ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል-ተገልጋዮች
Nov 12, 2025 21
ሆሳዕና ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሆሳዕና ማዕከል ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ሥራ መጀመሩ ይታወቃል። የማዕከሉን የሥራ እንቅስቃሴ በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር በስፍራው በመገኘት ተገልጋዮችና የሚመለከታቸውን የሥራ ሃላፊዎች አነጋግሯል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ዳንኤል በየነ፣ አቶ ደስታ ኤርቻዮ እና አቶ ደመቀ ሙሉነህ ፤ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። አገልግሎቱ በአንድ ማዕከል በርካታ ጉዳዮችን ጨርሶ መውጣት ከማስቻሉ ባለፈ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም መሰል የአገልግሎት ማዕከላትን በማስፋት በተገልጋዮች ላይ ሲደርስ የነበረን እንግልት እና የብልሹ አሰራር መንስኤዎችን ማስቀረት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የማዕከሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከበደ ሻሜቦ፤ በማዕከሉ የተለያዩ ተቋማት 20 አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶች እየሰፋ ይሄዳሉ ብለዋል። በማዕከሉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረት እያስቻለ በመሆኑ በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል።
ኢትዮጵያ መድን እና ቤንች ማጂ ቡና በኢትዮጵያ ዋንጫ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፉ
Nov 12, 2025 23
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዋንጫ የሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ጨዋታዎች ዛሬ መካሄድ ጀምረዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን በአማኑኤል ኤርቦ ግብ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ አርቴፊሻል ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው መርሃ ግብር ቤንች ማጂ ቡና ጋሞ ጨንቻን 1 ለ 0 ረቷል። ፅዮን ተስፋዬ ለቤንች ማጂ ቡና ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ መድን እና ቤንች ማጂ ቡና በኢትዮጵያ ዋንጫ የመጨረሻውን 16 የተቀላቀሉ የመጀመሪያ ቡድኖች ሆነዋል። የኢትዮጵያ ዋንጫ ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብር ከሰዓትም ሲቀጥል የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ወላይታ ድቻ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም፣ አርባምንጭ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተመሳሳይ ከቀኑ 9 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ሀዋሳ ከተማን ለመኖሪያ፣ ለቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ለማድረግ ይሰራል-ከንቲባ ጥራቱ በየነ
Nov 12, 2025 40
ሀዋሳ ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ሀዋሳ ከተማን ለመኖሪያ፣ ለቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ከተማ ለማድረግ ከፍ ያለ ራዕይ በመሰነቅ ይሰራል ሲሉ አዲሱ የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 2ኛ ዙር አስረኛ ዓመት 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ጥራቱ በየነን የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል። አዲሱ የከተማዋ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ለምክር ቤቱ አባላት ባደረጉት ንግግር እንዳሉት፤ ከተሞችን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በአዲስ እሳቤ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በሀዋሳ ከተማም እየተከናወነ ነው። በከተማዋ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ሀዋሳን ከአዲስ አበባ በመቀጠል በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ለመኖሪያ፣ ቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ለማድረግ ከፍ ያለ ራዕይ ሰንቀን ያለመዘናጋት እንሰራለን ብለዋል። ለዚህ ራዕይ ስኬት የመንግስት፣ የነዋሪውና የግል ሴክተሩ የተቀናጀና የተናበበ ስራ ወሳኝ መሆኑን ያነሱት አቶ ጥራቱ ሁሉንም ማህበረሰብ በማሳተፍ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የሀዋሳን በፍቅር ተከባብሮና ተደጋግፈው በወንድማማችነትና በአንድነት የሚኖሩባት የፍቅር ከተማነቷን ለማስቀጠል ጠንክረው እንደሚሰሩም ጠቁመዋል። የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ አጠናክሮ በማስቀጠል ለነዋሪዎቿ ምቹ ከተማ እንድትሆን ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሰላምና ጸጥታ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ መስፈርቶችንና የከተማ ፕላንን መሰረት ባደረገ መልኩ በከተማዋ መሰረተ ልማቶችንና አረንጓዴ ስፍራዎችን የማስፋፋት ሥራ እንደሚሰራ ገልጸው፣ የሀዋሳ ሐይቅን ከብክለት የመጠበቅና የታቦር ተራራን ልማት በማፋጠን ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራ ይሰራል ብለዋል። የቆሻሻ አወጋገድና አያያዝን ከማዘመን ባለፈ ዘላቂ የከተማ ልማትን ተግባራዊ በማድረግ ንጹህና ምቹ ሀዋሳን ለመፍጠርም ትኩረት እንደሚሰጥ አመልክተዋል። ሀዋሳ ከተማን ተመራጭ የቱሪዝምና የኮንፈረንስ መዳረሻ ለማድረግም ደረጃቸውን የጠበቁ የቱሪስት መዳረሻዎችን ቁጥር ከማሳደግ ባለፈ የከተማዋን የቱሪስት ሀብቶች ለማስተዋወቅ በትኩረት እንደሚሰራም አስታውቀዋል። ከንቲባው በከተማዋ የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የተጀመሩ የከተማ ግብርና የሌማት ትሩፋት መርሀግብሮች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በስራ ዕድል ፈጠራ ለግሉ፤ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ሴቶች ወጣቶችና የተለያዩ ወገኖች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ የስራ አጥነትን ጫና ለማቃለል እንደሚሰራም አቶ ጥራቱ አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ የቀረበለትን የአቶ ጥራቱ በየነን የከንቲባነት ሹመት በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ በማጽደቅ ጉባኤውን አጠናቋል።
መፍጠር፣ መፍጠን እና በጥራት መሥራት የሁልጊዜም የስራ መመሪያችን ሊሆን ይገባል-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Nov 12, 2025 27
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦መፍጠር፣ መፍጠን እና በጥራት መሥራት የሁልጊዜም የስራ መመሪያችን ሊሆን ይገባል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በሰሜን ሸዋ ዞን በደብረ ብርሃን ከተማ በነበራቸው ቆይታ የመኪና መገጣጠሚያ እንዲሁም የብርጭቆና የጠርሙስ ማምረቻዎችን መመልከታቸውን አስታውቀዋል። በቆይታቸው የተመለከቷቸው ፋብሪካዎች የሀገር ውስጥ ግብዓትን በመጠቀምና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬን እያዳኑ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከብየዳ ጀምሮ ትላልቅ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶችን እየገጣጠመ የሚገኘው የፊቤላ ኢንዱስትሪያል መኪና መገጣጠሚያ በቀን 12 መኪና ማምረት የሚያስችል አቅም እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡ መገጣጠሚያው በቅርቡ ያስጀመረው አዲስ የቀለም መቀቢያ በርካታ ቀናትን ይወስዱ የነበሩ ስራዎችን በሰዓታት ለማከናወን አስችሏልም ነው ያሉት፡፡ በአንድ ቀን 450 ሺህ ጠርሙስ የሚያመርተው ዴዴ ቦትል የብርጭቆና የጠርሙስ ማምረቻ ደግሞ 86 በመቶ የሚሆነውን ግብዓት ከሀገር ውስጥ ተጠቅሞ ለበርካታ የመጠጥ እና የመድሃኒት ፋብሪካዎች ጥቅም የሚሰጡ ጠርሙሶች እንደሚያመርት አስታውቀዋል፡፡ በኢንዱስትሪዎቹ የተመለከትናቸው አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴዎች በየዘርፉ በጥራትና በፍጥነት በመትጋት የምናልመውን እድገት በአጠረ ጊዜ እንደምናሳካ የሚያሳዩ ናቸው ሲሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
እስካሁን ከ2ሺህ 96 ቶን በላይ እሸት ቡና ተሰብስቧል
Nov 12, 2025 28
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፡- በ2018 በጀት ዓመት እስካሁን በተሰራ ስራ 2ሺህ 96 ነጥብ 37 ቶን እሸት ቡና መሰብሰቡን የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በበጀት ዓመቱ 7ሺህ 880 ቶን እሸት ቡና ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን የመምሪያው ምክትል እና የቡናና ቅመማቅመም ዘርፍ ኃላፊ ከአብነህ ተስፋዬ ለኢዜአ ገልጸዋል። በዚህም እስካሁን 2ሺህ 96 ነጥብ 37 ቶን እሸት ቡና መሰብሰቡን ገልጸው፤ አሁንም ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚላክ ቡና በተለያዩ ግብይቶች እየተሰበሰበ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሌላ በኩል 8 ነጥብ 9 ቶን የታጠበ እንዲሁም 343 ነጥብ 5 ቶን ያልታጠበ የተቀሸረ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ መላኩን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም ብክነት እንዳይኖር የደረሰ ቡና ከስር ከስር በቅንጅት እየተሰበሰበ መሆኑንም አመላክተዋል።
ፖለቲካ
የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማፅናት አግዟል
Nov 12, 2025 36
ድሬዳዋ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ጠንካራ ሀገረ መንግስት እንዲገነባ እያገዘ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፈትህያ አደን ተናገሩ። በድሬዳዋ 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ህብረ ብሔራዊ አንድነትንና ልማትን በሚያፀኑ ሁነቶች ከዛሬ ጀምሮ መከበር ጀምሯል። የአስተዳደሩ ምክርቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ ፈትህያ አደን እንደተናገሩት፤ ባለፉት ዓመታት የተከበረው የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በማፅናት የሀገረ መንግስት ግንባታውን እያጠናከረ ይገኛል። በተለይም በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በፍቅር፣ በአንድነትና በተጋመደ ኢትዮጵያዊ መከባበር በሚኖሩባት ድሬዳዋ ዘላቂ ሰላምና ህብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲጠናከር አበርክቶው የጎላ መሆኑን አንስተዋል። "ዴሞክራሲያዊ መግባባት-ለህብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ ዘንድሮ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረው በዓል በህብረ ብሔራዊ አንድነት፣ በቆራጥ ተሳትፎና ብሔራዊ ጀግንነት የህዳሴውን ግድብ ባጠናቀቅንበት ወቅት መከበሩ ድርብ በዓል ያደርገዋል ብለዋል። በዓሉ ይህን ተስፋ ሰጪ የልማት ጉዞ እና ድህነትን ለማስወገድ የተጀመሩና ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በሚያስችሉ ሁነቶች በደመቀ መንገድ በአስተዳደሩ እንደሚከበርም አስታውቀዋል ። በተለይም የገጠርና የከተማ ወረዳዎች፣ ተቋማት እና ነዋሪዎችን ባሳተፈ መንገድ በውይይት፣ በልማት ስራዎች እና በስፖርታዊ ውድድሮች ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ይከበራል ብለዋል። በተጨማሪም የኢፌዴሪ ህገ መንግስት መሠረታዊ ዕውቀቶችን በሚያስጨብጡ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኮች እንደሚኖሩም በማስታወስ ። የዘንድሮ 20ኛው የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል እንደ አገር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ይከበራል።
የዘንድሮው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል
Nov 12, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የኢትዮጵያን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር የፌደሬሽን ምክር ቤት አስታወቀ። በፌደሬሽን ምክር ቤት የመንግስታት ግንኙነት፣ የዴሞክራሲያዊ አንድነትና የሕገ መንግስት አስተምህሮ ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ ባንቺይርጋ መለሰ 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን አከባበር አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል። 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኀብረብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ሀሳብ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ይከበራል። ጸሐፊዋ በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት አመታት የተከበሩት በዓላት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ትሩፋቶች ማስገኘታቸውን ገልጸዋል። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የኢትዮጵያን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት በሚያጠናክሩ ተግባራት እንደሚከበርም አንስተዋል። በቀኑ ሀገራዊ መግባባት እንዲፈጠር፣ ህብረ ብሔራዊነት እንዲጎለብትና ፌደራላዊ አስተሳሰብ እና እሴቶችን የሚያሳድጉ ስራዎች እንደሚከናወኑም አመላክተዋል። በዓሉ ከህዳር 1 ጀምሮ በሁሉም ክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች፣ የትምህርት ተቋማት እንዲሁም በኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ሲከበር ቆይቶ ማጠቃለያው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ይሆናል ነው ያሉት። በዚህም ህዳር 25 "የወንድማማችነት ቀን" በሚል የሚከበር ሲሆን እለቱ አብሮነትን የሚያጎለብቱ ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል። ህዳር 26 "የአብሮነት ቀን" በሚል የሚከበር ሲሆን የብሔር ብሔረሰቦች ልዑካን ሆሳዕና የሚገቡበት ቀን መሆኑን ተናግረዋል። ህዳር 27 "የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀን" በሚል የሚከበር ሲሆን በእለቱ የክልሉ ጸጋዎች የሚተዋወቁበት መሆኑን አንስተዋል። ህዳር 28 "የምክክር ቀን" በሚል የሚከበር ሲሆን በፓናል ውይይቶች እንደሚከበር ጠቁመዋል። ህዳር 29 "የኢትዮጵያውያን ቀን" በሚል ዋናው በዓል የሚከበርበት መሆኑን የቋሚ ኮሚቴው ጸሐፊዋ አመላክተዋል።
በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራሮች በፈጠራና ፍጥነት ለላቀ አፈፃፀም ዝግጁ ሊሆኑ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
Nov 12, 2025 52
ቦንጋ፤ ህዳር 03/2018(ኢዜአ)፦ በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራሮች በፈጠራና ፍጥነት ለላቀ አፈፃፀም ዝግጁ ሊሆኑ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በክልሉ በበጀት ዓመቱ በልዩ ትኩረትና ንቅናቄ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ በማተኮር የክልሉ አመራሮች የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራሮች በፈጠራና ፍጥነት ለላቀ አፈፃፀም ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል። የተጀመሩ እና በእቅድ የተያዙ የልማት ስራዎችን ለማሳካት መትጋት፣ ለውጤት ማብቃትና ማሳካት ያስፈልጋል ሲሉም አስገንዝበዋል። ለዚህም በየደረጃው ያሉ አመራሮች ቁርጠኝነት፣ የመፈፀም አቅምና ለህዝብ አገልግሎት የላቀ ዝግጁነት ሊኖራቸው እንደሚገባ አፅዕኖት ሰጥተዋል። በክልሉ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን ለማሳካትና የህዝቡን የልማትና የአገልግሎት ፍላጎቶች መሰረት አድርጎ ምላሽ ለመስጠት የተቀናጀ ጥረትና የስራ ትጋት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት በመንግሥት የተቀመጡ አቅጣጫዎችን በመከተል መተግበር የግድ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራሮች በፈጠራና ፍጥነት ለላቀ አፈፃፀም ዝግጁ ሊሆኑ ይገባል በማለትም አሳስበዋል። በተለይም በግብርናው፣ በኢንዱስትሪ እና በቱሪዝም ዘርፎች በክልሉ ያሉ እምቅ ሃብቶችን አሰናስሎ በማልማት ምርታማነትን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የወረዳ እንዲሁም የከተማ አስተዳደር አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ኢትዮጵያ በዲሞክራሲ ተቋማት ላይ ወሳኝ ሪፎርም በማከናወን በኢጋድ ቀጣና ሰላምና ደህንነት እንዲሰፍን ሚናዋን እየተወጣች ነው
Nov 12, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በዲሞክራሲ ተቋማት ላይ ወሳኝ ሪፎርም በማከናወን በኢጋድ ቀጣና ሰላምና ደህንነት እንዲሰፍን ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። 3ኛው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን /ኢጋድ/ ሀገራት ፎረም "ሰላምና ደህንነትን ለማጠናከር የብሔራዊ የዲሞክራሲ ተቋማት ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢጋድ ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር የሚያደርገው ጥረት የሚደነቅ ነው። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከራሷ አልፎ በቀጣናው ሰላምና ደህንነትን ማስፈን የሚያስችል ተቋማዊ ሪፎርም ማድረጓን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሰላም ላበረከቱት አስተዋፅኦ የሰላም ኖቤል ሽልማት ማግኘታቸውን ገልጸው፣ በዲሞክራሲ ተቋማት ሪፎርም ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል። ሰላም የዘላቂ ተቋማት ውጤት መሆኑን የገለጹት ቢቂላ (ዶ/ር)፤ የለውጡ መንግስት በጸጥታ አካላት፣ በሰብዓዊ መብት ተቋማት፣ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ በፍትሕ አካላትና በሌሎች የዲሞክራሲ ተቋማት ላይ ሪፎርም አድርጓል ብለዋል። ኢትዮጵያ እንደ ኢጋድ አባል ሀገር የዲሞክራሲ ተቋማትን በማጠናከር መልካም አስተዳደርን በማስፈን ለቀጣናው ሰላምና ደህንነት ገንቢ ሚና መወጣቷን ገልጸዋል። ብዝሀ የዲሞክራሲ ተቋማትን በማሻሻልና አዳዲስ ተቋማትን በመፍጠር ዕውቀት መር የመንግስት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባቱን አንስተዋል። ሰላማዊ የፖለቲካ ሽግግር ስርዓት ማንበር፣ ተጠያቂነት ያለበት የጸጥታና ደህንነት፣ ሙስናን መከላከል የሚያስችሉ ተቋማት ተገንብተዋል ብለዋል። ይሄውም ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ጥረት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። የኢጋድ ሰላምና ደህንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ፤ የኢጋድ ቀጣና እንደ ሽብርተኝነት፣ ግጭት፣ የአየር ንብረት ለውጥና በርካታ ፈተናዎች ያሉበት መሆኑን ተናግረዋል። ዲሞክራሲ ዜጎች በነፃነት መንቀሳቀስ እንዲችሉ፣ ለሰብዓዊ መብት መከበርና ለፖለቲካ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍ ያለ ዋጋ አለው ብለዋል። ነፃና ገለልተኛ ምርጫ ማካሄድ፣ የሲቪል ማህበራትን ተሳትፎ ማጠናከር አካታች የግጭት አፈታት ስርዓትን ማስፈን እና ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። ምክክርና የሽግግር ፍትህ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት መጎልበት ወሳኝ መሆናቸውን በማንሳት፣ የሰብዓዊ መብት ጥበቃና የህግ የበላይነትን በማስከበር ገቢራዊ ማድረግ ይገባል ነው ያሉት። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዘሪሁን አበበ፤ የኢጋድ ቀጣና የጸጥታ ጉዳይ ተለዋዋጭ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቀጣናው ሰላምና ደህንነትን ለማስፈን መልካም አስተዳደርን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን በመግለፅ፤ ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ እንደ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽንና መሰል የዲሞክራሲ ተቋማትን እያጠናከረች መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህም ባሻገር በኢጋድ ቀጣና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ሀገራት የተቋማት አቅም ማጠናከር እንዳለባችው ታምናለች ብለዋል። በቀጣናው የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ሰላምና ደህንነት መስፈን እንዳለበት ጠቅሰው፣ ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በትብብር መስራቷን አጠናክሮ እንደምትቀጥል ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የስዊድን ኤምባሲ ሁለተኛ ጸሀፊ ኤግነስ ጌጀር ፋራህ በበኩላቸው፤ ኢጋድ የቀጣናውን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ የዲሞክራሲ ተቋማትን ሚና ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያዘጋጀው መድረክ ትክክለኛና ወቅታዊ መሆኑን ተናግረዋል። በኢጋድ ቀጣና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን መልካም አስተዳደርን ማንበር ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፣ ስዊድን ለቀጣናው ሰላም በቅርበት ትሰራለች ብለዋል።
