ፖለቲካ
በመዲናዋ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እና የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል ህዝብን ያሳተፈ ስራ መሰራቱ ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ አስችሏል
Jul 25, 2024 216
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2016(ኢዜአ)፦ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመዲናዋ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እና የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል ቢሮው ህዝብን ያሳተፈ ስራ መስራቱ ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ አስችሏል ። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመዲናዋ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እና የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ህዝብን ያሳተፈ ስራ መስራቱ ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ማስቻሉን ገልጿል። ቢሮው በ2016 በጀት ዓመት አቅዶ ሲያከናውናቸው በነበሩ ተግባራት እና በ2017 የትኩረት አቅጣጫ ዙሪያ ከማዕከል እስከ ወረዳ ከሚገኙ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ አመራሮች ጋር ምክክር እያደረገ ይገኛል።   በዚሁ ወቅት የቢሮው ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከተማዋ ያስተናገደቻቸው ሃይማኖታዊ እና ህዝባዊ በዓላት ትውፊታቸውን ጠብቀው በሰላም ተከብረው ማለፋቸውን ገልፀዋል፡፡ ለዚህ ስኬት መሰረቱ ደግሞ ህዝቡ የሰላም ባለቤት በመሆን ያበረከተው አስተዋጽኦ መሆኑን ጠቅሰዋል። በከተማዋ የሚፈፀሙ ልዩ ልዩ የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል እና ወንጀለኞች በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ቢሮው ማህበረሰቡን ያሳተፈ ስራ ማከናወኑን አስታውቀዋል፡፡ በተለይም ህዝቡ ከሰላም ሰራዊት ጋር ተቀናጅቶ በመስራቱ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።   ለአብነትም በቅንጅት በተሰሩ ስራዎች ህገ ወጥ የመሬት ወረራ፣ የጦር መሳሪያና የገንዘብ ዝውውር እንዲሁም አዋኪ ድርጊቶችን መከላከል መቻሉን ገልፀዋል ። በአጠቃላይ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመዲናዋ የወንጀል ድርጊት የመፈፀም ምጣኔን ወደ 31 በመቶ ዝቅ ማድረግ የተቻለበት ነው ሲሉ አክለዋል ። በቀጣይም የከተማዋን ብሎም የማህበረሰቡን ሰላም ለማስጠበቅ እና የወንጀል ድርጊትን ለመከላከል የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።  
በተያዘው በጀት አመት የክልሉን የውስጥ አቅሞችና ጸጋዎች በአግባቡ በመጠቀም የህዝቡን ጉልህ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ ይሰራል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው
Jul 25, 2024 260
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 18/2016(ኢዜአ)፦ በተያዘው በጀት አመት የክልሉን የውስጥ አቅሞችና ጸጋዎች በአግባቡ በመጠቀም የህዝቡን ጉልህ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ ይሰራል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለጹ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ሲሆን በዛሬው እለት በክልሉ መንግሥት የ2017 በጀት አመት እቅድ፣ የትኩረት አቅጣጫዎች፣ በክልሉ በጀትና ሌሎች ቀሪ አጀንዳዎች ላይ በዝርዝር እየተወያየ ይገኛል።   የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ለምክር ቤቱ የ2017 በጀት አመት እቅድ ባቀረቡበት ወቅት የክልሉን የውስጥ አቅሞችና ምቹ ሁኔታዎች በአግባቡ ጥቅም ላይ በማዋልና የህዝቡን ጉልህ ተሳትፎና ድጋፍ ታሳቢ ባደረገ መልኩ ይሰራል ብለዋል። በክልሉ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ቀጣይነት ማረጋገጥ ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ተናግረው ዘላቂ ሰላምን ማስፈን እና ምርታማነትን ማሳደግ ላይ በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት። በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት የሚተገበሩ እቅዶችን ይበልጥ ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ ዝርዝር ውይይቶች እና ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ አጀንዳዎች መለየት መቻሉንም ጠቁመዋል። በበጀት ዓመቱ ከዚህ ቀደም የነበሩ መልካም ልምዶችን ማስቀጠል እንዲሁም መታረም የሚገባቸውን ጉድለቶች በመለየት ለላቀ የህዝብ ተጠቃሚነት እንደሚሰራም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል። የምክር ቤት አባላት በርዕሰ መስተዳድሩ በቀረበው የ2017 በጀት አመት እቅድ ላይ ውይይት እያካሔዱ እንደሚገኙ ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በጋምቤላ ክልል ፈተናዎችን በጽናት በማለፍ ለህዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ረገድ አበረታች ሥራዎች ተከናውነዋል - አፈ ጉባኤ ባንቻየሁ ድንገታ
