ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት ያጠናቀቁበት የጓድላሃራ ግማሽ ማራቶን - ኢዜአ አማርኛ
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት ያጠናቀቁበት የጓድላሃራ ግማሽ ማራቶን
አዲስ አበባ፤ የካቲት 16 /2018 (ኢዜአ)፡- በሜክሲኮ የጓድላሃራ ግማሽ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸንፈዋል።
በወንዶች አትሌት ገመቹ ዲዳ 1 ሰዓት ከ03 ደቂቃ ከ38 ሴኮንድ አሸንፏል።
በሴቶች ውድድር አትሌት ኮሎሌ መካሹ 1 ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ49 ሴኮንድ አሸንፋለች።
ደራርቱ ኃይሉ 1 ሰዓት ከ16 ደቂቃ ከ06 ሴኬንድ ስምንተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።