ፖለቲካ - ኢዜአ አማርኛ
ፖለቲካ
በድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Nov 17, 2025 25
ድሬዳዋ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ከሪማ አሊ ተናገሩ። የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች እና አመራሮች 20ኛውን የብሔሮች -ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በፓናል ውይይት አክብረዋል። በመድረኩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈጉባ ከሪማ አሊ፤ የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ስናከብር በየአካባቢው ያልተገለጡ እሴቶችን በማስተዋወቅና በመጋራት እንዲሁም ለሀገር ልማትና ብልጽግና በጋራ በመትጋት መሆን አለበት ብለዋል። ዘንድሮም ለልማት በመትጋትና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት ማክበር እንዳለበት አንስተዋል። በመሆኑም የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫና የፍቅር ምልክት በሆነችው ድሬዳዋ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት። የድሬዳዋ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ሐይር ሐጂ ኑር፤ የበዓሉ መከበር ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጽናት የተጀመሩ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማሳካት በጋራ ለመትጋት መሆኑን አንስተዋል። በዚህ ረገድ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ሰራተኞች የላቀ ሃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸው ለውጤታማነት ቅንና ፍትሃዊ አገልጋይ በመሆን መስራት አለብን ብለዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞችም በቅንነትና በታማኝነት ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ለለውጥና ማንሰራራት እንሰራለን ነው ያሉት።
የፖሊስ ተቋምን በማዘመን የሰላምና ልማት ሥራዎችን ለማጠናከር ይሰራል
Nov 17, 2025 47
ሆሳዕና፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖሊስ ተቋምን ከወቅቱ ጋር በማዘመን የሰላምና ልማት ሥራዎችን ለማጠናከር ይሰራል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ። በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን "ከጂኦስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሀሳብ ለፖሊስ አመራሮችና አባላት ያዘጋጀው ስልጠና በሆሳዕና ከተማ እየተሰጠ ነው፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት፤ ፖሊስ ጸጥታና ደህንነትን በማስጠበቅ የክልሉ ሰላምና ልማት እንዲጠናከር አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። ፖሊስ ከማህበረሰቡ ጋር የቅርብ ቁርኝት ያለው መሆኑን አስታውሰው ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባና በየአካባቢው ልማት እንዲፋጠን ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በማፋጠን የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰላምና ደህንነት አጠናክሮ ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ፖሊስ ይህን ሀላፊነቱን በላቅ ብቃት እንዲወጣ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። ለዚህም አሰራሩን ወቅቱን በሚመጥን መልኩ የማዘመን ሥራ እንደሚሰራና የፖሊስ አባላትን አቅም በተለያየ መንገድ የመገንባት ሥራም ትኩረት እንደተሰጠው ተናግረዋል።
በዓሉ ብዝሃነትን ለማስረጽ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው
Nov 17, 2025 66
አሶሳ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ብዝሃነትን ለማስረጽ እና አንድነትን ለማጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አስካለች አልቦሮ ገለጹ፡፡ አፈ ጉባኤዋ በሰጡት መግለጫ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር አስታውቀዋል። በዓሉ በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች በስፖርታዊ ውድድሮች፣ በጥያቄና መልስ እንዲሁም ብዝሃነትን በሚያንፀባርቁ ሁነቶች እንደሚከበር ጠቁመዋል። በዓሉ በክልሉ ደረጃ በካማሽ ዞን ካማሽ ከተማ እንደሚከበር የገለፁት አፈ ጉባኤዋ፤ በበዓሉ ላይ ከክልሉ በተጨማሪ የአጎራባች ክልሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ ብለዋል። የካማሽ ዞን ከነበረበት የፀጥታ ችግር ተላቆ በተለያዩ የልማት ስራዎች አመርቂ ውጤቶችን እያሳየ በመሆኑ በዓሉ የዞኑን አሁናዊ ሁኔታ ለሌሎች አካባቢዎች ለማሳየት እንደሚያግዝ ተናግረዋል። የካማሽ ዞን በዓሉን ለማስተናገድ እና እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት መጀመሩንም አፈ ጉባኤዋ ገልጸዋል። የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል በህዝቦች መካከል ያለውን አብሮነት በማጠናከርና ሀገራዊ ትርክት ለመገንባት የሚያግዝ መሆኑን አስታውቀዋል።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የእጩ ምዝገባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል
Nov 17, 2025 65