Jul 25, 2024 144
ጋምቤላ ፤ሐምሌ 18/2016 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ፈተናዎችን በጽናት በማለፍ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑት ስራዎች አበረታች እንደሆኑ የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ ባንቻየሁ ድንገታ ገለጹ። የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባዔውን ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል፡፡   የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ባንቻየሁ ድንገታ ጉባዔውን ሲከፍቱ እንደገለጹት በክልሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አጋጥሞ የነበረው የጸጥታ ችግር በልማት ስራዎች ላይ ተጽዕኖ ፈጥሮ የነበረ መሆኑን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ የጸጥታ ችግሩ ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ በጽናት በማለፍ በበጀት ዓመቱ የታለሙ የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶችን በመፈጸም ረገድ አበረታች ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል። ምክር ቤቱ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ተግባርና ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት በርካታ ሰራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ የታቀዱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች በተያዘላቸው ጊዜ ሰሌዳ መፈጸማቸውን በመከታተልና በመቆጣጠር ረገድ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል። እንዲሁም የወቅቱን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘቡ አዳዲስ አዋጆችን ከማውጣት ባለፈ የወጡ ህጎች በአግባቡ ስራ ላይ መዋላቸውን እየተከታተለ የእርምት እርምጃዎችን በመውሰድ በኩልም በምክር ቤቱ አጥጋቢ ስራዎች መከናወናቸውን አፈ ጉባኤዋ ገልጸዋል። ጉባዔው ከዛሬ ጀምሮ በሚኖረው የሶስት ቀናት ቆይታ የ2016 የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅድ ክንውን፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ሪፖርት አድምጦ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል። እንዲሁም የ2017 በጀት ዓመት የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅድ፣ በማስፈጸሚያ በጀትና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ከወጣው የድርጊት መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል። በጉባዔው ላይ የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ ከ350 በላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራር አባላት፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀቶች ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ናቸው።  
አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
Jul 25, 2024 135
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 17/2016(ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቢየርግ ሳንጃር ጋር ተወያዩ። በውይይታቸው በኢትዮጵያ እና በኖርዌይ መካከል ስላለው ጠንካራ አጋርነት በተለይም በትምህርት፣ በአየር ንብረት ለውጥ እንዲሁም በሰላምና ደህንነት ዙሪያ አተኩረው ሃሳብ ተለዋውጠዋል። የሁለቱን ሀገራት ትብብር የበለጠ ማስፋት እንደሚያስፈልግ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ገልጸዋል። አክለውም የኖርዌይ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። የኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቢየርግ ሳንጃር በበኩላቸው ኢትዮጵያ በቀጣናው መረጋጋት ላላት ሚና ኖርዌይ አድናቆት እንዳላት ገልጸዋል። ሁለቱ ወገኖች በአየር ንብረት ለውጥ መከላከል፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በውሃ ሃብትና በጤና ላይ ትብብርን ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም መምከራቸውም ተገልጿል። በተጨማሪም በሁለትዮሽ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።  