ምክር ቤቱ አቶ ጥራቱ በየነን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አድርጎ ሾመ
Nov 12, 2025 61
ሀዋሳ ፤ ሕዳር 3/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ጥራቱ በየነን የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾመ፡፡ ምክር ቤቱ በሁለተኛ ዙር አስረኛ ዓመት የስራ ዘመን ሁለተኛ አስቸኳይ ጉባኤው ነው አቶ ጥራቱን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አድርጎ የሾመው። በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ አቅራቢነት ምክር ቤቱ ሹመቱን በሙሉ ድምጽ አፅድቋል። የከተማዋ ከንቲባ በመሆን የተሾሙት አቶ ጥራቱ በየነ፤ የሀዋሳ ከተማን የወደፊት ልማት አጠናክሮ በማስቀጠል ለነዋሪዎችና ለእንግዶች ምቹ ለማድረግ መላውን ሕብረተሰብ በማሳተፍ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ከተማዋ ያላትን ሰላም በማፅናት የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል ብሎም የልማት፣ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የኑሮ ውድነትንና የስራ አጥነት ችግሮችን ለመፍታት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ-ብሔራዊ እውነተኛ የፌዴራሊዝም ስርዓት እንዲገነባ ጉልህ ሚና እያበረከተ ነው
Nov 11, 2025 201
አዲስ አበባ፤ ህዳር 2/2018(ኢዜአ)፦ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የተከበሩ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲጠናከርና እውነተኛ የፌዴራሊዝም ስርዓት እንዲገነባ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኀብረ-ብሔራዊ አንድነት’’ በሚል መሪ ሀሳብ የሚከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን መሪ ሃሳብ የትንተና መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በዓሉ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እርስ በርስ እንዲተዋወቁ፣ መሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት እንዲነቃቃ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። የሀገረ መንግስት ግንባታው ስኬታማ እንዲሆን የሚያስችሉ ስራዎች በመንግስት በኩል በትኩረት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ኅብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲጠናከር እና እውነተኛ የፌዴራሊዝም ስርዓት እንዲገነባ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን ጠቁመዋል። በዓሉ በሚከበርበት ወቅት የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበበት ስለመሆኑ እንደሚታይበት ተናግረዋል። በዓሉን ስኬታማ ለማድረግም በርካታ ዝግጅቶች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፤ ኅብረ ብሔራዊነትን ይበልጥ በሚያጠናክርና አብሮነትን በሚያጸና መልኩ እንደሚከበር ገልጸዋል፡፡ በሚኒስትር ማዕረግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ እናትዓለም መለሰ በበኩላቸው፤ በዓሉ ትልቅ የሀሳብ ገበያና የአንድነት ማጽኛ መሆኑን ተናግረዋል። የተመረጠው መሪ ሐሳብም ኢትዮጵያ ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገልጽ መሆኑን ጠቁመዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ፤ የተመረጠው መሪ ሀሳብ የኢትዮጵያን ሁኔታ በተጨባጥ የሚያሳይ መሆኑን አንስተው፤ በሀገር ደረጃ የተገኙ ውጤቶችን ማስረጽ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በዓሉ በህዝቦች መካከል ያለው ግንኙነት እንዲጠናከር የሚያግዝ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አለማየሁ ባውዲ ናቸው። የተመረጠው መሪ ሀሳብም ከበዓል ተሻጋሪ ሀሳብ የያዘ መሆኑን ገልጸው፤ መገናኛ ብዙሃንም እንደ መሪ ሀሳብ ሁሉ ከፍ ያለ የዘገባ ስራ መስራት እንዳለባቸው አመልክተዋል። በመድረኩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ጨምሮ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዘሀራ ኡመድ፣ በሚኒስትር ማዕረግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ እናትአለም መለሰ፣ የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አመራር አባላት፣ የክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች አፈ-ጉባኤዎችና የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙሃን አመራር አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።
በክልሉ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል- ምክር ቤቱ
Nov 11, 2025 148
ባሕርዳር ፤ሕዳር 2/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ ማክበር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት አስታወቀ። የምክር ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ከፍያለው ማለፉ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ በዓሉ በየዓመቱ ሁሉም ክልሎች በአንድ ላይ በመሰባሰብ በተለያዩ ዝግጅቶች ሲያከብሩት እንደቆዩ አውስተዋል። ይህም የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ትስስር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረ ፣ በመተማመንና እኩልነት ላይ የተመሰረተ ሀገራዊ አንድነት እየጎለበተ እንዲመጣ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አንስተዋል። በዚህም የተገኘውን ውጤት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ክልሉ የድርሻውን ሲወጣ እንደቆዩ አመልክተው፤ የዘንድሮውም የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በሕዳር ወር በተለያዩ ዝግጅቶች ለማክበር በዐቢይ ኮሚቴ የሚመራ ስድስት ንዑሳን ኮሚቴዎች ተዋቅረው ስራ ጀምረዋል ብለዋል። ዓላማውም በዓሉ ሲከበር በብዝሃነት ላይ የተመሰረተ አንድነት ስር እንዲሰድና እንዲዳብር በማድረግ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ ለማጠናከር መሆኑን አስረድተዋል። በዓሉ የፌደራሊዝምና የሕገ መንግስት አስተምህሮዎችን በማጠናከር የክልሉና የሀገሪቱን ገጽታ በመገንባት ላይ በማተኮር እንደሚከበር ተናግረዋል። በዚህም በወሩ ያሉ አራት ሳምንታትን የአስተምሮ ሳምንት፣ የበጎ ፈቃድ፣ የሕብረብሔራዊ አንድነትና ግንኙነት ማጠናከሪያና የማጠቃለያ ሳምንት በሚል ከእነዚህ ስያሜዎች ጋር የተያያዙ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል። የዘንድሮውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በክልሉ ሕዳር 5/2018 ዓ.ም በይፋ የሚጀመር ሲሆን፤ ሕዳር 24 የማጠናቀቂያ መረሃ ግብር እንደሚካሄድ በመግለጫው ተመላክቷል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ለሚከበረው በዓልም ክልሉን ወክለው የሚሳተፉ የባሕል ቡድን አባላትና ሌሎችም እንግዶች እንደሚሳተፉ ተጠቁሟል።
ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የእውነተኛ ፌደራሊዝም ስርዓት ማሳያ መድረክ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል
Nov 11, 2025 173
አዲስ አበባ፤ሕዳር 2/2018 (ኢዜአ)፡-ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የእውነተኛ ፌደራሊዝም ስርዓት ማሳያ መድረክ ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኀብረ-ብሔራዊ አንድነት’’ በሚል መሪ ቃል የሚከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በመሪ ሃሳብ የትንተና መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣የፌደሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዘሀራ ኡመድ፣ በሚኒስትር ማዕረግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሀላፊ እናትአለም መለሰ፣የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች፣የክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች አፈ-ጉባኤዎችና የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙሃን አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ባለፉት 19 ዓመታት ሲከበር በቆየው በዓል አብሮነትን የሚያጎለብቱና አንድነትን የሚያጠናክሩ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። በዓሉ ሕዝቦች እርስ በርስ እንዲተዋወቁ፣ መሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት እንዲነቃቃ የጎላ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። ባለፉት የለውጥ አመታት ቀኑ በልዩ ሁኔታ እየተከበረ እንደሚገኝና የእውነተኛ ፌደራሊዝም ስርዓት ማሳያ መድረክ ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ዘንድሮ የሚከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሚደረግ የማጠቃለያ መርሃ-ግብር ፍፃሜውን እንደሚያገኝ ተናግረዋል። ክብረ በዓሉን የተሳካ ለማድረግም በርካታ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመው፤ በዓሉ ህብረ ብሔራዊነት በሚያጠናክርና አንድነትን በሚያጎለብት አግባብ እንደሚከበር አመላክተዋል። ዘንድሮ እንደሀገር በርካታ ስራዎች የሚሰሩበት አመት በመሆኑ በዓሉን የተለየ እንደሚያደርገው ጠቅሰው፥ መገናኛ ብዙሀን የህዝቦችን አንድነት እና ትስስር የሚያጠናክሩ ተግባራትን እንዲያከናውኑ ጥሪ አቅርበዋል። በፌደሬሽን ምክር ቤት የመንግስታት ግንኙነት፣የዴሞክራሲያዊ አንድነት እና የህገ መንግስት አስተምህሮ ቋሚ ኮሚቴ ጸሀፊ ባንቺይርጋ መለሰ በዓሉ በየአመቱ ህዳር 29 በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በበዓሉ ብሔር፣ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ባህላቸውን እንዲያስተዋውቁ እና ህብረ ብሔራዊነትን ለማጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። የዘንድሮው በዓል ብሔር፣ብሔረሰቦች እና ህዝቦች አሻራቸውን ያሳረፉበትና የበሳል የአመራር ውጤት የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ የተመረቀበት ዓመት መሆኑ የተለየ ያደርገዋል ብለዋል። በተጨማሪም ከመቸውም ጊዜ በላይ መጻኢ እድላችንን የምንወስንበት በመሆኑ በዓሉ በተለየ ሁኔታ እንደሚከበር ጠቁመዋል።
ፖለቲካ
የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማፅናት አግዟል
Nov 12, 2025 36
ድሬዳዋ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ጠንካራ ሀገረ መንግስት እንዲገነባ እያገዘ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፈትህያ አደን ተናገሩ። በድሬዳዋ 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ህብረ ብሔራዊ አንድነትንና ልማትን በሚያፀኑ ሁነቶች ከዛሬ ጀምሮ መከበር ጀምሯል። የአስተዳደሩ ምክርቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ ፈትህያ አደን እንደተናገሩት፤ ባለፉት ዓመታት የተከበረው የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በማፅናት የሀገረ መንግስት ግንባታውን እያጠናከረ ይገኛል። በተለይም በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በፍቅር፣ በአንድነትና በተጋመደ ኢትዮጵያዊ መከባበር በሚኖሩባት ድሬዳዋ ዘላቂ ሰላምና ህብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲጠናከር አበርክቶው የጎላ መሆኑን አንስተዋል። "ዴሞክራሲያዊ መግባባት-ለህብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ ዘንድሮ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረው በዓል በህብረ ብሔራዊ አንድነት፣ በቆራጥ ተሳትፎና ብሔራዊ ጀግንነት የህዳሴውን ግድብ ባጠናቀቅንበት ወቅት መከበሩ ድርብ በዓል ያደርገዋል ብለዋል። በዓሉ ይህን ተስፋ ሰጪ የልማት ጉዞ እና ድህነትን ለማስወገድ የተጀመሩና ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በሚያስችሉ ሁነቶች በደመቀ መንገድ በአስተዳደሩ እንደሚከበርም አስታውቀዋል ። በተለይም የገጠርና የከተማ ወረዳዎች፣ ተቋማት እና ነዋሪዎችን ባሳተፈ መንገድ በውይይት፣ በልማት ስራዎች እና በስፖርታዊ ውድድሮች ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ይከበራል ብለዋል። በተጨማሪም የኢፌዴሪ ህገ መንግስት መሠረታዊ ዕውቀቶችን በሚያስጨብጡ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኮች እንደሚኖሩም በማስታወስ ። የዘንድሮ 20ኛው የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል እንደ አገር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ይከበራል።
የዘንድሮው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል
Nov 12, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የኢትዮጵያን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር የፌደሬሽን ምክር ቤት አስታወቀ። በፌደሬሽን ምክር ቤት የመንግስታት ግንኙነት፣ የዴሞክራሲያዊ አንድነትና የሕገ መንግስት አስተምህሮ ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ ባንቺይርጋ መለሰ 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን አከባበር አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል። 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኀብረብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ሀሳብ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ይከበራል። ጸሐፊዋ በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት አመታት የተከበሩት በዓላት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ትሩፋቶች ማስገኘታቸውን ገልጸዋል። 20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የኢትዮጵያን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት በሚያጠናክሩ ተግባራት እንደሚከበርም አንስተዋል። በቀኑ ሀገራዊ መግባባት እንዲፈጠር፣ ህብረ ብሔራዊነት እንዲጎለብትና ፌደራላዊ አስተሳሰብ እና እሴቶችን የሚያሳድጉ ስራዎች እንደሚከናወኑም አመላክተዋል። በዓሉ ከህዳር 1 ጀምሮ በሁሉም ክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች፣ የትምህርት ተቋማት እንዲሁም በኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ሲከበር ቆይቶ ማጠቃለያው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ይሆናል ነው ያሉት። በዚህም ህዳር 25 "የወንድማማችነት ቀን" በሚል የሚከበር ሲሆን እለቱ አብሮነትን የሚያጎለብቱ ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል። ህዳር 26 "የአብሮነት ቀን" በሚል የሚከበር ሲሆን የብሔር ብሔረሰቦች ልዑካን ሆሳዕና የሚገቡበት ቀን መሆኑን ተናግረዋል። ህዳር 27 "የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀን" በሚል የሚከበር ሲሆን በእለቱ የክልሉ ጸጋዎች የሚተዋወቁበት መሆኑን አንስተዋል። ህዳር 28 "የምክክር ቀን" በሚል የሚከበር ሲሆን በፓናል ውይይቶች እንደሚከበር ጠቁመዋል። ህዳር 29 "የኢትዮጵያውያን ቀን" በሚል ዋናው በዓል የሚከበርበት መሆኑን የቋሚ ኮሚቴው ጸሐፊዋ አመላክተዋል።
በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራሮች በፈጠራና ፍጥነት ለላቀ አፈፃፀም ዝግጁ ሊሆኑ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
Nov 12, 2025 52
ቦንጋ፤ ህዳር 03/2018(ኢዜአ)፦ በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራሮች በፈጠራና ፍጥነት ለላቀ አፈፃፀም ዝግጁ ሊሆኑ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በክልሉ በበጀት ዓመቱ በልዩ ትኩረትና ንቅናቄ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ በማተኮር የክልሉ አመራሮች የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራሮች በፈጠራና ፍጥነት ለላቀ አፈፃፀም ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል። የተጀመሩ እና በእቅድ የተያዙ የልማት ስራዎችን ለማሳካት መትጋት፣ ለውጤት ማብቃትና ማሳካት ያስፈልጋል ሲሉም አስገንዝበዋል። ለዚህም በየደረጃው ያሉ አመራሮች ቁርጠኝነት፣ የመፈፀም አቅምና ለህዝብ አገልግሎት የላቀ ዝግጁነት ሊኖራቸው እንደሚገባ አፅዕኖት ሰጥተዋል። በክልሉ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን ለማሳካትና የህዝቡን የልማትና የአገልግሎት ፍላጎቶች መሰረት አድርጎ ምላሽ ለመስጠት የተቀናጀ ጥረትና የስራ ትጋት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት በመንግሥት የተቀመጡ አቅጣጫዎችን በመከተል መተግበር የግድ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራሮች በፈጠራና ፍጥነት ለላቀ አፈፃፀም ዝግጁ ሊሆኑ ይገባል በማለትም አሳስበዋል። በተለይም በግብርናው፣ በኢንዱስትሪ እና በቱሪዝም ዘርፎች በክልሉ ያሉ እምቅ ሃብቶችን አሰናስሎ በማልማት ምርታማነትን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ርእሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የወረዳ እንዲሁም የከተማ አስተዳደር አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ኢትዮጵያ በዲሞክራሲ ተቋማት ላይ ወሳኝ ሪፎርም በማከናወን በኢጋድ ቀጣና ሰላምና ደህንነት እንዲሰፍን ሚናዋን እየተወጣች ነው