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የእጩ ምዝገባ ከዛሬ ጀምሮ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የግል ዕጩዎች ምዝገባ የሚጀመርበት ጊዜ በቀጣይ ይፋ እንደሚሆንም ጠቁሟል። ምርጫ ቦርድ በጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ባደረገው ጥሪ እጩዎቻቸውን ቦርዱ በገለጸው ሲስተም ተጠቅመው እንደሚያስመዘግቡ ጥሪ አቅርቧል። ምዝገባውን ለማከናወን የሚያስችሉ አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ከህዳር 8 እስከ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በቦርዱ ዋና መሥሪያ ቤት እና ከዚህ ቀደም ፓርቲው ለቦርዱ ባሳወቀው/ባሳወቃት ወኪል አማካኝነት በአካል በመገኘት ሠነዱን እንዲያቀርቡ አሳስቧል። ፖለቲካ ፓርቲዎቹ ቅጾቹን ከ https://nebe.org.et/en/node/725 ላይ ማግኘት እንደሚችሉም ጠቁሟል። በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ለውድድር የተጠቀሙባቸው መወዳደሪያ ምልክቶችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጠቀም ቀዳሚ መብት እንዳላቸው ቦርዱ ገልጿል። ፖለቲካ ፓርቲዎች የሕጉን መሥፈርት የተከተለ የራሳቸውን የመወዳደሪያ ምልክት ማቅረብ እንደሚችሉና በአማራጭነት ቦርዱ ጋር በአካል በመቅረብ ቦርዱ ከሚያቀርበው የመወዳደሪያ ምልክት ዝርዝር ውስጥ መምረጥ እንደሚችሉም አመልክቷል። የግል ዕጩዎች ምዝገባ ቦርዱ በገለጸው መተግበሪያ እንደሚያከናውንና የሚጀመርበትን ጊዜ በተመለከተ ቦርዱ በቀጣይ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የልማት ስራዎች ከዳር እንዲደርሱ የፖሊስ አባላት ሚና ሊጠናከር ይገባል
Nov 17, 2025 43
ቦንጋ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-የተወጠኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶችና ሌሎች የልማት ስራዎች ከግብ እንዲደርሱ የፖሊስ አባላት ያለባቸውን ኃላፊነትና ሚና ሊያጠናክሩ ይገባል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አሳሰቡ። "ከጂኦ ስትራቴጂካዊ ኩስመና ወይ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሃሳብ ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ የፖሊስ አመራሮችና አባላት የተዘጋጀ ስልጠና በቦንጋ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል። የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ እንደገለፁት፣ ከለውጡ ወዲህ በርካታ ፈተናዎች ውስጥ በማለፍ በርካታ ድሎችን ማስመዝገብ ተችሏል። ለውጡ ብዙ መስዋእትነት የተከፈለበት መሆኑን ጠቅሰው የፖሊስ አባላቱ ከዚህ ቀደም ከነበረው የበለጠ ትጋትና ቁርጠኝነት እንዲሁም ጀግንነት የሚጠይቁ ተግባራት ከፊታቸው እንዳሉ ሊገነዘቡ እንደሚገባም አንስተዋል። ስለሆነም በመንግስት የተወጠኑ የልማት ስራዎች ከዳር እንዲደርሱ የፖሊስ አባላት ኃላፊነትና ሚና ሊጠናከር ይገባል ብለዋል። የፖሊስ አባሉ አሁን ያለውን ክልላዊ፣ ሀገር አቀፋዊና ቀጠናዊ ሁኔታዎችን በተገቢው ለማወቅና ለመረዳት የሚያስችለው ስልጠና መሆኑን አፈ-ጉባኤው አስረድተዋል። የክልሉ ሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ዓለሙ፤ ስልጠናው የዓለም-አቀፉን የጂኦ ፖለቲካ ሁኔታ በመገንዘብ ተገቢውን ቁመና ለመያዝና የፖሊስ ሠራዊቱን አረዳድ የተሻለ ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል። ስልጠናው ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥም ታውቋል።
የፖሊስ አባላት ሕግ የማስከበር ሚናቸውን ይበልጥ ማጠናከር አለባቸው
Nov 17, 2025 45
ወላይታ ሶዶ፤ ሕዳር 8/2018 (ኢዜአ)፡-በክልሉ የፖሊስ አባላት የሕግ የበላይነትን የማስከበር ሚናቸውን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለባቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሰተዳድር ጥላሁን ከበደ አስገነዘቡ። "ከጂኦ ስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና በሚል" መሪ ሐሳብ ለክልሉ የፖሊስ አመራሮች እና አባላት ስልጠና እየተሰጠ ነው። የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ በስልጠናው መድረክ ባደረጉት ንግግር፤ ከኩስመና ታሪካችን ወጥተን ወደ ታደሰ ቁመና ለመሻገር የሚሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ የሚወጣ ፖሊስ መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል። እንደ ሀገር የተመዘገበውን የጂኦ ስትራቴጂ አቅማችንን በማስቀጠል የክልሉና ኢትዮጵያን ሰላም ለማፅናት የፖሊስ አባላት ሕገ መንግስቱን በመጠበቅ የሕግ የበላይነት የማስከበር ሚናቸውን ይበልጥ ማጠናከር አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል።
የክልሉ ፖሊስ ሕግን በማስከበር ሚናውን እየተወጣ ነው
Nov 17, 2025 67
