አካባቢ ጥበቃ - ኢዜአ አማርኛ
አካባቢ ጥበቃ
በሲዳማ ክልል የአረንጓዴ አሻራ ልማት ውጤቶችን በማስቀጠል የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋን ለመከላከል እየተሰራ ነው
Jun 30, 2025 47
ሀዋሳ፤ ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል በአረንጓዴ አሻራ ልማት የተገኙ ውጤቶችን በማስቀጠል የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋን በዘላቂነት ለመከላከል እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። ''በመትከል ማንሰራራት'' በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ልማት በዳራ ኦቲልቾ ወረዳ ሾይቾ ቀበሌ ዛሬ ተጀምሯል፡፡ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በእዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሥራዎች ዘርፈ ብዙ ውጤቶች ተመዝግዋል፡፡ በዚህም የተራቆቱ መሬቶች፣ የደረቁ ወንዞችና ጅረቶች መልሰው በማገገማቸው የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባሻገር ምርታማነት ለመጨመርና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያስቻሉ መሆኑን ገልጸዋል። በአረንጓዴ አሻራ ልማት የተገኙ ውጤቶችን ቀጣይነት በማረጋገጥ በክልሉ ሊገጥም የሚችለውን የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ ለመከላከል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ልማት የክልሉ ህዝብና መንግስት የህልውና ጉዳይ ነው ያሉት አቶ ደስታ፣ ልማቱ ባህል እየሆነ በመምጣቱ ለትውልድ እንዲሻገር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል። የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሥራ የህዝቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም አቶ ደስታ ገልጸዋል፡፡ ዛሬ ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ልማት የተጀመረበት ቀበሌ ከዚህ ቀደም የተራቆተ እንደነበር አስታውሰው፣ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአካባቢው ስነምህዳር መቀየሩንም ጠቅሰዋል፡፡ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ሃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ከ23 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት በአረንጓዴ ለማልማት ታቅዶ ወደስራ ተገብቷል፡፡ በክልሉ በመርሃ ግብሩ ከሚተከሉ ችግኞች 60 ከመቶ የሚሆኑት ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የሚሰጡና ቡና ቀዳሚው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የደን ሽፋንን የሚያሳድጉ፣ ለምግብነትና ለእንሳሰት መኖነት የሚውሉ እንዲሁም ለኢኮ ቱሪዝም የሚጠቅሙ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰው፣ ለሚተከሉ ችግኞች ህዝቡን ባለቤት ለማድረግ ይሰራል ብለዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች የደን ሽፋንን በማሳደግ፣ የተጎዱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግና እና የመሬት ለምነትን በመጨመር ምርታማነትን አሳድገዋል ሲሉም ሃላፊው ተናግረዋል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ትውልድንና ሃገርና የሚያስቀጥል ሥራ በመሆኑ ሁሉም በሃላፊነት እየተሳተፈ መሆኑንና እሳቸውም የድርሻቸውን ለመወጣት በመርሃ ግብሩ መገኘታቸውን የተናገሩት ደግሞ በኩረ ትጉሃን ቀሲስ አማረ ግርማ ናቸው፡፡ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው፣ የተተከሉ ችግኞችን በአግባቡ መንከባከብ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የክልሉ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚሰጡ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል
Jun 30, 2025 70
ክልል ፤ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ) ፦ በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚሰጡ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። በክልሉ የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በነገው እለት እንደሚጀመርም ተመላክቷል። የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ተከላ አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ባለፉት ስድስት ዓመታት ከ6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ላይ የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን ጠቅሰው፣ ከተተከሉ ችግኞች መካከል 88 በመቶ የሚሆኑት መጽደቃቸውን ተናግረዋል። የአረንጓዴ ልማት ሥራው የውሃ አማራጮት እንዲሰፉ፣ በተፈጥሮ ሀብት መራቆት የደረቁ ሐይቆችና ወንዞች መልሰው እንዲያገግሙ ማድረጉንም ተናግረዋል። ከዚህ ባለፈ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትና እንዲረጋገጥ ማድረጉን ገልጸዋል። ልማቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል በዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በበጋ ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ በተከናወነባቸው የተራቆቱ መሬቶች ችግኝ የመትከል ስራ እንደሚከናወን ጠቅሰዋል። ለዚህም በክልሉ በ38 ሺህ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ላይ ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚሰጡ ችግኖች መዘጋጀታቸውን አስታውሰዋል። ችግኞቹን ለመትከል 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት መዘጋጀቱን ገልጸው፣ ለተከላ ከተዘጋጁት ችግኝ መካከል 40 በመቶው ለደን አገልግሎት የሚውሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። በተጨማሪም 30 በመቶ የሚሆኑት ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ፣ 19 በመቶ ለእንስሳት መኖ እና 10 በመቶው ለምግብ የሚውሉ ሲሆን ቀሪው ለውበት እንደሚውሉ አቶ ጌቱ አስታውቀዋል። የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩን ስኬታማ ለማድረግ ህዝቡ እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ በስፋት እንዲሳተፍም ጥሪ አቀርበዋል።
አረንጓዴ አሻራ የግብርና ምርታማነትን ከማሳደግ ጀምሮ በሁሉም የልማት መስኮች ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል
Jun 30, 2025 79