Nov 12, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በዲሞክራሲ ተቋማት ላይ ወሳኝ ሪፎርም በማከናወን በኢጋድ ቀጣና ሰላምና ደህንነት እንዲሰፍን ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ። 3ኛው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን /ኢጋድ/ ሀገራት ፎረም "ሰላምና ደህንነትን ለማጠናከር የብሔራዊ የዲሞክራሲ ተቋማት ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ኢጋድ ቀጣናዊ ትብብርን ለማጠናከር የሚያደርገው ጥረት የሚደነቅ ነው። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከራሷ አልፎ በቀጣናው ሰላምና ደህንነትን ማስፈን የሚያስችል ተቋማዊ ሪፎርም ማድረጓን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሰላም ላበረከቱት አስተዋፅኦ የሰላም ኖቤል ሽልማት ማግኘታቸውን ገልጸው፣ በዲሞክራሲ ተቋማት ሪፎርም ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል። ሰላም የዘላቂ ተቋማት ውጤት መሆኑን የገለጹት ቢቂላ (ዶ/ር)፤ የለውጡ መንግስት በጸጥታ አካላት፣ በሰብዓዊ መብት ተቋማት፣ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ በፍትሕ አካላትና በሌሎች የዲሞክራሲ ተቋማት ላይ ሪፎርም አድርጓል ብለዋል። ኢትዮጵያ እንደ ኢጋድ አባል ሀገር የዲሞክራሲ ተቋማትን በማጠናከር መልካም አስተዳደርን በማስፈን ለቀጣናው ሰላምና ደህንነት ገንቢ ሚና መወጣቷን ገልጸዋል። ብዝሀ የዲሞክራሲ ተቋማትን በማሻሻልና አዳዲስ ተቋማትን በመፍጠር ዕውቀት መር የመንግስት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባቱን አንስተዋል። ሰላማዊ የፖለቲካ ሽግግር ስርዓት ማንበር፣ ተጠያቂነት ያለበት የጸጥታና ደህንነት፣ ሙስናን መከላከል የሚያስችሉ ተቋማት ተገንብተዋል ብለዋል። ይሄውም ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ጥረት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። የኢጋድ ሰላምና ደህንነት ዘርፍ ዳይሬክተር ኮማንደር አበበ ሙሉነህ፤ የኢጋድ ቀጣና እንደ ሽብርተኝነት፣ ግጭት፣ የአየር ንብረት ለውጥና በርካታ ፈተናዎች ያሉበት መሆኑን ተናግረዋል። ዲሞክራሲ ዜጎች በነፃነት መንቀሳቀስ እንዲችሉ፣ ለሰብዓዊ መብት መከበርና ለፖለቲካ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍ ያለ ዋጋ አለው ብለዋል። ነፃና ገለልተኛ ምርጫ ማካሄድ፣ የሲቪል ማህበራትን ተሳትፎ ማጠናከር አካታች የግጭት አፈታት ስርዓትን ማስፈን እና ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። ምክክርና የሽግግር ፍትህ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት መጎልበት ወሳኝ መሆናቸውን በማንሳት፣ የሰብዓዊ መብት ጥበቃና የህግ የበላይነትን በማስከበር ገቢራዊ ማድረግ ይገባል ነው ያሉት። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዘሪሁን አበበ፤ የኢጋድ ቀጣና የጸጥታ ጉዳይ ተለዋዋጭ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቀጣናው ሰላምና ደህንነትን ለማስፈን መልካም አስተዳደርን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን በመግለፅ፤ ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ እንደ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽንና መሰል የዲሞክራሲ ተቋማትን እያጠናከረች መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህም ባሻገር በኢጋድ ቀጣና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ሀገራት የተቋማት አቅም ማጠናከር እንዳለባችው ታምናለች ብለዋል። በቀጣናው የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ሰላምና ደህንነት መስፈን እንዳለበት ጠቅሰው፣ ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያ በትብብር መስራቷን አጠናክሮ እንደምትቀጥል ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የስዊድን ኤምባሲ ሁለተኛ ጸሀፊ ኤግነስ ጌጀር ፋራህ በበኩላቸው፤ ኢጋድ የቀጣናውን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ የዲሞክራሲ ተቋማትን ሚና ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያዘጋጀው መድረክ ትክክለኛና ወቅታዊ መሆኑን ተናግረዋል። በኢጋድ ቀጣና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን መልካም አስተዳደርን ማንበር ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፣ ስዊድን ለቀጣናው ሰላም በቅርበት ትሰራለች ብለዋል።
ምክር ቤቱ አቶ ጥራቱ በየነን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አድርጎ ሾመ
Nov 12, 2025 61
ሀዋሳ ፤ ሕዳር 3/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ጥራቱ በየነን የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾመ፡፡ ምክር ቤቱ በሁለተኛ ዙር አስረኛ ዓመት የስራ ዘመን ሁለተኛ አስቸኳይ ጉባኤው ነው አቶ ጥራቱን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አድርጎ የሾመው። በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ አቅራቢነት ምክር ቤቱ ሹመቱን በሙሉ ድምጽ አፅድቋል። የከተማዋ ከንቲባ በመሆን የተሾሙት አቶ ጥራቱ በየነ፤ የሀዋሳ ከተማን የወደፊት ልማት አጠናክሮ በማስቀጠል ለነዋሪዎችና ለእንግዶች ምቹ ለማድረግ መላውን ሕብረተሰብ በማሳተፍ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ከተማዋ ያላትን ሰላም በማፅናት የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል ብሎም የልማት፣ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የኑሮ ውድነትንና የስራ አጥነት ችግሮችን ለመፍታት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ-ብሔራዊ እውነተኛ የፌዴራሊዝም ስርዓት እንዲገነባ ጉልህ ሚና እያበረከተ ነው
Nov 11, 2025 201
አዲስ አበባ፤ ህዳር 2/2018(ኢዜአ)፦ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የተከበሩ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲጠናከርና እውነተኛ የፌዴራሊዝም ስርዓት እንዲገነባ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኀብረ-ብሔራዊ አንድነት’’ በሚል መሪ ሀሳብ የሚከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን መሪ ሃሳብ የትንተና መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በዓሉ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እርስ በርስ እንዲተዋወቁ፣ መሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት እንዲነቃቃ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። የሀገረ መንግስት ግንባታው ስኬታማ እንዲሆን የሚያስችሉ ስራዎች በመንግስት በኩል በትኩረት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ኅብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲጠናከር እና እውነተኛ የፌዴራሊዝም ስርዓት እንዲገነባ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን ጠቁመዋል። በዓሉ በሚከበርበት ወቅት የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበበት ስለመሆኑ እንደሚታይበት ተናግረዋል። በዓሉን ስኬታማ ለማድረግም በርካታ ዝግጅቶች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፤ ኅብረ ብሔራዊነትን ይበልጥ በሚያጠናክርና አብሮነትን በሚያጸና መልኩ እንደሚከበር ገልጸዋል፡፡ በሚኒስትር ማዕረግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ እናትዓለም መለሰ በበኩላቸው፤ በዓሉ ትልቅ የሀሳብ ገበያና የአንድነት ማጽኛ መሆኑን ተናግረዋል። የተመረጠው መሪ ሐሳብም ኢትዮጵያ ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገልጽ መሆኑን ጠቁመዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ፤ የተመረጠው መሪ ሀሳብ የኢትዮጵያን ሁኔታ በተጨባጥ የሚያሳይ መሆኑን አንስተው፤ በሀገር ደረጃ የተገኙ ውጤቶችን ማስረጽ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በዓሉ በህዝቦች መካከል ያለው ግንኙነት እንዲጠናከር የሚያግዝ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አለማየሁ ባውዲ ናቸው። የተመረጠው መሪ ሀሳብም ከበዓል ተሻጋሪ ሀሳብ የያዘ መሆኑን ገልጸው፤ መገናኛ ብዙሃንም እንደ መሪ ሀሳብ ሁሉ ከፍ ያለ የዘገባ ስራ መስራት እንዳለባቸው አመልክተዋል። በመድረኩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ጨምሮ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዘሀራ ኡመድ፣ በሚኒስትር ማዕረግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ እናትአለም መለሰ፣ የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አመራር አባላት፣ የክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች አፈ-ጉባኤዎችና የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙሃን አመራር አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።
በክልሉ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል- ምክር ቤቱ
Nov 11, 2025 148
ባሕርዳር ፤ሕዳር 2/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ በሚያጠናክር መልኩ ማክበር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት አስታወቀ። የምክር ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ከፍያለው ማለፉ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ በዓሉ በየዓመቱ ሁሉም ክልሎች በአንድ ላይ በመሰባሰብ በተለያዩ ዝግጅቶች ሲያከብሩት እንደቆዩ አውስተዋል። ይህም የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ትስስር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረ ፣ በመተማመንና እኩልነት ላይ የተመሰረተ ሀገራዊ አንድነት እየጎለበተ እንዲመጣ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አንስተዋል። በዚህም የተገኘውን ውጤት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ክልሉ የድርሻውን ሲወጣ እንደቆዩ አመልክተው፤ የዘንድሮውም የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በሕዳር ወር በተለያዩ ዝግጅቶች ለማክበር በዐቢይ ኮሚቴ የሚመራ ስድስት ንዑሳን ኮሚቴዎች ተዋቅረው ስራ ጀምረዋል ብለዋል። ዓላማውም በዓሉ ሲከበር በብዝሃነት ላይ የተመሰረተ አንድነት ስር እንዲሰድና እንዲዳብር በማድረግ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ይበልጥ ለማጠናከር መሆኑን አስረድተዋል። በዓሉ የፌደራሊዝምና የሕገ መንግስት አስተምህሮዎችን በማጠናከር የክልሉና የሀገሪቱን ገጽታ በመገንባት ላይ በማተኮር እንደሚከበር ተናግረዋል። በዚህም በወሩ ያሉ አራት ሳምንታትን የአስተምሮ ሳምንት፣ የበጎ ፈቃድ፣ የሕብረብሔራዊ አንድነትና ግንኙነት ማጠናከሪያና የማጠቃለያ ሳምንት በሚል ከእነዚህ ስያሜዎች ጋር የተያያዙ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል። የዘንድሮውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በክልሉ ሕዳር 5/2018 ዓ.ም በይፋ የሚጀመር ሲሆን፤ ሕዳር 24 የማጠናቀቂያ መረሃ ግብር እንደሚካሄድ በመግለጫው ተመላክቷል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ለሚከበረው በዓልም ክልሉን ወክለው የሚሳተፉ የባሕል ቡድን አባላትና ሌሎችም እንግዶች እንደሚሳተፉ ተጠቁሟል።
ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የእውነተኛ ፌደራሊዝም ስርዓት ማሳያ መድረክ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል
Nov 11, 2025 173
አዲስ አበባ፤ሕዳር 2/2018 (ኢዜአ)፡-ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የእውነተኛ ፌደራሊዝም ስርዓት ማሳያ መድረክ ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኀብረ-ብሔራዊ አንድነት’’ በሚል መሪ ቃል የሚከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በመሪ ሃሳብ የትንተና መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣የፌደሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዘሀራ ኡመድ፣ በሚኒስትር ማዕረግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሀላፊ እናትአለም መለሰ፣የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች፣የክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች አፈ-ጉባኤዎችና የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የመገናኛ ብዙሃን አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ባለፉት 19 ዓመታት ሲከበር በቆየው በዓል አብሮነትን የሚያጎለብቱና አንድነትን የሚያጠናክሩ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። በዓሉ ሕዝቦች እርስ በርስ እንዲተዋወቁ፣ መሰረተ ልማትና ኢንቨስትመንት እንዲነቃቃ የጎላ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። ባለፉት የለውጥ አመታት ቀኑ በልዩ ሁኔታ እየተከበረ እንደሚገኝና የእውነተኛ ፌደራሊዝም ስርዓት ማሳያ መድረክ ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ዘንድሮ የሚከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሚደረግ የማጠቃለያ መርሃ-ግብር ፍፃሜውን እንደሚያገኝ ተናግረዋል። ክብረ በዓሉን የተሳካ ለማድረግም በርካታ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመው፤ በዓሉ ህብረ ብሔራዊነት በሚያጠናክርና አንድነትን በሚያጎለብት አግባብ እንደሚከበር አመላክተዋል። ዘንድሮ እንደሀገር በርካታ ስራዎች የሚሰሩበት አመት በመሆኑ በዓሉን የተለየ እንደሚያደርገው ጠቅሰው፥ መገናኛ ብዙሀን የህዝቦችን አንድነት እና ትስስር የሚያጠናክሩ ተግባራትን እንዲያከናውኑ ጥሪ አቅርበዋል። በፌደሬሽን ምክር ቤት የመንግስታት ግንኙነት፣የዴሞክራሲያዊ አንድነት እና የህገ መንግስት አስተምህሮ ቋሚ ኮሚቴ ጸሀፊ ባንቺይርጋ መለሰ በዓሉ በየአመቱ ህዳር 29 በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በበዓሉ ብሔር፣ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ባህላቸውን እንዲያስተዋውቁ እና ህብረ ብሔራዊነትን ለማጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል። የዘንድሮው በዓል ብሔር፣ብሔረሰቦች እና ህዝቦች አሻራቸውን ያሳረፉበትና የበሳል የአመራር ውጤት የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ የተመረቀበት ዓመት መሆኑ የተለየ ያደርገዋል ብለዋል። በተጨማሪም ከመቸውም ጊዜ በላይ መጻኢ እድላችንን የምንወስንበት በመሆኑ በዓሉ በተለየ ሁኔታ እንደሚከበር ጠቁመዋል።
ማህበራዊ
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ለመምህራን ልማትና ግብአት አቅርቦት ትኩረት ተሰጥቷል
Nov 12, 2025 52
አዳማ ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ለመምህራን ልማትና ግብአት አቅርቦት ትኩረት መሰጠቱን የትምህርት ዘርፍ አመራሮች ገለጹ። 34ኛው ሀገር አቀፍ የትምህርት ጉባዔ “ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም” በሚል መሪ ሀሳብ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል። በትምህርት ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ አቶ እሸቱ ገላዬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በትምህርት ዘርፉ ሪፎርም ስራዎች ለመምህራን ልማትና ፣ ለትምህርት አመራሩ አቅም ግንባታና ለመጻህፍት ተደራሽነት ትኩረት ተሰጥቷል። ሚኒስቴሩ ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ያለሙ የመማሪያ መጻህፍት ህትመት በማከናወን ለክልሎች ማከፋፈሉን ለአብነት አንስተዋል። በትምህርት ዘርፉ ሪፎርም የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማትና ግብአትን ማሟላት ላይም በትኩረት መሠራቱን ጠቅሰዋል። በዚህ ረገድ ባለፉት ሁለት የክረምት ወራቶች ልዩ የስልጠና መርሃ ግብር በማዘጋጀት ለ100 ሺህ የሚጠጉ መምህራንና አመራሮች ስልጠና መሰጠቱን አብራርተዋል። በጉባዔው ተሳታፊ ከሆኑት መካከል የሲዳማ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ በራሳ በበኩላቸው የትምህርት ዘርፉን ሪፎርም ለማሳካት ሀገራዊና ክልላዊ ሪፎርሞችን በማቀናጀት ተደራሽነትና ጥራትን ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል። በአገር አቀፉ የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተጀመሩ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በማስፋት በገጠር ሞዴል የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶችን የመገንባትና ነባር የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በማደስ ለህጻናቱ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትምህርት ቤቶቹን ለመማር ማስተማር ስራ ምቹ ከማድረግ ባለፈ የትምህርት መሣሪያዎችን የማሟላትና የመምህራንን አቅም ማጎልበት ላይ በተጠናከረ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። ከዚህ ጎን ለጎን በተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር በክልሉ ከ40 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። ሌላው የጉባዔው ተሳታፊ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አቡበከር አዶሽ እንዳሉት ለትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት የተጀመሩ የለውጥ ስራዎችን ለማሳካት ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተሻለ ስራ ተሰርቷል። የትምህርት ጥራት ለማስጠበቅ ኩረጃ ለማስቀረት የሚያስችል ግንዛቤ ከመስጠት ባለፈ የግብአት አቅርቦትን ማሟላት ላይም በሰፊው መሰራቱን አንስተዋል። የተማሪዎችን መጠነ ማቋረጥን ለማቃለልም ማህበረሰቡን በማሳተፍ ከ 30 ሺህ በላይ ህጻናትን ተጠቃሚ ያደረገ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራሙ በአስተዳደሩ ተግባራዊ መደረጉን ገልጸዋል።
ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነት መጎልበት የኃይማኖት ተቋማት የላቀ ሚናቸውን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል
Nov 12, 2025 57
አርባምንጭ ፤ ሕዳር 3/2018(ኢዜአ)፡- ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ሀገራዊ አንድነት መጎልበት የኃይማኖት ተቋማት የላቀ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል እንደሚጠበቅባቸው የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀኃፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ተናገሩ። "ሃይማኖቶች ለሰላም፣ለአንድነትና ለአብሮነት" በሚል መሪ ሀሳብ 5ኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው። በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀኃፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ፤ ለዘላቂ ሰላምና ለሕዝቡ አብሮነት መጠናከር የሃይማኖት ተቋማት የማይተካ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። ኮንፈረንሱ በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና አብሮነትን ይበልጥ በማጠናከር ሁለንተናዊ እድገት ለማምጣት በሚደረገው ጥረት የሃይማኖት ተቋማትን ሚና ለማጎልበት ታልሞ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። የሃይማኖት ተቋማት ለሰላም እሴቶች ግንባታ ፣ ልማት እና ሀገራዊ አንድነትን አፅንቶ ለማስቀጠል ሚናቸው እንዲጎለብት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለውም ብለዋል። በዚህም ተቋማቱ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ሀገራዊ አንድነት መጎልበት የላቀ ሚናቸውን ይበልጥ ማጠናከር የሚጠበቅባቸው መሆኑን አመልክተው፤ ሁሉም ዜጋ ለሰላም መፅናት የድርሻውን እንዲወጣም መልዕክት አስተላልፈዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) ፤ ሰላም ለሕዝብ ደህንነትና ለዘላቂ ልማት የማይተካ ሚና አለው ብለዋል። የሃይማኖት ተቋማት ለክልላችን ብሎም ለሀገራችን ሰላም፣ለሕዝቡ ትስስርና ትብብር የማይተካ ሚና ተጫውተዋል ሲሉም አክለዋል። በየአካባቢው አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የክልሉ ሕዝብ ሲያደርግ የቆየውን ትብበርና ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላልፈዋል። የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዞኑ ሕዝብ በ"ዱቡሻ " ባሕላዊ ሥርዓት በመታገዝ ሰላሙንና አብሮነቱን ጠብቆ ለዘመናት ኖሯል ፤ ለዘላቂ ሰላምና ብልጽግና የሃይማኖት ተቋማት ሚና ጉልህ ነው ብለዋል። የሰላም ተምሳሌት የሆነው የጋሞ ዞን ሕዝብ ለሀገር ሰላም ፣ ዕድገትና ልማት ሲያበረክት የቆየውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚጠበቅበትም አመልክተዋል። ሰላም በየትኛውም ዋጋ የማይተመን ሀብታችን ነው ያሉት ደግሞ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) ናቸው። የሕዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰላምን በመጠበቅ በቅንጅት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ኮንፍረንስ ላይ ከሁሉም ክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ የሃይማኖት ጉባኤ አባላት፣የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣የባህል መሪዎችና ሌሎች አካላት እየተሳተፉ ነው።
የዜጎችን መብትና ጥቅም ለማስከበር የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስመዘገቡ ነው
Nov 12, 2025 65