አሶሳ፤ ሕዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ የሕብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት እያስጠበቀ የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሚናውን እየተወጣ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ። ርዕሰ መስተዳድሩ "ከጂኦስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል መሪ ሐሳብ ለክልሉ ፖሊስ እና ፀጥታ አካላት የሚሰጠውን ስልጠና አስጀምረዋል። በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን እንደተናገሩት፤ የፀጥታ አካላት ዋነኛው ተልዕኮ የሕብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅና ሕግ ማስከበር ነው። ተለዋዋጭ የሆነውን ወቅታዊ ጂኦፖለቲክስ በመረዳት እና በተደመረ አቅም የክልሉን ሰላም ለመጠበቅ የሚያግዝ የፀጥታ ሀይል እንዲኖር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ከዚህ ባለፈ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ሀገሪቷ የምታከናውናቸው ግዙፍ የልማት እንቅስቃሴዎች ደህንነት ማስጠበቅ እንዳለባቸውም አሳስበዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ሀሩን ዑመር በበኩላቸው፤ ስልጠናው በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የፖሊስ አባላት ተቀራራቢ ግንዛቤ እንዲኖራቸው እና ለላቀ ተልዕኮ ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል። ለሁለት ቀናት በተሰናዳው ስልጠና ላይ የክልሉ የፖሊስ አመራሮች እና አባላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
የፌዴራል መንግስት ወደ ቀያችን እንድንመለስ ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም የቀድሞው ህወኃት እንቅፋት ሆኖብናል
Nov 17, 2025 67
ሽረ እንዳስላሴ፤ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦የፌዴራል መንግስት ወደ ቀያችን እንድንመለስ ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም የቀድሞው ህወኃት እንቅፋት ሆኖብናል ሲሉ የሽረ እንዳስላሴ ተፈናቃዮች ተናገሩ። በዚሁ ጉዳይ ላይ ቀደም ብለው ማብራሪያ የሰጡት የትግራይ ክልል የቀድሞ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዳይመለሱ በክልሉ መጠቀሚያ እያደረጉ ያሉ አካላት መኖራቸውን መግለፃቸው ይታወሳል። ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ሳይመለሱ በየመጠለያዎቹ ለእንግልት እየተዳረጉ መሆኑንና የዚህ ችግር ምክንያቱ የቀድሞ ህወሓት አመራሮች መሆናቸውን የኢዜአ ሪፖርተር በሽረ እንዳስላሴ ያነጋገራቸው ተፈናቃዮች ገልፀዋል። የፌዴራል መንግስት ተፈናቃዮች ወደ ቀያችን እንድንመለስ በተደጋጋሚ ቢገልፅም የቀድሞው ህወኃት አመራሮች እንቅፋት በመሆናቸው እስካሁን ሊሳካ አልቻለም ሲሉ አንስተዋል። ተፈናቃዮቹ ለዓመታት በመጠለያ ውስጥ ለችግርና እንግልት እየተዳረግን ቀጥለናል በማለት በምሬት ተናግረዋል። ከአምስት ዓመት በፊት ከአምስት ልጆቻቸው ጋር ከወልቃይት ተፈናቅለው በሽረ እንዳስላሰ ከተማ "አዲ ከንቲባይ" በትምህርት ቤት ተጠልለው የሚገኙት አቶ አንበሳ በርሄ፣ የመመለስ ተስፋ ይዘን ለአመታት ብንጠባበቅም ተግባራዊ ምላሽ አጥተናል ብለዋል። በዚህ ጉዳይ ላይ የፌዴራል መንግስት የፀና አቋም ይዞ እየሰራ መሆኑን ብናውቅም የመመለሱ ጉዳይ በቀድሞው ህወሓት አመራሮች ምክንያት ፈተና ሆኖብናል ብለዋል። በመሆኑም ካለንበት እንግልትና ስቃይ ወጥተን ወደ ቀያችን እንድንመለስ የመንግስትን እገዛና ድጋፍ አሁንም እንሻለን ብለዋል። ሌላኛዋ ተፈናቃይ ወ/ሮ ልእልቲ፣ ለአምስት አመታት ከቤት ወጥቶ በመጠለያ መኖር ምን ያክል ከባድና ዋጋ ያስከፈላቸው መሆኑን አንስተው፣ከእንግዲህ ይብቃን መልሱን ሲሉ ተማፅነዋል። በዚሁ መጠለያ ያገኘናቸው አቶ ኃብቶም ገ/ክርስቶስ፣ በመጠለያ ለዓመታት የደረሰብን እንግልትና ስቃይ ይብቃን መፍትሄ እንሻለን በማለት ተማፅነዋል። ሁላችንም ወደ ቀያችን እንድንመለስ በፌዴራል መንግስት የሚቀርበው ተደጋጋሚ ጥሪ ተቀባይነት ማግኘት አለበት ያሉት ተፈናቀዮቹ በመጠለያ የዓመታት የስቃይ ህይወት ይብቃን ወደቀያችን እንመለስ በማለት ጠይቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው ማብራሪያ በሰጡባቸው አጋጣሚዎች ሁሉ የትግራይ ክልል ህዝብ ሰላምና ልማት ይሻል፣ ተፈናቃዮችም ከምንም በፊት ወደ ቀያቸው መመለስ አለባቸው በማለት በተደጋጋሚ መናገራቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ በቀጣናው ደህንነት እና ልማት ያላትን ሚና አውስትራሊያ ትደግፋለች- አምባሳደር ፒተር ሃንተር
Nov 16, 2025 108
አዲስ አበባ፤ ህዳር 7/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቀጣናው ደህንነት እና ልማት ውስጥ እየተወጣች ያለውን ትርጉም ያለው ሚና አውስትራሊያ እንደምትደግፍ አምባሳደር ፒተር ሃንተር (ዶ/ር) ገለጹ። አውስትራሊያ ከኢትዮጵያ ጋር በአዳዲስ መስኮች ትብብር የመፍጠር ፍላጎት አላት ብለዋል። በኢትዮጵያ የአውስትራሊያ አምባሳደር ፒተር ሃንተር (ዶ/ር) የአፍሪካ ቀንድ ውስብስብ ፈተናዎች ያሉበት ቀጣና እንደሆነ ገልጸዋል። በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ በቀጣናው ደህንነት እና ልማት እያደረገች ያለውን ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ እንደምትደግፍም አመልክተዋል። አምባሳደር ሃንተር አውስትራሊያ እና ኢትዮጵያ ያላቸው የሁለትዮሽ የትብብር አድማስ እየሰፋ እንደሚገኝ አንስተዋል። የህዝብ ለህዝብ ትስስር፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ትምህርትን በማሳያነት ጠቅሰዋል። የአውስትራሊያ መንግስት ከኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስት ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር በቅርበት እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት። አምባሳደሩ ኢትዮጵያ እየተገበረች ያለችውን የኢኮኖሚ ሪፎርሞች ያደነቁ ሲሆን ሪፎርሙ የባለሀብቶችን የራስ መተማመን መጨመሩንና አዳዲስ እድሎችን መፍጠሩን አብራርተዋል። አውስትራሊያ ከኢትዮጵያ ጋር በቱሪዝም፣ ማዕድን እና ግብርና ዘርፍ ያላትን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል። በተጨማሪም አምባሳደሩ ለአዲስ አበባ ለውጥ ያላቸውን አድናቆት ገልጸው ይህም የኢትዮጵያን እድገት ምልክት ነው ብለዋል። ከዓለም አቀፍ ጉዳዮች ጋር በተገናኘም አውስትራሊያ የባለብዙወገን መድረክ ማሻሻያ እንዲደረግ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደምታደርግና አፍሪካ በዓለም የወሳኔ ሰጪነት ውስጥ ያላት ሚና ማደግ እንደሚገባው አመልክተዋል። አውስትራሊያ ደህንነት እና ልማትን ጨምሮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር ለማጠናከር እንደምትሻም አክለዋል