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ የጀመራቸውን የለውጥ ሥራዎች በማስቀጠል አቅሙ የተገነባ ሠራዊት የመገንባት ሂደቱን ሊያጠናክር ይገባል 
Jul 24, 2024 205
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2016(ኢዜአ)፦ የመከላከያ ዋር ኮሌጅ የጀመራቸውን የለውጥ ሥራዎች በማስቀጠል አቅሙ የተገነባ ሠራዊት የመገንባት ሂደቱን ሊያጠናክር ይገባል ሲሉ የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ደስታ አብቼ አመለከቱ። የመከላከያ ዋር ኮሌጅ በመደበኛና አጭር ኮርስ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በመጪው ቅዳሜ ያስመርቃል። ኮሌጁ የምረቃ በዓሉን ምክንያት በማድረግም በዛሬው ዕለት የተለያዩ መርሃ-ግብሮችን ያካሄደ ሲሆን፤ "የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ከየት ወዴት?" በሚል መሪ ኃሳብ የኮሌጁ ስኬቶች፣ የገጠሙ ፈተናዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ትኩረት ያደረገ የፓናል ውይይትም አካሂዷል። በመርሃ-ግብሩም የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ደስታ አብቼ ጨምሮ ጄኔራል መኮንኖችና ከፍተኛ መኮንኖች ተገኝተዋል። ኮሌጁ የጀመራቸው የማስፋፊያ ፕሮጀክት የደረሱበት ደረጃና የኮሌጁ የሥራ እንቅስቃሴንም ሌተናል ጄኔራል ደስታ አብቼ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።   ሌተናል ጄኔራል ደስታ አብቼ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ ዘመናዊ ሠራዊት ለመገንባት ቀጣይነት ያለው ሥልጠና ተደራሽ ማድረግ የግድ ይላል። በተለይም ከለውጡ ወዲህ ሠራዊቱን በሪፎርም የማጠናከር ጉዳይ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም አበረታች ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን ጠቁመዋል። መከላከያ ዋር ኮሌጅም የለውጡ ፍሬ ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ደስታ፤ ኮሌጁ ተልዕኮውን፣ ዓላማና ግቡን ለማሳካት የጀመራቸውን የለውጥ ሥራዎች ሊያጠናክር ይገባል ብለዋል። ኮሌጁ በሰው ኃይል፣ በሥርዓተ-ትምህርት እንዲሁም በመሠረተ-ልማት ራሱን ሊያጠናክር እንደሚገባም አጽንዖት ሰጥተዋል። የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ቡልቲ ታደሰ በበኩላቸው፤ ዘመኑን የዋጀ ፕሮፌሽናል ሠራዊት መገንባት ጊዜው የሚጠይቀው ጉዳይ ነው ብለዋል።   ለዚህ ደግሞ አካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮችን የተገነዘበ የሠራዊት አመራር መገንባት ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል። ከዚህ አኳያም ኮሌጁ ስትራቴጂያዊ አመራር የማፍራት ሥራውን በትኩረት እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ በረዥምና በአጫጭር ሥልጠናዎች በርካታ አመራር ማሰልጠን መቻሉን ተናግረዋል። ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ሥራዎቹ ጎን ለጎንም የጥናትና ምርምር ሥራዎችም በስፋት እያከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል። ኮሌጁ የተመሠረተበትን ዓላማ በላቀ ደረጃ ለመፈጸም የለውጥ ሥራዎችን ተግባራዊ ማድረጉን ጠቁመው፤ በዚህም ውጤታማ መሆን መቻሉን አብራርተዋል። ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የመከላከያ ጠቅላይ መምሪያ ጠቅላላ አገልግሎት የፋሲሊቲ ዳይሬክተር ኮሎኔል ዘካሪያስ ጥሩነህ በሰጡት አስተያየት፤ ኮሌጁ በመማር ማስተማሩ ሂደት የበለጠ ውጤታማ ለመሆን የመምህራንንና ስታፎችን አቅም መገንባት ላይ የበለጠ መሥራት አለበት ብለዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰላምና ደኅንነት ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፋና ገብረሰንበት በበኩላቸው፤ ኮሌጁ አገር በቀል እውቀቶችንና ልምድ ያላቸው የዘርፉ ባለሙያዎችን ይበልጥ በመጠቀም ተቋሙን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።   ኮሌጁ የምረቃ በዓሉን ምክንያት በማድረግም የችግኝ ተከላና የደም ልገሳ መርሃ-ግብር አከናውኗል።    
ሰላምን ዘላቂ ከማድረግ ጎን ለጎን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው - የደሴ ከተማ አስተዳደር
Jul 24, 2024 101