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ዜጎችን መብትና ጥቅም ለማስከበር በትብብር የተከናወኑ ተግባራት ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ገለፁ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው የመመለሱ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን መግለፁ ይታወቃል። ሚኒስቴሩ በመግለጫው ባለፉት አራት ዓመታት በመካከለኛ ምስራቅ፣አፍሪካ፣ ማይናማር እና የእስያ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ማድረግ መቻሉን ጠቁሟል። በዚምባብዌ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርና በሞሪሽየስ፣ በዛምቢያ፣ በምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የኢትዮጵያ ተጠሪ ረሺድ መሀመድ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ የውጭ ዲፕሎማሲ ከሚያተኩርባቸው ጉዳዮች አንዱ የዜጎችን ክብርና መብት ማስጠበቅ ነው። ኤምባሲዎቹ ዜጎች ችግር ሲገጥማቸው የመከታተልና የመፍታት ስራዎችን ሲያከናውን መቆየታቸውንና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። ባለፈው ዓመት አንድ ሺህ የሚጠጉ ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት መመለስ መቻሉን ጠቅሰው፤ ኤምባሲው ፓስፖርት የማደስ፣ መረጃ የማረጋገጥና ተያያዠ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። በባህሬን የኢፌዴሪ ቆንስላ ጄኔራል ጽህፈት ቤት ቆንስል ጄኔራል አምባሳደር ሽፈራው ገነቲ፤ ሁለቱ ሀገራት የስራ ስምሪት ስምምነት ባይኖራቸውም የዜጎች ክብርና ጥቅም እንዲከበር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም በተለያየ ምክንያት ለእስር የተዳረጉ ዜጎች ነፃ የህግ አገልግሎት እንዲያገኙና ዜጎች በህጋዊ መንገድ እንዲንቀሳቀሱና በነጻነት እንዲሰሩ አስፈላጊውን ሁሉ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። ጽህፈት ቤቱ ባደረገው ጥረት ባለፈው ዓመት ከስድስት ሺህ በላይ ዜጎች ህጋዊ መኖሪያ ፈቃድ እንዲያገኙ ማስቻሉን አንስተው፤ ወደ ሀገራቸው መመለስ የሚፈልጉ 291 ዜጎችን እንዲመለሱ መደረጉንም ገልፀዋል። በዱባይና ሰሜን ኤምሬትስ የኢፌዴሪ ቆንስላ ጄኔራል ፅህፈት ቤት ተጠባባቂ ጉዳይ ፈፃሚ አስመላሽ በቀለ በበኩላቸው፤ የዜጎችን መብትና ጥቅም ለማስከበር የተለያዩ ተግባራትን እያከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በዚህም ፅህፈት ቤቱ ባለፉት ሁለት ዓመታት የፓስፖርት እድሳት፣ የውክልና እና የዳያስፖራ አገልግሎቱን በኦንላይን እየሰጠ መሆኑን ገልፀዋል። ዜጎች ከስራ ውል ጋር የተያያዙ ችግሮች ሲገጥማቸው መብታቸውን ለማስከበር ከኢትዮጵያ ኮሙዩኒቲ ማህበር ጋር በመተባበር እየተሰራ ነው ብለዋል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ፤ ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ብሄራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። ከስደት ተመላሾች በሀገር ውስጥ የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑና በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የሚሳተፉ ደላሎች በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። ሚኒስቴሩ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ዜጎች ደህንነቱ በተጠበቀ ህጋዊ መንገድ እንዲጓዙ ግንዛቤ የማስጨበጥና ለተመላሾች የማህበራዊ አገልግሎትና የአገር ውስጥ የስራ እድል ፈጠራ ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አመላክተዋል። የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍፁም አረጋ መንግስት ከተለያዩ ሀገራት ጋር ምክክር በማድረግና ስምምነት በመፈጸም የዜጎችን መብት ለማስጠበቅ እየሰራ ነው ብለዋል። በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ኤምባሲዎች የኢትዮጵያ ኮሙዩኒቲ ማህበሮችን በማደራጀት ዜጎች የሚገጥማቸውን ችግር ለመፍታት እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
ዜጎች አስከፊነቱን ተገንዝበው መደበኛ ካልሆነ ፍልሰት ሊቆጠቡ ይገባል
Nov 12, 2025 72
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 3/2018(ኢዜአ)፡- በመንግሥት ደረጃ ብሎም ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት የሚያከናውነው መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን የመከላከልና መቆጣጠር ሥራ እንደተጠበቀ ሆኖ ዜጎች ከድርጊቱ እራሳቸውን ማቀብ እንዳለባቸው ተገለጸ። በሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር መከላከልና ከፍልሰት ተመላሽ ዜጎች ድጋፍና ክትትል መሪ ሥራ አስፈፃሚ ደረጀ ተግይበሉ እንዳሉት፤ መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ወደ ተለያዩ ሀገራት የሄዱና ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን የመመለስ ሥራ እየተከናወነ ነው። ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላ ተገቢው የሥነ-ልቦናና ማኅበራዊ ድጋፍ እንዲያገኙ ተደርጎ ከቤተሰብ እና ከማኅበረሰቡ ጋር መቀላቀላቸውን ጠቅሰዋል። በክልሎች የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮዎች እና በሥራና ክኅሎት ቢሮዎች አማካኝነት ተገቢውን ስልጠና ወስደው የማቋቋም ሥራ እየተሠራ መሆኑንም አረጋግጠዋል። በመንግሥት በኩል ተገቢው ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ገልጸው፤ በግላቸው ለመንቀሳቀስ የፈለጉም በራሳቸው ጥሪት የግል ሥራቸውን እየሠሩ መሆኑን አመላክተዋል። በሀገር ውስጥ ያሉ የሥራ አማራጮችን ማስተዋል እና ወደ ውጭ መሄድ ሲያስፈልግም በሕጋዊ መንገድ ብቻ እንዲሆን መክረው፤ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት ዘርፈ-ብዙ ጉዳት እንደሚስከትል አስገንዝበዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው የመመለሱ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል። ባለፉት አራት ዓመታትም በተለያዩ የመካከለኛ ምሥራቅ፣ የአፍሪካ እና እንደ ማይናማር ያሉ የእስያ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ማድረግ መቻሉን አስታውቋል።
ኢኮኖሚ
ሀዋሳ ከተማን ለመኖሪያ፣ ለቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ለማድረግ ይሰራል-ከንቲባ ጥራቱ በየነ
Nov 12, 2025 40
ሀዋሳ ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ሀዋሳ ከተማን ለመኖሪያ፣ ለቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ከተማ ለማድረግ ከፍ ያለ ራዕይ በመሰነቅ ይሰራል ሲሉ አዲሱ የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 2ኛ ዙር አስረኛ ዓመት 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ጥራቱ በየነን የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል። አዲሱ የከተማዋ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ለምክር ቤቱ አባላት ባደረጉት ንግግር እንዳሉት፤ ከተሞችን የብልጽግና ማሳያ ለማድረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በአዲስ እሳቤ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በሀዋሳ ከተማም እየተከናወነ ነው። በከተማዋ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ሀዋሳን ከአዲስ አበባ በመቀጠል በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ለመኖሪያ፣ ቱሪዝምና ለኮንፈረንስ ተመራጭ ለማድረግ ከፍ ያለ ራዕይ ሰንቀን ያለመዘናጋት እንሰራለን ብለዋል። ለዚህ ራዕይ ስኬት የመንግስት፣ የነዋሪውና የግል ሴክተሩ የተቀናጀና የተናበበ ስራ ወሳኝ መሆኑን ያነሱት አቶ ጥራቱ ሁሉንም ማህበረሰብ በማሳተፍ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የሀዋሳን በፍቅር ተከባብሮና ተደጋግፈው በወንድማማችነትና በአንድነት የሚኖሩባት የፍቅር ከተማነቷን ለማስቀጠል ጠንክረው እንደሚሰሩም ጠቁመዋል። የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ አጠናክሮ በማስቀጠል ለነዋሪዎቿ ምቹ ከተማ እንድትሆን ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሰላምና ጸጥታ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ መስፈርቶችንና የከተማ ፕላንን መሰረት ባደረገ መልኩ በከተማዋ መሰረተ ልማቶችንና አረንጓዴ ስፍራዎችን የማስፋፋት ሥራ እንደሚሰራ ገልጸው፣ የሀዋሳ ሐይቅን ከብክለት የመጠበቅና የታቦር ተራራን ልማት በማፋጠን ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራ ይሰራል ብለዋል። የቆሻሻ አወጋገድና አያያዝን ከማዘመን ባለፈ ዘላቂ የከተማ ልማትን ተግባራዊ በማድረግ ንጹህና ምቹ ሀዋሳን ለመፍጠርም ትኩረት እንደሚሰጥ አመልክተዋል። ሀዋሳ ከተማን ተመራጭ የቱሪዝምና የኮንፈረንስ መዳረሻ ለማድረግም ደረጃቸውን የጠበቁ የቱሪስት መዳረሻዎችን ቁጥር ከማሳደግ ባለፈ የከተማዋን የቱሪስት ሀብቶች ለማስተዋወቅ በትኩረት እንደሚሰራም አስታውቀዋል። ከንቲባው በከተማዋ የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የተጀመሩ የከተማ ግብርና የሌማት ትሩፋት መርሀግብሮች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በስራ ዕድል ፈጠራ ለግሉ፤ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ሴቶች ወጣቶችና የተለያዩ ወገኖች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ የስራ አጥነትን ጫና ለማቃለል እንደሚሰራም አቶ ጥራቱ አስታውቀዋል። የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ የቀረበለትን የአቶ ጥራቱ በየነን የከንቲባነት ሹመት በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ በማጽደቅ ጉባኤውን አጠናቋል።
መፍጠር፣ መፍጠን እና በጥራት መሥራት የሁልጊዜም የስራ መመሪያችን ሊሆን ይገባል-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Nov 12, 2025 27
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦መፍጠር፣ መፍጠን እና በጥራት መሥራት የሁልጊዜም የስራ መመሪያችን ሊሆን ይገባል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በሰሜን ሸዋ ዞን በደብረ ብርሃን ከተማ በነበራቸው ቆይታ የመኪና መገጣጠሚያ እንዲሁም የብርጭቆና የጠርሙስ ማምረቻዎችን መመልከታቸውን አስታውቀዋል። በቆይታቸው የተመለከቷቸው ፋብሪካዎች የሀገር ውስጥ ግብዓትን በመጠቀምና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬን እያዳኑ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከብየዳ ጀምሮ ትላልቅ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶችን እየገጣጠመ የሚገኘው የፊቤላ ኢንዱስትሪያል መኪና መገጣጠሚያ በቀን 12 መኪና ማምረት የሚያስችል አቅም እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡ መገጣጠሚያው በቅርቡ ያስጀመረው አዲስ የቀለም መቀቢያ በርካታ ቀናትን ይወስዱ የነበሩ ስራዎችን በሰዓታት ለማከናወን አስችሏልም ነው ያሉት፡፡ በአንድ ቀን 450 ሺህ ጠርሙስ የሚያመርተው ዴዴ ቦትል የብርጭቆና የጠርሙስ ማምረቻ ደግሞ 86 በመቶ የሚሆነውን ግብዓት ከሀገር ውስጥ ተጠቅሞ ለበርካታ የመጠጥ እና የመድሃኒት ፋብሪካዎች ጥቅም የሚሰጡ ጠርሙሶች እንደሚያመርት አስታውቀዋል፡፡ በኢንዱስትሪዎቹ የተመለከትናቸው አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴዎች በየዘርፉ በጥራትና በፍጥነት በመትጋት የምናልመውን እድገት በአጠረ ጊዜ እንደምናሳካ የሚያሳዩ ናቸው ሲሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
እስካሁን ከ2ሺህ 96 ቶን በላይ እሸት ቡና ተሰብስቧል
Nov 12, 2025 28
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፡- በ2018 በጀት ዓመት እስካሁን በተሰራ ስራ 2ሺህ 96 ነጥብ 37 ቶን እሸት ቡና መሰብሰቡን የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ። በበጀት ዓመቱ 7ሺህ 880 ቶን እሸት ቡና ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን የመምሪያው ምክትል እና የቡናና ቅመማቅመም ዘርፍ ኃላፊ ከአብነህ ተስፋዬ ለኢዜአ ገልጸዋል። በዚህም እስካሁን 2ሺህ 96 ነጥብ 37 ቶን እሸት ቡና መሰብሰቡን ገልጸው፤ አሁንም ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚላክ ቡና በተለያዩ ግብይቶች እየተሰበሰበ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በሌላ በኩል 8 ነጥብ 9 ቶን የታጠበ እንዲሁም 343 ነጥብ 5 ቶን ያልታጠበ የተቀሸረ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ መላኩን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም ብክነት እንዳይኖር የደረሰ ቡና ከስር ከስር በቅንጅት እየተሰበሰበ መሆኑንም አመላክተዋል።
በክልሉ የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ ይገባል - ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን
Nov 12, 2025 34
አሶሳ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር አመራሮች በተገኙበት የክልሉን ፀጋዎች አልምቶ መጠቀም በሚቻልበት መንገድ ላይ የውይይት መድረክ አካሂደዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ ላይ ባቀረቡት የመወያያ ሰነድ በክልሉ የአካባቢውን ፀጋዎችን በማልማት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል። በክልሉ ገቢዎችን አሟጦ በመሰብሰብ የራስን ወጪ በራስ አቅም በመሸፈን ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶችን ማከናወን ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የክልሉን ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ከለውጡ ወዲህ በግብርና፣ በማዕድንና ሌሎች ዘርፎች በክልሉ የተገኙ ውጤቶችን በተቀናጀ መልኩ ማስቀጠል ይገባል ያሉት አቶ አሻድሊ፤ በዚህ ረገድ አመራሩ በላቀ ቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በክልሉ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ማስፋት፤ ጠንካራ ተቋማት ግንባታ እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከልን አጠናክሮ በመቀጠል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባም አሳስበዋል።
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል-ተገልጋዮች
Nov 12, 2025 21
ሆሳዕና ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሆሳዕና ማዕከል ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ሥራ መጀመሩ ይታወቃል። የማዕከሉን የሥራ እንቅስቃሴ በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር በስፍራው በመገኘት ተገልጋዮችና የሚመለከታቸውን የሥራ ሃላፊዎች አነጋግሯል። ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ዳንኤል በየነ፣ አቶ ደስታ ኤርቻዮ እና አቶ ደመቀ ሙሉነህ ፤ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል። አገልግሎቱ በአንድ ማዕከል በርካታ ጉዳዮችን ጨርሶ መውጣት ከማስቻሉ ባለፈ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ መሆኑንም ተናግረዋል። በመሆኑም መሰል የአገልግሎት ማዕከላትን በማስፋት በተገልጋዮች ላይ ሲደርስ የነበረን እንግልት እና የብልሹ አሰራር መንስኤዎችን ማስቀረት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የማዕከሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከበደ ሻሜቦ፤ በማዕከሉ የተለያዩ ተቋማት 20 አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶች እየሰፋ ይሄዳሉ ብለዋል። በማዕከሉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረት እያስቻለ በመሆኑ በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል።
በሶማሌ ክልል ከ340 ሺህ በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ አከናውነዋል
Nov 12, 2025 55
ጅግጅጋ፤ ህዳር 3/2018 (ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል ከ340 ሺህ በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ማከናወናቸውን የክልሉ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ። በብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የምስራቅ ሪጅን የጅግጅጋ አካባቢ የምዝገባ አስተባባሪ አቶ ጌዲዮን ጌታቸው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለዜጎች ዘርፈ ብዙ አገልግሎትን በተቀላጠፈ መልኩ እንዲያገኙ የሚያስችል ነው። የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ኢትዮጵያ ለያዘችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬታማነትም ቁልፍ ሚናን የሚጫወት ነው ብለዋል። በዚህም በክልሉ የህብረተሰቡን የዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታው ተሳትፎዋቸውን ለማረጋገጥ አደረጃጀቶችን በመጠቀም እየተሰራ መሆኑን አቶ ጌዲዮን አስታውቀዋል። በክልሉ ባሉት ዞኖችና በ66 ወረዳዎች በትምህርት ቤቶች፣ በዩኒቨርሲቲዎች፤ በባንኮች፤ በንግድ ማዕከላት እንዲሁም በሌሎች የመንግሥት ተቋማት ምዝገባው በመካሄድ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ ፕሮግራሙ ከተጀመረ ከግንቦት 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን 340 ሺህ ዜጎች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ ከዚህ ውስጥ 180 ሺህ የሚሆኑት ከጅግጅጋ ከተማ ውጭ ባሉ ወረዳዎችና ዞኖች የተመዘገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በክልሉ እሰከ ሰኔ 2018 ዓ.ም ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመመዝገብ መታቀዱን ገልጸው፤ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ወራት ብቻ ከ160 ሺህ በላይ ዜጎች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በክልሉ የፕሮግራሙን ተደራሽነት በማስፋት ተጨማሪ የምዝገባ ማዕከላት ለመጨመር የሚያስፈልገውን የሰው ሃይል የማሰማራትና የአቅም ግንባታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን ተናግረዋል። ህብረተሠቡ ከምዝገባው በኋላ ከኢትዮ-ቴሌኮምና እውቅና ባላቸው ተቋማት ዲጂታል መታወቂያውን በመውሰድ በጥንቃቄ መጠቀም እንዳለበትም አሳስበዋል።
በድሬዳዋ የሠራተኛውን የዲጂታል ክህሎት በማሳደግ ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ነው
Nov 11, 2025 113
የድሬዳዋ ፤ ህዳር 2/2018 (ኢዜአ)፡-በድሬዳዋ የሠራተኛውን የዲጂታል ክህሎት በማሳደግ ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የአስተዳደሩ የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ገለፀ ። በድሬዳዋ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የመንግስት ሠራተኛውን የቴክኖሎጂ ክህሎት ለማሳደግ በሚቻልበት አግባብ ላይ ቢሮው ከአስተዳደሩ የማዕከል ተቋማት የሰው ሃብት አመራሮች ጋር ዛሬ ተወያይቷል። ውይይቱን የመሩት የቢሮው የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ የመሠረተ ልማት አቅርቦትና አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ኢማድ አብዱልቀዩም፤ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የሠራተኞችን የቴክኖሎጂ ክህሎት በማሳደግ የተገልጋዩን ፍላጎት ለማርካት እየተሰራ ነው። የሠራተኛውን የቴክኖሎጂ ክህሎት ለማሳደግ ያልተቋረጠ ስልጠና እየሰጠ መሆኑንም አንስተዋል። ስልጠናውም ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ የመገንባት ጉዞን ለማሳካት ቁልፍ ሚና በመጫወቱ ሠራተኞች በእድሉ እንዲጠቀሙ ከተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንተናግረዋል ። የተሰጠውን ስልጠና በአግባቡ የወሰዱ ሰራተኞች በየተቋማቸው ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመተግበር ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ እያደረጉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። እነዚህን አበረታች ስራዎች በላቀ መጠንና ፍጥነት ለማሳደግ የማዕከል ተቋማት የሰው ሃብት አመራሮች ተግተው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል ። በቀጣይም ተመሳሳይ ውይይት በሁሉም ተቋማት በማካሄድ ሠራተኛው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናው ተጠቃሚ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የድሬዳዋ አስተዳደር የፍትህ ፀጥታና የህግ ጉዳዮች ቢሮ የሰው ሃብት አመራር ዳይሬክተር ወይዘሮ ማሾ መሐመድ በበኩላቸው፤ ሠራተኞች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ሠራተኞች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን በአግባቡ በመውሰድ ተገልጋይን ለማርካት በሚደረገው የአሰራር ሂደት ለውጥ ማምጣት እንደሚገባቸው የገለጹት ደግሞ የአስተዳደሩ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን የሰው ሃብት አመራር ዳይሬክተር ወይዘሮ ፌይሩዝ መሐመድ ናቸው።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ዘመናዊ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎትን መስጠት ያስችላል
