 12ቱ በአፍሪካውያን የሚሰለጥኑ ናቸው። የአዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከዛው ከሀገራቸው ናቸው። የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በ22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮን ለግማሽ ፍጻሜ አድርሰዋል።ሀገሪቷ በዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ የደረሰች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ከእ.አ.አ 2022 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እየመሩት የሚገኙት ሬግራጉዊ ሞሮኮን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የወቅቱ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ኮትዲቭዋር አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋች ኤመርሰን ፋኤ ነው። ፋኤ እ.አ.አ በ2023 በኮትዲቭዋር አስተናጋጅነት በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቡድኑን በመምራት ዋንጫውን እንዲያነሳ አድርጓል። በውድድሩ መሐል በውጤት ማጣት የተሰናበቱትን ፈረንሳዊውን አሰልጣኝ ጂን-ሉዊስ ጋሴት በመተካት በጊዜያዊነት አሰልጣኝ የተሾመው ፋኤ ቡድኑን ለዋንጫ ማብቃቱ አስወድሶታል። በዘንድሮው ውድድር ዋንጫውን ለማንሳት የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ተርታ የተመደበችው ሴኔጋል አሰልጣኝ የ41 ዓመቱ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ፓፔ ታው ነው። ፓፔ ታው በተጫዋችነት ዘመኑ ለሴኔጋል ባደረጋቸው 16 ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። አሰልጣኙ ሴኔጋል ለ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንድታልፍ አድርጓል። ከሶስት ዓመት በፊት በአልጄሪያ በተካሄደው የሰባተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና(ቻን) ሴኔጋል ዋንጫውን ስታነሳ የቡድኑ አሰልጣኝ ሆኖ መርቷል። የሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ግብጽ የምትሰለጥነው በቀድሞ ኮከቧ ሆሳም ሀሰን ነው። በተጫዋችነት ዘመኑ በአፍሪካ ዋንጫ 11 ግቦችን አስቆጥሯል። በ177 ጨዋታዎች 69 ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የብሄራዊ ቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ሆሳም ሀሰን የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ በተጫዋችነት በማንሳት ስኬታማ አሰልጣኝ ነው። ሌላኛው የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሮን አሰልጣኝ የ56 ዓመቱ ዴቪድ ፓጉ ነው። ካሜሮናዊው አሰልጣኝ የተሾሙት ከሰሞኑ ነው። ቤልጂየማዊውን አሰልጣኝ ማርክ ብራይስን በመተካት ቡድኑን እንዲመሩ ኃላፊነት ተጠሎባቸዋል። በካሜሮን እግር ኳስ ባላቸው የታክቲክ መረዳት እና ብቃት የሚሞካሹት ፓጉ ቡድኑን አንድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል። ሌላኛው የውድድሩ ተሳታፊ ሀገር ዛምቢያ ናት።የ48 ዓመቱ የዛምቢያ ብሄራዊ ቡድን የቀድሞ ተከላካይ ሞሰስ ሲቾኔ የቡድኑ የወቅቱ ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2022 እስከ 2024 በጊዜያዊነት እና በረዳት አሰልጣኝነት ያገለገሉት ሲቾኔ በ2025 ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል። ምስራቅ አፍሪካን በውድድሩ ከሚወክሉ ሶስት ሀገራት መካከል አንዷ ሱዳና ናት። ጋናዊው ጀምስ ክዌሲ አፒያ የቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። አፒያ ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የጋቦን አሰልጣኝ ቲዬሪ ሞዩማ የብሄራዊ ቡድኑ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ነበር። ለ11 ዓመታት ለጋቦን ተጫውተዋል። ከእ.አ.አ 2023 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን በአሰልጣኝነት እየመሩ ይገኛል። የ44 ዓመቱ ደቡብ አፍሪካዊ ሞሬና ራሞሬቦሊ የቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ናቸው። ከእ.አ.አ 2025 አንስቶ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛል። ሞሬና ከዚህ ቀደም የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ። የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪናፋሶ አሰልጣኝ የቀድሞ የብሄራዊ ቡድን የአማካይ ተጫዋች ብራማ ትራኦሬ ነው። አሰልጣኙ ከእ.አ.አ ማርች 2024 አንስቶ ቡርኪናፋሶን እየመራ ይገኛል። ትራኦሬ ቡድኑ የተሻለ ውጤት እንዲያመጣ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። የአንድ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነችው ቱኒዚያ አሰልጣኝ የቀድሞ የቡድኑ የተከላከይ መስመር ተጫዋች ሳሚ ትራቤልሲ ናቸው። የ57 ዓመቱ አሰልጣኝ ለቱኒዚያ ብሄራዊ ቡድን ለ10 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግሏል። ብሄራዊ ቡድኑን ከእ.አ.አ 2025 ቱኒዚያን እየመራ ይገኛል። በአፍሪካ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ሞዛምቢክ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት። ፍራንቺስኮ ኩዌሪዮል ኮንዴ ጁኒየር (ቺኩዊኒዮ ኩንዴ) የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ናቸው። የ60 ዓመቱ አንጋፋ አሰልጣኝ ለሞዛምቢክ ለ15 ዓመታት በተጫዋችነት አገልግለዋል። ለሀገራቸው በ43 ጨዋታዎች 12 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ኩንዴ ከእ.አ.አ 2021 አንስቶ ብሄራዊ ቡድኑን እያሰለጠኑ ይገኛሉ። የናይጄሪያ አሰልጣኝ የሆነው ኤሪክ ቼሌ የኮትዲቭዋር፣ ማሊ እና ፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው አሰልጣኝ ናቸው። ይሁንና ቼሌ የአፍሪካ የዘር ግንድ ቢኖራቸውም በፈረንሳይ መወለዳቸው የውጭ ሀገር ዜጋ ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። የአፍሪካውያን አሰልጣኞች በአፍሪካ ዋንጫ የማሰልጠን ምጣኔ ከሌሎቹ ወቅቶች አንጻር የአሁኑ የተሻለ ነው ማለት ይቻላል። ይህም ሀገር በቀል አሰልጣኞች እየተሰጣቸው ያለውን ትኩረት ያሳያል። 12 ሀገራት በውጭ ሀገር ዜጎች ይሰለጥናሉ። በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አፍሪካውያን የሚያሰለጥኗቸው ወይስ የውጭ ሀገር ዜጋዎች የሚመሯቸው ሀገራት ዋንጫውን ያነሳሉ? የሚለው ጉዳይ ትኩረትን ስቧል።
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን
Dec 22, 2025 728
የኢትዮጵያ ዲጂታል ዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወቅቱ የኤሌክትሮኒክ መሳሪዎችን ተጥቅሞ መረጃን በመተንተን እና መረጃን እንደ ልዩ ገጽታ በመጠቀም እና መለያ ቁጥር (ኮድ) በመስጠት አገልግሎት ላይ ይውል ነበር። ከዛ ጊዜ በኋላ በርካታ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች እና ማሽኖች ተፈብርከው ጥቅም ላይ መዋል ጀምረዋል። እ.አ.አ በ1946 በአሜሪካ የፔንሲሊቫኒያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅል አገልግሎት የሚሰጥ የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ኮምፒዩተር በመስራት የዲጂታል ዘመን ጅማሮን አበሰረ። ከእ.አ.አ 1943 እስከ 45 ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰራው ይህ ኮምፒዩተር ባለቤቶች ጆን ማውችሊ እና ጄ ፕሬስፐርት ኤከርት ናቸው። በ150 ኪሎ ዋት ኃይል የሚሰራው ኮምፒዩተር በሴኮንዶች ውስጥ በርካታ ስራዎችን ያከናውን ነበር። ኮምፒውተሩ በወቅቱ በነበሩ ባለሙያዎች ማርሽ ቀያሪ እና መሰረት ጣይ የሚል ስያሜ አግኝቷል። የዘመናዊ የዲጂታል ስርዓቶች ምሰሶ ነው የሚባለው ኢንተርኔት የተጀመረው እ.አ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ ነበር። “አርፓኔት” የተሰኘ የአሜሪካ የጥናት ፕሮጀክት ኮምፒዩተሮችን ዘመኑ ከደረሰበት የኔትወርክ ስርዓቶች ጋር በማገናኘት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። እንግሊዛዊው የኮምፒዩተር ሳይንቲስት ቲም በርነርስ ሊ እ.አ.አ 1969 “ወርልድ ዋይድ ዌብ” (WWW) በመፍጠር ትስስርን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ አሸጋግሯል። ድረ ገጾችን በመፍጠር እና በህዝብ ደረጃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሰፋ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል። ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኮምፒዩተር መሰራት ተነስቶ ወደ ዓለም አቀፍ የትስስር መሰረተ ልማትነት የተቀየረ ሲሆን በየዕለት ተዕለት የሰዎች ኑሮ፣ማህበራዊ መስተጋብር፣ ንግድ እና የመንግስታት አሰራር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ከማምጣት ባለፈ ዘርፎች በቴክኖሎጂ እንዲቃኙ አድርጓል። ዓለም ላይ አሁን ካለው ህዝብ 73 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው። የዲጂታል ኢኮኖሚ የዓለምን ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) የ15 በመቶ ድርሻን እንደሚያግዝ የተለያዩ ጥናቶች ያመለክታሉ። ሞባይል ለኢንተርኔት መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ሀገራት እ.አ.አ 2025 በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ክላውድ ኮምፒዩቲንግ፣ ኔትወርኪንግ እና ለሌሎች ትራንስፎርሜሽ ስራዎች ያወጡት ኢንቨስትመንት ከአራት ትሪሊዮን ዶላር በላይ እንደሚልቅም ይገመታል። በአፍሪካ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ480 ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል። ዲጂታል ስርዓቱን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማቶች እና የዳታ ማዕከላት በአፍሪካ መንግስታት እና የልማት አጋሮች ትብብር እየተገነቡ ነው። ዲጂታል ኢኮኖሚ ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለትምህርት እና ክህሎት፣ ለመንግስት የአሰራር ውጤታማት፣ ለፋይናንስ አካታችነት እና ኮሙኒኬሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 በፊት የዲጂታል ምህዳሯ የተገደበ ነው ማለት ይቻላል። ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተደራሽነት፣ ለቴሌኮም አገልግሎት ከፍተኛ ክፍያ ወጪ የሚወጣበት እና በቴሌኮም አገልግሎት የመንግስት ብቻ የበላይነት የሚታይበት ነበር። ከለውጡ በኋላ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች አማካኝነት ዲጂታል ተጠቃሽ ነው። የዲጂታል ዘርፍ ከብዝሃ የኢኮኖሚ ምንጮች አንዱ ሆኖ ነው።ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል። ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ካስገባች ሰነባብታለች። ኢትዮጵያ ከእ.አ.አ 2020 አንስቶ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በማዘጋጀት ስተገብር ቆይታለች። ስትራቴጂው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እና መንግስታዊ አገልግሎቶችን ዲጂታል የማድረግ አላማ ያደረገ ነው። በዚህም 900 ገደማ የሚሆኑ መንግስታዊ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ ሆነዋል።3000 የሚሆኑ የዲጂታል አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አግኝተዋል። የፋይዳ መታወቂያ ኢኒሼቲቭ አማካኝነት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል። የሞባይል እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በከፍተኛ መጠን ጨምሯል። የአራተኛ እና አምስተኛው ትውልድ የኢንተርኔት አገልግሎት እየሰፋ መጥቷል።የዲጂታል ክህሎትም ተስፋ ሰጪ እድገት ታይቶበታል። የቴሌኮም ዘርፉ ለውጭ ክፍት እንዲሆን መንግስት ባስቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ መሰረት ሳፋሪኮም ኩባንያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን “ምፔሳ” የተሰኘ የሞባይል የገንዘብ አገልግሎት እየሰጠም ይገኛል። የመንግስት የዲጂታል ፖሊሲዎች እና የህግ ማዕቀፎች ለዘርፉ ምቹ ምህዳር በመፍጠር ትስስር እንዲሰፋ እና አገልግሎቶች እንዲዘምኑ አስችሏል። ኢትዮጵያ ከአምስት በፊት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በማቋቋም በርካታ ስራዎችን አከናውናለች። ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በክረምት መርሃ ግብር (ሰመር ካፕም) ወጣቶች ሲማሩ እንደቆዩ አውስተው በዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል። ሁሉንም ዘርፍ የሚነካው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በግብርና፣ጤና፣ አገልግሎት እና ሌሎች ዘርፎች ላይ በመግባት ስራን እያቀላጠፈ ይገኛል። በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት የሚሰበሰቡ ዳታዎች ለመንግስት እና ግል ተቋማት አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝም ተገልጿል። መንግስት ወጣቶች በሰው ሰራሽ አስተውሎት አማካኝነት ሀገርን አልፎም ዓለምን የሚጠቅሙ ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያቀርቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ቴሌብር፣ መሶብ እና ዘመንን ጨምሮ ያሉ የዲጂታል አገልግሎቶች የዘርፉን እድገት በማሳለጥ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት የዲጂታል 2030ን ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ መጠናቀቁን ገልጸዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ያበሰሩ ሲሆን ተደራሽነትን ማስፋት፣ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸውን አመልክተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ተደራሽ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ምህዳር መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል።ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ም ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን አንስተዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሦስት ቁልፍ ትልሞች እንዳሉት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህም ተደራሽነትን ማስፋት፤ እኩል እድል ማመቻቸትና በተቋማትና ህዝብ መካከል መተማመንን መፍጠር መሆናቸውን አብራርተዋል። ትልሞቹ እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካም ሁሉም በትብብር መስራት እንዳለበት ነው ጥሪ ያቀረቡት። የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በቴሌኮም ዘርፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው። ለአብነትም የሞባይል ደንበኞች ቁጥርን 97 ሚሊዮን ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 57 ሚሊዮኑ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ሆነዋል ሲሉ አንስተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለው እንደገለጹት፥ አንድ ሺህ ሰላሳ ከተሞችም የ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ሆነዋል ነው ያሉት። በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የሞባይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 128 ሚሊዮን የሚደርስ ሲሆን፣ የ5ጂ ኔትወርክ ሽፋንን 100 ከተሞች ይደርሳል ብለዋል። በ2030 የዲጂታል ክፍያን ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር አሁን ካለበት ከሰባት እጥፍ በላይ እንዲያድግም በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉም አረጋግጠዋል።ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ አካታችነት እና ማህበራዊ ለውጥ ቁልፍ ምሰሶ ነው። ስትራቴጂው በሚገባ ከተተገበረ፣ በቂ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ከተገነቡ እና ዜጎች በንቃት ከተሳተፉ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘመን ትሩፋቶች ተጠቅማ ትልሞቿን ማሳካት እንደምትችል አያጠራጥርም።
መልካምነት ይከፍላል..!!!
Dec 11, 2025 880
መልካምነት ይከፍላል...!!! በማስረሻ ሀብታሙ (ኢዜአ-ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ) መልካም ስነ ምግባርና ባህሪ ከራስ ባለፈ ቤተሰብን ያኮራል፤ ከዚህ ከፍ ሲልም ለማህበረሰብ ግንባታና ለሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው። ሌብነትና ሙስናን ለመከላከልም እንዲሁ አስተዋጾ አለው። በመልካም ስነምግባር ታንጾ ያደገ ሰው በላቡና በወዙ ጥሮ ግሮ ያፈራውን እንጂ የሌሎች የሆነን ሀብትና ንብረት አይመኝም። ዛሬ የራሱ ያልሆነውን ንብረት በሀሰት ምሎና ተገዝቶ ለመውሰድና ለመክበር የሚጥር ሰው በበዛበት በዚህ ዘመን ላይ ወድቆ ያገኙትን ንብረት ለባለቤቱ ለመመለስ "ገንዘብ የጣለ" እያለ በአደባባይ ባለቤቱን የሚያፈላለግ ሰው ሲገጥም ግርምትን ከማጫር ባለፈ እንዲህ አይነት ሰውም አለ ወይ? ያስብላል። ነገሩ የተከሰተው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሻሌ ቀበሌ ነው። በአካባቢው ባህልና እምነት የሰው ገንዘብም ሆነ ንብረት ያለአግባብ መውሰድ "ጎሜ" ወይም እንደ "ሀጥያት" ተደርጎ ይቆጠራል። በኮሻሌ ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በዚህ ባህልና እምነት ውስጥ ያደጉ ቢሆንም በቤተሰባቸው በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው ማደጋቸው አሁን ላላቸው ታማኝነትና ቅንነት ትልቁን ድርሻ ይይዛል። አርሶ አደሩ ታማኝነታቸውን በተግባር ጭምር በማሳየታቸው ከመንግስት ጭምር እውቅና ተችሯቸዋል። ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ቀን ገበያ ውለው ሲመለሱ በመንገዳቸው ላይ ተጠቅልሎ የታሰረ ነገር ይመለከታሉ። መሬት ወድቆ ያገኙት ነገር እስሩን ፈትው ሲያዩ በርከት ያለ የገንዘብ ኖት ነው። ለማመን እያቃታቸው ገንዘቡን መቁጠር ጀመሩ። በላስቲክ የተጠቀለለው ብር 30 ሺህ ነበር። የራሳቸው ያልሆነውን ገንዘብ ይዞ ወደ ቤት መግባት የህሊና እዳ መስሎ ስለታያቸው አማራጭ ያሉትን አደረጉ፡፡ የገንዘቡ ትክክለኛ ባለቤት ከተገኘ በሚል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" እያሉ በአደባባይ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው መጠየቅ ጀመሩ። የሰማቸው ሁሉ ግራ ስለተጋባ ቀረብ ብሎ ሊጠይቃቸው ይቅርና ጤነኛ ሰውም አድርጎ አላያቸውም። የገንዘቡ ባለቤት እኔ ነኝ የሚል ትክክለኛ ሰውም ባለመገኘቱ ልፋታቸው ድካም ብቻ ሆነ። የያዙትን 30 ሺህ ብር ይዘው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ተገደዱ። በአካባቢው የገበያ ቀን በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው። እናም የገንዘቡን ባለቤት ለማግኘት እስከ ሳምንት ድረስ መቆየት ግድ ሆኖባቸው። ባለቤቱ ይገኛል ወይስ አይገኝም በሚል ሀሳብ ሳምንቱን አሳለፉ። ቀጣይ የገበያ ቀን ሲደርስም ገንዘቡን እንጨት ላይ አስረው በማንጠልጠል "ገንዘብ የጠፋበት! ገንዘብ የጠፋበት" አያሉ በገበያ ስፍራ በመዘዋወር ዳግም የጠፋበትን ሰው ማፈላለግ ጀመሩ። ገንዘቡ የእኔ ነው፤ ጠፍቶብኛል እያለ የሚመጣ ሰው ቢበዛም ትክክለኛውን የገንዘብ መጠንና ምልክቱን የሚጠራ ሰው አለመኖሩ ግን ፍለጋቸውን አድካሚ አድርጎታል። የገንዘቡን ባለቤት አግኝተው እስኪያስረክቡ ድረስ ተስፋ አልቆረጡም፤ “ገንዘብ የጠፋበት፣ ገንዘብ የጠፋበት...” እያሉ ገበያውን ከዳር ዳር ዞሩ። የኋላ ኋላ ግን ድካማቸው በከንቱ አልቀረም። በስተመጨረሻ ትክክለኛውን የገንዘብ መጠን ከእነምልክቱ እና ቦታው የሚናገር አንድ ግለሰብ ተገኘ። ከገንዘቡ ባለቤት ጋር ከተወያዩ በኋላ ገንዘቡ ወድቆ ወዳገኙበት ስፍራ ይዘው በመሄድ የያዙትን ገንዘብ መሬት ላይ ጥለው ራሱ ባለቤቱ ምሎ እንዲያነሳ ያደርጋሉ። በእዚህ ሁኔታ ወደቆ ያገኙትን ገንዘብ በታማኝነት ያስረከቡት አቶ ሴዳ ለዚህ መልካም ተግባራቸው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ እውቅና ተችሯቸዋል። የእሳቸው መልካም ተግባር መረጃ የደረሰው ኮሚሽኑም የአርሶ አደሩን አርአያነት ለሌላው ለማስተማር አፈላልጎ ያገኛቸዋል፡፡ ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ሲያከብር በማጠቃለያው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ በተገኙበት የእውቅና ምስክር ወረቀትና የ15 ሺህ ብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል፡፡ የክልሉ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሙስናና ብልሹ አሰራር መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አብደላ ከቤተሰብ ጀምሮ በትምህርት ቤቶች በዜጎች ስነ ምግባር ላይ አበክሮ መስራት እንዲህ ያሉ ዜጎችን በብዛት ለማፍራት የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጹት። ታማኝ የሆኑ ሰዎች ሲበራከቱ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚጎዳውን ሙስና ለመከላከል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል፡ እንደ አርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ የሚገነባው ከቤት ጀምሮ በሚሰራ ሥራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ኮሚሽኑ ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ የጀመረውን ስራ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ እንደ አርሶ አደሩ ያሉ ታማኞች ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተቋቋመው የጸረ ሙስና ግብረ ኃይልም በጸረ ሙስና ትግሉ ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡም ታማኝነትን ባህሉ ከማድረግ ባለፈ የጸረ ሙስና ትግሉን በመደገፍ ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣም ነው ያሳሰቡት። የአርሶ አደር ሴዳ ጋርዜ መልካም ተግባርና ታማኝነትም ለብዙዎች ምሳሌ ይሆናል። በተለይ ያለፉበትን ለማግኘትና በአቋራጭ ለመክበር የሚሯሯጡ ሰዎች ከእሳቸው መልካም ተግባር ሊማሩ ይገባል። የሰው ሀብት ወስዶ ከመክበር ይልቅ በታማኝነት ከምናቆየው ንጹህ ህሊና ይበልጥ አትራፊ እንሆናለን። ለሰዎች መልካም መስራት ክብርና ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑንም የእኚህ አርሶ አደሩ ተሞክሮ ያሳያልና እንደእሳቸው ለሰራነው መልካም ተግባር ዋጋ እንዲከፈለን ታማኝነትን የህይወታችን መርህ ማድረግ አለብን። መልካምነት ቢቆይም እንኳ በራሱ ይከፍላልና።
ትንታኔዎች
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 2, 2026 540
ክፍል ሁለት የቀጠለ የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ተሳትፎ በአህጉራዊው መድረክ እ.አ.አ 1982 ኢትዮጵያ በሊቢያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለዘጠነኛ ጊዜ ተሳትፎዋን ማድረግ ቻለች። በውድድሩ ላይ አሁንም ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ ሁለት ከአልጄሪያ፣ዛምቢያና ናይጄሪያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዎቿን አድርጋለች። በምድብ ጨዋታዎቹ በናይጄሪያ 3 ለ 0 እንዲሁም በዛምቢያ 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ከአልጄሪያ ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይታለች። ኢትዮጵያ በምድቧ አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች። በፍጻሜው ጨዋታ ጋና ሊቢያን በመለያ ምት በማሸነፍ ለሶስተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካው ዋንጫ የተመለሰችበት ታሪካዊ ሁነት ኢትዮጵያ ከ13ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ በአህጉራዊው የእግር ኳስ ውድድር መድረክ ለመሳተፍ ሶስት አስርት ዓመታታን መጠበቅ ግድ ሆኖባታል። በነዚህ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ 15 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ተካሄደዋል። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ ውድድሩ ዳግም ተመለሰች። ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፈችበት መንገድ ልብ አንጠልጣይ ነበር። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2012 በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከሱዳን ጋር ባደረገችው የመጨረሻ ዙር የደርሶ መልስ ጨዋታ በመጀመሪያ ዙር ኦምዱርማን ላይ 5 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ሱዳን ጨዋታውን ያሸነፈችው በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠሩ ሁለት አጨቃጫቂ የፍጹም ቅጣት ምት በግቦች ነበር። ጥቅምት 4 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚደረገው የመልስ ጨዋታ በስታዲየሙ ዙሪያ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ በርካታ ተመልካች ተሰልፎ ነበር። ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ምንም መጠናቀቁ በስታዲየሙ የተገኘውን ተመልካች ጭንቅ ውስጥ ከቶ ነበር። ጭንቀቱ በስታዲየሙ ላሉት ብቻ ሳይሆን በቴሌቪዥን መስኮት ለሚከታተሉት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ያደረጉት ዋልያዎቹ አዳነ ግርማ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ቻሉ። ይሁንና ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው ለመሳተፍ አንድ ተጨማሪ ጎል ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አጥቂ ሳላዲን ሰዒድ ወሳኟን ሁለተኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳረፈ። ግቡ ሲቆጠር በስታዲየሙ ተመልካቾች ላይ የነበረው ስሜት በከፍተኛ ደስታ የተሟላ ሲሆን ስሜታቸውንብ በእንባ የገለጹም ነበሩ። ጨዋታው በድምር ውጤት 5 ለ 5 ተጠናቆ ከሜዳ ውጪ ብዙ ባስቆጠረ በሚል ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ መመለስ ቻለች። ከጨዋታው በኋላ በአዲስ አበባ ስታዲየም፣በመስቀል አደባባይና በመዲናዋ የተለያዩ አውራ ጎዳናዎች፣መንደሮችና የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍሎች የነበረው የደስታ ስሜትና ፈንጠዝያ የሚረሳ አልነበረም። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የደስታው ተቋዳሽ ነበሩ። ኢትዮጵያን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው እንድትመለስ ያደረጉት አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ነበሩ። ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 16 አገራት በስድስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። ኢትዮጵያም በምድብ ሶስት ከቡርኪናፋሶ፣ናይጄሪያና ዛምቢያ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከዛምቢያ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። አዳነ ግርማ በ65ኛው ደቂቃ ለኢትዮጵያ ግቡን አስቆጥሯል። በሁለተኛው ጨዋታ ኢትዮጵያ በቡርኪናፋሶ የ4 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዳለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ በናይጄሪያ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ከምድቧ ሳታልፍ ቀርታለች። ኢትዮጵያ ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ብትመለስም በውድድሩ ላይ ያስመዘገበችው ውጤትና ያሳየችው ብቃት የእግር ኳስ ቤተሰቡን ያስደሰተ አልነበረም። ይሁንና ብሔራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ ሲመለስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በበርካታ ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። በፍጻሜው ጨዋታ ናይጄሪያ ቡርኪናፋሶ 1 ለ 0 በማሸነፍ የአፍሪካን ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ አንስታለች። ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፈችው እ.አ.አ በ2021 ካሜሮን ባዘጋጀችው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነበር። ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ውድድሩ የተመለሰችው ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ካሜሮን፣ቡርኪናፋሶና ኬፕቨርዴ ጋር ተደልድላ ጨዋታዋን አድርጋለች። ኢትዮጵያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በኬፕቨርዴ 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛው ጨዋታ ዋልያዎቹ በአዘጋጇ አገር ካሜሮን 4 ለ 1 ተሸንፈዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ አጥቂው ዳዋ ሁቴሳ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ መሪ መሆን ብትችልም ቪንሰንት አቡበከርና ቶኮ ኢካምቢ በተመሳሳይ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የማይበገሩትን አንበሶች አሸናፊ አድርገዋል። በወቅቱ በአሰልጣኝ ውበቱ የተመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ከቡርኪናፋሶ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት ነበር። ኢትዮጵያ በምድቡ አንድ ነጥብ ብቻ በማግኘት ከምድቧ የመጨረሻውን ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። የኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ በቁጥሮች ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የ11 ጊዜ ተሳትፎ ኢትዮጵያ 31 ጨዋታዎችን አድርጋ 8ቱን ስታሸንፍ 19 ጊዜ ተሸንፋለች። አራት ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥታለች። በነዚህ 31 ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 33 ግቦችን ስታስቆጥር 67 ጎሎችን አስተናግዳለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ በሰፊ ግብ ያሸንችባቸው ጨዋታዎች ሁለት ናቸው። እ.አ.አ በ1962 ራሷ አዘጋጅታ ራሷ በወሰደችው ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቱኒዚያና ግብጽን በተመሳሳይ 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫው በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈችው እ.አ.አ በ1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሲሆን በወቅቱ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረታለች። ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በውድድሩ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግብ ያስተናገደችበት ሲሆን 12 ጎሎች ተቆጥረውባታል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ከፍተኛ ግቦችን ያስቆጠረችባቸው ውድድሮች እ.አ.አ በ1952 እና በ1968 በቅደም ተከተል ሶስተኛውንና ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባዘጋጅበት ወቅት ነው። በነዚህ ውድድሮች ላይ በተመሳሳይ ስምንት ግቦችን አስቆጥራለች። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ሶስት ጊዜ አዘጋጅታለች። ኢትዮጵያውያኖቹ አጥቂዎች ሉቺያኖ ቫሳሎና መንግስቱ ወርቁ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ 8 ግቦችን በማስቆጠር በአፍሪካ ዋንጫ የምንጊዜም የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ዝርዝር ውስጥ 21ኛ እና 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። እንደ መውጫ ኢትዮጵያ ሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አትሳተፍም። የአፍሪካ እግር ኳስ መስራችና ፈር ቀዳጅ እየተባለች የምትጠራው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎዎቿ ከሰሜን፣ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አገራት ጋር ብርቱ ፉክክር በማድረግ መልካም የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ተሳትፎ እየተቀዛቀዘ መጥቶ ብሔራዊ ቡድኑ ከምድቡ ማለፍ እየተሳነው ነው። የስፖርት ቤተሰቡና ተንታኞች ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን መገንባት አለመቻሉ፣የእግር ኳስ እድገቱ ወደ ኋላ መቅረቱ፣ የአጥቂ መስመሩ ክፍል የአጨራረስ ድክመት፣ ለወጣት ተጫዋቾች እድል አለመስጠት፣የአሰልጣኞች በየጊዜው መለዋወጥ፣ለእገር ኳሱ የሚሰጠው ትኩረት የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑና እግር ኳሱ በስፖርቱ ባለፉ ሰዎች አለመመራቱን ጨምሮ በርካታ ምክንያቶች ይቀመጣሉ። ጠንካራና ተወዳዳሪ ቡድን የመገንባት ስራ ትኩረት ያሻዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2029 የሚካሄደውን 37ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ ማቅረቧ የሚታወቅ ነው። በዚህም ውድድር ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፍ ጠንካራና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መገንባት የሚያስችል "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡ “ሮድ 2029"ን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ከሁሉም አካባቢዎች 85 ብቃት ያላቸው ታዳጊዎች ተመርጠው ለዘጠኝ ወራት ስልጠና ወስደው ብቃት ያላቸው ተመርጠዋል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከል 26ቱ በብቃታቸው ተመርጠው የ"ሮድ 2029" ግብን ማሳካት የሚያስችል የክፍል ውስጥ እና የሜዳ ላይ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያ በህዳር ወር ባስተናገደችው ከ17 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ማህበር ምክር ቤት ዞን (ሴካፋ) ተሳትፎ አድርጓል። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ በሞሮኮ በሚካሄደው 16ኛው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ይታወቃል። "ሮድ 2029" የታዳጊዎች እግር ኳስ የስልጠና ፕሮጀክት በአሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ አሰልጣኞች ጥምረት የሚካሄድ ሲሆን በኢትዮጵያ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል። በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሥልጠና መሆኑን በማንሳት፤ በእስካሁኑ ሂደት ተስፋ ሰጭ ውጤት ታይቶበታል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የ2029 የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንድትመረጥ የቴክኒክ ጉዳዮችን ጨምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። ታዳጊዎችን እግር ኳስ ልማት፣ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን እንዲያሞሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መስፋት ተስፋ ሰጪ ጅማሮዎች ነው። መንግስት የጀመራቸው ስራዎች በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርባቸዋል። አጠቃላይ የእግር ኳሱ እደግት የስፖርት ባለድርሻ አካላትን የጋራ ትብብር ይጠይቃል። ተስፋ ሰጪ እና ብርሃን ፈንጣቂ ጅማሮዎችን ነገ ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም መድረክ በእግር ኳሱ ስኬታማ ለመሆን መሰረት የሚጥሉ ናቸው።
የአፍሪካ እግር ኳስ ፈር ቀዳጇ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ዋንጫ
Jan 1, 2026 485
ክፍል አንድ እንደ መነሻ እ.አ.አ የካቲት 8 ቀን 1957 በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ ታሪካዊ ከሚባሉ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። በካርቱም ግራንድ ሆቴል ሱዳን፣ኢትዮጵያ፣ግብጽና ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራውን ተቋም ለመመስረት ምክክር ላይ ናቸው። አህጉሪቷን የሚወክለው ኮንፌዴሬሽን ለማቋቋም መነሻ የሆነው ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር(ፊፋ) እ.አ.አ በ1956 በፖርቹጋል ሊዝበን ባካሄደው ዓመታዊ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች ከሌሎች አህጉራዊ የእግር ኳስ ማህበራት ጋር ያደረጓቸው መደበኛ ምክክሮች ናቸው። በካርቱም የተሰበሰቡት አራት አገራት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን በይፋ መሰረቱ። ግብጻዊውን አብደል አዚዝ አብደላ ሳሌምን በሙሉ ድምጽ የካፍ የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት አድርገው መረጡ። ካፍን ያቋቋሙት አገራት እ.አ.አ በ1957 የአፍሪካ ዋንጫ በሱዳን እንዲካሄድ ወሰኑ። የመጀመሪያውን የካፍ መተዳደሪያና የውድድር ደንቦች ያዘጋጁት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው። የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና የፎርፌ ውጤት የመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ ከየካቲት 10 እስከ 16 1957 በሱዳን ካርቱም ተካሄዷል። በውድድሩ ላይ ሱዳን፣ኢትዮጵያና ግብጽ ተሳታፊ ነበሩ። በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማንችስተር ሲቲ ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው አስቀድሞ በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ትሳተፋለች ተብሎ የነበረው ደቡብ አፍሪካ ከአገሪቷ በነበረው የአፓርታይድ የዘር መድሎ ምክንያት ከውድድሩ ውጪ ሆናለች። ደቡብ አፍሪካ ከውድድሩ ውጪ የሆነቸው በአፓርታይድ ሕግ ነጮች ሙሉ በሙሉ በነጭ ወይም በሙሉ የተገነባ ብሔራዊ ቡድን እንጂ መቀላቀል አንችልም በማለታቸው ምክንያት ነው። በዚህም ምክንያት ከደቡብ አፍሪካ ጋራ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋን ልታደርግ የነበረችው ኢትዮጵያ 2 ለ 0 በፎርፌ በማሸነፍ ለፍጻሜው አልፋለች። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች። እ.አ.አ የካቲት 16 1957 በካርቱም ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ኢትዮጵያን 4 ለ 0 በማሸነፍ ታሪካዊውን የአፍሪካ ዋንጫ አነሳች። አራቱንም ግቦች ያስቆጠረው የፊት መስመር ተጫዋቹ መሐመድ ዲያብ አል-አታር ሲሆን በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ አራት ግቦችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋችና በአምስት ግቦች የመጀመሪያው የውድድሩ ኮከብ ግቢ አግቢ በመሆን ድርብ ታሪክ ጽፏል። ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች። በመጀመሪያው የአፍሪካ ዋንጫ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ምንም የማጣሪያ ውድድር አልተደረገም። በመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂ ሚካኤል ጊላ ተከላካዮች አየለ ተሰማ፣መኩሪያ ከበደ አስፋው፣አዳሙ ዓለሙ፣አዳል ተክለስላሴ አማካዮች ናስር በርሄና ሳሙኤል ዘውዴ አጥቂዎች አብርሃም ባይሩ፣አምደስላሴ ነጸረ፣አስፋው ብርሃኔና ከበደ መታፈሪያ ናቸው። በአፍሪካ ዋንጫና እግር ኳስ ፈር ቀዳጅ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎዋን በሱዳን አሀዱ ብላ ጀመረች። የኢትዮጵያ ሁለተኛ ተሳትፎ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1959 በግብጽ በተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ አድርጋለች። ሱዳን ሌላዋ በውድድሩ ላይ የተሳተፈች አገር ናት። የውድድሩ ፎርማት በአገራቱ መካከል እርስ በእርስ በሚደረጉ ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የሚያነሳበት ነበር። በዚሁ መሰረት ኢትዮጵያ በውድድሩ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በግብጽ 4 ለ 0፤ በሱዳን 1 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ግብጽ ሱዳንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ብቸኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የተካሄደው በኢትዮጵያ አዘጋጅነት እ.አ.