የከሚሴ እና የወሎ ሕዝብ ሰላምንና አብሮነትን በማስቀደም ለብልጽግና የምታደርጉትን ርብርብ ማስቀጠል አለባችሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
Nov 15, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የከሚሴ እና የወሎ ሕዝብ ሰላምንና አብሮነትን በማስቀደም ለብልጽግና የምታደርጉትን ርብርብ ማስቀጠል አለባችሁ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በከሚሴ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ የወሎን የመሰለ የልብ ፍቅር ካለ ክፋት እና ጥላቻ መቼም እንደማያሸንፉ ገልጸዋል፡፡ የልብ ፍቅር ምን እንደሆነ ለሚያውቀው እና ፍቅርን በተግባር እየኖረ ላለው ለከሚሴ እና ለወሎ ሕዝብ መንገር አይጠበቅብንም ሲሉም ተናግረዋል። ከወሎ ሕዝብ የሚመነጭ ፍቅር እንኳን ለወሎ ለመላው ኢትዮጵያም የሚተርፍ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡ የከሚሴ እና የወሎ ሕዝብ እንደሚያውቀው ሰላም ከእውነተኛ ልብ ይመነጫል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዚህም ለሌላውም የሚተርፍ ፍቅር እንዳለው ጠቅስዋል፡፡ የከሚሴ ሕዝብ በፍቅር እና በጠንካራ ሠራተኛነቱ የሚታወቅ ህዝብ መሆኑንም ተናግረዋል። ፍቅር ከልብ እንደሚመነጨው ሁሉ ሰላምም ከውስጥ ይመነጫል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ውስጡ ሰላም የሌለው ከውጪ ለመግዛት ቢሞክር እንደማይችል ገልጽዋል። በመሆኑም ሰላም ሁልግዜም ከውስጥ መጥፋት የሌለበትና ለሌሎችም የምታስተምሩት መሆን አለበት ብለዋል። ከዚህ በፊት በአንድነት አስቸጋር የነበሩ ግዚያትን አሳልፋችኋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከአሁን በኋላ ግን ቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ኑሮ እንዲኖር በጋራ እንሰራለን ነው ያሉት።
ሰራዊታችን በባንዳነት በተሰለፈው ፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን እያፀና ነው - ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ
Nov 15, 2025 99
ባሕርዳር፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፡- ሰራዊቱ የኢትዮዽያ ታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ በመሆን በባንዳነት በተሰለፈው ፅንፈኛ ቡድን ላይ ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን በዘላቂነት እያፀና መሆኑን የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ ገለጹ፡፡ ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ፤ በሰሜን ጎጃም እና በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች በግዳጅ ላይ የሚገኘውን ኮር የግዳጅ አፈጻጸም የመስክ ምልከታ አድርገዋል። ከመስክ ምልከታቸውም በኋላ ከዞንና ከወረዳ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አመራሮች ጋር የተወያዩ ሲሆን በሰሜን አቸፈር ወረዳ ሊበን ከተማ በአንድ ክፍለ ጦር የስልጠና ማጠናቀቂያ ላይ በመገኘትም የስራ መመሪያና ስምሪት ሰጥተዋል። ሌተናል ጄኔራሉ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሰራዊቱ የኢትዮዽያ ታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪ በመሆን በባንዳነት የተሰለፈውን ፅንፈኛ ቡድን ተከታትሎ እርምጃ በመውሰድ ሰላምን በዘላቂነት እያፀና ይገኛል ብለዋል። በተለያዩ አካባቢዎች በመሽሎክሎክ ሕብረተሰቡን በማገትና በመዝረፍ ወንጀል የሚፈፅመውን ፅንፈኛ ቡድን ሰራዊቱ ከሕዝቡ ጋር በመተባበር ተከታትሎ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተው፤ ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። የታሪካዊ ጠላቶችን ተልዕኮ በመቀበል በክህደት በዜጎች ላይ ወንጀል ለመፈፀም የሚንቀሳቀሰውን ፅንፈኛ ቡድን በየደረጃው የሚገኘው አመራር፣ ሕዝቡና የፀጥታ ሃይሉ በትብብር ሕግ የማስከበር ስራውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። በኢትዮዽያ ሁሉም አካባቢዎች ሰላምን በማፅናትና የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማሳካት የኢትዮጵያን እድገትና ብልፅግና ማረጋገጥ የሁላችንም አደራ እና ሃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል። የሰላምና የጀግንነት ተምሳሌት የሆነው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለኢትዮዽያ ክብርና ሉአላዊነት መከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ በላቀ ዝግጁነት የሚገኝ መሆኑን ሌተናል ጄኔራል መሀመድ ተሰማ አረጋግጠዋል።
በክልሉ የጋራ ትርክት ግንባታን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን እውን ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቷል - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ
Nov 15, 2025 74
ጋምቤላ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የጋራ ትርክት ግንባታን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን እውን ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ። በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ውይይት አካሂደዋል። ርዕሰ መስተዳድሯ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የክልሉ ህዝብ አንድነቱንና አብሮነቱን በማጠናከር መንግስት የጀመረውን የዘላቂ ሰላም ግንባታና የልማት ስራዎች ማገዝ ይጠበቅበታል። የክልሉ አመራርም የአስተሳሰብና የተግባር አንድነቱን በማጠናከር በክልሉ የታለሙ የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶችን ዳር ለማድረስ ከምንጊዜውም በላይ በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በክልሉ የጋራ ትርክት ግንባታን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምና ልማትን እውን ለማድረግ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ነው ያሉት። በክልሉ የሚፈለገውን ልማትና እድገት ማሳካት የሚቻላው ዘላቂ ሰላምን ማስፈን ሲቻል መሆኑን ጠቁመው የክልሉን ሰላም ለማደናቀፍ የሚሰሩ አካላትን በጋራ መታገል ይገባል ብለዋል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) በበኩላቸው ዘላቂ ሰላም በማስፈን የተጀመሩ የልማት እቅዶችን ለማሳካት ህዝብን አስተባብረን ልንሰራ ይገባል ነው ያሉት። በተለይም የክልሉን ሰላም ለማወክ የሚሰሩ አካላትን እኩይ ተግባር በመመከቱ ረገድ ሁሉም በጋራ ተባብሮ መስራት እንደለበት ገልጸዋል። የጋራ ትርክት ግንባታ ስራዎችን በማጎልበት መልካም እሴቶችን ማጠናከር ላይ ትኩረት አድረጎ መሰራት እንዳለበት ያመለከቱት ደግሞ የክልሉ መንግስት የዴሞክራሲ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሸኔ አስቲን ናቸው።
የድሬዳዋ ልማትና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የወጣቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል - ከንቲባ ከድር ጁሃር
Nov 15, 2025 120
ድሬደዋ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የድሬዳዋ ልማትና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የወጣቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ። የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶች ምክር ቤት ሁለተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። ጉባኤው በሁለት ቀናት ቆይታው በአገርና በድሬዳዋ ልማት፣ ሰላም እና ዘላቂ ዕድገት ላይ ወጣቱ ያለውን አበርክቶ እና ተጠቃሚነት ይገመግማል ተብሏል። በጉባኤ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እንደተናገሩት ወጣቶች የድሬደዋን የብልጽግና ጉዞና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የላቀ ሚናቸውን እየተወጡ ናቸው። ወጣቶች በድሬዳዋ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ያላቸውን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማስቀጠልም አስተዳደሩ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። አገራዊ ለውጡ ወጣቶች በግልና በማህበር ታቅፈው በገጠርና በከተማ ልማት እንዲሳተፉ ማገዙን የገለጹት፤ ደግሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽነር ካሊድ መሐመድ ናቸው። ወጣቶች በበጋ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በመሳተፍ የአረጋውያንን ቤቶች በመገንባት፣ ደም በመለገስ፣ ማዕድ በማጋራት፣ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ሰላምን በማረጋገጥ ላይ በንቃት በመሳተፍ ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን እየተወጡ መሆናቸውን አንስተዋል። እነዚህን ስራዎች ከማጠናከር ጎን ለጎን በሁሉም ዘርፍ ያላቸውን ተጠቃሚነት ለማጎልበት ጉባኤው መሠረታዊ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ ተናግረዋል ። የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ወጣት ሃሚድ አብደላ በበኩሉ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ ለወጣቶች የተሰጠው ትኩረት የወጣቱን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን አንስቷል። እነዚህን እንቅስቃሴዎች በማጠናከር የድሬዳዋን ዘላቂ ሰላምና የልማት ጉዞ ከዳር ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል። ለሁለት ቀናት የሚካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ በአገራዊ መሠረታዊ አቅጣጫዎች ላይ በመወያየት የተሻለ ስራ ለማከናወን የሚያስችል ሁኔታ የሚፈጠር መሆኑን በማረጋገጥ ።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ በሂደቱ የድርሻችንን እንወጣለን - የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
Nov 15, 2025 86