ደሴ ፤ሐምሌ 17/2016(ኢዜአ)፡- ሰላምን ዘላቂ ከማድረግ ጎን ለጎን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የደሴ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። የደሴ ከተማ አስተዳደር ከሀይማኖት አባቶች ጋር የሰላም ምክክር አካሂዷል። የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ለዘላቂ ሰላም መስፈን ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል። የታጠቁ ቡድኖችም የመንግስትን ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም መምጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል። ሰላም የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በየደረጃው ለመመለስ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ “በከተማው ህብረተሰቡን በማስተባበር ሰላም ከማስፈን ባለፈ ሰፋፊ የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል” ብለዋል። ሰላምን ዘላቂ ከማድረግ ጎን ለጎን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች የማከናወን ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። “ለዘላቂ ሰላም መስፈን ሁሉም የድርሻቸውን ሊወጣ ይገባል” ያሉት ደግሞ በምክክር መድረኩ የተገኙት በሀገር መከላከያ ስራዊት የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አሰፋ ቸኮል ናቸው።   “ህብረተሰቡ አንድነቱን ጠብቆ ሰላሙን ለማጽናት መስራት ይኖርበታል'' ሲሉ አስገንዝበዋል ። ከመንግስት ጎን በመሆን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ሁሉ የድርሻቸውን እንደሚወጡ የገለፁት ደግሞ የመድረኩ ተሳታፊ ሊቀ መዘምራን አክሊሉ አረጋዊ ናቸው። የከተማውን ሰላም በጋራ መጠበቅ በመቻሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እንዲመለሱ እድል መፍጠሩን ጠቅሰው “በቀጣይም ትብብሩ ተጠናክሮ ይቀጥላል” ብለዋል። ሌላው ተሳታፊ ሻምበል ሙሉጌታ አብርሃ በበኩላቸው ሁሉም ለሰላም መስፈን የድርሻውን ሊወጣ ይገባል” ብለዋል ።   ዘላቂ ሰላምና ልማት እውን እንዲሆን መስራት እንደሚገባ ጠቁመው፤ እርሳቸውም ሚናቸውን እንደሚወጡ አስታውቀዋል።    
በሀረሪ ክልል ህዝብና መንግስት በጋራ ባከናወኑት ስራ የተሻለ አፈፃፀም ተመዝግቧል-- አቶ ኦርዲን በድሪ
Jul 24, 2024 96
ሀረር፤ ሀምሌ 17/2016(ኢዜአ)፡- በሀረሪ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ህዝብና መንግስት በጋራ ባከናወኑት ስራ የተሻለ አፈፃፀም መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ። በክልሉ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የ2016 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማና የ2017 በጀት አመት የትኩረት አቅጣጫ ላይ ያተኮረው መድረክ ተጠናቋል።   በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እንደተናገሩት በክልሉ በ2016 በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፍ አበረታች ስራዎች ተከናውነዋል። በዚህም በክልሉ በከተማና በገጠር ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች መከናወናቸውን ነው የተናገሩት። በተለይ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ ማጠናቀቅ እንዲሁም በጥራትና በአነስተኛ ወጪ በማከናወን ለህዝብ አገልግሎት እንዲውሉ ማድረግ ስለመቻሉም ገልፀዋል። በከተማም ሆነ በገጠር የሚከናወኑ የሌማት ትሩፋት ስራዎች የዋጋ ንረትን ከማረጋጋት አንጻር አበርክቶ ማድረጋቸውንም አውስተዋል። በክልሉ ለረጅም አመታት ስራ ያልጀመሩ ኢንቨስትመንቶች ስራ የጀመሩበት፣ የጀጎል ዓለም አቀፍ ቅርስ እንክብካቤና መልሶ የማልማት ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ለኢንተርፕራይዞች የተላለፉ የገንዘብ ብድር ከማስመለስ፣ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ከመታገል አንፃር የተሻለ ስራ መከናወኑን አመላክተዋል። በበጀት ዓመቱ ለተገኘው ስኬት በአመራሩ መካከል ቅንጅታዊ አሰራር መጎልበቱ እንዲሁም ህዝቡን ያሳተፈ ስራ መከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል። አንደ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን ገለፃ በተቋምና ወረዳዎች ውስጥ የሚስተዋሉ የማስፈፀም አቅም ማነስና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በ2017 በጀት ዓመት ለመቅረፍ ይሰራል ብለዋል። ምርትና ምርታማነትን በማጎልበት፣ ህገ ወጥ ንግድን መከላከልና የቅዳሜና እሁድ ገበያን በማዘመን የዋጋ ንረትን የማረጋጋት ስራ ማከናወን እንደሚገባም ጠቅሰዋል። ተረጂነትን ትርጉም ባለው መልኩ መቅረፍ፣ የቱሪዝም ልማት ስራዎችን ማጎልበት የግብዓት የባለሞያና የአሰራር ቴክኖሎጂን በማዘመን የአርሶ አደሩን ኑሮ መቀየር ይገባል ብለዋል። የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራና ኢንቨስትመንትን የማጎልበት