Nov 11, 2025 133
ሐረር፤ ህዳር 2/2018 (ኢዜአ)፡- መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ዘመናዊ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎትን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪና የኢፌዴሪ ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አልማዝ መሰለ በከተማው የተገነባውን የሐረሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀምረዋል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ባደረጉት ንግግር በመደመር መንግስት እይታ እና ተግባራዊ እንቅስቃሴ በሁሉም ዘርፎች እመርታ እያስመዘገብን እንገኛለን ብለዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ዘመናዊ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው ብለዋል። የማዕከሉ ስራ መጀመር በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል ለመስጠት የሚያስችል እና የተገልጋዩን ማህበረሰብ ምልልስና የአገልግሎት ቆይታ ጊዜን የሚያሳጥር መሆኑን ጠቅሰዋል። ማዕከሉ በክልሉ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የሚኖረው ፋይዳ የላቀ መሆኑንም ተናግረዋል። በተለይ ተመጋጋቢ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን በአንድ ማዕከል በማሰባሰብ ለህብረተሰቡ የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳለጥ እንደሚያግዝ ነው የጠቆሙት። የክልሉ መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማጎልበት የጀመረውን ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። የኢፌዴሪ ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አልማዝ መሰለ በበኩላቸው በስምንት ክልሎች፣ በሁለት የከተማ አስተዳደሮችና በፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከልን ጨምሮ 18 ማዕከላት ተገንብተው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ተናግረዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአንድ ቦታ ላይ በክብርና በቅልጥፍና አገልግሎት የሚገኝበትን ስርዓት የያዘና መንግስትና ህዝብን የሚያቀራርብ ትልቅ ስኬት መሆኑንም ተናግረዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች የተሻለ የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም በቀላሉ የፌዴራልና የክልል ተቋማት አገልግሎቶችን የሚያገኙበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሐረሪ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ ጆርዳን ኢስሃቅ ናቸው። ማዕከሉ በበቁ ሰዎች የተደራጀና ዘመኑን በሚመጥን አስተሳሰብና በላቀ የስራ ተነሳሽነት እንዲሁም በቴክኖሎጂ ለማገልገል መገንባቱን ገልጸዋል። በሐረሪ መሶብ አንድ ማዕከል የተለያዩ የፌዴራልና የክልሉ ተቋማት አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን ከ50 በላይ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል ማግኘት ያስችላልም ተብሏል።
ስፖርት
ኢትዮጵያ መድን እና ቤንች ማጂ ቡና በኢትዮጵያ ዋንጫ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፉ
Nov 12, 2025 23
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዋንጫ የሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ጨዋታዎች ዛሬ መካሄድ ጀምረዋል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን በአማኑኤል ኤርቦ ግብ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 አሸንፏል። በሃዋሳ አርቴፊሻል ስታዲየም በተካሄደው ሌላኛው መርሃ ግብር ቤንች ማጂ ቡና ጋሞ ጨንቻን 1 ለ 0 ረቷል። ፅዮን ተስፋዬ ለቤንች ማጂ ቡና ብቸኛውን ጎል ከመረብ ላይ አሳርፏል። ውጤቶቹን ተከትሎ ኢትዮጵያ መድን እና ቤንች ማጂ ቡና በኢትዮጵያ ዋንጫ የመጨረሻውን 16 የተቀላቀሉ የመጀመሪያ ቡድኖች ሆነዋል። የኢትዮጵያ ዋንጫ ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብር ከሰዓትም ሲቀጥል የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ወላይታ ድቻ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም፣ አርባምንጭ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተመሳሳይ ከቀኑ 9 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድል ቀንቶታል
Nov 12, 2025 44
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሶስተኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባምንጭ ከተማን 5 ለ 1 አሸንፏል። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ምርቃት ፈለቀ ሁለት ግቦችን ከመረብ ላይ ስታሳርፍ እፀገነት ግርማ፣ ንግስት በቀለ እና መሳይ ተመስገን ቀሪዎቹን ግቦች አስቆጥረዋል። ድንቅነሽ በቀለ ለአርባምንጭ ከተማ ብቸኛውን ጎል አስቆጥራለች። የንግድ ባንኳ እፀገነት ግርማ የጨዋታው ኮከብ ሆና ተመርጣለች። ውጤቱን ተከትሎ የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዘጠኝ ነጥብ ደረጃውን ከስድስተኛ ወደ አራተኛ ከፍ አድርጓል። ንግድ ባንክ በካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ምክንያት ከሲዳማ ቡና እና ሸገር ከተማ ያላደረጋቸውን ተስተካካይ ጨዋታዎች በቀጣይ በሚገለጹ ቀናት የሚያደርግ ይሆናል። በውድድር ዓመቱ አራተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አርባምንጭ ከተማ በአንድ ነጥብ 14ኛ ደረጃን ይዟል። በተያያዘም የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ስድስተኛ ሳምንት ዛሬ ከቀኑ 7 ሰዓት ሸገር ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀመራል።
የኢትዮጵያ ዋንጫ ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብር ዛሬ እና ነገ ይካሄዳል
Nov 12, 2025 66
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ዋንጫ ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ቀን ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ወላይታ ድቻ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከቀኑ 9 ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ። በአዲስ አበባ ስታዲየም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ከረፋዱ 4 ሰዓት፣ አርባምንጭ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከቀኑ 9 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ። ቤንች ማጂ ቡና ከጋሞ ጨንቻ በሃዋሳ አርቴፊሻል ስታዲየም ከረፋዱ 4 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ነገ በኢትዮጵያ ዋንጫ 12 ጨዋታዎች ይከናወናሉ። በመጀመሪያው ዙር ውድድር የከፍተኛ ሊግ ክለቦች ብቻ የተሳተፉ ሲሆን አሸናፊ ቡድኖች በሁለተኛው ዙር ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቡድኖች ጋር በመቀላቀል ይጫወታሉ። ወላይታ ድቻ የወቅቱ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ነው። የኢትዮጵያ ዋንጫ የሚያሸንፍ ቡድን በቀጣዩ ዓመት ኢትዮጵያን ወክሎ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ይሳተፋል።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ስድስተኛ ሳምንት ዛሬ ይጀመራል
Nov 12, 2025 54
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የአምስተኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ውሎ ሸገር ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ይጫወታሉ። የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ከቀኑ 7 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይካሄዳል። አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ በሊጉ እስከ አሁን ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች ሶስት ጊዜ ሲያሸንፍ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። ቡድኑ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው በዘጠኝ ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል። ተጋጣሚው ድሬዳዋ ከተማ በሊጉ ካደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች መካከል ማሸነፍ የቻለው አንዱን ብቻ ነው። በቀሪ አራት ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል። ድሬዳዋ ከተማ በሶስት ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል። ጨዋታው ሸገር ከተማ ተከታታይ ድሉን ለማስመዝገብ፣ ድሬዳዋ ከተማ ወደ አሸናፊነት መንገድ ለመመለስ የሚያደርጉት ነው። በአራተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ሸገር ከተማ አዲስ አበባ ከተማን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ድሬዳዋ ከተማ በሃዋሳ ከተማ የ2 ለ 0 አስተናግዷል። የስድስተኛ ሳምንት መርሃ ግብር እስከ ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። በተያያዘም የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሶስተኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታውን ዛሬ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ ከአርባምንጭ ከተማ ያደርጋል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ምክንያት በሊጉ የመጀመሪያ ሶስት ጨዋታዎቹን አላደረገም። ጨዋታዎቹም በተስተካካይ መርሃ ግብርነት ተይዘዋል። ከተስተካካይ ጨዋታዎቹ የመጀመሪያውን ከአርባ ምንጭ ከተማ ጋር ያደርጋል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በስድስት ነጥብ አምስተኛ፣ አርባምንጭ ከተማ በአንድ ነጥብ የመጨረሻውን 14ኛ ደረጃን ይዟል። ንገድ ባንክ ቀሪ ተስተካካይ ጨዋታዎቹን ከሲዳማ ቡና እና ሸገር ከተማ ጋር በቀጣይ በሚገለጹ ቀናት የሚያደርግ ይሆናል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ15 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው። የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን ዳግማዊ ሰለሞን ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በዘጠኝ ጎሎች ትመራለች። ብርቄ አማረ ከመቻል እና መሳይ ተመስገን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተመሳሳይ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ይከተላሉ።
አካባቢ ጥበቃ
ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እንድታስተናግድ ተመረጠች
Nov 12, 2025 70
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) እንድታስተናግድ ተመርጣለች። 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 30) በብራዚል ቤለም እየተካሄደ ይገኛል። ኢትዮጵያ በስብሰባው ላይ ኮፕ 32ትን የማስተናገድ ጥያቄ በይፋ ያቀረበች ሲሆን የአፍሪካ ሀገራት ጉባኤውን እንድታስተናግድ ድጋፍ ሰጥተዋታል። የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀ መንበር ሪቻርድ ሙዩንጊ ቡድኑ የኢትዮጵያን የኮፕ 32 የማስተናገድ ጥያቄ ተቀብሎ ማጽደቁን ለኤኤፍፒ ገልጸዋል። የኮፕ 30 ፕሬዝዳንት የሆነችው ብራዚልም የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያን መምረጣቸውን አረጋግጣለች። የተደራዳሪ ቡድኑ መደበኛ ያልሆነ ውሳኔ በሁሉም የጉባኤው ተሳታፊ ሀገራት መጽደቅ እንደሚጠበቅበት እና ይህም ኮፕ 30 በሚጠናቀቅበት ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ አስተናጋጅነት በድርጅቱ ስር ባሉ አምስት ቀጣናዎች ውስጥ ያሉ ሀገራት በመፈራረቅ የሚያዘጋጁት ነው። ብራዚል የላቲን እና የካሪቢያን ሀገራት ወክላ መመረጧን ተከትሎ ኮፕ 30ን እያካሄደች ትገኛለች። ኮፕ 30 እስከ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን ጉባዔ ለማስተናገድ ከአፍሪካ ሙሉ ድጋፍ አገኘች
Nov 11, 2025 117
አዲስ አበባ፤ ህዳር 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ እንድታስተናግድ ከአፍሪካ ሀገራት ሙሉ ድጋፍ አግኝታለች። በብራዚል ቤሌም እየተካሄደ የሚገኘው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ መደበኛ ጉባዔውን እያካሄደ ነው። አስቀድሞ በመሪዎች ስብሰባ በጀመረው ጉባዔ ላይ ኢትዮጵያ 32ኛውን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን በአዲስ አበባ ለማዘጋጀት ፍላጎቱም ዝግጁነቱም እንዳላት መግለጿ ይታወሳል። አስቀድሞ በርካታ የጎንዮሽ ውይይቶችን ሲያካሂድ ቆይቶ፥ ቴክኒካዊ ድርድርና ውይይቶችን በሚያስተናግደውና ትላንት በጀመረው ጉባዔ ላይ የኢትዮጵያን ጥያቄ የአፍሪካ ሀገራት መስማማታቸውን ይፋ ማድረጋቸውን የኢቢሲ ዘገባ ያመላክታል። የወቅቱ የአፍሪካ ተደራዳሪዎች ቡድን ሊቀመንበር በሆነችው ታንዛኒያ በኩል የኢትዮጵያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ ተገልጿል። ይህንኑ አስመልክቶ በጉባዔው ንግግር ያደረጉት በብራዚል ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ኢትዮጵያ ጉባዔውን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ አፍሪካውያን በመደገፋቸው ኢትዮጵያ ትልቅ አክብሮት አላት፣ እንደምታሳካው መተማመናቸውም አስደሳች ነው፣ ለዚህም ኢትዮጵያ ታመሰግናለች ማለታቸውንም አስነብቧል። አዲስ አበባ እንግዶቿን በሚመጥን ደረጃ ጉባዔውን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ያረጋገጡት አምባሳደሩ፥ ለኢትዮጵያ ጥያቄ ሌሎች ሀገራትም ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ዳፋን ለመከላከል እየወሰደቻቸው ያሉ ተግባራዊ እርምጃዎች፣ አዲስ አበባ 2ኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔን ጨምሮ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶችን በስኬት ማስተናገዷ፣ እንዲሁም በሁሉም ረገድ ያላትን ዝግጁነት በመግለጽ ጥያቄዋን ለዘንድሮው ጉባዔ በይፋ ማቅረቧ ይታወሳል። አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ኢትዮጵያ አሁንም የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም ተግባራዊ እርምጃዎችን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል። ጉባዔውን ለማስተናገድ ኢትዮጵያ ያቀረበችው ጥያቄ በቀጣይ ሂደቶች ተቀባይነት ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል።
በአዋሽ ወንዝ ከልማት ውጪ የነበረን ከ70 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ወደ ልማት ማስገባት ተችሏል
Nov 10, 2025 280
አዳማ፤ ህዳር 1/2018(ኢዜአ)፦ በአዋሽ ወንዝ ከልማት ውጪ የነበረን ከ70ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ወደ ልማት ማስገባት መቻሉን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) ገለፁ። በአዋሽ ተፋሰስ የጎርፍ አደጋ ስጋትን በዘላቂነት ለማስቀረት የተከናወኑ ተግባራት የአዋጭነት ጥናት ግኝት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለፁት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ተፋሰሶች የጎርፍ አደጋ ተጋላጭነትና የአፈር መሸርሸርን ለመቀነስ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በስምጥ ሸለቆና ኦሞ ተፋሰሶች የጎርፍ አደጋ ስጋት ተጋላጭነትን ለመቀነስ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል። በተለይም ባለፉት ሁለትና ሦስት ዓመታት በመካከለኛውና ታችኛው አዋሽ ተፋሰስ ላይ ከ250 ኪሎ ሜትር በላይ በወንዝ ግራና ቀኝ የውሃ መገደቢያ በመስራት የጎርፍ አደጋን የመከላከል ሥራ መከናወኑን አንስተዋል። በዚህም ወንዙ ሲሞላ መገደቢያውን አልፎ በመውጣት አደጋ ሲያደርስ የነበረውን ጎርፍ በመከላከል 70ሺህ 140 ሄክታር መሬት ወደ ልማት እንዲገባ መደረጉን ገልጸዋል። በዚህም ከ129 ሺህ በላይ የሚሆን የህብረተሰብ ክፍልን ከመፈናቀል አደጋ መታደግ ተችሏል ብለዋል። የአዋጭነት ጥናቱ ዓላማ የአዋሽ ወንዝን በዘላቂነት ከስጋት ነፃ በማድረግ ሙሉ በሙሉ ወደ ልማት ለማስገባትና ወንዙን በሚፈለገው መልኩ ጥቅም ላይ ለማዋል እንዲቻል ያለመ መሆኑንም ተናግረዋል። በወንዙ ግራና ቀኝ በተሰራው የጎርፍ መከላከል ሥራ የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ከማረጋገጥ ባለፈ የአደጋ ስጋትና ተጋላጭነትን መቀነስ መቻሉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የሚካሄደው አህጉራዊ የመሬት ፖሊሲ ጉባኤ
Nov 10, 2025 140
አዲስ አበባ፤ ህዳር 1/2018(ኢዜአ):- ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከዛሬ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል። “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያንና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የሚካሄደው ኮንፍረንስ መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ኮንፍረንሱን በጋራ አዘጋጅተውታል። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ይቀርባሉ። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠርና ቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ባርነት፣ የቅኝ ግዛት ዘመን መሬት የመንጠቅ ተግባርና በዘር ምክንያት መሬት ከማግኘት መገለል በአፍሪካውያንና ትውልደ አፍሪካውያን የመሬት መብቶች፣ ሀብት አጠቃቀምና እኩልነት ላይ ያሳደራቸውን አሉታዊ ተጽእኖዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ በመፍጠር ችግሩን በዘላቂነት መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይቶች ይካሄዳሉ። በመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ያሉ ውይይቶች ማጠናከር እና ፖሊሲ ተኮር ምላሾችን መስጠት ሌላኛው የኮንፍረንሱ አላማ ነው። የስርዓተ ጾታ እኩልነት፣ የአየር ንብረት ለውጥና ቴክኖሎጂዎችን ከመሬት ፖሊሲ እና አስተዳደር ጋር ማስተሳሰር ትኩረት ተሰጥቶታል። በኮንፍረንሱ የመሬት ፖሊሲ፣ የመሬት ፍትህ፣ የማካካሻ ፍትህ እና የመሬት ባለቤትነትን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ የፖሊሲ፣ የህግ እና ተቋማዊ ምክረ ሀሳቦች ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማትና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ። ኮንፍረንሱ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወትን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር ማስተሳሰር ይገባቸዋል -አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ
Nov 6, 2025 376
አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ መሪዎች የብዝሃ ህይወት አጀንዳን ከብሄራዊ ፖሊሲዎቻቸው ጋር በማቆራኘት ሊተገብሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ገለጹ። ከጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በቦትስዋና ጋቦሮኒ ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ጉባኤ በመሪዎች ደረጃ በተደረገ ስብስባ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የሀገራት መሪዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች፣ የዓለም የብዝሃ ህይወት ጥበቃ መሪዎች እና ተመራማሪዎች፣ ሀገር በቀል የማህበረሰብ መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። “የብዝሃ ህይወትን በዘላቂነት በመጠቀም የአፍሪካን ብልጽግና ማረጋገጥ” የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ መንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ ሃዳዲ ጉባኤው አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ በጀመረችው ጉዞ ውስጥ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ከኮንጎ ጥብቅ ደን እስከ ደቡብ አፍሪካው የኬፕ የአበባ ሀብት ቀጣና በአህጉሪቷ የሚገኙ ተፈጥሯዊ ምህዳሮች የህይወት፣ ባህል እና የኢኮኖሚ እድገት ምንጮች መሆናቸውን አመልክተዋል። የአየር ንብረት ለውጥ፣ ብክለት እና ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም በአፍሪካ የብዝሃ ህይወት ላይ ስጋቶችን እንደደቀኑ ተናግረዋል። የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ የተቀናጀ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋል ያሉት አምባሳደሯ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከአባል ሀገራት፣ ከቀጣናዊ ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት እና የግሉ ዘርፍ ጋር በመሆን የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ስትራቴጂ ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጠመ መልኩ እንዲተገበር በትብብር እንደሚሰራ ነው የገለጹት። ብዝሃ ህይወት እንደ ተጓዳኝ ጉዳይ ሳይሆን ለአፍሪካ ሰላም፣ አይበገሬነት እና ዘላቂ ልማት ባለው ቁልፍ ድርሻ ሊታይ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድም የአፍሪካ መሪዎች ብዝሃ ህይወት ከብሄራዊ ፖሊሲዎች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አሳስበዋል። ወጣቶች እና ሀገር በቀል ማህበረሰቦችን ማብቃት እንዲሁ በፋይናንስ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዓለም አቀፍ እኩልነት ለማስፈን መትጋት ትኩረት እንደሚያሻቸው ነው ያነሱት። የአፍሪካ ብልፅግና አረንጓዴ፣ ሁሉን አቀፍ እና ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል። የጋቦሮኒው ጉባኤ የአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ድንጋጌ ቀጣይ ለሚመጡ ትውልዶች መሰረት የሚጥል እንደሚሆንም ገልጸዋል። ጉባኤው በአፍሪካ ብዝሃ ህይወት ሀብቶች፣ እድሎች፣ ፈተናዎችና ቀጣይ እርምጃዎች በዋናነት መምከሩን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሄይቲ እና ጃማይካ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው ጎርፍ ሳቢያ የበርካቶች ሕይዎት አለፈ
Oct 31, 2025 528
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-በሄይቲ እና ጃማይካ የተከሰተው ‘ሃሪኬን ሜሊሳ’ የተሰኘው ወጀብና ዝናብ የቀላቀለ ከባድ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል። በሄይቲ የ30 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና ከ20 በላይ ሰዎች የገቡበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስካሁን ያሉበት ሁኔታ ያልታወቁ ሰዎችን የመፈለጉ ሥራም መቀጠሉን ባለሥልጣናቱ ለአልጄዚራ ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመላክተዋል። እንዲሁም የአውሎ ነፋሱ ሰለባ በሆነችው ሌላኛው ሀገር ጃማይካ የ19 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል። እስካሁን ከተመዘገቡት በጣም ኃይለኛ የአትላንቲክ አውሎ ነፋሶች አንዱ እንደሆነ የተነገረለት ሃሪኬን ሜሊሳ በሠዓት 295 ኪሎ ሜትር እንደሚከንፍ ተገልጿል። አውሎ ነፋሱ የጃማይካን ምዕራባዊ ክልል በመምታት አስከፊ ጉዳት ማድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ተናግረዋል። ሃሪኬን ሜሊሳ በካሪቢያን ቀጣና ኩባ፣ሄይቲ እና ጃማይካ በሰው ሕይወት እንዲሁም በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎም በካሪቢያን የሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ውጭ መሆናቸውን ዘገባው አመላክቷል። የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለመመለስና አካባቢዎቹንም የማጽዳት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተጠቅሷል።
የአፍሪካ ህብረት የ30 ቢሊዮን ዶላር የአቪዬሽን መሰረተ ልማት የኢንቨስትመንት እቅድ ይፋ አደረገ
Oct 31, 2025 434
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ):-የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ማዘመንን አላማ ያደረገ የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ከጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በአንጎላ ሉዋንዳ ሲካሄድ የነበረው ሶስተኛው የአፍሪካ መሰረተ ልማት ፋይናንስ ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአንጎላ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ጆአኦ ሎሬንቾ፣ የህብረቱ ተቋማት አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የአየር መንገዶች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ አማካኝነት የአህጉሪቷን አቪዬሽን መሰረተ ልማት በፋይናንስ በመደገፍ እና በማዘመን የተቀናጀ የአየር አገልግሎት እና ነጻ እንቅስቃሴን መፍጠር ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የምክክር መድረክ ተከናውኗል። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ በመድረኩ ላይ በአየር ትራንስፖርት ገበያው አማካኝነት የአህጉሪቷን የአቪዬሽን መሰረተ ልማት ለማዘመን የሚውል የ30 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት እቅድ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። እቅዱ አፍሪካ በቀጣይ 10 ዓመት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማሻሻል የሚያስፈልጋትን ከ25 እስከ 30 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በአፍሪካ እ.አ.አ በ2024 160 ሚሊዮን የነበረው የመንገደኞች መጠን እ.አ.አ በ2050 ወደ 500 ሚሊዮን ገደማ እንደሚደርስ የገለጸው ህብረቱ ኢንቨስትመንቱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና አቅምን ለማጎልበት እንደሚያስችል አመልክቷል። በኢንቨስትመንት እቅዱ አማካኝነት ገንዘቡ ለአውሮፕላን ማረፊያ፣ አውሮፕላን ጣቢያ እና ጥገና ማዕከላት መሰረተ ልማት፣ የአቪዬሽን ስርዓቶች ማዘመን፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለቁጥጥር ስራ፣ ለቴክኖሎጂ እና ተጓዳኝ ስራዎች እንደሚውል ተገልጿል። የአፍሪካ ህብረት 10 ቢሊዮን ዶላሩን ከአፍሪካ መንግስታት፣ ከቀጣናዊ የልማት ባንኮች እና ከባለቡዙ ወገን አጋሮች ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውቋል። ቀሪው 20 ቢሊዮን የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አጋሮች፣ የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች (sovereign wealth funds) እና የጡረታ ፈንዶችን ጨምሮ ከግል እና የተቋማት ኢንቨስተሮች ለማግኘት መታሰቡን ነው ያመለከተው። የሀብት ማሰባሰቡ የሚከናወነው በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት ገበያ ማዕቀፍ ሲሆን የ30 ቢሊዮን ዶላሩ ከእ.አ.አ 2025 እስከ 2035 ለሚተገበሩ ስራዎች የሚውል ነው። የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ ልማት እና ኢነርጂ ኮሚሽነር ሌራቶ ማታቦጅ አቪዬሽን የትራንስፖርት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ትስስር ስትራቴጂካዊ ሞተር እንዲሁም የአጀንዳ 2063 እና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ቁልፍ አቅም ነው ብለዋል። በኢንቨስትመንት እቅዱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ልማት መመዘኛዎችን ባሟላ እና ከካርቦን ልህቀት ነጻ በሆነ መልኩ እንደሚገነቡ አመልክተዋል። ህብረቱ ዘመናዊ፣ ውጤታማ እና ዘላቂ የአቪዬሽን ኔትወርክ በመፍጠር ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር፣ የአየር ትራንስፖርት ግንኙነት ስር እንዲሰድ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንዲያድግ በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት።
ለአህጉሪቷ ለዘላቂና አስተማማኝ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው
Oct 24, 2025 701
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ):-ለአህጉሪቷ አስተማማኝና ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ግንባታ አባል ሀገራት ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ ገለጹ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የአባል አገራት በግብርና፣ በእንስሳት፣ በዓሳ ሀብት፣ በገጠር ልማት፣ በውሃ፣ በአካባቢ እና በአየር ንብረት ለውጥ ዘርፎች ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡ በስብሰባው የሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም የማላቦ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2014 እስከ 2025) መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ አስር ዓመታት የሚተገበረው የካምፓላ አጀንዳ (እ.ኤ.አ 2026 እስከ 2035) ጸድቋል፡፡ በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የብሉ ኢኮኖሚ እና ዘላቂ አካባቢ ኮሚሽነር ሞሰስ ቪላካቲ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ብሎም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም አባል ሀገራት የራሳቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥም የግብርና ግብዓቶችንና ምርጥ ዘርን መጠበቀ እንዲሁም ብዝሃ ህይወትን ማልማትና መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የውሃ ኃብትን ከማሳደግ አኳያም ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ - ኒፓድ የግብርና፣ የምግብ ዋስትና እና የአካባቢ ዘላቂነት ዳይሬክተር ኤስቴሪን ፎታቦንግ የካምፓላ አጀንዳ (2026–2035) በአፍሪካ የግብርና-ምግብ ሥርዓቶች ላይ የለውጥ ምዕራፍ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ገልጸዋል፡፡ ከአጀንዳው ግቦች መካከልም ዘላቂ የምግብ ምርትን፣ አግሮ-ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እና ንግድን ማጠናከር፣ ለግብርና-ምግብ ሥርዓት ለውጥ ኢንቨስትመንትና ፋይናንስን ማሳደግ ብሎም የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚሉ እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ልማት ኤጀንሲ የካምፓላ አጀንዳ ስትራቴጂ እንዲሳከ ምቹ ሁኔታዎችን ሲያዘጋጅ መቆየቱንም ጠቁመዋል፡፡ የዩጋንዳ ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ እና የአምስተኛው የአፍሪካ ኅብረት የግብርና፣ የገጠር ልማት፣ የውሃ እና የአካባቢ ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካይ ፍሬድ ብዊኖ ክያኩላጋ የካምፓላ አጀንዳ የእንስሳት ሃብትን ማሳደግ ላይ ትልቅ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል፡፡ በዚህም ለእንስሳትና ለዓሳ እርባታ ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የእንስሳት መኖ ማሳደግ፣ ለእንስሳት ጤና እንዲሁም የዘረመል መሻሻልም ከትኩረት መስኮች መካከል ናቸው ብለዋል፡፡ የካምፓላ አጀንዳ የአፍሪካ ግብርና ልማት መርሃ ግብር ታላላቅ ግቦች መሳካት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ሐተታዎች
" መሬት እና ፍትህ" - የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የእድገት ጉዞ
Nov 11, 2025 202
መሬት በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ነው። መሬት ከአፍሪካውያን የአኗኗር ዘይቤ፣ ማንነት፣ ባህል እና ማህበራዊ መስተጋብር ጋር የተቆራኘ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ከቅኝ ግዛት ዘመን በፊት የአፍሪካ በርካታ ማህበረሰቦች መሬት በልማዳዊ እና ባህላዊ ስርዓት ያስተዳድሩ ነበር። የቤተሰብ ጎሳዎች ወይም ማህበረሰቦች መሬት የመጠቀም፣ የማስተዳደር እና ባህላዊ መንገዶች በሰጣቸው መብት ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። በእንደዚህ አይነት ስርዓት ውስጥ መሬት ከሀብት ባለፈ ከማህበራዊ ግንኙነቶች፣ መንፈሳዊ መስተጋብሮች እና የተፈጥሮ ሀብቶችን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት ጋር ትስስር አለው። በቅኝ ግዛት ዘመን የአውሮፓ ኃይሎች በስምምነቶች፣ በአዋጆች እና ኃይል በመጠቀም መሬት የቁጥጥር፣ የብዝበዛ እና ሀብትን የመንጠቂያ መሳሪያ አድርገውታል። መሬት ፖሊሲ ኃይልን ማጠናከሪያ እና የኢኮኖሚ ብዝበዛ መንገድ ሆኗል። አፍሪካውያን በልማዳዊ እና ባህላዊ መንገዶች የነበራቸውን የመሬት መብቶች በመንጠቅ ከአፍሪካ ውጪ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የሰፈራ ፕሮግራም ማካሄጃ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። በዚህም ከፍተኛ የሆነ የአፍሪካ ሀብት ሲበዘበዝ ቆይቷል። ሀገር በቀል ማህበረሰቦች ከመሬታቸው የመፈናቀል እና የመገለል ሰለባ ሆነዋል። በቅኝ ገዢዎች የወጡ የመሬት ፖሊሲዎች፣ የመሬት ምዝገባ እና የመሬት አስተዳደር ስርዓት የአፍሪካ መሬት ተጠቃሚዎችን መብት የነፈገ ነበር። የቅኝ ግዛት የቀረጸው የመሬት አስተዳደር ስርዓት አፍሪካውያንን ህጋዊ የመሬት ባለቤትነትን ያሳጣ ነው። የአፍሪካ ሀገራት ከነጻነታቸው በኋላ እኩልነት ያልተረጋገጠባቸውን የመሬት መብቶች እና ስርዓቶች ወርሰዋል። ሀገራት የመሬት ፖሊሲዎቹን አሁን ያሉ የልማት ግቦችን፣ የፍትህ ፍላጎቶች እና ወቅታዊ የአስተዳደር ማዕቀፎች ባማከለ ሁኔታ የመቀየር ስራ በማከናወን ላይ ናቸው። በቅኝ ግዛት ዘመን የመሬት መብታቸውን ላጡ ዜጎች በተለይም ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተመለሰላቸው ይገኛል። ይሁንና የቅኝ ግዛት የመሬት ቅድሚያ መጥፎ፣ በሀገራት ብሄራዊ ህግ ውስጥ ያሉ የተደባለቁ የህግ ማዕቀፎች (ለምሳሌ ልማዳዊ ህጎች ከመደበኛ ህጎች ጋር መደባለቅ) እና የተቋማት የአስተዳደር ስርዓት አለመናከር በአፍሪካ ፍትሃዊ እና እኩልነት የመሬት ስርዓት የማስፈን ጉዞ ላይ ጋሬጣ ሆኗል። ዛሬ ላይ አፍሪካ አጀንዳ 2063 እና ዘላቂ ልማት ግቦች እየተገበረች ትገኛለች። የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎች አንኳር ምሰሶ ተደርገው ከሚጠቀሱት ጉዳዮች መካከል አንዱ መሬት ነው። እኩል የመሬት መብት የምግብ ዋስትና እና ስርዓተ ጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ፣ ለከባቢ አየር ጥበቃ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ የአጀንዳ 2063 ሰነድ ያስረዳል። የአፍሪካ ህብረት ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በመተባበር በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ላይ ማዕቀፎች እና የህግ አሰራሮችን በመቅረጽ እያስተዋወቁ ይገኛሉ። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመሬት ህጎችን የተሰናነሰኑ እንዲሆኑና የተቋማት አቅምን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ ላይ ነው። “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ኮንፍረንሱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በጋራ በመተባበር ነው። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙ እና ለነባራዊ እውነታዎች ምላሽ የሚሰጡ የመሬት ፖሊሲ ምርጥ ተሞክሮዎች በኮንፍረንሱ ላይ እየቀረቡ ይገኛል። ህዳር 1 በነበረው የጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ስብሰባ በወሳኝ ወቅት የተዘጋጀ ነው ብለዋል። አፍሪካውያን ያላቸውን ሰፊ የመሬት ሀብት በቅኝ ግዛት አሰራሮች ሳቢያ በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው በአፍሪካ መሬት ዛሬም የግጭትና የኢ-ፍትሐዊነት መገለጫ ሆኗል ብለዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር በሴቶች፣ በወጣቶችና በዝቅተኛ አርሶ አደሮች ዘንድ ኢ-ፍትሐዊነትን በማንገስ ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት መፍጠሩን ገልጸዋል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ስብሰባ ከአፍሪካ ሕብረት 2025 "የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን" መሪ ሀሳብ ጋር የተጣጣመ መሆኑን አንስተው፤ ዓላማው አፍሪካውያን ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ብለዋል። የአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የካሳ ጥያቄ ያለፈውን ማስመለስ ሳይሆን አሁን ባለው የዓለም የፋይናንስ ስርዓት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል። አፍሪካ 65 በመቶ ያልታረሰ መሬት፣ ከዓለም ኢንዱስትሪ ሁለት በመቶ ብቻ ድርሻ ያላት፣ ለአየር ንብረት ለውጭ ተፅዕኖ ያላት ድርሻ ከአራት በመቶ በታች የሆነ አህጉር መሆኗን አንስተዋል። በአፍሪካ የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን በማዘመን ፍትሐዊነትን ማስፈን ጊዜው አሁን ነው ያሉት ዋና ጸኃፊው፣ ሴቶችን ወጣቶችና ዝቅተኛ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን የዜጎችና ዳያስፖራ ዳይሬክተር አምር አልጆዋሊ የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ የአህጉሪቱን መፃኢ ጊዜ ለመቀየር ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። በአፍሪካና ዘርዓ አፍሪካውያን ላይ የደረሰው በደል ዕውቅና ማግኘት እንዳለበት ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ለሕብረቱ መሪ ሀሳብ ትግበራ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የመሬት አስተዳደር የፍትሐዊነት ምልክት መሆኑን በማንሳት፤ የመሬት ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መስፈን አለበት ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 በማሳካት አካታች ብልፅግናና ሰላምን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። ሕብረቱ በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ግልፅ አሰራር እንዲሰፍን ለአባል ሀገራት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ እስከ ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል። ውጤታማ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመሬት አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣ ተቋማዊ አቅምን መፍጠር እና የቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የቅኝ ግዛት አሻራዎች እና ወቅታዊ የኢ-ፍትሃዊነት ጉዳዮች በመሬት ባለቤትነት እና አስተዳደር ያሳደሯቸውን ተጽእኖዎች ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ይገልጻሉ። በመሬት ፖሊሲ ቀረጻ፣ ትግበራ እና ቁጥጥር አቅምን መገንባት፣ የእውቀት ሽግግርን ማሳደግ እና የፖሊሲ ቁርጠኝነትን ወደ ሚጨበጥ የተግባር ምላሽ የመቀየር ጉዳይም አጽንዖት የሚሰጣቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ህብረቱ ገልጿል። በአህጉራዊ ኮንፍረንሱ ላይ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት፣ የህብረቱ ተቋማት እና አደረጃጀቶች ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ የፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ትውልደ አፍሪካውያንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ ሁነት ነው። የመሬት ፖሊሲ ጉባኤው አፍሪካውያን ፍትሃዊ እና ዘላቂ የመሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነታቸውን እያሳዩበት የሚገኝ መድረክ ነው። ጉባኤው አፍሪካውያን ከባለፈው ታሪክ በመማር ፖሊሲ፣ ጥናት እና የማህበረሰብ ድምጾችን በማቀናጀት ረገድ ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው። ጉባኤው የመሬት ፍትህን የማስፈን፣ አይበገሬነትን የመገንባት እና ለሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ብልጽግና የማረጋገጥ የጋራ ራዕይ በመደገፍ ረገድ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