አዳማ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ ለምላሹ በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን ሲሉ የተለያዩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ እንደሆነ ማንሳታቸው ይታወሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የተለያዩ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፤ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የሀገር ህልውና ጉዳይ እና የሁላችንም የጋራ አጀንዳ ነው ብለዋል። በዚህ ሂደት ውስጥ የመንግስትን ጠንካራ አቋም ያደነቁት አመራሮቹ ለስኬቱ ሁላችንም አደራ እና ሃላፊነት አለብን ሲሉም ተናግረዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የሀገር ህልውና ጉዳይ በመሆኑ ለምላሹ በሚደረገው ጥረት የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል። ከፓርቲዎቹ አመራሮች መካከል የቤንሻንጉል ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ሊቀመንበር አብዱሰላም ሸንገል፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ በሁሉም መመዘኛዎች ትክክልና ምላሽ ማግኘት ያለበት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም ፓርቲያቸው የመንግስትን አቋም በመደገፍ ለተግባራዊነቱ የድርሻውን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። የትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ለብሔራዊ ጥቅም መከበር በጋራ መቆም እንዳለበት እናምናለን ያሉት ሊቀመንበሩ፤ ጥያቄው ምላሽ እንዲያገኝ እጅ ለእጅ ተያይዘን በአንድ ልብ እንሰራለን ብለዋል። ፓርቲው በቀጣይም ለሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች ስለ ባሕር በር አስፈላጊነትና ብሔራዊ ጥቅም ዙሪያ ግልፅ ግንዛቤና አረዳድ እንዲኖረው የሚጠበቅብትን ይወጣል ነው ያሉት። የሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አለማየሁ ሻሮ በበኩላቸው፤ የባሕር በር ጥያቄ በግልፅ መነሳቱ ትክክለኛ እና ወቅቱን የጠበቀ በመሆኑ የሚደገፍ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ ለመልማት፣ ለማደግ፣ የወጪና ገቢ ምርቶችን ለማሳለጥ የግድ የባሕር በር ያስፈልጋታል ያሉት አቶ አለማየሁ፤ ጉዳዩ ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ የሚጠበቅባቸው እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። መንግስት ሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ በሆነ አካሄድ የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ እያደረገ ያለው ጥረት በመደገፍ ሁላችንም በጋራ በመቆም መረባረብ አለብን ነው ያሉት። የባሕር በር ጉዳይ ትውልድና ሀገርን የማስቀጠል የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ለስኬታማነቱ የሚጠበቅብንን እንወጣለን ያሉት ደግሞ የኩሽ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ፓርቲ ፕሬዘዳንት ማንአይቶት በየነ ናቸው። ፓርቲያቸው የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄው ትክክለኛና ፍትሃዊ መሆኑን አመልክተው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በዚህ ወሳኝ ጉዳይ በጋራ በመቆም መረባረብ አለብን ብለዋል።
“ውድብ ወለዶ ትግራይ (ወለዶ)" ሕጋዊ ክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት አገኘ
Nov 15, 2025 82
አዲስ አበባ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ“ውድብ ወለዶ ትግራይ (ወለዶ)" ሕጋዊ ክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት ሰጥቷል። ለትግራይ ክልል አማራጭ የፖለቲካ ሃሳብ ለማቅረብ ወጣቶች የፖለቲካ ፓርቲ በመመስረት ሕጋዊ ማረጋገጫ እንዲሰጣቸው ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ ማቅረባቸው ተመላክቷል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጁ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለ“ውድብ ወለዶ ትግራይ (ወለዶ)" ሕጋዊ ክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት ኅዳር 05 ቀን 2018 ዓ.ም. መስጠቱን አስታውቋል።
በጋምቤላ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል
Nov 15, 2025 72
ጋምቤላ፤ ህዳር 6/2018(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ በተለያዩ ሁነቶች ለማክበር ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ መሰረት ማቲዎስ ገለጹ። አፈ-ጉባዔዋ አከባበሩን አስመልክተው እንዳስታወቁት፤ 20ኛው የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በክልል ደረጃ በአኝዋሃ ዞን ዲማ ወረዳ አስተናጋጅነት በድምቀት ይከበራል። ሕብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ለማክበር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል። በዓሉ በክልሉ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦች በባህላዊ እሴቶቻቸው የሚያሳዩበትና ይህም የቱሪዝም ልማቱን ለማጎልበት በሚደረገው ጥረት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል። በዓሉ በክልሉ በሚገኙ የአስተዳደር እርከኖችና አደረጃጀቶች በፌዴራሊዝም ሥርዓትና በህገ መንግስት አስተምሮን ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረኮች እየተካሄዱ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም በትምህርት ቤቶች በጥያቄና መልስ እና በስፖርታዊ ውድድሮች እንዲሁም በሌሎች ሁነቶች በዓሉ እንደሚከበርም አንስተዋል። አካባበሩ በክልል ደረጃ እስከ ህዳር 20/2018ዓ.