እንዲሁም በከተማው የሚከናወኑ የኮሪደር፣ የጽዳትና ውበት ስራዎችን በተጠናከረ መልኩ ማከናወን ይገባል ሲሉም አክለዋል። በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በበኩላቸው የአመለካከትና የተግባር አንድነትን በማጎልበትና ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የተከናወኑ የልማት፣ የሰላምና ሌሎች ስራዎችን ማጠናከር ይገባል። እንዲሁም በጎነትና አብሮነትን የሚያጎለብቱ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ ስራዎችን በትጋትና በትብብር መስራት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በማጠቃለያ መድረኩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ሱልጣን አብዱሰላምን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የመንግስትና የፓርቲ አመራሮችና ሃላፊዎች ተሳትፈዋል።  
ኢትዮጵያ እና ኩባ የሁለትዮሽ የፖለቲካ ምክክር ስምምነት ተፈራረሙ
Jul 24, 2024 111
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2016(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ኩባ የሁለትዮሽ የፖለቲካ ምክክር ስምምነት መፈራረማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከኩባ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢልዮ ኤድዋርዶ ሮድርጌዝ ፕርዶሞ ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም አምባሳደር ምስጋኑ ኩባ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ጠንካራ ግንኙነት አውስተው የሁለቱን ሀገራት ወዳጅነት በተለያዩ መስኮች ማጎልበት እንደሚገባ ገልጸዋል። የሁለትዮሽ ስምምነት የተካሄደባቸው የውሐ አስተዳደር፣ ትምህርት፣ የአየር ትራንስፖርት እና የንግድ ዘርፎች ላይ አጽንኦት የሰጡት ሚኒስትር ዴኤታው በህክምናና በስኳር ልማት ረገድ ያለውን ጠንካራ ግንኙነት አንስተዋል። የኩባ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢልዮ ኤድዋርዶ ሮድርጌዝ ፕርዶሞ በኩላቸው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩባ ሀቫና ዳግም መከፈት ለሀገራቱ ግንኙነት መሳለጥ የሚጫወተውን ሚና አውስተዋል። በውይይቱ ሁለቱም አካላት አለም አቀፍ ጫናዎችን በመቋቋም የጋራ ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ጉዳዮችን በትኩረት መስራት እንደሚገባ አረጋግጠዋል። በውይይታቸው ወቅትም ኢትዮጵያ እና ኩባ የሁለትዮሽ የፖለቲካ ምክክር ስምምነት መፈራረማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ቀጥሏል - ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን
Jul 24, 2024 99
አሶሳ፤ ሐምሌ 17/2016(ኢዜአ)፡-በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለሀገራዊ ምክክር ግብዓት የሚሆን አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት በ10 የማህበረሰብ ቡድኖች ተለይቶ ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል። በኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች እና የዲያስፖራዎች አስተባባሪ አቶ ረታ ጌራ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በክልሉ ዛሬ ጠዋት የተጀመረው ለሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ከሰዓት በኋላ በ10 የማህበረሰብ የውይይት ቡድኖች ተለይቶ ውይይት እየተደረገ ነው።   በቡድን ውይይቱ ከክልሉ አሶሳ፣ መተከል እና ካማሽ ዞኖች እንዲሁም ማኦኮሞን ጨምሮ ከ27 ወረዳዎች የተውጣጡ ከ450 በላይ ተወካዮች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። አጀንዳ የማሰባሰብ ስራውን በቡድን ማካሄድ ያስፈለገው ከተመሳሳይ ማህበረሰብ የሚነሱ የተለያዩ ሀሳቦችን በጥራት፣ በተቀላጠፈ እና ግልጽነት በተሞላበት መንገድ ለማከናወን እንደሆነ አቶ ረታ አመልክተዋል። የውይይት ቡድኑ የተዋቀረው በአርሶ አደሮች፣ ወጣቶች፣ በሴቶች፣ መምህራን፣ መንግስት ሠራተኞች፣ እድሮች፣ በንግዱ ማህበረሰብ፣ በተፈናቃዮች እና በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ነው ብለዋል ። እያንዳንዱ የማህበረሰብ የውይይት ቡድኖች አጀንዳ የማሰባሰቡን ስራቸውን የጀመሩት አሳታፊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የየራሳቸውን ሰብሳቢ እና ጸሃፊዎች በመምረጥ እንደሆነም አቶ ረታ አስረድተዋል።   የቡድኖችን አጀንዳ የማሰባሰቡን ሂደት በቋንቋ ትርጉም እና ሌሎች ድጋፎችን የሚያደርጉ ከፖለቲካ እና ሌሎች ጉዳዮች ገለልተኛ የሆኑ አመቻቾች እንደተመደቡም አስተባባሪው አብራርተዋል። የማህበረሰብ ቡድኖች እስከ መጪው ዓርብ ሐምሌ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ለሀገራዊ ምክክሩ ከተወከሉበት ማህበረሰብ ያመጡትን አጀንዳ አጠቃለው ለኮሚሽኑ እንደሚያስረክቡ አስታውቀዋል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ይኸው የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ቀሪ ሂደቶችን በማካተት ለአንድ ሳምንት ይቆያል።    
