ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ጋር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሔዱ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ጋር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሔዱ

አዲስ አበባ ፤ሰኔ 21/2017 (ኢዜአ)፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማ ጋር በመሆን በጉለሌ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሒደዋል።
በችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩ ላይ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች መገኘታቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ ይካሄዳል።