ም በማጠናቀቅ በሀገር አቀፍ ደረጃ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሚከበረው የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ላይ ለመታደም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ለኢዜአ ጨምረው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ከጎረቤቶቿ ጋር አብሮ የማደግ ፍላጎቷን ለማሳካት እየሰራች ነው - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)
Nov 14, 2025 110
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ከጎረቤት ሀገሮች ጋር አብሮ የማደግና የመበልጸግ ፍላጎቷን ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) አስታወቁ። "ሆርን ሪቪው" የተባለው ቲንክ ታንክ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ትናንት የፖሊሲ ፎረም አካሂዷል። በፎረሙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡና አጋር አካላትን ጨምሮ ፖሊሲ አውጪዎችና ምሁራን የታደሙ ሲሆን፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ(ዶ/ር) በአፍሪካ ቀንድ በተለይም በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም፤ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ግጭትና አለመረጋጋት ዋነኛ መገለጫ እየሆነ መጥቷል በሚል ከሁሉም የሚዲያ አማራጮች መስማት የተለመደ ነው። ቀጣናው ሰፊ የሚታረስ መሬት፣ የውሃ ሀብት፣ እምቅ የተፈጥሮ ማዕድንና ጠንካራ ሰራተኛ ሕዝብ ያለው መሆኑን አመልክተው፤ በአካባቢው በሚፈጠሩ ግጭቶች ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ አዳጋች እንዳደረገውም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ይህን ለረጅም ጊዜ የልማት፣ የሰላምና የደህንነት ስጋት የሆነውን ቀጣና ለመቀየር በመሰረተ ልማትና በኢኮኖሚ ትስስር እንዲፈጠር ጥረቶች እያደረገች መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ቅድሚያ ለጎረቤት የሚሰጥ፣ ከሁሉም ጋር በሰላማዊና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ አብሮ የመስራት ዓላማ መያዙን አንስተዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገሮች ጋር በሰላማዊና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ አብሮ የማደግ ፍላጎቷን በመሰረተ ልማትና በኤሌክትሪክ ሃይል ትስስር በተግባር ማሳየቷንም አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት እያደገ ከመጣው የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር አኳያ እንዲሁም እየተመዘገበ ያለውን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስቀጠል የባህር በር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ ቀደም ባሉት ዓመታት የባህር በር የነበራት ሀገር ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንድታጣ መደረጉን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ እና ኤርትራ አንድ ሀገር እንደነበሩ ያስታወሱት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ በወቅቱ ኢትዮጵያን የመሩ መንግስታት ሃላፊነት በጎደለው መልኩ ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንድትገነጠልና ከባህር እንድትነጠል ማድረጋቸውን አመልክተዋል። በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ለዘመናት የዘለቀው ግጭት መነሻ ከድንበር ውዝግብና ከባህር በር ፍላጎት የተሻገረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የኢትዮጵያን የሰላምና የልማት ፍላጎት በየጊዜው የሚገዳደር መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት እያደረገች መሆኑን ያብራሩት ሚኒስትሩ፤ ሁሉም ሀገሮች ለዚህ ሊተባበሩ ይገባል ብለዋል። የውጭ ጣልቃ ገብነትን መከላከልና የንግድና ኢንቨሰትመንት ግንኙነትን ማሳደግ ለቀጣናዊ ኢኮኖሚ ውህደት መሳካት ወሳኝ መሆኑንም ነው ያነሱት። እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፤ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም ዘላቂ ልማትን ለማምጣት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፉን ማጠናከር አለበት። ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ከሰሩ ለሌሎች ሀገሮች ምሳሌ የሚሆን ትብብር መፍጠር እንደሚችሉም ተናግረዋል።
በሶማሌ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል
Nov 14, 2025 78