በክልሉ ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር የማረጋገጥ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ
Jul 24, 2024 100
ሐረር፤ ሐምሌ 17/2016(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር የማረጋገጥ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለጹ። በክልሉ እየተካሄደ በሚገኘው ዓመታዊ የስራ አፈፃፀም ግምገማ የማጠቃለያ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እንደተናገሩት፤ የግምገማው ዋና ዓላማ ውስንነቶችን ለመፍታትና ጥንካሬዎችን ለማጎልበት ነው።   በእቅድ አፈፃፀሙ ግምገማ ላይ የተገኙትን አበረታች ነጥቦች በግብዓትነት በመጠቀም ያንን አጠናክሮ ማስቀጠልና የተሻለ ስራ ማከናወን እንደሚገባ አመልክተዋል። የተስተዋሉ ውስንነቶችን የመፍታት ስራም ትኩረት እንዲሰጠውና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መሥራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በተለይም በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ ለህዝብ በተገባው ቃል መሠረት በበጀት ዓመቱ የልማት ስራዎች መከናወናቸውንና ተግባራዊ መሆናቸውን ማረጋገጥ እና ይበልጥ መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል። በግምገማው ማጠቃለያ መድረክ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ፣ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ሱልጣን አብዱሰላምን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የአመራር አባላትና ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የክልሉ የ2016 በጀት ዓመት ዓመታዊ የስራ አፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መድረክ ዛሬ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የፀጥታ ችግሮች አስቀደሞ ለመከላከል የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ የልማት እንቅስቃሴዎች እንዲኖር አስችሏል
Jul 24, 2024 109
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2016 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የፀጥታ ችግሮች አስቀደሞ ለመከላከል የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ የልማት እንቅስቃሴዎች እንዲኖር አስችሏል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለጹ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ ለክልሉ ምክር ቤት ባቀረቡት የ2016 በጀት ዓመት ስራ አፈፃፀም ሪፖርት ክልሉ በአዲስ ተደራጅቶ ስራ ሲጀምር ቅድሚያ ከሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ የሰላም ማረጋገጥ አጀንዳ እንደሆነ አስታውሰዋል፡፡ በዚህም አንፃራዊ ሠላም በማረጋገጥ ለሌሎች የልማት እንቅስቃሴዎች ውጤታማነት መሰረት መጣሉን ገልፀዋል። በተለይ ግጭትን አስቀድሞ በመከላከል ረገድ የተሳካ ስራ መከናወኑን አንስተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በክልሉ 224 የግጭት ቅድመ-ማስጠንቀቂያ መረጃዎችን በመሰብሰብ፣ በመተንተንና አደራጅቶ ጥቅም ላይ በማዋል የክልሉን ሰላም፣ ፀጥታና ደህንነት ማስጠበቅ መቻሉንም ነው ያነሱት።   የክልሉን ሰላምና ደህንነት ለማናጋት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 546 ሀሰተኛ የኤሌክትሮኒክስና ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በተደረገ ክትትልና የመረጃ ልውውጥ እኩይ ድርጊታቸውን መከላከል እና ማክሸፍ እንደተቻለም አንስተዋል። የብዝሀነት፣ የአብሮነት፣ የመቻቻልና የመከባበር እሴት እንዲገነባ ለማድረግ ሰፋፊ የግንዛቤ የመፍጠር ሥራዎች መሰራታቸውንም ጠቅሰዋል። የመልካም አስተዳደር ችግሮችንና አቤቱታዎችን ምላሽ እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ የአስተዳደር ችግሮች፣ የማንነትና የአደረጃጀት ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ ብቻ እንዲቀርቡም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መሰራቱንም እንዲሁ። በሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርና ቁጥጥር ረገድ በድርጊቱ የተሳተፉ 13 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ውለው ለሕግ መቅረባቸውንም አብራርተዋል፡፡ በአጠቃላይ በተከናወነው ጠንካራ የሰላምና ፀጥታ ስራም የክልሉን የወንጀል መጠን 11 በመቶ መቀነሱን ተናግረዋል።  