Nov 7, 2025 291
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንገት በላይ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪም ኦሊያድ ታረቀኝ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለ ጆሮ ህመም መንስዔ እና መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ አብራርተዋል። የጆሮ ህመም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ኦሊያድ ገለጻ፤ በጆሮ አካባቢ ያሉ የአካል ክፍሎችን የሚያጠቁ ህመሞች የጆሮ ህመም ሊባሉ ይችላሉ። በሳይንሱ የውጨኛው፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው የጆሮ ክፍል ህመም ተብለው እንደሚለዩ ጠቅሰው፤ እነዚህን ክፍሎች የሚያጠቁ የተለያዩ የህመም ዓይነቶች እንዳሉም አመላክተዋል። የጆሮ ህመም ዓይነቶች በተለያዩ መንስዔዎች የተለያዩ ህመሞች እንደሚከሰቱ ጠቁመው፤ ከእነዚህ መካከል በስፋት የሚከሰተው በኤንፌክሽን የሚከሰት የጆሮ ህመም መሆኑን ተናግረዋል። ከአደጋዎች፣ ህመሞችና ጉዳቶች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የጆሮ ክፍሎች ህመሞች እንዳሉም በመጠቆም። እንዲሁም ከዕባጮች (ዕጢዎች) ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጆሮ ህመሞች እንዳሉ አመላክተዋል። በውጨኛው የጆሮ ክፍል የሚከሰቱ ከአጥንትና ከቆዳ የሚነሱ ዕባጭና ዕጢዎች፣ ከመካከለኛው የጆሮ ክፍል የሚነሱ በአብዛኛው ከደም ሥር ጋር የተያያዙ ዕጢዎች እንዲሁም ከውስጠኛው የጆሮ ክፍል ከነርቭ የሚነሱ የተለያዩ ዓይነት ዕጢዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም አብራርተዋል። ለጆሮ ህመም አጋላጭ ምክንያቶች የጆሮ ህመም በሁሉም ጾታና የዕድሜ ክልል ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ በአብዛኛው አጋላጭ ምክንያቶች ተብለው ከሚነሱት መንስዔዎች መካከል ከታች የተጠቀሱት ዋነኞቹ መሆናቸውን ያብራራሉ። o ባብዛኛው ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች (ልጆች ባላቸው ያልዳበረ በሽታዎችን የመከላከል ዐቅም እንዲሁም አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቻቸው በደንብ ባለመዳበራቸው ሊከሰት የሚችል ነው።) o ዕድሜ ሲጨምር የጆሮ መዳከም ችግር ሊኖር ስለሚችል የመስማት ዐቅም እየቀነሰ ሊሄድ ይችላል። o ለተለያየ ከባድ ድምጽ መጋለጥ ለጆሮ ህመም ወይም የተለያየ ደረጃ ላላቸው የመስማት ችግሮች ሊዳርግ ይችላል። o ሲጋራ ማጨስ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት ጭሶች መጋለጥ ለጆሮ ህመም ሊያጋልጥ ይችላል ተብሎ እንደሚታሰብ አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ምልክቶች ምልክቶቹ እንደ ህመሙና ህመሙ እንደተከሰተበት ቦታ የተለያዩ መሆናቸውን ዶክተር ኦሊያድ ይገልጻሉ። ለምሳሌ በኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት የጆሮ ህመም ከሆነ እንደተከሰተበት የጆሮ ክፍል ምልክቱ ይለያያል ይላሉ። ለአብነትም የውጨኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የጆሮ ኢንፌክሽን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል መጠዝጠዝ፣ ውጋትና ማሳከክ ዋናኞቹ ናቸው ብለዋል። ራሱ ይህ ህመም በመካከለኛው የጆሮ ክፍል ላይ ሲከሰት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ትኩሳት፣ አልፎ አልፎ ከባድ የጆሮ ውጋት መኖር፣ የህመሙ ደረጃ እየጨመረ ሲሄድም የተለያዩ ፈሳሾችን ሊያሳይ ይችላል (ለምሳሌ እንደ ውኃ የቀጠነ ፈሳሽ፣ ወፍራም መግል የመሰለ ፈሳሽ፣ አንዳንድ ጊዜ ደም የቀላቀለ ፈሳሽ ሊሆን ይችላል ሲሉ አብራርተዋል።) በተለያዩ ዕባጮችና ዕጢዎች የሚከሰት የጆሮ ህመም ሲሆን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል፤ የጆሮ መደፈን ስሜት (ጆሮ ድፍን ብሎ ለመስማት መቸገር)፣ የተለያየ ዓይነት የጆሮ ውስጥ ድምጽና ጩኸቶች መኖር (አንዳንድ ጊዜ ከልብ ምት ጋር አብሮ ሊሰማ የሚችል የጆሮ ውስጥ ጩኸት ሊሆን ይችላል) ብለዋል። በውስጠኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚከሰት የዕጢ ዓይነት ደግሞ የመስማት ደረጃ መቀነስ፣ ማዞር እና ቫላንስ እስከ ማጣት (ሚዛንን ጠብቆ ለመንቀሳቀስ እስከመቸገር) የሚያደርሱ ምልክቶችን ሊያሳይ እንደሚችል ጠቁመዋል። ሰዎች ለጆሮ ህመም እንዳይጋለጡ ምን ያድርጉ? ሰዎች የተለያዩ ጥንቃቄዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መክረው፤ ከእነዚህ ጥንቃቄዎች መካከልም፡- o በልማድ የሚደረጉ ጭራሽ ለጉዳት አጋላጭ የሆኑ ጆሮን የማጽዳት ተግባራት (‘የጆሮን ንጽህና እየጠበቅሁ ነው’ ብሎ በማሰብ ጆሮን ለማጽዳት የሚደረጉ ልማዶችን) ማስወገድ፤ o ጆሮ ለከባድ ድምጽ እንዳይጋለጥ ማድረግ። ለምሳሌ ለረጅም ሠዓት ‘ኤርፎን’ መጠቀም ለጆሮ ህመም እንደሚያጋልጥ በመገንዘብ የሠዓቱን እና የድምጹን መጠን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። ‘ኤርፎን’ በአንድ ጊዜ ለ60 ደቂቃ የድምጽ መጠኑ ከ60 በመቶ ባልበለጠ ጊዜ መጠቀም ይመከራል ያሉት ዶክተር ኦሊያድ፤ ከዚህ ደቂቃ በላይ በአንድ ጊዜ መጠቀም ሲያስፈልግ በየመሀሉ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ጆሮን ማሳረፍ እንደሚገባ ይመክራሉ። በሌላ በኩል ማሳከክን ጨምሮ የጆሮ ህመም ስሜት ሲኖር በወቅቱ ተገቢውን የሕክምና ዕርዳታ በማድረግ ህመሙ ወደ ከፋ ደረጃ ሳይደርስ መታከም የጥንቃቄው አካል መሆኑን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም ሕክምና ሕክምናው እንደ ህመሙ ዓይነት እንደሚለያይ አስገንዝበው፤ በአጠቃላይ በሚዋጡ፣ በመርፌ በሚሰጡ፣ በጆሮ ውስጥ በሚጨመሩ እንዲሁም በሚቀቡ አማራጮች ሕክምናው እንደሚሰጥ አብራርተዋል። ከላይ ከተጠቀሱት የሕክምና አማራጮች አልፎ የመስማት ደረጃ መቀነስና መቸገር ከተስተዋለ የቀዶ ሕክምና ማድረግ ብሎም የማዳመጫ ማገዣ መሣሪያ መጠቀም የሕክምናው አካል መሆናቸውን አስረድተዋል። የጆሮ ህመም በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ከ5 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ባላቸው ልጆች ላይ 8 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ60 በላይ በሆኑ ሰዎች ደግሞ እስከ 73 በመቶ ድረስ የመስማት ችግር እንደሚያጋጥም ጥናት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። ጆሮ ላይ የሚከሰቱ ህመሞች የመስማት ችግርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት
Nov 3, 2025 481
ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት አጋርነት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ያላቸው ታሪካዊ ወዳጅነት በርካታ ክፍለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ወገኖች ግንኙነት በአራተኛው ክፍለ ዘመን እንደጀመረ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአክሱም ንጉስ ኢዛና ወቅት ኢትዮጵያ ከምስራቅ ሮም መንግስት ጋር ዲፕሎማሲያዊ እና ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደነበራት ይነገራል። 15ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያው በሰነድ የተደገፈ የኢትዮጵያ እና አውሮፓ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ግንኙነቶች የተደረጉበት ወቅት ነው። እ.አ.አ በ1441 የኢትዮጵያ ልዑክ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምክር ቤት (The Council of Florence) ስብስባ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ከሰሃራ በታች በሚገኙ ሀገራት እና አውሮፓ መካከል የተደረገ የመጀመሪያው ግንኙነት እንደሆነ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ የኢትዮጵያ ልዑካን ወደ ሮም፣ ቬኒስ እና ሊዝበን ጉብኝቶችን አድርገዋል። ከዛ በኋላ ባሉ ክፍለ ዘመናት በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሀገራት መካከል በርካታ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ እንቅስቃሴዎች እና የጉብኝት ልውውጦች ተደርገዋል። እ.አ.አ 1975 ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ማህበረሰብ ጋር ዘመናዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመረችበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት (በቀድሞ አጠራሩ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ) እ.አ.አ ፌብሩዋሪ 28 1975 በቶጎ ሎሜ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱ የሎሜ ድንጋጌ እየተባለ ይጠራል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያ እና ለአውሮፓ ህብረት ትብብር መሰረት የጣለ ታሪካዊ ሁነት ነው። የኢኮኖሚ ልማት፣ የንግድ ትብብር፣ የልማት ድጋፍ እና የወጪ ንግድ የስምምነቱ አበይት ማዕቀፎች ናቸው። የሎሜ ስምምነት አራት ጊዜ ማሻሻያ ተደርጎበታል። ማሻሻያዎቹ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በፖለቲካ፣ ዴሞክራሲ፣ ኢንዱስትሪ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ቀጣናዊ ትስስርን ጨምሮ ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን የትብብር አድማስ ማስፋትን ያለሙ ናቸው። እ.አ.አ በ2000 የሎሜ ስምምነት ወደ ኮቶኑ ስምምነት ተሸጋገረ። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በቤኒን ኮቶኑ አዲስ የትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ። የኮቶኑ ስምምነት የሁለቱን ወገኖች አጋርነት ያስቀጠለ ነው። የፖለቲካ ምክክሮች፣ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶች አካቷል። ስምምነቱ ሁለት ጊዜ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን እ.አ.አ በ2020 ማዕቀፉ እስከ እ.አ.አ 2024 እንዲቀጥል ተወስኗል። እ.አ.አ በ2023 በሶሞአ በተደረገ ውይይት የድህረ ኮቱኑ ስምምነት የተባለለት ማዕቀፍ በአፍሪካ ህብረት እና አውሮፓ ህብረት መካከል ተፈርሟል።ኢትዮጵያ የዚህ ስምምነት ተጠቃሚ ናት። እ.አ.አ በ2016 የተፈረመው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ስትራቴጂካ ትስስር ማዕቀፍ ስምምነት የበለጠ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ያጸና ነው። የአውሮፓ ህብረት ያቋቋመው የአውሮፓ ቡድን በኢትዮጵያ (Team Europe in Ethiopia) ህብረቱን፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና 21 የህብረቱ አባል ሀገራትን አቅፎ የያዘ ነው። ከአውሮፓ ህብረት 27 አባል ሀገራት መካከል 21ዱ በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ውክልና አላቸው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ሰላም እና ፀጥታ፣ የምግብ ስርዓት፣ ዘላቂ ኢነርጂ ልማት፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የግሉ ዘርፍ ልማት እና ትራንስፖርት ጨምሮ በሌሎች መስኮች ትብብር አላቸው። የአውሮፓ ህብረት በኮቶኑ ስምምነት የነበረውን የአውሮፓ የልማት ፈንድ ድጋፍ በመተካት ከእ.አ.አ 2021 እስከ 2027 የሚቆይ የፋይናንስ ማዕቀፍ እየተገበረ ይገኛል። 629 ሚሊዮን ዩሮ ፈሰስ የሚደረግበት ይህ ማዕቀፍ ከአውሮፓ ህብረት ተቋማት እና አባል ሀገራት አስተዋጽኦ የሚገኝ ሲሆን በየዓመቱ በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ለሚከናወኑ ስራዎች የሚውል ነው። ታዳሽ ኢነርጂ፣ ዲጂታላይዜሽን፣ ዘላቂ የስርዓተ ምግብ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ የሰው ሀብት ልማት፣ የፍልሰት አስተዳደር እና ሰላም ግንባታ ድጋፍ የሚደረግባቸአው መስኮች ናቸው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ትብብር ውስጥ የሚጠቀሱ አንኳር ጉዳዮች አሉ። ከቅርቡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ወደ ቤልጂየም ብራሰልስ በማምራት ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ፍላጎታቸውን መሰረት አድርገው ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከርና ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ከውይይቱ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። "ግሎባል ጌትዌይ ፓርትነርሺፕ" በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን የሚመራ የአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ ሲሆን ህብረቱ ከተለያዩ ሀገራት በዲጂታላይዜሽን፣ በታዳሽ ኃይል፣ በስርዓተ ምግብ፣ በጤና፣ በዘላቂ ግብርና፣ በሰላም እና ደህንነትን ጨምሮ በቁልፍ ዘርፎች ያለውን ትብብር እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው። ስምምነቱ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የዲፕሎማሲ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርስ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ ገልጸዋል። በተጨማሪም ስምምነቱ ሁለቱ ወገኖች እ.አ.አ በ2016 ለተፈራረሙት የስትራቴጂክ ትስስር የጋራ ድንጋጌ አዲስ አቅም እንደሚፈጥርም ተመላክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ባለፈው ሳምንት ለ2025 ዓመታዊ የድርጊት መርሃ ግብር የ90 ሚሊዮን ዩሮ የፋይናንስ ስምምነት በአዲስ አበባ መፈራረማቸው የሚታወስ ነው። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ በመስከረም ወር 2018 ዓ.ም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብስባ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከስበሰባው ጎን ለጎን ከአውሮፓ የኢንቨስትመንት ባንክ ከዓለም አቀፍ አጋርነት ዳይሬክተር ቱራያ ትሪኪ ጋር መክረው ነበር። በወቅቱ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም (RUFIP III) ሶስተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ የሚታወስ ነው። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተፈራርመውታል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የ240 ሚሊየን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት በመጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል። ድጋፉ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን ልማት በተለያዩ ወሳኝ ዘርፎች ለማጠናከር የሚውል ነው። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም የጋራ ምክክር በአዲስ አበባ ያደረጉ ሲሆን በውይይቱ የጋራ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ሁለቱ ወገኖች በህዳር ወር 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተመሳሳይ የጋራ የምክክር መድረክ ማድረጋቸው አይዘነጋም። በ2011 ዓ.ም ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት በጤና ዘርፍ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የ20 ሚሊዮን ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል። ዲፕሎማሲያዊ ትስስሩ ሁለቱ ወገኖች በሰኔ ወር 2008 ዓ.ም ከተፈራረሙት የስትራቴጂክ የጋራ ድንጋጌ በኋላ የበለጠ እየተጠናከረ መጥቷል። ዛሬ በፈረንሳይ ፓሪስ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው። በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን የአፍሪካ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጌዛ ስትራመር፣ የፈረንሳይ የወጪ ንግድ እና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር መልዕክተኛ ኒኮላስ ፎርሲየር፣ የሜዴፍ ኢንተርናሽናል ምክትል ፕሬዝዳንት ፋብሪስ ላሳች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች እና የንግድ መሪዎች ተገኝተዋል። ፎረሙ በኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከርና አዳዲስ የኢንቨስትመንት እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በዝርዝር አስረድተዋል። ሪፎርሙ የግል ኢንቨስመንት መሳብ እና ኢትዮጵያ ከዓለም ኢኮኖሚ ጋር ያላትን ትስስር የበለጠ ማጠናከርን ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የኢኮኖሚ ትብብር እያደገ መምጣቱን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም በኢትዮጵያ ተቋማትና በአውሮፓ ኩባንያዎች መካከል በኢኖቬሽን፣ በእሴት መጨመርና የጋራ ብልጽግናን መደገፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል። ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጿል። ፎረሙ የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪዬሽን፤ በታዳሽ ኃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ነው። የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያልም ተብሏል። የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ከግማሽ ክፍለ ዘመናት በላይ ጸንቶ የቆየ ወዳጅነት ነው። የሁለቱ ወገኖች ትብብር በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ላለው ግንኙነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
የብዙዎች ቤት…
Oct 27, 2025 633
እስካሁን በተደረገ የጥናት ውጤት መሠረት ከ81 በላይ የአጥቢ እንስሣት፣ ከ450 በላይ የአዕዋፍ እና ከ400 በላይ የእፅዋት ዝርያዎች መኖሪያ ነው። ከእነዚህ መካከል አምስቱ የአዕዋፍ ዝርያዎች በዚህ ሥፍራ ብቻ ይገኛሉ፤ ከአምስቱ መካከል በተለይም የአንዷ ዝርያ ዓለም አቀፍ የዘርፉ ተመራማሪዎችንና ጎብኚዎች ቀልብ መሳቡ ይጠቀሳል። ከአካባቢው ተፈጥሯዊ አቀማመጥና የአየር ሁኔታ ጋር መጣጣም የቻሉ የቆላ እፅዋት (ዛፎች) በምቾት በስፋት እንደሚገኙበትም ይገለጻል። የተመሠረተው በ1958 ዓ.ም ሲሆን፤ ስፉቱም 591 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ነው፤ በቁጥርም ሆነ በሥብጥር የብዙዎች መኖሪያ የሆነው ይህ ሥፍራ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ይሰኛል። መንግሥት በሰጠው ትኩረት ከነበረው በተሻለ ሁኔታ እንስሣቱም ሆኑ እፅዋቱ እየኖሩ ነው፤ ከሕገ ወጥ ድርጊትም እንዲጠበቁ ማድረግ መቻሉን የፓርኩ ኃላፊ አደም መሐመድ ለኢዜአ አረጋግጠዋል። በፓርኩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁንም ለ247 ወገኖች ቋሚ እና ለ2 ሺህ 535 ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል። ባሳለፍነው ዓመትም በ1 ሺህ 751 የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች እንደተጎበኘ ኃላፊው ገልጸዋል።
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 2008
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ 7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 2279
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 3150
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 3244
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ?