ጅግጅጋ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር ተገለጸ። በክልሉ አከባበሩን በተመለከተ የዝግጅቱ አብይ ኮሚቴ በአከባበሩ ዙሪያ ዛሬ ተወያይቷል። የሶማሌ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ መሀመድ አዳን እንደገለጹት በክልሉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ይከበራል። በክልሉ በዓሉ በወረዳ፣ በዞንና በከተማ አስተዳደሮች ከዛሬ ጀምሮ እስከ ህዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም በደም ልገሳ፣ በንግድና ባዛር፣ በችግኝ ተከላ፣ በስፖርታዊ ውድድሮች፣ በፓናል ውይይት፣ አረጋውያንን በመደገፍና በሌሎች ዝግጅቶች እንደሚከበር ተናግረዋል። በክልል ደረጃ ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም በጅግጅጋ ከተማ የበዓሉ ማጠቃላይ ፕሮግራም እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።
የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ለጋራ ልማትና ዕድገት በአንድነት እንድንተጋ መነሳሳትን ፈጥሯል - የመንግስት ሰራተኞች
Nov 14, 2025 81
ወልዲያ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ለጋራ ልማትና ዕድገት ሁላችንም በህብረ ብሔራዊ አንድነት እንድንተጋ መነሳሳት ፈጥሮልናል ሲሉ የወልዲያ ከተማና የሰሜን ወሎ ዞን የመንግስት ሠራተኞች ተናገሩ። በአገራችን የሚከበረው 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ብሄራዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ በወልዲያ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል። ውይይቱ ላይ የተሳተፉ የመንግስት ሠራተኞች እንዳሉት፤ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ለጋራ ልማትና ዕድገት በህብረ ብሔራዊ አንድነት እንድንተጋ መነሳሳትን ፈጥሯል። ከተሳተፊዎቹ መካከል አቶ ታምራት ወራሴ በዓሉ ስለ ህገ መንግስት፣ ዴሞክራሲና የፌደራል ስርዓት ፋይዳ ዙሪያ እውቀት እንድንጨብጥ አስችሎናል ብለዋል። የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች አገር የሆነችው ኢትዮጵያ የህዝቦቿ አንድነት ዛሬም በእኛ ዘመን ተጠናክሮ እንዲቀጥል የጋራ ትርክት ላይ በማተኮር መስራት እንደሚገባም አመልክተዋል። ነጠላ ትርክትን በማስወገድ ለጋራ ልማትና ዕድገት በአንድነት ልንተጋ ይገባል ያሉት ደግሞ ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ጀማል ሙሐመድ ናቸው። የህገ-መንግስቱ መልካም ትሩፋቶች ለጋራ ተጠቃሚነታችን ፈር ቀዳጅ በመሆናቸው ተጠብቆ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ማዋል ይገባል ብለዋል። የሰሜን ወሎ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊና ውይይቱን የመሩት አቶ ፍስሃ መንግስቴ በበኩላቸው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀንን ስናከብር ለህዝቦች ሠላም፣ ፍቅርና አንድነት በመስራት መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። በዓሉን ስናከብር በህብረ ብሔራዊ አንድነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ሃገረ መንግስትን እውን ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሊሆን ይገባልም ብለዋል። የዘንድሮውን በዓል ለየት የሚያደርገው የህዳሴ ግድባችን ባስመረቅንበት ማግስት የሚከበር በመሆኑ ደስታችንን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል ያሉት ደግሞ የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ አቶ ኢትዮጲስ አያሌው ናቸው። በዓሉን ስናከብርም በህብረ ብሔራዊ አንድነት የተገነባችውን ኢትዮጵያ ወደፊት ለማሻገር ቁርጠኛነታችንን በማረጋገጥ መሆን አለበት ብለዋል። በመድረኩ ላይም የወልዲያ ከተማ አስተዳደር፣ የሰሜን ወሎ ዞን የመንግስት ሠራተኞችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት "ዴሞክራሲና የኢትዮጵያ ፌደራል ስርዓት" በሚል ርእስ ውይይት አካሄደዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እንግዶቹን መቀበል የሚያስችል የተሟላ ዝግጅት አድርጓል - ምክር ቤቱ
Nov 14, 2025 126
አዲስ አበባ፤ ህዳር 5/2018(ኢዜአ)፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ለማክበር የሚመጡ እንግዶቹን ለመቀበል የተሟላ ዝግጅት ማድረጉን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ገለጹ። ምክትል አፈ ጉባኤዋ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአጭር ጊዜ በዓሉን ለማስተናገድ ያከናወነው ቅድመ ዝግጅት የሚደነቅ ነው። እንደ ክልል አብዛኛዎቹ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን አንስተው፤ ቀሪ ስራዎችን በቀሩት ጊዜያት እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ መቀመጡን ተናግረዋል። በዓሉን የክልሉን ሁለንተናዊ አቅሞች ለማስተዋወቅ መጠቀም ይገባል ሲሉም ምክትል አፈ ጉባኤዋ አሳስበዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤት ሀላፊ ትግሉ መለሰ በበኩላቸው፤ ክልሉ በአጭር ጊዜ የመሰረተ ልማት ክፍተቶችን ለማሟላት ያደረገው ዝግጅት ሰፊና የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል። በዓሉን በሚመጥን መልኩ የተገነቡ የመንገድ፣ የስቴዲየም፣ የሆቴሎችና የሁነት ማሳያ ፕሮጀክቶች መሰረተ ልማቶችን በአጭር ጊዜ በጥራት ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ሲሉ ተናግረዋል። ክልሉ ቀኑን በድምቀት ማስተናገድ የሚያስችል በቂና የተሟላ ዝግጅት ማድረጉን መመልከታቸውን የጽህፈት ቤት ሀላፊው አስታውቀዋል።