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ አረንጓዴ አሻራ የግብርና ምርታማነትን ከማሳደግ ጀምሮ በሁሉም የልማት መስኮች ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን ሚኒስትሮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማ፣ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር መካሄዱ ይታወቃል። በመርሃ ግብሩ ከተሳተፉ ሚኒስትሮች መካከል አስተያየታቸውን የሰጡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር)፥ ባለፉት ዓመታት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሁሉም መስክ መሰረት መጣሉን ተናግረዋል። የደን ሽፋንን በማሳደግ፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃን በማጎልበትና የግብርና ምርታማነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ የወጪ ንግድ አቅምን ማስፋት ማስቻሉን ጠቅሰዋል። በሁሉም የልማት መስኮች የኢኮኖሚ ዕድገትን በማፋጠን ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ኢትዮጵያ እንድታንሰራራ እያደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በመሳተፍ የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍም ጥሪ አቅርበዋል። የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፥ አረንጓዴ አሻራ ጤናችን፣ ምግባችን እና ሁሉ ነገራችን ነው ብለዋል። በአረንጓዴ አሻራ ለባህላዊና ዘመናዊ መድሃኒት የሚያገለግሉ ዕጽዋቶች እየተተከሉ መሆኑን ጠቅሰው፥ ይህም የመርሃ ግብሩን ሀገራዊ የጤና ዘርፍ ፋይዳ የላቀ ያደርገዋል ነው ያሉት። መርሃ ግብሩ ምቹና አረንጓዴ አካባቢን በመገንባት ለህብረተሰብ ጤና አጠባበቅ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፥ ሁሉም ህብረተሰብ በችግኝ ተከላው የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት ገልጸዋል። የፍትሕ ሚኒስትር ሀና አርዓያ ሥላሴ፥ ኢትዮጵያውያን በአረንጓዴ ልማት አኩሪ የሆነ ባህል አለን ሲሉ ገልጸዋል። ይህን መልካም ባህል ማስቀጠል እንደሚገባ በመግለጽ፥ ኢትዮጵያን አረንጓዴ በማልበስ ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስረከብ ሁሉም ጥረቱን ማጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተይዟል።
በሲዳማ ክልል የአረንጓዴ አሻራ ልማት የአየር ንብረት ለውጥን ከመጠበቅ ባለፈ ምርታማነትን እያሳደገ ነው
Jun 30, 2025 48
ሀዋሳ፤ ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የአየር ንብረት ለውጥን ከመጠበቅ ባለፈ ምርታማነትን ማሳደጋቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ደስታ ዛሬ በዳራ ኦቲልቾ ወረዳ ሾይቾ ቀበሌ ተገኝተው የክልሉን የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር አስጀምረዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሥራዎች የአየር ንብረት ለውጥን በመጠበቅና የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችን አስገኝተዋል። ዛሬ በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የሚተከሉ ችግኞች ለመጪው ትውልድ የሚሻገሩ በመሆኑ ከመትከል ባለፈ በአግባቡ ጸድቀው እንዲያድጉ መንከባከብ ይገባል ብለዋል። ዛሬ ክልል አቀፉ ተከላ የተጀመረበት ቦታ ከዚህ ቀደም የተራቆተ እንደነበረና በተደጋጋሚ በተሰራው የአረንጓዴ ልማት ሥራ ውጤት የተመዘገበበት በመሆኑ ወደሌሎች አካባቢዎችም ማስፋት ይገባል ብለዋል። በክልሉ በክረምት ወራት የተለያየ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ለመትከል ዝግጅት መደረጉን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ የክልሉ ህዝብ በልማት ሥራው በተደራጀ መንገድ እንዲሳተፍም ጥሪ አቅርበዋል። በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ፣ የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የማንሰራራት ጉዞ እንዲሳካ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው- ሚኒስትሮች
Jun 30, 2025 96
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የማንሰራራት ጉዞ እንዲሳካ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ሚኒስትሮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማ፣ የፌደራልና የክልል መንግሥታት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ የወንዝ ዳር ዳርቻ ልማት የችግኝ የተከላ መርሐ ግብር መካሄዱ ይታወቃል። በመርሐ ግብሩ ላይ የተሳተፉ ሚኒስትሮች እንደገለጹት፥ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ኢኮኖሚው እንዲያንሰራራ የተያዙ ግቦችን ለማሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለቀጣዩ ትውልድ የተበረከተ ስጦታ መሆኑን ጠቁመው መርሐ ግብሩ ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙበት መሆኑንም አንስተዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ደ/ር) እንዳሉት፤ ባለፉት 6 ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከ40 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ኢኮኖሚው ፈጣንና ተከታታይ እድገት እያስመዘገበ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሯ፥ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል። በመርሐ ግብሩ በርካታ የቡና ችግኞች መተከላቸውን ገልጸው ይህም ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ ከቡና የምታገኘው የውጭ ንግድ ገቢ እየጨመረ እንዲመጣ ማስቻሉን ተናግረዋል። አቮካዶን ጨምሮ የተለያዩ የፍራፍሬ ምርቶች ወደ ውጭ በመላክ ገቢ እየተገኘ መሆኑን ጠቅሰው፥ የሌማት ትሩፋት ግቡን እንዲመታ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ጉልህ ሚና አለው ብለዋል። አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እንዲያንሰራራ በሚደረገው ሀገራዊ ጥረት ውስጥ የማይተካ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል። የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ በበኩላቸው አረንጓዴ አሻራ ለትውልድ የሚበረከት ስጦታ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት እየታየ መሆኑን ጠቅሰው፥ ኢኮኖሚው እንዲሳለጥ ከማገዝ ባለፈ ለኑሮ ምቹ ከባቢን እየፈጠረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)፤ አረንጓዴ አሻራ የከርሰ ምድር እና ገጸ-ምድር ውሃ እንዲጨምር እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። መርሐ ግብሩ ምንጮች እንዲጎለበቱ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው ደርቆ የነበረው የሀረማያ ሀይቅ ማገገምና ማንሰራራት የአረንጓዴ አሻራ ውጤት መሆኑን አስረድተዋል። አፈር እንዳይሸረሸርና ግድቦች በደለል እንዳይሞሉም መርሃ ግብሩ ትልቅ ሚና እንዳለው አመልክተዋል። በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች እንደሚተከሉም ተገልጿል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ለተያዘው ዕቅድ ስኬታማነት ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል
Jun 29, 2025 83
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦በአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተያዘው ዕቅድ ስኬታማነት ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ የ7ኛው የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሀግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል። መርሀግብሩን ተከትሎም ከከተማዋ የተወጣጡ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡ በዚሁ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ያለ አንዳች ልዩነት መከናወን የሚገባው የሁሉም ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ የወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ነጻነት ጣሰው እንዳሉትም፤ ለ7ኛ ጊዜ እየተከናወነ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ሁሉም ያለ አንዳች ልዩነት መሳተፍ ይገባዋል ብለዋል፡፡ የአሁኑ ትውልድ ችግኝ ሲተክል ከራሱ አልፎ ለመጪው ትውልድ የማሰቡ ማሳያ ነው ያሉት አቶ ነጻነት ችግኝ በመትከል ሀገርን አረንጓዴ የማልበስ ግቡ እንዲሳካ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡ ችግኝ በመትከል ለመጪው ትውልድ የለመለመችና ምቹ አየር ያላት ሀገርን ለማስረከብ ሁሉም ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ዋና ጸሐፊ አቶ ክፍለማርያም ሙሉጌታ በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ አሻራ የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ የማይተካ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል፡፡ ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ተንከባክቦ ማጽደቅ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ኃላፊነት መሆን እንዳለበትም ተናግረዋል፡፡ በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ለተያዘው ዕቅድ ስኬታማነት ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
ችግኝ በመትከል ጤንነቱ የተጠበቀ ትውልድ ለመፍጠር ሁሉም ሊረባረብ ይገባል - የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች
Jun 29, 2025 82
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦በአረንጓዴ አሻራ ውብና ንጹህ ከባቢን በመፍጠር ጤንነቱ የተጠበቀ ትውልድ እንዲኖር ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ የ7ኛው የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል። መርሐ ግብሩን ተከትሎም ከከተማዋ የተወጣጡ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡ በዚሁ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው አትሌቶች፣ አርቲስቶች እና የጤና ባለሙያዎች የአረንጓዴ አሻራ የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ ጉልህ ሚና አለው ብለዋል፡፡ ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በሁሉም ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ላይ መሳተፍ በመቻሏ የተሰማትን ደስታ ገልጻለች፡፡ አረንጓዴ አሻራ ዘርፍ ብዙ ጠቀሜታን የሚያስገኝ ነው ያለችው ኮማንደር ደራርቱ፤ በተለይም አትሌቶች በልምምድ ቦታ ጥሩ አየር ተንፍሰው ለድል እንዲበቁ ከማድረግ አኳያ ሚናው ከፍተኛ ነው ብላለች፡፡ በስፖርቱ ዘርፍ ያሉ ባለሙያዎች የአረንጓዴ አሻራን በማኖር ሀገር የያዘችው ግብ ስኬታማ እንዲሆን የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ብላለች፡፡ አርቲስት የትናየት ታምራት በበኩሏ፤ ሀገርን አረንጓዴ ለማልበስ የተጀመረው መርሐ ግብር ላይ በመሳተፍ አሻራዋን በማኖሯ መደሰቷን ተናግራለች፡፡ ተፈጥሮን በመንከባከብ ንጹህ እና ውብ ከባቢን መፍጠር የሁሉም ሚና መሆኑን ጠቁማ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው መርሐ ግብር ለሌሎችም ምሳሌ የሚሆን ነው ብላለች፡፡ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችን ጨምሮ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች እንደጀመሩት ሁሉ ለስኬታማነቱ መረባረብ እንዳለባቸውም ጠቁማለች፡፡ የቀበና ጤና ጣቢያ ሜዲካል ዳይሬክተር ታመነ መርክኝ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለጤናው ዘርፍ ስኬት ትልቅ አጋዥ ነው ብለዋል፡፡ ጤንነቱ የተረጋገጠ ትውልድ ለመፍጠር ብሎም ጽዱና ምቹ ከባቢን ከመገንባት አንጻር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
አረንጓዴ አሻራን በማኖር የተሻለች ሀገር ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ ለሚደረገው ጥረት ስኬት ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል - የኃይማኖት አባቶች
Jun 29, 2025 87
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦አረንጓዴ አሻራን በማኖር የተሻለች ሀገር ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ ለሚደረገው ጥረት ስኬት ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የኃይማኖት አባቶች ተናገሩ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ የ7ኛው የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሐግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ ተካሂዷል። መርሀግብሩን ተከትሎም ከከተማዋ የተወጣጡ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡ የተለያዩ የኃይማኖት አባቶችም አረንጓዴ አሻራቸውን ያኖሩ ሲሆኑ ትውልዱ ችግኝ በመትከል የተሻለች ሀገር ለማስተላለፍ መትጋት እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርሰቲያን የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ፤ እንደ ሀገር አረንጓዴ አሻራ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ አረንጓዴ አሻራ የሀገርን ገጽታ በእጅጉ እየቀየረ የሚገኙ መሆኑን አንስተው፤ ጽዱና ለነዋሪዎች ምቹ የሆነች ሀገር ከመገንባት አንጻርም ትልቅ ተስፋ መታየቱን ገልጸዋል፡፡ የሁሉም ቤተ እምነት ተከታዮችም የአረንጓዴ አሻራ ስራን በማከናወን ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስተላለፍ የሚደረገውን ጥረት ማገዝ እንዳለባቸውም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሱልጣን አማን ኤባ እንዳሉትም፤ የአረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተለያየ እውቅና እንድታገኝ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡ መጪው ትውልድ የተራቆተች ሀገር እንዳይረከብ እና አሁን ያለው ትውልድም ጤናው ተጠብቆ ምቹ አካባቢ እንዲኖር ለማስቻል የአረንጓዴ አሻራ ስራዎች መጠናከር እንደሚገባቸውም ገልጸዋል፡፡ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ለፍሬ ማብቃት እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ሉተራን ቤተክርስቲያን መሪ ቄስ ሙሴ አላዓዛር እንዳሉትም፤ የአረንጓዴ አሻራ አካባቢን ጽዱና ውብ በማድረግ ገጽታን የሚለውጥ በመሆኑ ሁሉም ሰው በዚህ ተግባር መሳተፍ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡ የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ በበኩላቸው፤ በዛሬው ዕለት ከሁሉም ቤተ እምነቶች የተወጣጡ አባቶች የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ላይ መሳተፋቸውን ተናግረዋል፡፡ ትውልዱም የኃይማኖት አባቶቹን አርዓያ በመከተል የአረንጓዴ አሻራውን ማሳረፍ እንዳለበትም ጠቁመዋል፡፡
ፅዱ እና ጤናማ አካባቢን ለትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው ጥረት የሁሉም ተሳትፎ እና እገዛ ሊኖር ይገባል
Jun 29, 2025 74
ሀረር ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦ፅዱ እና ጤናማ አካባቢን ለትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው ጥረት የሁሉም ተሳትፎ እና እገዛ ሊኖር ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ ተናገሩ። ሁለተኛው ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ በሐረሪ ክልል በይፋ ተጀምሯል። በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ፤ የኢትዮጵያን ጽዳትና ውበት በጋራ በመጠበቅና በመንከባከብ ምቹና ተመራጭ ማድረግ የዜጎች ሁሉ ሃላፊነት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመረው "ፅዱ ኢትዮጵያ" ንቅናቄ አላማው ይሄው መሆኑን አንስተው ለስኬቱ መረባረብ ይጠበቅብናል ብለዋል። በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች ፅዱ እና ለመኖር ምቹ የሆኑ ከተሞችን በመፍጠርና የአረንጓዴ አሻራ ስራዎችን በማጠናከር ብዙ መስራት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በኮሪደር ልማትና ኢኮ ቱሪዝም ዘርፍ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማስፋት፣ የወንዞች ዳርቻን በማጽዳትና መልሶ በማልማት ምቹና ውብ መኖሪያ የማድረግ ጉዳይ ለነገ የሚተው ስራ አይደለም ብለዋል። በዚህ ረገድ በመጀመሪያው ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስታውሰው በሁለተኛውም የተሻለ ስኬት ለማስመዝገብ ተዘጋጅተናል ሲሉ አረጋግጠዋል። በመሆኑም ለስድስት ወራት በሚከናወነው ሁለተኛው ዙር የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል። የሐረሪ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ነቢላ መሃዲ ሐረርን ውብ እና ፅዱ የማድረግ ጥረታችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል። በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወየሳ በበኩላቸው ሐረርን ውብ እና ፅዱ በማድረግ ሂደት ህብረተሰቡ ተሳትፎውን ሊያጠናክር እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በመድረኩ የባለስልጣኑ አመራርና ሰራተኞች፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎችም እንግዶች የተገኙ ሲሆን በእለቱ የችግኝ ተከላ አካሂደዋል።
ችግኝ በመትከል ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ የመገንባት ተግባራችንን እናጠናክራለን - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 29, 2025 69
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦ችግኝ በመትከል ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ የመገንባት ተግባራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ የ7ኛው የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሀግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ ተካሄዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፤ ባለፋት ስድስት ዓመታት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ተሳትፈው 40 ቢሊዮን ችግኞችን መትከላቸውን ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃም ባለፉት ስድስት ዓመታት 85 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን ጠቁመው፤ የከተማዋ የደን ሽፋንም ከ2 ነጥብ 8 በመቶ አሁን ላይ 22 በመቶ መድረስ መቻሉን ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ ስራዎች ወንዞች ማንሰራራት ጀምረዋል፣ በአፈርና ውሃ ጥበቃ ውጤቶችም መታየት መጀመራቸውን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ችግኝ በመትከል ተረጂነትን ታሪክ ለማድረግ እየሰራች ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ በአዲስ አበባ ለዘንድሮው ተከላ 916 ሄክታር መሬት መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል። ችግኝ በመትከል ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ የመገንባት ተግባራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ አረጋግጠዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አሁን ያለው ትውልድ ለመጪው የምትሆን ሀገርን የመፍጠር ማሣያ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ የሚያስቀምጥ ለተጀመረው የሀገር ግንባታ ሂደት ቀጣይነት መሠረት የሚጥል መሆኑንም ተናግረዋል። አረንጓዴ አሻራ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ያነሱት የቢሮ ሃላፊው በከተማ ደረጃ ይህንን ለማረጋገጥ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማ ደረጃ የተያዘውን ግብ በማሳካት አረንጓዴ አሻራ ለአካባቢ ውበትና ለጤና መሠረት መሆኑን በተግባር እናረጋግጣለን ብለዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ማስጀመሪያ መርሃግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት መካሄዱ ይታወቃል። በሀገር አቀፍ ደረጃ "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች እንደሚተከሉም ይታወቃል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአካባቢ መራቆትን ከመከላከል ባሻገር በፍራፍሬ ልማት ላይ ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል- የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች
Jun 29, 2025 70
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአካባቢ መራቆትን ከመከላከል ባሻገር በፍራፍሬ ልማት ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ገለጹ። ክልሎች ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ስኬታማነት የተሻለ ዝግጅት ማድረጋቸውንም ነው ርዕሳነ መስተዳደሮቹ ያረጋገጡት። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማን ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች እንዲሁም ሚኒስትሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ የወንዝ ዳር ዳርቻ ልማት የችግኝ የተከላ መርሃ ግብር ተካሄዷል። በመርሃ ግብሩ የተገኙ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እንዳሉት፤ የአረንጓዴ አሻራ ዜጎች በተደመረ አቅም ኢትዮጵያን ለመለወጥ በጋራ የቆሙበት ሀገራዊ የልማት አጀንዳ መሆኑን አብራርተዋል። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ፤ በክልሉ በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች በመርሃ ግብሩ የነቃ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብረ አማካኝነትም በክልሉ ተራቁተው የነበሩ አካባቢዎች መልሰው ማገገማቸውን ጠቅሰው፤ ከሀገር ውስጥ ባለፈ ለውጭ ገበያ የሚቀርብ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርታማነት አቅም መፈጠሩንም ገልጸዋል። በዘንድሮው ዓመትም የክልሉ ነዋሪዎች በመርሃ ግብሩ ላይ በስፋት እንዲሳተፉ የሚያደርግ ዝግጅት መጠናቀቁን በመጠቆም። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ በበኩላቸው፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በርካታ ህዝብ በማሳተፍ ለውጥ ማምጣት መቻሉን ተናግረዋል። መርሃ ግብሩ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው ጠቅሰው፤ በትግራይ ክልል ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም መርሃ ግብሩ በይፋ እንደሚጀመር ጠቁመዋል።ለዚሁ ስራ የሚውል የችግኝ ዝግጅት መደረጉንም ነው የገለጹት። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተለያዩ የፍራፍሬ አይነቶችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ማስፋት ያስቻለ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሌ ሀሰን ናቸው። መርሃ ግብሩ ከቡና በተጨማሪ ኢትዮጵያ በፍራፍሬ ኤክስፖርት እንድትታወቅ እያደረጋት ስለመሆኑም ጠቁመዋል። የአረንጓዴ አሻራ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለሚገኝበት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትልቅ ትርጉም እንዳለው ጠቅሰው፤ የክልሉ ነዋሪዎች በመርሃ ግብሩ የሚያደርጉት ተሳትፎ መጨመሩንም ገልጸዋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተጀመሩ ስራዎች መሰረት የጣለ ነው-የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች
Jun 29, 2025 65
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተጀመሩ ስራዎች መሰረት የጣለ መሆኑን የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማን፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች እንዲሁም ሚኒስትሮች በተገኙበት ትናንት በአዲስ አበባ የወንዝ ዳር ዳርቻ ልማት የችግኝ የተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ የተገኙ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለጋራ ዓላማ በአንድነት መቆም ያለውን ውጤታማነት በተግባር የገለጠ ስለመሆኑ አብራርተዋል። የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፌ መሀመድ፤ የክልሉ ነዋሪዎች በመርሃ ግብሩ ላይ በስፋት እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከዚህ ቀደም ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ወደ ምርታማነት እንዲለወጡ እድል የፈጠረ መሆኑንም አብራርተዋል። የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙ በማድረግ የግብርና ምርታማነት እንዲሻሻል አዎንታዊ ሚና እያበረከተ መሆኑንም ገልጸዋል። ከዚህ አኳያ መርሃ ግብሩ በተደጋጋሚ በድርቅ ሲጎዳ ለነበረው የሱማሌ ክልል ልዩ ትርጉም እንዳለው አንስተው፤ በዘንድሮው ዓመትም የተሻለ ለውጥ ለማምጣት ሰፊ ተሳትፎ እንደሚደረግ ተናግረዋል። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር አወል አርባ በበኩላቸው፤ በክልሉ ከዚህ ቀደም በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ የፍራፍሬ ተክሎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ መጀመራቸውን ጠቁመዋል። ይህም የዜጎችን ገቢ በማሻሻል ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን አንስተዋል። አሁን ላይ በክልሉ ችግኝ መትከል ባህል እየሆነ መምጣቱን አንስተው፤ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም ሰፊ ተሳትፎ እንደሚደረግ ገልጸዋል። በጋምቤላ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካኝነት ከዚህ ቀደም በክልሉ የማይታወቁ አዳዲስ የፍራፍሬ ዓይነቶችን ማልማት መጀመሩን ያነሱት ደግሞ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ናቸው። ይህም በምግብ ራስን ለመቻል እና የህብረተሰቡን ገቢ ለመጨመር የተጀመሩ ጥረቶችን እያገዘ ስለመሆኑም ነው የተናገሩት። የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኦርዲን በድሪ፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከምግብ ሉዓላዊነት ጋር የተሳሰረ ሀገራዊ የልማት አጀንዳ መሆኑን አውስተዋል። ህብረተሰቡ ያለ ልዩነት በጋራ እያደረገ ያለው ተሳትፎ ደግሞ መርሃ ግብሩ ውጤታማ እንዲሆን ትልቅ ሚና አበርክቷል ነው ያሉት። "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው በዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ይተከላሉ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ 3 ነጥብ 7 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት በተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ ማልማት ተችሏል
Jun 29, 2025 69
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦በሀገር አቀፍ ደረጃ በዘንድሮ በጋ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ከ3 ነጥብ 7 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት ማልማት መቻሉን በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ፋኖሴ መኮንን ገለጹ። መሪ ስራ አስፈፃሚው ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ በኢትዮጵያ የተጎሳቆለ መሬትና አካባቢን ለማከም መንግስት ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የአፈር ለምነት ማጣት፣ የአፈር መሸርሸር፣ የማህበረሰቡ የጎርፍ ተጋላጭነት መጨመር እና ሌሎች ተግዳሮቶችን ለመፍታት ህብረተሰቡን ያሳተፈ የተፈጥሮ ሀብት ጥብቃ ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችም ወደ 33 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት እንዲያገግም መደረጉን ጠቅሰዋል። በየዓመቱም እንደ አካባቢው ነባራዊ ሁኔታ ከ30 እስከ 60 ቀናት በሚቆዩ ጊዜያት ህብረተሰቡ በሚያደርገው የነቃ ተሳትፎ የሥነ አካላዊ፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ተግባር በልዩ ትኩረት መሰራቱን ገልጸዋል። እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት ከ21 ሺህ በላይ በሚሆኑ ተፋሰሶች ላይ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል። በተፋሰስ ልማቱ ከ 3 ነጥብ 7 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት መሸፈን መቻሉን ነው ያነሱት። የተፈጥሮ ሀብት፣ የአፈርና ውሀ ጥበቃ እና የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት የአፈር ለምነትን እና ጤንነትን በመጠበቅ ትልቅ ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል። የአፈር መሸርሸርን በከፍተኛ መጠን መቀነሱን፣ የውሃ ሀብቶች እንዲጎለብቱ ማስቻሉን አንስተዋል። አርሶ አደሮች የተቀናጀ የተፋሰስ ልማቱን በባለቤትነት በማልማት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በንብ ማነብና ሌሎችም ዘርፎች ተጠቃሚ እየሆኑ የግብርና ምርትና ምርታማነት እየጨመረ እንደሚገኝ ነው የጠቀሱት። አቶ ፋኖሴ አያይዘውም በተፋሰስና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ መትከያ ጉድጓዶች እንዲዘጋጁ መደረጉን አንስተዋል። የተፋሰስ ልማቱ ከአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ጋር በተሳሰረ መልኩ እየተተገበረ መሆኑም ሀገራዊ የአረንጓዴ ልማትና አካባቢ ጥበቃ ኢኒሼቲቭን እያሳካ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባን ምቹ እና ጽዱ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 29, 2025 71
አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017 (ኢዜአ) አዲስ አበባን ለመኖር ምቹ እና ጽዱ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ የ7ኛው የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሐግብር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ይገኛል። በመርሐግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ቡዜና አልከድር፣ በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ፣ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የስፖርት ማህበረሰብ ፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች፣ የጤናና የትምህርት ማህበረሰብ፣ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮችን ጨምሮ ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ አካላት ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፤ ባለፋት ስድስት ዓመታት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ተሳትፈው 40 ቢሊዮን ችግኞችን መትከላቸውን ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃም ባለፉት ስድስት ዓመታት 85 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን ጠቁመው፤ የከተማዋ የደን ሽፋንም ከ2 ነጥብ 8 በመቶ አሁን ላይ 22 በመቶ መድረስ መቻሉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ችግኞችን በመትከል ተረጂነትን ታሪክ ለማድረግ እየሰራች ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ በአዲስ አበባ ለዘንድሮው ተከላ 916 ሄክታር መሬት መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል። በመትከል ለአየር ንበረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ እንደሚገነባ የጠቆሙት ከንቲባዋ፤ አዲስ አበባን ለመኖር ምቹ እና ጽዱ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ ስራዎች ወንዞች ማንሰራራት ጀምረዋል፣ በአፈርና ውሃ ጥበቃም ውጤቶችም መታየት መጀመራቸውን ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አሁን ያለው ትውልድ ለመጪው የምትሆን ሀገርን የመፍጠር ማሣያ ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ የሚያስቀምጥ ለተጀመረው የሀገር ግንባታ ሂደት ቀጣይነት መሠረት የሚጥል መሆኑንም ተናግረዋል። አረንጓዴ አሻራ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ያነሱት የቢሮ ኃላፊው በከተማ ደረጃ ይህንን ለማረጋገጥ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማ ደረጃ የተያዘውን ግብ በማሳካት አረንጓዴ አሻራ ለአካባቢ ውበትና ለጤና መሠረት መሆኑን በተግባር እናረጋግጣለን ብለዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ማስጀመሪያ መርሐግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት መካሄዱ ይታወቃል። በሀገር አቀፍ ደረጃ "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች እንደሚተከሉም ይታወቃል።
የበለጸገችና ጽዱ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ሁሉም ዜጋ የአካባቢ ጥበቃ አምባሳደር መሆን አለበት
Jun 28, 2025 86
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፦ የበለጸገችና ጽዱ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ሁሉም ዜጋ የአካባቢ ጥበቃ አምባሳደር መሆን እንደሚጠበቅበት የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ ገለጹ። በመዲናዋ የ90 ቀን ልዩ የንቅናቄ አጀንዳ አካል የሆነው የፅዱ ኢትዮጵያ ከተማ አቀፍ ንቅናቄ "ፅዱ፣ ውብ እና ደህንነቷ የተጠበቀች አዲስ አበባ" በሚል መሪ ሀሳብ በይፋ ተጀምሯል። የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ፤ የጠቅላይ ሚነስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጽዱ ኢትዮጵያ ትልም ቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ሀገር እንዲረከብ የሚያስችል መሰረት መጣሉን ገልጸዋል። በዚህም የኮሪደር፣ የወንዝ ዳርቻ ልማቶችና የመንግስት መስሪያ ቤቶች የስራ ከባቢ ጽዳትና የኢኮ-ቱሪዝም መዳረሻ ልማት ዜጎች የተሻለ የኑሮ ከባቢ እንዲኖራቸው እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ባለፈው ዓመት በተካሄደው የመጀመሪያው የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ብክለትን በመግታት የተሻለ የኑሮ ከባቢን መፍጠር የሚያስችል የጽዳትና ውበት ስራ መሰራቱን አስታውሰዋል። ባለስልጣኑም በህግ በተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መሰረት ዜጎችን በንጹህና ጤናማ አካባቢ የመኖር መብታቸውን እውን ለማድረግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በዚህም የአፈር፣ የፕላስቲክ፣ የውሃ፣ የአየር፣ የድምጽ ብክለቶችንና የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማን መሰረት በማድረግ ጽዳትና ውበትን ባህሉ ያደረገ ዜጋ ለማፍራት መሰረት እየተጣለ መሆኑን አንስተዋል። የአካባቢ ጽዳትና ውበት ጉዳይ የአንድ ተቋምና ግለሰብ ብቻ ሳይሆን የሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል ትብብር ተሳትፎ የሚጠይቅ መሆን እንደሚኖርበት ገልጸዋል። በብክለት ሳቢያ የሚደርሱ የጤና እክሎችን ቀድሞ በመከላከል የበለጸገችና ጽዱ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ዜጋ የአካባቢ ጥበቃ አምባሳደር መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ፤ በተያዘው የክረምት ወቅት በዘጠና ቀናት መዲናዋን እያፈኳት የሚገኙ የጽዳትና ውበት የበጎ አድራጎት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። በዚህም የጎርፍ አደጋን የመከላከል፣ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮች ጽዳት፣ ደረቅ ቆሻሻ ማስወገድን ጨምሮ ሌሎች ተግባራት እንደሚከናወኑ ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ድዳ ድሪባ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት የመዲናዋን ጽዳትና ውበት በመጠበቅ ለጽዱ ኢትዮጵያ መሰረት የሆኑ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ተሰርተዋል። የኮሪደርና የወንዝ ዳር ልማት እንዲሁም የመልሶ ልማት ስራዎችም ፋይዳቸው የላቀ መሆኑን ጠቅሰው፥ የወንዞችን ብክለት መከላከል የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ተቀርፆ ስራ ላይ ማዋል እንደተቻለም ገልጸዋል። የአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብርም ለአካባቢ ፅዳትና ውበት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራል፣ የከተማ አስተዳደሩና የዓለም አቀፍ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች፣ የሲቪክ ማህበራት ተወካዮች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የኪነ-ጥበብ ሙያተኞች ተገኝተዋል።
በመዲናዋ ሁለተኛው ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ከተማ አቀፍ ንቅናቄ በይፋ ተጀመረ
Jun 28, 2025 129
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የ90 ቀን ልዩ የንቅናቄ አጀንዳ አካል የሆነው የፅዱ ኢትዮጵያ ከተማ አቀፍ ንቅናቄ "ፅዱ፥ ውብ እና ደህንነቷ የተጠበቀች አዲስ አበባ" በሚል መሪ ሀሳብ በይፋ ተጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የፌዴራልና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የሲቪክ ማህበራት ተወካዮች፣ ተፅእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፤ የዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎችና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ተገኝተዋል። የፌዴራል የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፥ የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት ነው ብለዋል። የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ከብክለት የጸዳ አካባቢያዊ ሥርዓተ ምህዳር እየፈጠረ መምጣቱንም ገልጸዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በበኩላቸው፥ ንቅናቄው መዲናዋን ፅዱና ከብክለት የፀዳች በማድረግ በኩል ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰዋል። ህዝቡም በአካባቢ ጥበቃ እንቅስቃሴ ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመዋል። በአካባቢ ጥበቃና በብክለት ዙሪያ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ በንቅናቄው ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ተጠቃሽ መሆኑን ተናግረዋል። በንቅናቄው የአፈር፣ የውሀ፣ የፕላስቲክ፣ የአካባቢ ብክለትን ለማስቀረት የጽዳት ዘመቻ፣ የግንዛቤ ማስጨበጫና ሌሎች ተግባራት እንደሚከናወኑ ተገልጿል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁሉም ዜጋ ሀገር ለመለወጥ በባለቤትነት የሚሳተፍበት የትውልድ አሻራ ነው - አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ
Jun 28, 2025 113
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፦ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁሉም ዜጋ ሀገር ለመለወጥ በባለቤትነት የሚሳተፍበት የትውልድ አሻራ መሆኑን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማን እንዲሁም ሌሎች የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላትና ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ትናንት ተካሂዷል። በዛሬው ዕለትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማን፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች እንዲሁም ሚኒስትሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ የወንዝ ዳር ዳርቻ ልማት የችግኝ የተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በመርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ልማት ጋር የተሳሰረ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ በምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እንዳለው ጠቁመው፤ ከዚህ አኳያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አካባቢን ከመለወጥ ባሻገር ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማንሰራራት ትልቅ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ ኢትዮጵያ በቡና ምርታማነት ላይ ያስመዘገበችው ውጤት ለዚህ ማሳያ መሆኑን በማንሳት። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁሉም ዜጋ ሀገር ለመለወጥ በባለቤትነት የሚሳተፍበት የትውልድ ስራ መሆኑንም ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ሁሉም የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግ አፈ ጉባኤ ታገሰ ጥሪ አቅርበዋል። ሁሉም ዜጋ እጅ ለእጅ ተያይዞ በጋራ መስራት ከቻለ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ እንደምትለወጥ ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ የተጀመሩ ስራዎችን በትብብር ማስቀጠል ይገባል ብለዋል። "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው በዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ይተከላሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ጋር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሔዱ
Jun 28, 2025 93
አዲስ አበባ ፤ሰኔ 21/2017 (ኢዜአ)፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማ ጋር በመሆን በጉለሌ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሒደዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩ ላይ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች መገኘታቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ ይካሄዳል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባሻገር የዜጎችን ተጠቃሚነት እያሻሻለ ይገኛል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Jun 28, 2025 113
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፦የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባሻገር የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሻሻለ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማን እንዲሁም ሌሎች የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላትና ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ትናንት ተካሂዷል። በዛሬው ዕለትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማን፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች እንዲሁም ሚኒስትሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ የወንዝ ዳር ዳርቻ ልማት የችግኝ የተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ማንሰራራት የሚያሳልጥ ሀገራዊ ፕሮጀክት ነው። መርሃ ግብሩ በተለይ የአዲስ አበባን የአረንጓዴ ሽፋን በማሳደግ ገጽታዋን በመቀየር ረገድ ትልቅ ፋይዳ ማበርከቱንም ነው የገለጹት። የአዲስ አበባ ከተማ የደን ሽፋን ከዚህ ቀደም ከነበረበት ሁለት ነጥብ ስምንት በመቶ ወደ 22 በመቶ ማደጉን አንስተው፤ ይህም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተጨባጭ ውጤትን እንደሚያሳይ ተናግረዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ከማዘጋጀት እስከ መንከባከብ ባለው ሰንሰለት ውስጥ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል መፈጠሩንም ጠቁመዋል። በአዲስ አበባ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከወንዝ ዳር ልማት ጋር በማስተሳሰር እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም በተለይ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት እየተተከሉ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በጎ ሚና እንዳለው አንስተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ በከተማ ደረጃ በነገው ዕለት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን እንደሚያስጀምር ያነሱት ከንቲባ አዳነች፤ የከተማዋ ነዋሪዎች በመርሃ ግብሩ በንቃት እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተግቶ በመስራት ሀገርን መለወጥና ለመጪው ትውልድ ዕዳን ሳይሆን ምንዳን ማውረስ እንደሚገባ በተግባር የሚታይበት እንደሆነም ነው የገለጹት። "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው በዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ይተከላሉ።
በደቡብ ወሎ ዞን ከ29 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ችግኝ ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል
Jun 28, 2025 71
ደሴ ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፡-በደቡብ ወሎ ዞን በአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብር ከ29 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ችግኝ ለመትከል ዝግጅት መደረጉን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡ ከዝግጅቱም መካከል የችግኝና የመትከያ ጉድጓድ ቁፋሮ ማካሄድ እንደሚገኙበት መምሪያው ጠቅሷል። የመምሪያው ምክትል ኃላፊ አቶ ደመቀ አድማሱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብር በዞኑ ጉዳት ደርሶበት የቆየ ደን እንዲያገግም ፣ መሬቱ በጎርፍ እንዳይሸረሸርና ምርታማነት እንዲጨምር እያስቻለ ነው። ሕብረተሰቡም ከደን ልማቱ የሚያገኘውን ጥቅም ለማስፋት ችግኝ የመትከልና የመንከባከብ ባሕሉ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። በክረምቱ በሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብር በርካታ ችግኝና ጉድጓድ ተቆፍሮ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡ ችግኙ በ29 ሺህ 673 ሄክታር መሬት ላይ እንደሚተከል ጠቁመው፤ ሕብረተሰቡም ከመትከል ባለፈ በኃላፊነት በመንከባከብ ተጠቃሚነቱን በተግባር እያረጋገጠ ነው ብለዋል፡፡ በቃሉ ወረዳ የ06 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ይማም ካሳው በሰጡት አስተያየት፤ ከአሁን ቀደም የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኝ በማፍላት በማሳቸው ላይ ከመትከል ባለፈ ችግኝ እየሸጡ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ዘንድሮም ከ20 ሺህ በላይ የማንጎ፣ አቡካዶና ሌላም የፍራፍሬ ችግኝ ያዘጋጁ መሆኑን ጠቁመዋል። ተሁለደሬ ወረዳ የ09 ቀበሌ አርሶ አደር ያሲን ጅብሪል በበኩላቸው ፤ በዘንድሮው ክረምት የሚተከል የባህርዛፍ፣ ጽድና ሌላም ዓይነት ችግኝ ለተከላ ች እያዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከሚተክሉት የተረፈውን በመሸጠም ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት ማቀዳቻውንም ጠቁመዋል፡፡ በደቡብ ወሎ ዞን ባለፈው ክረምት 30 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት ላይ ከተተከለው ችግኝ ውስጥ 80 በመቶው መፅደቅ መቻሉን ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