በሶማሌ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ የልማት ዘርፎች የተሻለ አፈጻጸም ተመዝግቧል - አቶ ሙስጠፌ ሙሐመድ 
Jul 24, 2024 82
ጅግጅጋ፤ ሐምሌ 17/2016 (ኢዜአ):- በሶማሌ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ የልማት ዘርፎች የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሐመድ ገለፁ። የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባዔ በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። በጉባዔው የክልሉ አስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች የ2016 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ቀርቦ ውይይት እየተካሄደበት ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለምክር ቤቱ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በገቢ አሰባሰብ፣ በአርብቶ አደር ልማት፣ በግብርና፣ በትምህርት፣ በጤናና በሌሎች የልማት ዘርፎች የተሻሉ አፈፃፀሞች ተመዝግበዋል። በክልሉ በሌማት ትሩፋት፣ መስኖን በማጎልበት እና የገበያ ተኮር ሰብሎች ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን አንስተዋል።   የክልሉን የገቢ አቅም ለማሳደግ በተከናወኑ ስራዎች በዓመቱ ከተለያዩ የገቢ እርዕስቶች 16 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ13 ቢሊዮን 500 ሚለዮን ብር በላይ መሰብሰቡንና ይህም የእቅዱ 84 ነጥብ 5 በመቶ መሆኑን አንስተዋል። በዓመቱ የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ3 ነጥብ 7 ቢልዮን ብር ብልጫ እንዳለው በመጥቀስ። የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ 118 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውንም እንዲሁ።   በዓመቱ በክልሉ የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የንጹህ መጠጥ ውሃ ለማዳረስ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን በሪፖርታቸው ገልጸዋል። የትምህርት ጥራት ከማጎልበትና የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ከማረጋገጥ አንጻርም አበረታች ውጤቶች ስለመመዝገባቸው ርዕሰ መስተዳደሩ ገልጸዋል። የልማት ስራዎቹ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች በመሆናቸው ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። ምክር ቤቱ በርእሰ መስተዳድሩ የቀረበው ሪፖርት ላይ ከተወያየ በኋላ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል።  
በኢትዮጵያ ዘላቂ ሠላም ለመፍጠር ምክክር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው - ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው
Jul 24, 2024 150
አሶሳ፤ ሐምሌ 17/2016(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሠላም ለመፍጠር ምክክር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው ገለጹ:: ኮሚሽኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለሀገራዊ ምክክር የሚሆን አጀንዳ የማሰባሰብ ሥራ ዛሬ በይፋ ጀምሯል። ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው የውይይት መድረኩን ሲከፍቱ እንዳሉት፤ በመሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች የሀሳብ ልዩነቶች ይታያሉ። ልዩነቶችን መፍታት የሚያስችል የውይይት መድረክ ለማመቻቸት ኮሚሽኑ ሰፊ ጥረት እያደረገ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፤ በእስካሁኑ ሂደት ስኬታማ የሚባሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።   የሀገሪቱን ሠላም ዘላቂ ለማድረግ የሀሳብ ልዩነታችንን ለመፍታት መምከር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ሲሉም ኮሚሽነር ዘገየ ገልጸዋል። የሀሳብ ልዩነት ግለሰቦችን ጫካ የሚያስገባ ሳይሆን የብዝሃነት ጌጥ መሆኑን መረዳት አለብን ያሉት ደግሞ ኮሚሽነር ዶክተር ዮናስ አዳዬ ናቸው።   የአጀንዳ ማሰባሰቡን ሥራ በተሳካ ሁኔታ በማድረግ በመከባበር እና በመደማመጥ ላይ የተመሠረተ ምክክር ማድረግ አለብን ብለዋል። ለአንድ ሳምንት በሚካሄደው በዚሁ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት በክልሉ የሚገኙ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች እየተሳተፉ ነው።