Oct 13, 2025 1277
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 859
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6697
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 5169
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
መጣጥፍ
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ"
Nov 12, 2025 144
"ከትውስታ ወደ አዲስ ተስፋ" ብርሃኑ ፍቃዱ -ከሰቆጣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልካዓምድራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረት ያለው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ማብራራታቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ የባህር በሯን ያጣችበትን የ30 ዓመታት ታሪክ ለመቀልበስ ይህን ያህል ዓመት እንደማይወስድ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ ሕጋዊና ተቋማዊ መሰረት የሌለው የሚያስቆጭ ብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል ስለመሆኑም አንስተዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ እና አቶ አድማሱ ደሳለኝ፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር የተወለዱበት ስፍራ፣ የኖሩበት ቀዬ፣ ያሳደጋቸው ማህበረሰብ ... የዘመናት ትዝታና ትውስታቸው እንደሆነ ይገልጻሉ። ይህን የታሪካቸው አካል የሆነውን የባሕር በር ማጣትም የሁል ጊዜ ፀፀትና እንደ ሰውነት ጥላ አብሮዋቸው የሚዞር እውነታ ነው። ከአካባቢው ርቆ ለሚገኝ ሰው ትውስታውን ሲያወራ ለሌላው ተረት ተረት፤ ለራስ ደግሞ የውስጥ ቁስል ማገርሸት ሆኖ ነው የሚሰማው ይላሉ። ኢትዮጵያም የአሰብ ወደብንና የቀይ ባህር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሸፍጥ ማጣቷ በቀይ ባህር ላይ እየዋኙ፣ ውሃ እየተራጩ፣ በዳርቻው ነፋሻማ ስፍራ እየተዝናኑ... ለኖሩት ለእነ መለሰ እና አድማሱ መቼም የማይረሳ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ለአለም ማሕበረሰብ ጥያቄውን ሲያሳውቁ ተደብቆ ለቆየው ትውስታቸው አዲስ ተስፋ እንደሰጣቸውም ለኢዜአ ተናግረዋል። አቶ መለሰ ይሄይስ በአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል ለ12 ዓመታት እንዳገለገሉ በትውስታና ቁጭታቸውን ወደ ኋላ ተመልሰው ያወሳሉ። አሁን በሰቆጣ ከተማ የሚኖሩት አቶ መለሰ ይሄይስ ፤ የአሰብ ወደብ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት ተደማሪ አቅም ነበር በወቅቱ ይላሉ። ይህን የአሰብ ወደብንና የቀይ ባሕር መዳረሻን በፖለቲካዊ ሴራ ኢትዮጵያ ስታጣ ይሰሩበት ከነበረው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ስራ አቁመው ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሰቆጣ መምጣታቸውን አውስተዋል። በራሳቸው ላይ ከደረሰባቸው የስራ እና ሃብትና ንብረት ማጣት ፣ እንግልትና ሌሎች ችግሮች በላይ ኢትዮጵያ ከባሕር በር የተነጠለችበትን ሁኔታ ሲያስቡና ሲያሰላስሉ እንደሚያስቆጫቸው ይገልጻሉ። ኢትዮጵያ የቀይ ባሕርን በማጣት የባሕር በር ብቻ ሳይሆን የገቢና ወጭ ንግድን፣ የነዳጅ ማጣሪያ ጭምር ነው ያጣችው ያሉት አቶ መለሰ፤ አሁን ጥያቄው መነሳቱ ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ ገናናነቷ ለመመለስ ያለመ አበረታች ተግባር እንደሆነ ተናግረዋል። መንግስት ያነሳው የባሕር በር ጥያቄም የዘመናት ቁጭታችንን፣ ብስጭታችንን እና ህልማችንን ከተደበቀ ትውስታ፤ ወደ አዲስ ተስፋ የወሰደ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ህጋዊና ታሪካዊ ነው ያሉት አቶ መለሰ ፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝም ለአዲሱ ትውልድ በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል። ከ1973 ዓ.ም ጀምረው ለአስር ተከታታይ ዓመታት በአሰብ ወደብ የሲቪል መሃንዲስ ክፍል ሰራተኛ እንደነበሩ ያወሱት አቶ አድማሱ ደሳለኝ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የባሕር ባር ባለቤት በሆነችባቸው ዘመናት ገናና እና የተከበረች ሀገር ሆና መቆየቷን አንስተዋል። የባሕር በሩ የኢትዮጵያ የገቢና ወጭ ንግድ የሚሳለጥበት እንደነበር አስታውሰው፤ ይሄን ታላቅ ትሩፋትና ፀጋ ለማስመለስ የተጀመረው እንቅስቃሴ ቁጭትና ትውስታችንን ወደ አዲስ ተስፋ የቀየረ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በታሪካዊ ጠላቶችና ባንዳዎች እኩይ ሴራ የባሕር በር ካጣች ወዲህ ጥያቄውን ማንሳት የማይቻልበት የአፈናው ዘመን አክትሞ በለውጡ መንግስት መነሳቱ አበረታችና ለማስመለስም ከፍተኛ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። እኔም ባለኝ አቅም ሁሉ ስለባሕር ባር አስፈላጊነት፣ ጥቅምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤ በመፍጠር ለስኬታማነቱ የድርሻዬ እወጣለሁ ሲሉም ገልጸዋል።
ባሕር በር -የታሪክና የእድገት ስብራት ወጌሻ
Nov 5, 2025 490
ባሕር በር የታሪክ እና የእድገት ስብራት ወጌሻ በቀደሰ ተክሌ የምሥራቅ አፍሪካዋ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ስሟ ገኖ እንዲነሳ ካደረጓት መካከል የሰው ዘር መገኛነት፣ የራሷ የሆነ የአስተዳደር ሥርዓት፣ የዘመን አቆጣጠር፣ ቋንቋና ፊደል ያላት ሉዓላዊት ሀገር መሆኗ ተጠቃሽ ነው ። የገናና የጥበብ ባለቤት መሆኗን አክሱም እና ላሊበላ ዛሬም ቆመው ይመሰክሩላታል። በጥንት ጊዜ ወደብ የስልጣኔ ተጽዕኖ ፈጣሪነት መገለጫ በነበረበት ጊዜ ኢትዮጵያም ስሟ ጎልቶ ይነሳ ነበር። ወደብ ዓለምን እርስ በእርስ ከማስተሳሰር ባለፈ የግብይት የጀርባ አጥንት ሆኖ ሲያገለግል ቆይቷል፤ ዛሬም እያገለገለ ይገኛል። ሀገራት አዋጭ የንግድ ስትራቴጂ ቀይሰው የተለያዩ ወደቦችን የመጠቀም ልምዳቸው በታሪክ ውስጥ ጎልቶ የሚነሳ ነው። የንግድ ሥርዓታቸውን በወደብና በየብስ ከሚያከናውኑ የዓለም ሀገራት መካከል ደግሞ ኢትዮጵያ አንዷ ናት። የታሪክ ድርሳናት እንደሚያሳዩት ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘመነ መንግስታት የተለያዩ ወደቦችን በባለቤትነት አስተዳድራለች። ከአክሱም ዘመነ መንግሥት ጀምሮ እስከ ደርግ መንግስት ድረስ አዱሊስ፣ አሰብ፣ ዘይላ፣ ምጽዋና ሌሎች ወደቦችን ለኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ትገለገል ነበር። ይሕ የኢትዮጵያ የወደብ ባለቤትነት ታሪክ እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ የዘለቀ እንደነበር በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሰቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር ትምሕርት ክፍል መምሕር አጥናፉ ምትኩ ይናገራሉ። ወደብ ከኢኮኖሚያዊ ጥቅም ባሻገር ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ፋይዳው ከፍተኛ እንደሆነም አውስተዋል። በታሪክ ኩነት ውስጥ የተፈጠረ ሴራና ተንኮል ኢትዮጵያ የባሕር በር አልባ ሀገር እንድትሆን አድርጓታል። ይሕም ከሆነ ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ ተቆጥሯል። በዚሕም ኢትዮጵያ ለወደብ ኪራይ በየዓመቱ ብዙ ቢሊዮን ብር እየከፈለች የወጪ እና ገቢ ንግድን የማንቀሳቀስ እዳ ተጭኖባታል። ይሕም የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ወደ ኋላ ከሚጎትቱ ጉዳዮች አንዱ ሆኖ ዛሬ ድረስ ዘልቋል። የወደብ አገልግሎት ነጻነት ማጣት፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ዋጋ መጨመር፣ ማዳበሪያን ጨምሮ አስፈላጊ ግብአቶች መዘግየትና በወቅቱ አለመድረስ፣ በዚሕም የሰብል ልማት ስራዎች ላይ ችግሮች መስተዋል ከባሕር በር ባለቤትነት እጦት ጋር የመያያዝ እድላቸው ሰፊ ነው። እነዚሕ ችግሮች ደግሞ ተደማምረው ለኑሮ ውድነት መፈጠር አስተዋጾኦ ይኖራቸዋል ማለት ይቻላል። በታሪክ አጋጣሚ የተፈጠረው ስብራት እያስከተለ ያለው ጉዳት አሁን ላይ ለኢትዮጵያ የሕልውና ጉዳይ በመሆኑ በታሪካዊ ዳራ መሠረት መጠገን ያስፈልጋል። ለኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ከ130 ሚሊዮን ያሻቀበ የሕዝብ ቁጥር፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና ሀገራዊ የቆዳ ስፋት ገፊ ምክንያቶች ከሚባሉት ውስጥ ይጠቀሳሉ። በሌላ በኩል ከዚሕ ቀደም የነበረው የሀገሪቱ ባሕር በር ባለቤትነት ማስረጃ ዛሬ ላይ አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። መንግሥት የጀመረው የባሕር በር ባለቤት የመሆን ጥያቄ በመሬት ተዘግቶ የመኖር ታሪክ እንዲያበቃ የሚያደርግና በዓለም አቀፍ ሕግ ተፈጥሮን በጋራ ተጠቅሞ የመልማት መብትን የሚያስጠብቅ መሆኑ እውን ነው። ለሦስት አስርት ዓመታት ታፍኖ የቆየው የቀይ ባሕር ባለቤትነት ጥያቄ የመንግስት ቁርጠኝነት እንዳለ ሆኖ ዜጎችም አጥብቀው በመያዝ መልስ እስኪያገኝ ድረስ መስራት ይጠበቃል። የሀገርና የሕዝብ የዘመናት ጥያቄ የሆነው የባሕር በር እስኪሳካ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ መሥራት ከሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደሚጠበቅ መምሕር አጥናፉ ይገልጻሉ። ለኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት መሆን የታሪኳና ዕድገቷ ወጌሻ ነው ያሉት መምሕር አጥናፉ ኢትዮጵያ የባሕር በር ለመጠቀም የሚያስችላት ታሪካዊ መብት አላት። ይሕን ታሪካዊ መብቷን የምታረጋግጥበት ትልቁ መሣሪያ ደግሞ ያላት ጠንካራ የዲፕሎማቲክ አቅሟ ነው። ከዓለም ሀገራት ጋር ያላት መልካም ግንኙነት ተናግሮ ለማሳመን እውነታን ለመግለጽ የሚያስችላት ነው። ይሕንንም በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በዓለም ፊት አረጋግጣለች። ይሕን የሕዳሴ ድል በቀይ ባሕር ላይ የማትደግምበት ምንም ምክንያት አይኖርም። በተለይ ኢትዮጵያ ያላት የጋራ ተጠቃሚነት መርሕ በዓለም ላይ ተቀባይነት ያለውን ሀሳብ ይዛ እንድትቀርብ እያስቻላት ይገኛል። ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የሚሰጠው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲዋ ተፈጥሮን ተባብሮ በማልማት እንጠቀም የሚል መሠረት ያለው ነው። መምሕር ይስሐቅ ንጉሤ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሰቲ የምጣኔ ሀብት መምሕር ሲሆኑ የባሕር በር ጉዳይ የኢኮኖሚ ዕድገት ማጠንጠኛ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን አንስተው ኢትዮጵያ የባሕር በር ማጣቷ በፈጣን ዕድገቷ ላይ መሰናክል ሆኖ መዝለቁን ተናግረዋል። በተለይ የዓለም ሀገራት ከፍተኛው የንግድ፣ የኢኮኖሚና ሀብት እንቅስቃሴ የሚታይበት እና የሀገራት የንግድ ልውውጥ የሚካሄድበት የቀይ ባሕር ቀጠና ላይ ያለውን አብሮ የመስራትና ከማደግ ዕድል ኢትዮጵያ ያለአግባብ መገለሏን ያነሳሉ።ይሕም በሀገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገትና በሌሎች ላይ ያሳደረው አሉታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ እንደሆነ ነው ያገለጹት። የባሕር በር ጥያቄ የምጣኔ ሀብት ዕድገትን በማሳለጥ ሀገሪቱ ከልመና ለመውጣት ያላትን ዕድል እንድትወስን ያስችላታል የሚሉት መምሕሩ ፤ለስኬቱም የተጀመረውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማጠናከር እንደሚገባም ነው የገለጹት። እንደ መምሕሩ ገለጻ ከዓለም አቀፍ መርሆችና ስምምነቶች እንዲሁም ካለን መልከአ ምድራዊ አቀማመጥና ታሪክ አንጻር ለኢትዮጵያ የባሕር በር ተገቢ ነው። ይሕ እንዲሳካም መንግስት ካሳየው ቁርጠኝነት በተጨማሪ ሁሉም በተቀናጀ መንገድ የሚያደርገውን ጥረት ማጠናከር ይኖርበታል። መንግስት የዘመናት የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ የቆየውን የባሕር በር ጉዳይ በግልጽና በይፋ መረጃ በመስጠት ዓለም አቀፍ አጀንዳ እንዲሆንም ጭምር እያደረገ ያለውን ጥረትንም አድንቀዋል። ታሪክ በኩነቶች መካከል መጥፎም መልካም ሆኖ ያልፋል። በታሪክ የባሕር በር ባለቤትነታችን የገጠመውን ስብራት ለመጠገን የሚያስችል ወጌሻ ያስፈልጋል። በታሪክ ሂደት መልካሙ ወደ መጥፎ ሁኔታ እንደሚቀየር ሁሉ የተበላሸን ወደ መልካም የመቀየር ዕጣ ፈንታ ያለው የዛሬው ትውልድ ላይ ነው። ለእዚሕ ደግሞ ትውልዱ በሕዳሴው ግድብ ከመንግስት ጎን ሆኖ ያሳየውን አንድነትና ሕብረት በባሕር በርም መድገም አለበት። ታሪካዊ ዳራን፣ ዲፕሎማሲን፣ ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታና ሕግን ተከትሎ በአብሮነት ከተሰራ ያኔ የተበላሸው ይቃናል፤ ያጣነውን እናገኛለን። "እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል" ዓይነት እንስሳዊ ግብር በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሊሰማ አይገባም፤ መሰማትም አይኖርበትም። ኢትዮጵያ ብታደግ ለቀጣናው ኩራት፤ ለአፍሪካም ልዕልና እንጂ ጥፋት የሚያስከትል እንዳልሆነ መገንዘብና የትብብር ልማትና ዕድገትን ባሕል ማድረግ ሊለመድ ይገባል። ሰላም!