አ በ1962 ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ቀደም ብለው ከተካሄዱት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ለየት የሚያደርገው አራት አገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፉበት ነው። ኢትዮጵያ የውድድሩ አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራችን በቀጥታ ለውድድሩ ስታልፍ ፤ በተመሳሳይ የግብፅ ቡድንም የ1959 የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዋንጫ አሸናፊ ቡድን ስለነበር በቀጥታ ለ3ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ሲያልፉ ዩጋንዳና ቱኒዚያ የማጣሪያ ጨዋታ አድርገው ለአፍሪካ ዋንጫ አልፈዋል። በሶስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ሲሆኑ ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዋ ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። አጥቂው ሉቺያኖ ቫሳሎ በ32ኛው በፍጹም ቅጣት ምት ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ያስቆጠረችው የመጀመሪያ ግቧ ሆኖ ተመዝግቧል። ቫሳሎ በ75ኛው ደቂቃ በጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ እና ግርማ ተክሌ ቀሪዎችን ግቦች ለኢትዮጵያ ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። በሌላኛው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ግብጽ ዩጋንዳን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ከኢትዮጵያ ጋር ደረሰች። በፍጻሜው ጨዋታ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በ35ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት በግብ ግብጽን መሪ ማድረግ ችላ ነበር። ከእረፍት መልስ ግርማ ተክሌ በ74ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጋለች። በ75ኛው ደቂቃ አሊ መሐመድ ባዳዊ አብደል ፋታህ በድጋሚ ግብጽን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጠረ። አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በ84ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን በድጋሚ አቻ አደረገ። ጨዋታው በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት በመጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሬ ሰዓት አምርቷል። በጭማሬ 30 ደቂቃው ኢታሎ ቫሳሎ በ101ኛው እና መንግስቱ ወርቁ በ118ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች ኢትዮጵያ 4 ለ 2 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ አህጉራዊውን ዋንጫ ከፍ አድርጋለች። በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦች ያስቆጠረው አጥቂው መንግስቱ ወርቁ በአጠቃላይ በውድድሩ ላይ ሶስት ጎሎችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል። ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት አገራት የተሳተፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ እ.አ.አ በ1963 በጋና አስተናጋጅነት በተካሄደው አራተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ነው። በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስድስት ብሔራዊ ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን በሁለት ምድብ እያንዳንዳቸው ሶስት አገራት ተደልድለው ጨዋታቸውን አድርገዋል። የውድድሩ ፎርማት በየምድቡ አንደኛ ሆኖ የጨረሰ አገር ወደ ፍጻሜው እንዲሁም ሁለተኛ የወጡ አገራት ለደረጃው ያለፉበት ነበር። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከአዘጋጅ አገር ጋና ቱኒዚያ ጋር ተደልድላች። በአክራ ስፖርት ስታዲየም ኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረገችው ጨዋታ 2 ለ 0 ተሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁ ሁለት እንዲሁም ግርማ ተክሌና ግርማ ተስፋዬ ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች ቱኒዚያን 4 ለ 2 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ከምድቡ ሁለተኛ ሆና በማጠናቀቋ ለደረጃ ጨዋታ የቀረበች ሲሆን በግብጽ 3 ለ 0 ተሸንፋለች። በፍጻሜው ጋና ሱዳንን 3 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አነሳች። ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ተከታታይ ጊዜ የተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1965 በቱኒዚያ አስተናጋጅነት በተካሄደው አምስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስድስት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከቱኒዚያና ሴኔጋል ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋ በቱኒዚያ 4 ለ 0 ተሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታዋ በሴኔጋል 5 ለ 1 ተሸንፋለች። በጨዋታው ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ነበር። በፍጻሜው ጋና ቱኒዚያን 3 ለ 2 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ ማንሳት ችላለች። ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ እ.አ.አ 1968 የተካሄደውን ስድስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ኢትዮጵያ ነበረች። ውድድሩን ያስተናገደው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ስታዲየም(የአሁኑ አዲስ አበባ ስታዲየም) ነበር። በሻምፒዮናው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣አልጄሪያና ዩጋንዳ ጋር የተደለደለች ሲሆን ሶስቱንም የምድብ ጨዋታዎቿን አሸንፋለች። በመጀመሪያ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ግርማ አስመሮም ተስፋይ በጨዋታና ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 1 አሸንፋለች። ኢትዮጵያ በሁለተኛ ጨዋታዋ በኩረጽዮን ገብረሕይወት ባስቆጠራት ግብ ኮትዲቭዋርን 1 ለ 0 ረታለች። በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ አጥቂው መንግስቱ ወርቁና ሸዋንግዛው አጎናፍር በጨዋታ እንዲሁም ሉቺያኖ ቫሳሎ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠሯቸው ግቦች አልጄሪያን 3 ለ 1 በማሸነፍ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ለግማሽ ፍጻሜው አልፋለች። ኢትዮጵያ በግማሽ ፍጻሜው ጨዋታዋን ያደረገችው ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ነበር። ራውል አልበርት ኪዱሙ ማንታንቱ በሶስተኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን መሪ አድርጎል። ሊኦን ሙንጋሙኒ በ16ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ የኮንጎን መሪነት ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርጓል። ሉቺያኖ ቫሳሎ በ25ኛው ደቂያ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን ወደ ጨዋታው እንድትመለስ አድርጓል። መንግስቱ ወርቁ በ65ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት መጠናቀቁ ጨዋታው ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አመራ። በጭማሬ ሰዓቱ ሊኦን ሙንጋሙኒ በ100ኛው ደቂቃ ያስቆጠራትን ግብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን አሸናፊ በማድረግ ወደ ፍጻሜው እንድታልፍ አድርጎታል። ኢትዮጵያ ለደረጃው ባደረገችው ጨዋታ ላውረን ፖኩ ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ተሸንፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር አራተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግብ ያስተገደችበት ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሱዳን እ.አ.አ 1970 ሱዳን ባዘጋጀችው ሰባተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ለሰባተኛ ጊዜ በአህጉራዊው የውድድር መድረክ ተሳትፋለች። በውድድሩ ላይ ስምንት አገራት ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ በምድብ አንድ ከኮትዲቭዋር፣ካሜሮንና ሱዳን ጋር ተደልድላለች። ኢትዮጵያ በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሱዳን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተረታለች። በሁለተኛው ጨዋታም በካሜሮን 3 ለ 2 የተሸነፈች ሲሆን መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በኮትዲቭዋር 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ተሸንፋለች። መንግስቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብቸኛዋን ግብ ከመረብ ላይ ያሳረፈ ተጫዋች ነበር። በዚህ ጨዋታ አጥቂው ላውረን ፖኩ አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በምድቡ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን በውድድሩ 12 ግቦችን ተቆጥረውባታል። በፍጻሜው ሱዳን ጋናን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን አንስታለች። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ስምንተኛ ተሳትፎዋን ለማድረግ ስድስት ዓመት መጠበቅ ነበረባት። እ.አ.አ በ1976 ራሷ ለሶስተኛ ጊዜ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ በድጋሚ ወደ ውድድር ተሳትፎ ተመልሳለች። በውድድሩ ላይ አሁንም የተሳተፉ አገራት ቁጥር ስምንት ነበር። ኢትዮጵያ በውድድሩ በምድብ አንድ ከግብጽ፣ዩጋንዳና ጊኒ ጋር ተደልድላለች። በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሰለሞን ሽፈራውና ተስፋዬ ስዩም ግቦች ዩጋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች። በሁለተኛ ጨዋታዋ ኢትዮጵያን በጊኒ የ2 ለ 1 ሽንፈት አጋጥሟታል። ሰለሞን ሽፈራው ኢትዮጵያን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። በመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋ ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር አንድ አቻ ተለያይታለች። መሐመድ አሊ ለኢትዮጵያ ግቧን ያስቆጠረ ተጫዋች ነው። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ ከምድቧ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ማለፍ ሳትችል ቀርታለች። በፍጻሜው ሞሮኮ ጊኒን በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ማንሳት ቻለች። ይቀጥላል ….
ብክነትን መቀነስ የኃይል አቅርቦትን ማሳደግ፤ የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳ
Dec 8, 2025 1130
አፍሪካ በዓለማችን በታዳሽ ኃይል እምቅ ሀብቶችን የያዘች አህጉር ናት። የዓለም 60 በመቶ የፀሐይ ኃይል ሀብት የሚገኘው በአፍሪካ ነው። አህጉሪቱ ከፀሐይ በየዓመቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ቴራዋት ሰዓት ኢነርጂ የማመንጨት አቅም አላት። ይሁንና በፀሐይ የምታመነጨው ኃይል ድርሻ አነስተኛ መሆነን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የእ.አ.አ 2023 ጥናት ያመለክታል። የዓለም ባንክ ተቋም የሆነው ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በበኩሉ አፍሪካ 25 በመቶ የዓለም የንፋስ ኃይል አቅም ያላት ሲሆን 180 ሺህ ቴራ ዋት ሰዓት ማመንጨት እንደምትችል ይገልጻል። ይሁንና በዓለም ላይ በዘርፉ ያላት ድርሻ ከአንድ በመቶ በታች መሆኑን ያነሳል። ሃይድሮ ፓወር የአፍሪካ ሌላኛው የኢነርጂ ሀብት ማሳያ ነው። የአህጉሪቷ ወንዞች እና ተፋሰሶች በየዓመቱ 1 ሺህ 500 ቴራ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ቢኖራም ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶውን ብቻ ነው። የናይል ተፋሰስ፣ የኮንጎ ተፋሰስ እና የዛምቤዚ ተፋሰሶችን የያዘችው አፍሪካ ከፍተኛ የሃይድሮ ፓወር አቅሟን መጠቀም አልቻለችም ይላል የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ጥናት። ወደ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ያለው የእንፋሎት ኃይል ሌላኛው ትልቅ እድል ነው። የአፍሪካ የእንፋሎት (ጂኦተርማል) አቅም ከ15 እስከ 20 ጊጋዋት መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት መረጃ ያሳያል። አፍሪካ ከዓለም የኢነርጂ ምርት ውስጥ ከአራት በመቶ በታች እንዲሁም በታዳሽ ኃይል ደግሞ ከ1 ነጥብ 6 በመቶ ያነሰ ድርሻ እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ የኢነርጂ ምህዳር ሁለት ተጻራሪ እውነታዎችን የያዘ ነው። አህጉሪቷ የዓለምን 17 በመቶ ህዝብ ብትይዝም በዓለም የኢነርጂ አጠቃቀም ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች ነው። በአሁኑ ሰዓት 600 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን የአፍሪካ ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። 21 በመቶ አፍሪካውያን ብቻ ንጹህ የማብሰያ ነዳጅ እና ቴክኖሎጂዎችን ያገኛሉ። ባህላዊ የምግብ ማብሰያ አማራጮች ለጤና አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ናቸው። በአፍሪካ ከከተሜነት መስፋፋት እና ከፈጣን የህዝብ እድገት ጋር በተያያዘ የኢነርጂ ፍላጎት በፍጥነት እየጨመረ ይገኛል። እ.አ.አ በ2040 የአፍሪካ ህዝብ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ህዝብ እንደሚያልፍ ትንበያዎች ያሳያሉ። በተለይም የህዝብ ብዛት መጨመሩ በኢነርጂ አቅርቦት ላይ ጫና ያሳድራል። ከእ.አ.አ 2014 እስከ 2023 የአፍሪካ የታዳሽ ኢነርጂ በእጥፍ አድጎ ከ32 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ወደ 62 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ማደጉ መልካም የሚባል እምርታ መሆኑን የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኢነርጂ ኤጀንሲ ይገልጻል። የአፍሪካ ሌላኛው ፈተና የምትጠቀመውን ኢነርጂ የብክነት ምጣኔ ነው። በበቂ ሁኔታ ባልተደራጀው የኢነርጂ ስርዓት ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት ገንዘብ ታጣለች። እንደ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ አፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀሟን የምታሻሽል ከሆነ 30 በመቶ የኢነርጂ ወጪዋን መቀነስ ትችላለች። ይህም የአፍሪካ መንግስታት ለማህበራዊ ልማት የሚያወጡትን በጀት እንደሚያሳድግ እና አዲስ የኃይል ማመንጫዎችን ሳትገነባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ የምትችልበትን እድል ይፈጥርላታል። ኢትዮጵያ ከወራጅ ወንዞች በአመት 124 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያላት ሲሆን ከ36 እስከ 40 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የከርሰ ምድር የውሃ ሃብት እንዳላት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከገፀ ምድር የውሃ ሃብቷ 83 በመቶ የሚገኘው ከተከዜ፣ ባሮ፣ አባይና ጊቤ ኦሞ ወንዞች ነው። አንዱ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመነጨው ካላት የውሃ ሀብት ነው። ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ፣ በነፋስ እና በጂኦ-ተርማል የኃይል አማራጮች በአጠቃላይ ከ300 እስከ 400 ጊጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ። በ10 ዓመት መሪ ልማት እቅዱ ኢትዮጵያ አሁን እያመነጨች ያለውን 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ አቅዳለች። ከለውጡ በኋላ በኢነርጂው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። ከስራዎቹ መካከል ለሶስት አስርት ዓመታት ስራ ላይ የነበረውን የኢነርጂ ፖሊሲ ማሻሻል ይገኝበታል። ፖሊሲው ከ2013 ዓ.ም አንስቶ የማሻሻያ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል። የፖሊሲ ማሻሻያው የተዘጋጀው አሁን ያለውን ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ነባራዊ እውነታ መሰረት ባደረገ መልኩ ነው። ለኢነርጂ ፖሊሲው ማሻሻል ምክንያቶች ከሆኑት መካከልም ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ፣ ከአረንጓዴ ልማት፣ ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድና ከዘላቂ የልማት ግቦች ጋር ማጣጣም በማስፈለጉ እንደሆነም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በአፍሪካ ግዙፉ የኢነርጂ ፕሮጀክት ሲሆን ለቀጣናው እና ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ አቅምን ይዞ መጥቷል። ከፖሊሲው ትኩረት አንዱ ከአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ለጎረቤት አገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር እንደሆነም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። በ10 ዓመቱ የመሪ ልማት እቅዱም ዜጎችን በስፋት የአሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግብ ተይዟል። ከዚህ ባሻገር በእቅዱ ኢትዮጵያ የቀጣናው ሀገራትን በኃይል የማስተሳሰር ዕቅድ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች። በእቅዱ ለጎረቤት አገራት እየቀረበ ያለውን 2 ሺህ 803 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ወደ 7 ሺህ 184 ጊጋ ዋት ሰዓት የማሳደግ ውጥን ተይዟል። የአፍሪካ የኢነርጂ አጠቃቀምን ለማሻሻል እና ብክነትን ለመቀነስ የተቀናጀ ምላሽ የመስጠት ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው ነው። የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency Conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ኮንፍረንሱ እ.አ.አ በ2024 በአዘርባጃን ባኩ በተካሄደው 29ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-29) ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢነርጂ ውጤታማነት ጥምረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ ነው። የጥምረቱ ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መጽደቁ ይታወቃል። “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ ነው። አህጉራዊው ሁነት የተዘጋጀው የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተቋም በሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ መንግስት ትብብር ነው። ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ራሺድ አሊ አብደላ ኮንፍረንሱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት የኢነርጂ ውጤማነት የአፍሪካ ዘላቂ ልማት ዋንኛ ሀብት ነው ሲሉ ተናግረዋል። የኢነርጂ ውጤማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልህቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች፣ ሚኒስትሮች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ፣ ተመራማሪዎች እና ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ ነው። ባለድርሻ አካላቱ በአፍሪካ ዘላቂ የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠን የሚያስችሉ ውጤታማ የኢንቨስትመንት አማራጮችና ፖሊሲዎች ላይ በመምከር ቀጣይ ስራዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ከፍተኛ እና በሰፊው ጥቅም ላይ ያልዋለ የታዳሽ ኢነርጂ አቅም በቀጣይ የዓለም የኢነርጂ ሽግግር እና አቅርቦት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው። የኢነርጂ አቅሙን ትሩፋቶች የመጠቀም ጉዳይ አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያላቸውን የታዳሽ ኃይል ምንጭን ለመጠቀም እየወሰዷቸው የሚገኟቸው እርምጃዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው። የኢነርጂ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የተቀናጁ ፖሊሲዎች፣ የተቀናጀ ቀጣናዊ የኃይል ቋቶችን መፍጠር፣ የኢነርጂ ፋይናንስን ማሳደግ እና የመንግስታት የፖለቲካ ቁርጠኝነት የአፍሪካ ኢነርጂ አቅሞች ወደ ዘላቂ ልማት፣ የኢነርጂ ደህንነት የማረጋገጥ፣ የአየር ንብረትን የሚቋቋም ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶች ይዞ ይመጣል።
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 3459
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 3099
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 1970
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 7789
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 6274
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት
Jan 14, 2026 169
ዕድሜ ያልገደበው የልማት አርበኝነት ብርቱዎች ነገን በማሰብ ሁሌም ታትረው ይሰራሉ፤ ይደክማሉ፤ ይጥራሉ…ለቀጣዩ ትውልድም ጥሪት በማስቀመጥ አሻራቸውን ያኖራሉ። አገር የምትገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው። “አባት ያበጀው፤ ለልጅ ይበጀው” እንደሚባለው ልጆች ከአባቶቻቸው ያገኙትን ጥሪት በአዲስ እውቀትና አሰራር ለአገር እድገት በሚበጅ መልኩ አጠናክረው መጠቀማቸው አይቀርም። “ዕድሜ ጸጋ ነው” የሚለው አባባል አንዳንዴ በዕድሜ ብንገፋም ጠንክረን ከሰራን ብዙ ነገር እናያለን ከሚለው ጋር የተያያዘ ነው። በሰቆጣ ከተማም እድሜ ሳይገድባቸው በልማት ውጤታማ የሆኑ ግለሰቦች ለዚህ ማሳያ ናቸው። የከተማዋ ነዋሪ የ67 ዓመቱ አቶ ብርሃኑ አወቀ እና የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ዕድሜያቸው ቢገፋም ጠንክሮ ከተሰራ ውጤታማ መሆን እንደሚቻልና ዕድሜ ጸጋ ሆኖ ብዙ ለውጥ ማየት እንደሚቻል ማሳያ ናቸው። ግለሰቦቹ ከዕድሜ ብዛት ጉልበቴ ደከመ፣ አይኔ ፈዘዘ፣ እጄም ተሳሰረ…ሳይሉ ጊዜያቸውን በደን፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ በማሳለፍ ለወጣቶች የልማት አርአያነት ያለው ተግባር እየፈጸሙ ነው። አቶ ብርሃኑ አወቀ በሰቆጣ ከተማ ዳርቻ የሚገኝ አለቱ ያገጠጠና የተራቆተ አካባቢን ከሌላ አካባቢ ለም አፈር በማምጣትና በመደልደል አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ደን በማልማት ውጤታማ ስራ እያከናወኑ ነው። ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከወጣሁ ጀምሮ ጠንክሬ በመስራት የምለወጥበትን ሥራ ማሰብ ስነበረብኝ፤ የቆሻሻ መጣያ ሆኖ ለዘመናት የቆየን ጭንጫ መሬት ጠርጌና ደልድዬ ማልማት ችያለሁ ይላሉ ወደኋላ መልስ ብለው የተነሱበትን ሁኔታ ሲያስታውሱ። ግማሽ ሄክታር በማይሞላ መሬት ላይ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ ዘይቱና፣ ጌሾ፣ ቡና፣ ማንጎና አቮካዶ አልምተዋል። በተጨማሪም ቆስጣ፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመንና ሽንኩርት በማምረት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ጥሪት አፍርተዋል። ጊዜን በአግባቡ ተጠቅሞ ተግቶ መስራት ከተቻለ ሀብት ማፍራትና ህይወትንም መለወጥ እንደሚቻል የገለጹት አቶ ብርሀኑ፣ ወጣቱም ከእሳቸው የሥራ ትጋት በመማር በአካባቢው ያለውን ፀጋ ለይቶ በማልማት ሊጠቀም ይገባል ሲሉ ይመክራሉ። ሌላው የ83 ዓመቱ የዕድሜ ባለፀጋ አቶ ታደሰ አዳነ ባለፉት 18 ዓመታት በተሰማሩበት የአትክልትና ደን ልማት ሥራ የአካባቢያቸውን ገጽታ ቀይረዋል። የዕድሜ ዘመናቸውን በውትድርናና በመንግስት ሠራተኝነት በማገልገል ሃገራዊ ግዳጃቸውን ሲወጡ ነው የቆዩት። ከመንግስት ሥራ በጡረታ ከተገለሉ በኋላም ቤት ውስጥ መቀመጥን አልመረጡት። አካፋና ዶማቸውን ይዘው ባላቸው ትንሽ መሬት ላይ ጌሾ፣ ዘይቱና እና ማንጎ በማልማት ምርቱን ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል። በአካባቢያችን ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ ለይተን ማልማት ከቻልን ድህነትን ማስወገድ የሚከብድ አይሆንም ያሉት አቶ ታደሰ፣ የተራቆተና በጎርፍ የተጎዳን መሬት በማልማት አካባቢውን ሳቢና ማራኪ ማድረጋቸውን ነው የገለጹት። ወጣቱም ከእሳቸው አርአያነት ያለው ተግባር በመማር በአካባቢው እጁ ላይ ባለ ሀብት ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል በተግባር ማሳየት እንዳለበት መክረዋል። የዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ መስኖ ውሃ አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ እንደገለጹት፤ በብሔረሰብ አስተዳደሩ 24ሺህ 847 አርሶ አደሮች በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተዋል። ከአርሶ አደሮቹ መካከል ዕድሜ ሳይገድባቸው ወደ ልማት የገቡ አረጋዊያን እያከናወኑት ያለው የግብርና ልማት ሥራ ለወጣቱ ትልቅ ትምህርት እንደሚሆንም ተናግረዋል። ከእነሱ ልምድ በመውሰድ በዞኑ ወጣቶች፣ ሴቶችና አረጋዊያን በጓሮና ባላቸው መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲያለሙ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ይህም በዞኑ የሚስተዋለውን የስርዓተ ምግብ ችግር ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።
ከማላጋ እስከ አፍሪካ ዋንጫ፤ የሞሮኮው አዲስ እንቁ ብራሂም ዲያዝ
Jan 13, 2026 186
የግል ክህሎት፣ ፈጣን አስተሳሰቡ እና በጠባብ ክፍተቶች ውስጥ ሰብሮ የመግባት አቅሙ ሙገሳ እንዲጎርፍለት አድርጓል። አንድ ለአንድ ሲገናኝ ተከላካዮችን በፈጣን አካላዊ ቅልጥፍና እና በድንገት አቅጣጫ በመቀየር የሚያልፍበት መንገድ እንዲሁም የመፍጠር አቅሙ የተመልካቾችን ቀልብ የሚይዝ ነው። የአማካይ እና የአጥቂ መስመርን በማገናኘት እና በአስገራሚ ሁኔታ አጭር ኳሶችን በማቀበልም የተዋጣለት ተጫዋች ነው ማለት ይቻላል። በቦታ አያያዙ የእግር ኳስ ልኅቀቱ ከፍተኛ ነው የሚል አድናቆት ከእግር ኳስ ባለሙያዎች አግኝቷል። ኳስን ሲያንከባልልም ለዐይን ይስባል። ከክህሎቱ እና ከማራኪ እንቅስቃሴው ባለፈ ወደ ኋላ እየመለሰ ተከላካዮችን ያግዛል፣ ኳስ ይነጥቃል። ይህ ተጫዋች የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ክስተት የሆነው የሞሮኮው ብራሂም ዲያዝ ነው። የ26 ዓመቱ የሪያል ማድሪድ የክንፍ መስመር ተጫዋች ዲያዝ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አምስት ጨዋታዎችን አድርጎ አምስት ግቦችን በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመራ ነው። አዘጋጇ ሞሮኮ በዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ መክፈቻ ኮሞሮስን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የውድድሩን የመጀመሪያ ግብ አስቆጥሯል። ብራሂም አብዱልቃድር ዲያዝ የተወለደው እ.አ.አ ኦገስት 3 ቀን 1999 በስፔን ማላጋ ግዛት ነው። እናቱ ስፔናዊ አባቱ ሞሮኳዊ ናቸው። ዲያዝ ያደገው በማላጋ ነው። እግር ኳስንም በአንዳሉሺያዊቷ ከተማ ሲጫወት ቆይቷል። በ16 ዓመቱ ካደገበት ማላጋ በመውጣት እ.አ.አ በ2015 ወደ ማንችስተር ሲቲ ወጣት አካዳሚ በ200 ሺህ ፓውንድ ወጪ ተዘዋወረ። ዲያዝ እ.አ.አ ሴፕቴምበር 21 ቀን 2016 በካራባኦ ካፕ (በቀድሞ አጠራሩ ሊግ ካፕ) ማንችስተር ሲቲ ከስዋንሲ ሲቲ ባደረገው ጨዋታ በ80ኛው ደቂቃ በኬሌቺ ኢናቺዩ ተቀይሮ በመግባት ለውኃ ሰማያዊዎቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያውን ጨዋታ ካደረገ ከሶስት ቀናት በኋላ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለሶስት ዓመታት የሚያቆየውን ፕሮፌሽናል ኮንትራት ተፈራርሟል። እ.አ.አ ኖቬምበር 21 ቀን 2017 ማንችስተር ሲቲ ከፌይኖርድ ሮተርዳም ጋር ባደረገው የሻምፒዮናስ ሊግ ጨዋታ ላይ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል። በወቅቱ ብራሂም ስተርሊን መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በጭማሪ ሰዓት ላይ ነበር ተቀይሮ የገባው። ዲያዝ በውኃ ሰማያዊዎቹ ማልያ ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የተጫወተው እ.አ.አ ዲሴምበር 19 ቀን 2017 ነው። ማንችስተር ሲቲ ከሌስተር ሲቲ በካራባኦ ካፕ ጨዋታ ላይ ለ88 ደቂቃዎች ተሰልፎ ተጫውቷል። እ.አ.አ ጃንዋሪ 20 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ኒውካስትል ዩናይትድን 3 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በወቅቱ ማንችስተር ሲቲ የሊጉን ዋንጫ ያነሳ ሲሆን፤ በውድድር ዓመቱ አራት ጨዋታዎች ላይ ብቻ ተሳትፎ ያደረገው ብራሂም ዲይዝ የሜዳሊያ ሽልማት አግኝቷል። እ.አ.አ ኦገስት 5 ቀን 2018 ማንችስተር ሲቲ ቼልሲን 2 ለ 0 ባሸነፈበት የኮሙዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ ላይ በፊል ፎደን ተቀይሮ በመግባት ለ15 ደቂቃዎች ተጫውቷል። ዲያዝ እ.አ.አ 2018/19 ማብቂያ ላይ ማንችስተር ሲቲ ፉልሃምን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ በማሳረፍ የመጀመሪያ ግቦቹን ለሲቲ አስቆጥሯል። በማንችስተር ሲቲ ያለው ውል እ.አ.አ 2019 ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ወቅት ስሙ ከዝውውር ጋር በስፋት ይነሳ ነበር። ዲያዝ እ.አ.አ ጥር 2019 በ17 ሚሊዮን ዩሮ ከማንችስተር ሲቲ ወደ ሪያል ማድሪድ ተዘዋወረ። ለስድስት ዓመታት የሚያቆየውን ውልም ፈርሟል። የክንፍ ተጫዋቹ የመጀመሪያ ጨዋታውን በነጮቹ ማልያ ያደረገው እ.አ.አ ጥር 9 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ ሌጋኔን በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ 3 ለ 0 ባሸነፈበት ወቅት ነው። ከአራት ቀናት በኋላ በስፔን ላሊጋ ሪያል ማድሪድ ሪያል ቤቲስን 2 ለ 1 ባሸነፈበት ጨዋታ ተቀይሮ በመግባት በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። የመጀመሪያ ግቡን ለማስቆጠር ሶስት ወራትን ጠብቋል። እ.አ.አ ግንቦት 12 ቀን 2019 ሪያል ማድሪድ በላሊጋው በሪያል ሶሲዬዳድ 3 ለ 1 ሲሸነፍ ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል። በወቅቱ ዲያዝ ስድስት ጨዋታዎች ላይ በላሊጋው የተጫወተ ሲሆን፤ በመጀመሪያ ዓመቱ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ሪያል ማድሪድ እ.አ.አ በ2021/21 የውድድር ዓመት ብራሂም ዲያዝ ወደ ኤሲ ሚላን በውሰት ማምራቱን ይፋ አደረገ። ዲያዝ ሚላን እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2020 ክሮቶኔን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ የመጀመሪያ ግቡን ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ ግንቦት 2021 ኤሲ ሚላን ጁቬንቱስን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ያስቆጠረው ግብም ተጠቃሽ ነው። ዲያዝ በኤሲ ሚላን የውሰት ውሉ ሲያበቃ በድጋሚ ለሁለት ዓመታት በውሰት የሚቆይበት ስምምነት ሪያል ማድሪድ ከጣልያኑ ክለብ ጋር የተፈራረመ ሲሆን፤ ውሉ ሚላን ተጫዋቹን የማቆየት መብት ሰጥቶታል። እ.አ.አ መስከረም 15 ቀን 2021 ኤሲ ሚላን በሻምፒዮንስ ሊጉ የ3 ለ 2 ሽንፈት ሲያስተናግድ የመጀመሪያ የአውሮፓ መድረክ ግቡን አስቆጥሯል። በ2023 ኤሲ ሚላን ቶተንሃም ሆትስፐርስን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ 1 ለ 0 ሲያሽንፍ ብቸኛውን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል። እ.አ.አ በ2023 ሰኔ ወር ላይ ሪያል ማድሪድ ዲያዝ ከኤሲ ሚላን የሶስት ዓመታት የውሰት ቆይታ በኋላ ወደ ክለቡ መመለሱን አሳውቋል። ተጫዋቹ በኤሲ ሚላን ቆይታው 91 ጨዋታዎችን አድርጎ 13 ግቦችን ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ዲያዝ ወደ ሪያል ማድሪድ ከተመለሰ በኋላ ኮንትራቱን እስከ 2027 አራዝሟል። እ.አ.አ መስከረም 27 ቀን 2023 ወደ ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ሪያል ማድሪድ ላስ ፓልማስን 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ግብ አስቆጥሯል። የክንፍ መስመር ተጫዋቹ ሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥ እና በአውሮፓ መድረክ በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ላይ ግብ በማስቆጠር እና ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ዲያዝ እስከ አሁን ለሪያል ማድሪድ ባደረጋቸው 129 ጨዋታዎች 20 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ከነዚህም ውስጥ 13ቱ በላሊጋው ያስቆጠራቸው ናቸው። ከክለብ ወጣ ስንል የተጫዋቹን የብሔራዊ ቡድን ቆይታ እናገኛለን። ዲያዝ በታዳጊነቱ በተለያዩ የእድሜ እርከኖች ለስፔን ወጣት ቡድኖች ተጫውቷል። እ.አ.አ በ2016/17 የውድድር ዘመን ለስፔን ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በ16 ዓመቱ ተሰልፎ መጫወት ችሏል። በተለይም አዘርባጃን እ.አ.አ በ2017 ባዘጋጀችው 15ኛው የአውሮፓ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ላይ ያሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆት አስችሮታል። በዚያ ቀጥለው በነበሩ ዓመታትም ለስፔን ከ19 እና ከ21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቷል። ብራሂም ዲያዝ በስፔን ታዳጊና ወጣት ቡድኖች ላይ በአጠቃላይ 28 ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ግቦችን አስቆጥሯል። የስፔን ታዋቂ የስፖርት ጋዜጣ ማርካ እ.አ.አ ጥር 23 ቀን 2023 ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን መጫወት ማቀዱን የሚመለከት ዘገባ ይዞ ወጥቷል። ከዜግነቱ ጋር በተያያዘ ያሉ አንዳንድ የአስተደዳር ጉዳዮች በወቅቱ መፍትሄ አግኝተዋል። ይሁንና ኮትዲቯር እ.አ.አ በ2023 ባዘጋጀችው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሞሮኮው አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ከተጫዋቹ ጋር በተደረገ የቅድሚያ ስምምነት ለተጫዋቹ ጥሪ አልተደረገለትም። ዲያዝ እ.አ.አ መጋቢት 10 ቀን 2024 ለሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሀገሪቷ ብሔራዊ መጫወት እንደሚፈልግ በይፋ ማሳወቁን ማርካ በወቅቱ ዘግቧል። ጥያቄውም ተቀባይነት አገኘ። በወቅቱ የሞሮኮ አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ ብሔራዊ ቡድኑ ከአንጎላ እና ሞሪታኒያ ጋር ለነበረበት የወዳጅነት ጨዋታ ለዲያዝ ጥሪ አድርገውለታል። እ.አ.አ መጋቢት 22 ቀን 2024 ሞሮኮ አንጎላን 1 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። እ.አ.አ ጥቅምት 6 ቀን 2024 ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከጋቦን ጋር ባደረገችው ጨዋታ 4 ለ 1 ስታሸንፍ የመጀመሪያ ግቡን ለሞሮኮ ማስቆጠር ቻለ። እ.አ.አ ሕዳር 15 ቀን 2024 ሞሮኮ በማጣሪያው ጋቦንን 5 ለ 1 ስትረታ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል። ከሶስት ቀናት በኋላ ሞሮኮ ከሌሴቶ ጋር ባደረገችው የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ 7 ለ 0 ስታሸንፍ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር በሀገሩ ማልያ የመጀመሪያ ሀትሪኩን ሰርቷል። እ.አ.አ ጥቅምት 2025 ሞሮኮ ራባት ላይ ኮንጎ ሪፐብሊክን 1 ለ 0 በማሸነፍ በስፔን ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተይዞ የነበረውን 15 ተከታታይ ጨዋታዎችን የማሸነፍ ክብረ ወሰን በመስበር ወደ 16 ማድረስ ችላለች። በዚህ ታሪካዊ ጨዋታ ላይ ዲያዝ ተሰልፎ ተጫውቷል። የሞሮኮ ተከታታይ የማሸነፍ ጉዞ 19 ጨዋታዎች ደርሶ የነበረ ሲሆን በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከማሊ ጋር አንድ አቻ ስትለያይ አብቅቷል። ሞሮኮ ለ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በማጣሪያ ብታልፍም አስቀድማ ውድድሩን እንድታዘጋጅ እድል አግኝታ የነበረው ጊኒ በዝግጅት ማነስ ምክንያት በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ከሁለት ዓመት በፊት አዘጋጅነቷ ተነጥቆ ለሞሮኮ ተሰጥቷል። ሞሮኮ የዘንድሮውን ውድድር በደማቅ ሁኔታ እያካሄደች ትገኛለች። በውድድሩ ላይ ጎልተው ከታዩ ተጫዋቾች መካከል ብራሂም ዲያዝ ተጠቃሽ ነው። በአፍሪካ ዋንጫው እስከ አሁን ባደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አምስት ግቦችን አስቆጥሯል። በተሰለፈባቸው በእያንዳዱ ጨዋታዎች ጎሎችን ከመረብ ላይ አሳርፏል። ለሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን በአምስት የአፍሪካ ዋንጫ ተከታታይ ጨዋታዎች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል። ሞሮኮ በሩብ ፍጻሜው ማሊን 2 ለ 0 ስታሸንፍ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጥሯል። ሀገሩ ወደ ግማሽ ፍጻሜ እንድታልፍ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱንም እየመራ ይገኛል። ሞሮኮ በዚሁ ግስጋሴዋ ከቀጠለች ዲያዝ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እና ኮከብ ተጫዋች የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። ሞሮኮ በግማሽ ፍጻሜው ከናይጄሪያ ጋር ረቡዕ ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም በፕሪንስ ሙላይ አብደላ ስታዲየም ታደርጋለች። ዲያዝ በዚህ ጨዋታ ላይ ልዩነት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። አንዳንድ የእግር ኳስ ተንታኞች ብራሂም ዲያዝ እ.አ.አ በ2026 ወጥነት ያለው ብቃት ማሳየት ከቻለ የአፍሪካ ኮከብ ተጫዋችነት ሽልማቱን የሚወስድበት የለም እያሉ ይገኛሉ። ሞሮኳውያን በተጫዋቹ ፍቅር ልባቸው ከንፏል። በየጨዋታው ዲያዝ ዲያዝ እያሉ ከፍተኛ ድጋፍ እና ሙገሳ እየሰጡት ይገኛሉ። እሱም በድንቅ ብቃቱ ምላሽ እየሰጣቸው ነው። በተወለደበት ማላጋ ከተማ የጀመረው የእግር ኳስ ሕይወት በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የበለጠ አብቧል። የሞሮኮው አዲሱ ኮከብ ብራሂም ዲያዝ ቀጣይ የእግር ኳስ ሕይወት በስኬት እና በድል የደመቀ እንደሚሆን ከአሁኑ ድንቅ ብቃቱ ተነስቶ መናገር ይቻላል።