የክልሉን ሕዝብ የጋራ ማንነትና ፍላጎት በማቀናጀት የጋራ ትርክት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሁሉም በትብብር ሊሰራ ይገባል - አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ
Jul 24, 2024 79
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2016(ኢዜአ)፦ የክልሉን ሕዝብ የጋራ ማንነትና ፍላጎት በማቀናጀት አሰባሳቢ የጋራ ትርክት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት በተለይም አስፈፃሚው አካል በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ ገለጹ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን አንደኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል። በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ፤ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ለውጥ ማምጣት የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ ሕዝብ የተሳሰረ ማንነትና የጋራ እሴቶች ያሉት መሆኑን ገልፀው፤ በክልሎ የተቀናጀ ልማትና አደረጃጀትን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል። የክልሉን ሕዝብ የጋራ ማንነት እና ፍላጎት በማቀናጀት የጋራ ትርክት ለመገንባት ሁሉም በኃላፊነት እንዲሰራም አሳስበዋል። ምክር ቤቱ የክልሉን ሕገ መንግስት ጨምሮ በርካታ የሕግ ማዕቀፎችን የማፅደቅ እና ታላላቅ ውሳኔዎችን የማሳለፍ ተግባራት ማከናወኑን አስታውሰዋል።   ምክር ቤቱ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታን ታሳቢ ያደረጉ እስከ ታችኛው እርከን የግምገማ፣ ክትትልና ቁጥጥር ስራዎችን በማካሄድ ውጤታማ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ከተረጅነት የምንወጣበትና ሰፊ የስራ ዕድል የምንፈጥርበት የግብርና ዘርፍ ነው ያሉት አፈ ጉባኤዋ፤ በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል። ከእርዳታ ጠባቂነት ለመውጣት ወጥነት ያለውና አዳዲስ ኢኒሼቲቭ በመተግበር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየደረጃው ያለ አስፈፃሚ አካል በትኩረት ሊሰራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። የክልሉን ሕዝብ የጋራ ማንነትና ፍላጎት በማቀናጀት አሰባሳቢ የጋራ ትርክት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት በተለይም አስፈፃሚው አካል በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎቶ ማስፋት፣ የኑሮ ውድነት ማረጋጋት፣ መልካም አስተዳደር እና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች አሁንም ልዩ ትኩረት ተሰጥቷቸው በቅንጅት መስራት ይገባል ነው ያሉት። የሕግ የበላይነት ማረጋገጥ እና ልማትን ማጠናከር የቀጣይ ትኩረት እንደሚሆን አንስተው፤ በዚህ ረገድ የፍትሕ ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
 የሶማሌ ክልል ምክር ቤት 6ኛ የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባዔ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል
Jul 24, 2024 81
ጅግጅጋ፤ ሐምሌ 17/2016(ኢዜአ)፦ የሶማሌ ክልል ምክር ቤት 6ኛ የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባዔ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። በጉባዔው ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሐመድ የክልሉን የ2016 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። እንዲሁም የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና ዋና ኦዲት ቢሮ ዓመታዊ የስራ እንቅስቃሴ ለጉባዔው ቀርቦ ውይይት ይካሄዳል። ምክር ቤቱ በቆይታው የክልሉ የ2017 በጀት ዓመት የልማትና መልካም አስተዳደር እቅድና የክልሉን በጀት እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል። ለሁለት ቀናት የሚቆየው የምክር ቤቱ ጉባዔ የክልሉ መገናኛ ብዙሃን የስራ አፈፃፀም ሪፖርትና የክልል ምክር ቤቱን ጽህፈት ቤት ሪፖርት ያዳምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅም ከወጣው መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል። በጉባዔው ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሐመድ፣ የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ አያን መሐመድ፣ ምክትል አፈ ጉባዔ ኢብራሂም ሐሰን፣ የምክር ቤት አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ነው።  
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም