ኢዜአ - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትንና ካሳ የሚከፈልበት ረቂቅ አዋጅ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ተመራ
Mar 19, 2024 20
አዲስ አበባ፣መጋቢት 10 / 2016 (ኢዜአ)፡- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትን ካሳ የሚከፈልበትንና ተነሺዎች የሚቋቋሙበትን ረቂቅ አዋጅ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ18ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው እለት አካሂዷል። በመደበኛ ስብሰባውም የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት፣ ካሳ የሚከፈልበትና ተነሺዎች የሚቋቋሙበትን በተመለከተ በወጣው ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ሰፊ ውይይት አድርጓል። የረቂቅ አዋጁን አስፈላጊነት በተመለከተ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ፤ ለምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም አዋጁ ለልማት ተነሺዎች ተገቢ የሆነ የካሳ ክፍያ እንዲከናወን እንዲሁም የልማት መጓተት ችግርን የሚፈታ መሆኑን አስረድተዋል። አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት፣ካሳ የሚከፈልበትንና ተነሺዎች መልስው የሚቋቋሙበትን አሰራር የሚያሳልጥ ስለመሆኑም አብራርተዋል። የመሰረተ ልማት ስራዎች ሲከናወኑ የንብረት መገመት፣ የመክፈልና የማስነሳት ስራ ለክልሎችና ለከተማ አሥተዳደሮች የሚሰጥ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በአሰራር ሂደቱ የባለቤትነት ስሜት ለመፍጠርና ቀልጣፋ የአሰራር ስርአት ለመዘርጋት መሆኑ ተገልጿል። ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላም ለዝርዝር ዕይታ ለከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች እና ለሕግ እና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል።
በዞኑ ሰላምን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Mar 19, 2024 29
ደብረ ብርሃን፣መጋቢት 10 /2016 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሰላምን በዘላቂነት በማረጋገጥ የጽንፈኛውን ቡድን ሴራ ለማምከን እየተከነወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖሰት አስታወቀ። ኮማንድ ፖስቱ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሰረት የተከናወኑ የሰላም ማስፈንና የጸጥታ ተግባራትን በደብረ ብርሃን እየገመገመ ነው። የኮማንዶና አየር ወለድ አዛዥና የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብዴታ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ኮማንድ ፖስቱ የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማረጋገጥ የጽንፈኛውን ቡድን ሴራ ለማምከን በትኩረት እየሰራ ነው። የመከላከያ ሰራዊት ከሌሎች የፌዴራልና የክልል የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመተባበር በተከናወኑ የጸጥታ ማስከበር ተግባራት ሰላምን ማስፈን መቻሉን ተናግረዋል። የዛሬው መድረክ ዓላማም በኮማንድ ፖስት አባላት እስካሁን የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም የተመዘገቡ ተጨባጭ ለውጦችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና ክፍተቶችን በማረም ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅት የተገኘውን ሰላም ወደ ዘላቂ በማሸጋገር አካባቢውን ለልማትና መልካም አስተዳደር የተመቸ የሚያደርጉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን አስረድተዋል። በግምገማው መድረክ በአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ዶክተር አህመዲን መሀመድን ጨምሮ ከደብረ ብርሃን ከተማ እና ከሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
በዞኑ ከ6 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት መልሶ እንዲያገግም የማድረግ ተግባር እየተከናወነ ነው
Mar 19, 2024 28
ሽሬ እንዳስላሴ ፤ መጋቢት 10/2016(ኢዜአ)፦ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች የተመናመኑ ከ6 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት መልሶ እንዲያገግም ለማድረግ እየተከናወነ መሆኑን በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን የተፈጥሮ ሀብት ፅህፈት ቤት አስታወቀ። አስተባባሪው አቶ ሃብተስላሴ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በዞኑ በሚገኙ አራት ወረዳዎች የሚገኝ ከ6 ሺህ ሄክታር በላይ ደን መልሶ እንዲያገግም ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ በመከለል ጥበቃና እንክብካቤ እየተደረገለት ነው። በአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፎ ተከልሎ እንዲጠበቅና እንክብካቤ እየተደረገለት ያለው ደን በአብዛኛው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባለው የእጣን ዛፍ የተሸፈነ እንደሆነ አስተባባሪው ገልፀዋል። ጉዳት የደረሰበት ይኸው የተፈጥሮ ደን መልሶ እንዲያገግም በህዝብ ነፃ ተሳትፎ የተለያዩ ጎርፍ አልባ እርከኖች እየተገነቡለት መሆኑን አስረድተዋል። እንዲሁም ጉዳት የደረሰበትን የደን ክፍል መልሶ ለማልማት የተለያዩ አገር በቀል ችግኞችን ለመትከል የችግኝ ማፍላት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ደኑ ሙሉ በሙሉ ካገገመ በኋላ በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ንብ በማነብና እጣን በማምረት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እድል እንደሚፈጠርላቸውም አስተባባሪው ተናግረዋል። በዞኑ አስገደ ወረዳ ፀሊሞይ በተባለ የገጠር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ገብረመድህን በላይ በሰጡት አሰተያየት በተከለለው ደን ውስጥ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ስራ በማከናወን ደኑ መልሶ እንዲለማና ወደ ቀድሞ ይዞታው እንዲመለስ ጥረት እያደረጉ እንደሆነ ገልፀዋል። ሌላው የዚሁ ገጠር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አስገደ ግርማይ በበኩላቸው ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ ሆኖ እንዲከለል የተደረገው ደን ሙሉ በሙሉ አስኪያገግም ከመጠበቅና ከመንከባከብ ወደ ኋላ እንደማይሉ ቃል ገብተዋል። በዞኑ በደን የተሸፈነው 52 ሺህ ሄክታር መሬት በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች የተጎዳ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በክልሉ በሰፈነው ሰላምም በየዓመቱ ቢያንስ ከአምስት ሺህ በላይ ሄክታር ደን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነጻ በማድረግ መልሶ እንዲያገግም እየተሰራ መሆኑን ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
በከተማ ግብርና ስራ ፈጥረን በመንቀሳቀስ የተሻለ ገቢ ማግኘት ችለናል - ወጣቶች
Mar 19, 2024 33
ሐረር መጋቢት 10/2016 (ኢዜአ)፦በከተማ ግብርና ስራ ፈጥረው በመንቀሳቀስ የተሻለ ገቢ ማግኘት መቻላቸውን በሐረር ከተማ ከስደት ተመላሽና የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተመራቂ ወጣቶች ተናገሩ። የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በክልሉ በመገኘት በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የተከናወኑ ሥራዎችን፣ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን፣ የወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚነትና በተለያዩ ዘርፎች የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ተመልክተዋል። በስራ ሃላፊዎቹ ስራቸው የተጎበኘላቸው ከስደት ተመላሽና የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተመራቂ ወጣቶች እንዳሉት በከተማ ግብርና ስራ ፈጥረው በመንቀሳቀስ የተሻለ ገቢ ማግኘት ችለዋል። ከወጣቶቹ መካከል በዱባይ በርካታ ዓመታትን በስደት ያሳለፈው ወጣት ነስረዲን አህመድ በርካታ አሳዛኝና መጥፎ ህይወትን ማሳለፉን ጠቅሷል። ወደ አገሩ በመመለስ በሱፐርማርኬት ስራ መጀመሩንና ስራውም አዋጭ ባለመሆኑ በልጅነት የሚመኘውን የንብ ማነብ ስራ ላይ ተሰማርቶ እንደሚገኝና ሁለት ሚሊየን ብር ካፒታል ማፍራት መቻሉን ተናግሯል። የክልሉ መንግስትም ተጨማሪ መስሪያ ቦታ እንዳስረከበው የሚጠቅሰው ወጣት ነስረዲን ወጣቶች የስደት ህይወትን በመተው በአገራቸው ሰርተው እንዲለወጡ መልዕክት አስተላልፏል። ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ማኔጅመንት በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀው ወጣት አንዋር ሸምሰዲን በሐረር ከተማ በዶሮ እርባታ ተሰማርቶ እራሱን ከመቻሉ ባለፈ ለሌሎች ሰባት ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። በአሁኑ ወቅትም በቀን የተጣራ 1ሺህ ሁለት መቶ ብር ገቢ እንደሚያገኝና በሚያገኘውም ገቢ እራሱንና ቤተሰቡን እየጠቀመ እንደሚገኝ ተናግሯል። ማንኛውም ስራ መጀመሪያ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ያጋጥሙታል የሚለው ወጣት አንዋር ይህንም እንደ ጸጋ በመውሰድ ለስኬት ለመብቃት መትጋት ያስፈልጋል ሲል ሃሳቡን ገልጿል። የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር በበኩላቸው የክልሉ መንግስት በከተማ ግብርና በማር ምርት፣ በዶሮ እርባታ፣ በወተት ሀብትና በሌሎች ለሚሳተፉ ወጣቶች አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። በተለይም በከተማው በማር ምርት እየተሳተፉ ለሚገኙ ከስደት ተመላሽ ወጣቶች በክላስተር ተደራጅተው ማር እንዲያመርቱ 1 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት መስጠቱን ተናግረዋል። በሌሎች በወተትና እንቁላል ተዋጽኦ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች የሚያጋጥማቸውን የመኖ አቅርቦት ለመፍታትም ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የወጣቶቹን ሥራ የተመለከቱ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል በሰጡት አስተያየት የክልሉ መንግስት ወጣቶችን በከተማ ግብርና ስራ በማሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እያከናወነ ያለው ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል ይገባል። በተለይም በከተማ ግብርና ስራ ፈጥረው የተንቀሳቀሱ ከስደት ተመላሽና የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተመራቂ ወጣቶች የተሻለ ገቢ ማግኘት መቻላቸውን መታዘባቸውን ገልጸዋል። ወጣቶቹ ከራሳቸው አልፈው ቤተሰቦቻቸውንና ሌሎች ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን መመልከት እንደቻሉ ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት ወጣቶችን በከተማ ግብርና ስራ በማሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በመሬት አቅርቦትና በሌሎች የሚያከናወነውን ስራ ማጠናከር ይገባል ሲሉም ሚኒስትሯ ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማን ኢንቨስትመንት ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ናቸው
Mar 19, 2024 34
ጎንደር ፤ መጋቢት 10 /2016 (ኢዜአ)፡-የጎንደር ከተማን ኢንቨስትመንት ለማሳደግና የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ለማሳካት የተከናወነው ተግባር አበረታች ውጤት የታየበት መሆኑ ተገለጸ። በከተማ አስተዳደሩ ባለፉት ስምንት ወራት ከ80 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ከ200 በላይ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የከተማው አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ባዩህ አቡሃይ አስታውቀዋል፡፡ በፍትህ ሚኒስትር ዶክተር ጌዲዮን ጤሞቲዎስ የተመራ የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ቡድን በጎንደር ከተማ የተከናወኑ የኢንቨስመንት፣ የሌማት ትሩፋት፣ የአረንጓዴ አሻራና የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እንቅስቃሴን ተዘዋውሮ ተመልክቷል። በዚህ ወቅት ዶክተር ጌዲዮን ጤሞቲዎስ እንደገለጹት፤ የከተማ አስተዳደሩ ሰላምን ከማስፈን በተጓዳኝ ያከናወናቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት አድናቆት የሚቸራቸው ናቸው፡፡ ባለሃብቱን በመደገፍ የከተማው የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲጨምር ያከናወናቸው ተግባራት አምራች ኢንዲስትሪዎች እንዲስፋፉና የሀገሪቱ የኤክስፖርት ምርት እንዲጠናከር የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በከተማው የተሰማሩ ባለሀብቶች ተግዳሮቶችን ተቋቁመው የዕለት ተዕለት ተግባራቸውን ለማከናወን እያደረጉት ያለው ጥረት የሚያበረታታ እንደሆነም ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል፡፡ በከተማው የወተት ፣የስጋና የእንቁላል ምርት ከፍ እንዲል በማድረግ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተፈጻሚ የተደረጉ ተግባራትም ገበያን በማረጋጋት የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የአካባቢን የልማት ጸጋዎች አሟጦ በመጠቀም ረገድ እንደ ሀገር የተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በሁሉም አካባቢዎች ውጤታማ መሆኑን በመስክ ምልከታችን አረጋግጠናል ብለዋል፡፡ በከተማው ስራ አጥ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ ከማድረግ ሌላ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና ሌሎች የልማት ስራዎች አተገባበር አበረታች ውጤት የታየባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በመስክ ምልከታው ቡድኑ በቀጣይ ከተማ አስተዳደሩ የሚያስፈልገውን ድጋፍና እገዛ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ግብአት ማሰባሰብ እንዳስቻለውም የፍትህ ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡ ባለፉት ስምንት ወራት ብቻ ከ80 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ከ200 በላይ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ያስታወቁት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሃይ ናቸው፡፡ በተጨማሪም በከተማው በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ 56 ኢንተር ፕራይዞች ከ200 ሺህ በላይ የእንቁላል ጣይ ዶሮዎችን በማርባት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመው፤ በስራ እድል ፈጠራና የኑሮ ውድነትነትን በመቀነስ አበረታች ውጤት መመዝገቡን አስታውቀዋል፡፡ የፌደራል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎቹ የከተማው አስተዳደር የአመራር አባላት ባለሀብቱና ህዝቡ በመቀናጀት ያከናወኑዋቸውን ተግባራት ለመገምገምና ለመደገፍ በአካል መገኘታቸው ለቀጣይ ስራ ትልቅ የሞራል ስንቅ የሚሰጥ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በፌደራል በጀት የሚገነቡት የመገጭ የመስኖና የመጠጥ ውሃ ግድብና የአዘዞ የኮንክሪት አስፋልት መንገድ ግንባታ በአጭር ጊዜ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ቡድኑ ድጋፍ እንዲያደርግ አቶ ባዩህ ጠይቀዋል፡፡ የቲኬኬ አምራች ኢንዱስትሪ የጎንደር ቅርንጫፍ ስራ አስኪጅ አቶ አስናቀው ዘውዱ በበኩላቸው፤ በከተማው በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በ1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ወጪ የምግብ ዘይትና የሳሙና ማምረቻ ፋብሪካ በማቋቋም ወደ ስራ መግባቱን አስታውቀዋል፡፡ ፋብሪካው በአሁኑ ወቅት ከ600 በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የስራ እድል መፍጠሩን ጠቁመው የአካባቢውን የግብርና ምርቶች በጥሬ እቃነት በመጠቀም ምርቱን ወደ ውጪ በመላክ የውጪ ምንዛሬ ለማስገኘት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ ቡድኑ የአባይ ጋርመንት የአልባሳት ማምረቻን፣ የቲኬኬን የዘይትና የሳሙና ፋብሪካን፣ የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት የዳቦና ዱቄት ማምረቻና ሌሎች የልማት ስራዎችን እንቅስቃሴ ጎብኝቷል፡፡ በተጨማሪም በከተማው በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እየተከናወኑ የሚገኙ የዶሮ እርባታና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎችን ተዘዋውሮ ምልከታ አካሂዷል፡፡
ፖለቲካ
በአዲስ አበባ በሚገኘው የስዊዘርላንድ ኤምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሕንጻ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ
Mar 19, 2024 73
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2016(ኢዜአ)፦የስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢግናዚዮ ካሲስ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ጋር በመሆን በአዲስ አበባ በሚገኘው የስዊዘርላንድ ኤምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሕንጻ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ። በመርኃ ግብሩ የሁለቱ አገራት የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የሥራ ኃላፊዎች፣ የስዊዘርላንድ ፓርላማ ተወካዮችና ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል። በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ያሉት የስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢግናዚዮ ካሲስ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ጋር በሁለትዮሽ፣ በቀጣናዊና በዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያና ግሪክ ለዘመናት የቆየ ግንኙነታቸውን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርትና ስልጠናም ያጠናክራሉ - አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ
Mar 19, 2024 77
አዲስ አበባ፤መጋቢት 10/2016(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና ግሪክ ለዘመናት የቆየ ግንኙነታቸውን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርትና ስልጠና ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ ገለጹ። ተቀማጭነታቸው በሮም ሆኖ በግሪክ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ ከግሪክ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር አምባሳደር አሌክሳንደራ ፓፓዶፖሉ ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸውም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ እና የባለ ብዙ ወገን ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። ሁለቱ ሀገሮች ያላቸውን ታሪካዊ ግንኙነት ያወሱት አምባሳደሯ ፣ በሀገራቱ መካከል ያለውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርትና ስልጠና ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል። ምክትል ሚኒስትሯ በበኩላቸው ግሪክ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ታሪካዊ ግንኙነት ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። አክለውም ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እንዲሁም በትምህርት ዘርፍ ያላትን ትብብር እንደምታሳድግ መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በመዲናዋ በሲቪል ሰርቪስ ተቋማት ላይ ለሚካሄደው የሪፎርም ትግበራ ውጤታማነት አመራሩ በትጋት መስራት ይጠበቅበታል
Mar 18, 2024 275
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2016(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ በ16 የሲቪል ሰርቪስ ተቋማት ላይ ለሚካሄደው ሪፎርም ትግበራ ውጤታማነት አመራሩ በትጋት መስራት እንዳለበት የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ገለጸ። ቢሮው በ16 ተቋማት ላይ የሪፎርም ስራ የዝግጅት ምዕራፍን በማጠናቀቅ ወደ ትግበራ መሸጋገሩን አስታውቋል፡፡ የቢሮው ኃላፊ ጣሰው ገብሬ(ዶ/ር ) ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት በተቋማት የአሰራር ስርዓት ለውጥ በማስፈለጉና ብቃት ያለው የሰው ኃይል አደረጃጀትና ተጠያቂነትን ለማስፈን በ2016 በጀት ዓመት በ16 ተቋማት ላይ የሪፎርም ስራ ሲሰራ ቆይቷል። ሪፎርሙን ተከትሎ የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ የማድረግና በሶስተኛ ወገን የሚሰሩ አገልግሎቶችንና ተቋማትን የመለየት ስራ ተከናውኗል ብለዋል። በቴክኖሎጂ የሚደገፉ አገልግሎቶች መለየታቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት መገንባት የሚያስችሉ 42 ፕሮጀክቶች እንደሚተገበሩ አብራርተዋል። የሰራተኛ ብቃት ምዘና በገለልተኛ ተቋማት መሰጠቱንም በመግለጫቸው አንስተዋል። የብቃት ምዘናው ከ19ሺህ በላይ የሆኑ ሰራተኞች መውሰዳቸውን ጠቅሰው ከተፈታኞቹ መካከል 33 ነጥብ 3 በመቶ አመራሮች እንዲሁም 50 ነጥብ 6 በመቶ ሠራተኞች ማለፋቸውን ተናግረዋል። ምዘናውን ካለፉት መካከል 99 በመቶ የሚሆኑ ኃላፊዎች፣ 88 በመቶ የቡድን መሪና ሰራተኞች መመደባቸውን ጠቁመው ፈተናውን ያላለፉትም በድልድል ደንቡ መሰረት ሁለት ደረጃ ዝቅ ብለው መመደባቸውን ገልጸዋል። ምዘናውን ተከትሎ ከ17 ሺህ በላይ ሰራተኞች በሁለት ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና መውሰዳቸውን ተናግረዋል። የሪፎርሙ የዝግጅት ምዕራፍ ተጠናቆ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ትግበራ መግባቱን ገልፀው እንደዝግጅት ምዕራፉ ሁሉ ለትግበራ ምዕራፉ ውጤታማነት በተለይ የተቋማት አመራሮች በትጋት መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
ኢትዮጵያና ስዊዘርላንድ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በተለያዩ የትብብር መስኮች ለማጠናከር ይሰራሉ
Mar 18, 2024 310
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2016(ኢዜአ)፦ለበርካታ ዓመታት የቆየውን ኢትዮጵያንና የስዊዘርላንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በተለያዩ የትብብር መስኮች ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰሩ የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ካሉት ከስዊዘርላንድ አቻቸው ኢግናዚዮ ካሲስ ጋር በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት እንዲሁም በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ተወያይተዋል። የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ከውይይቱ በኋላ በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያና ስዊዘርላንድ ግንኙነታቸውን በተለያዩ የትብብር መስኮች ለማጠናከር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ሁለቱ ሀገራት ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው ብለዋል። በርካታ የስዊዘርላንድ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ በኢንቨስትመንት መሰማራታቸውን ጠቁመው ይህንን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል ከዚህ ቀደም የተደረሱ የትብብር ሥምምነቶች ተግባራዊ ለማድረግም እንዲሁ። በሌላ በኩል በፕሪቶሪያው የሠላም ሥምምነት፣ በሽግግር ፍትህና ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአፈፃጸም ሂደት ላይ አጽንኦት ሰጥተው መምከራቸውንም አንስተዋል። የስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢግናዚዮ ካሲስ በበኩላቸው፤ የሀገራቱን የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ተስማምተናል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ልማት፣ ሰላምና ደኅንነት ወሳኝ ሚና የምትጫወት ሀገር መሆኗን ገልጸዋል። ስዊዘርላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በፍልሰት ጉዳዮች ላይ በትብብር እየሰራች መሆኑን ተናግረዋል። የሥራ ጉብኝታቸውም የስዊዘርላንድና ኢትዮጵያን የቆየ ታሪካዊ ወዳጅነት አጠናክሮ ለማስቀጠል ዓላማ ያደረገ መሆኑንም አንስተዋል።
በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ግዳጃቸውን በአኩሪ ገድል በመፈፀም ረገድ የሴቶች ሠራዊት አባላት ሚና እየጨመረ ነው
Mar 18, 2024 214
ድሬዳዋ ፤ መጋቢት 9/2016(ኢዜአ)፦ በተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ግዳጃቸውን በአኩሪ ገድል በመፈፀም ረገድ የሴቶች ሠራዊት አባላት ሚና እየጨመረ መሆኑን ብርጋዴር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ተናገሩ። ብርጋዴር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ይህን የተናገሩት ሁርሶ ኮንቲንጀንት ትምህርት ቤት ለሰላም ማስከበር ተግባር የሰለጠኑ የሠራዊት አባላት ባስመረቀበት ስነስርዓት ላይ ነው። በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት ብርጋዴር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ በዘመቻው ለሚሳተፉት ተመራቂ ሴት የሠራዊቱ አባላት ተሞክሯቸውን በማካፈል የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አበረታትተዋል። ብርጋዴር ጄኔራል ሁሉአገርሽ በዚሁ ወቅት ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ሴቶች የአገር መከላከያ ሠራዊትን ተቀላቅለው የአገራችንን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት በማስከበር ረገድ እያደረጉት የሚገኘው ተሳትፎና ውጤታማነት እየጨመረ ይገኛል። ከዚህ ጎን ለጎን በተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ አገራችን ያላትን ከፍታና ተመራጭነት በማሳደግ ረገድም አበርክቷቸው እየጎለበተ መምጣቱን በመግለፅ። ወደ ደቡብ ሱዳን ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ የተዘጋጁት ሴት የሠራዊት አባላትና አመራሮች ቁጥር ከምንጊዜውም በላይ ከፍ ማለቱን ለአብነት አንስተዋል። ይህም ሴቶች በአፍሪካ በተለይም በምስራቅ አፍሪካ አገሮችና ህዝቦች መካከል ትስስር በመፍጠርና አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ እንዲሰፍን እየፈፀሙ የሚገኙት ጀብድና ተቀባይነት እያደገ መምጣቱን ያመላክታል ብለዋል። በቀጣይም አገርን በአምባሳደርነት ወክለው ለሰላም ማስከበር በሚጓዙበት አካባቢዎች ህዝባዊ ባህሪያትን በመላበስ አገራዊና ተቋማዊ ግዳጆችን በብቃት በመወጣት የኢትዮጵያን ገፅታ ያሳድጋሉ ብለዋል። ለሰላም ማስከበር ዘመቻ ዝግጁ ከሆኑት የመከላከያ ሠራዊት መካከል ፍሬህይወት ግርማ በሰጠችው አስተያየት እናቶችና አያቶቼ ሴትነታቸው ሳይበግራቸው ለአገር ሉዓላዊነትና ነፃነት የከፈሉትን ዋጋ ተገንዝቤ እኔም ለአገሬ ክብርና ታላቅነት ሠራዊቱን ተቀላቅያለሁ" ብላለች። ይህን የአገር ክብርና ታላቅነት በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ በመድገም የሠራዊቱን ህዝባዊነትና ሙያዊ ትህትና ለማረጋገጥ መዘጋጀቷንም ገልጻለች። አገርንና ታላቁን የኢትዮጵያ ሠራዊት በመወከል ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ መታጨት በራሱ ሴቶች ያለንን ተሳትፎና ተቀባይነት እያደገ መምጣቱን ያመለክታል ያሉት ደግሞ ሌላዋ የሰላም አስከባሪ መቶ አለቃ ደጅጥኑ አያሌው ናቸው። በምንሰማራበት የሰላም ማስከበር ዘመቻ አኩሪ ገድል በመፈፀም ሠራዊቱ ያለውን ተቀባይነት ይበልጥ እንዲጨምር እተጋለሁ ብለዋል። በተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ለማሳካት ወደ ደቡብ ሱዳን ለመጓዝ ከሰለጠኑት መካከል 17 በመቶዎቹ ሴቶች መሆናቸውም በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል።
በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሩሲያውያን በአዲስ አበባ የሩሲያ ኤምባሲ በተዘጋጀ ድምጽ መስጫ ተገኝተው ድምጽ ሰጡ
Mar 17, 2024 301
የሩሲያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ስነ ስርዓት ከባለፈው አርብ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ቀጥሎ እየተካሄደ እንደሚገኝ ዘገባዎች ያመለክታሉ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8/2016 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሩሲያውያን በአዲስ አበባ የሩሲያ ኤምባሲ በተዘጋጀ ድምጽ መስጫ ተገኝተው በሀገራቸው እየተካሄደ ላለው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ድምጽ ሰጥተዋል። የሩሲያ ማእከላዊ የምርጫ ኮሚሽን በ2024 የሩሲያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር የሚፎካከሩ ሶስት እጩዎች መመዝገቡን አስታውቋል። በኢትየጵያ የሩሲያ አምባሳደርን ጨምሮ ሌሎች ሩሲያዊያን በኤምባሲው በተዘጋጀው የድምጽ መስጫ በምርጫው መሳተፋቸውን የኤምባሲው መረጃ ያሳያል፡፡ የሩሲያ ምርጫ ባለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ዛሬ ማምሻውን የሚጠናቀቅ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰላም ለማፅናት ለፀጥታ መዋቅር ሪፎርምና አቅም ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል- አቶ ኡሞድ ኡጁሉ
Mar 17, 2024 265
ጋምቤላ ፤ መጋቢት 8 /2016(ኢዜአ)፡-በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰላም ለማፅናት ለፀጥታ መዋቅሩ ሪፎርምና አቅም ግንባታ ትኩረት ተሰጥቶ ወደ ተግባር መገባቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ገለጹ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በቦንጋ የፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም ያሰለጠናቸውን መደበኛ የፖሊስ አባላት ዛሬ አስመርቋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ለክልሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መቃናት ሰላም ወሳኝነት አለው፤ ለሰላም መከበር ደግሞ የፖሊስ አባላት የላቀ ቁርጠኝነት ይጠበቅባቸዋል። አገራዊ ለውጡን ተከትሎ ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች መካከል የፀጥታ መዋቅር ሪፎርም አንዱ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህንኑ መሠረት በማድረግ የክልሉን የፖሊስ አባላት አቅም የመገንባት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በዕለቱ የአቅም ግንባታ ስልጠና ወስደው ያጠናቀቁ የፖሊስ አባላት በቀጣይ የክልሉን ህዝብ ሰላምና ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ኃላፊነታቸውን በቁርጠኝነት ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቾል ኩን በበኩላቸው ፤ ክልሉ ሰፊ የድንበር ወሰን የሚጋራ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ ድንበር ዘለል ወንጀሎችን በመከላከሉ ረገድ ከዕለቱ ሰልጣኝ የፖሊስ አባላት ከፍተኛ ኃላፊነት ይጠበቃል ብለዋል። በተለይም ህገ ወጥ የጦር መሳሪያና ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እንዲሁም የቀንድ ከብት ዝርፊያ ወንጀሎችን ለመከላከል ለፖሊሶቹ የተሰጠው ስልጠና ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ተመራቂ የፖሊስ አባላት በክልሉ አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ የፀጥታ ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል አቅም የገነቡ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ኡሞድ ኡሞድ ናቸው። በተለይም በከተማ ውስጥ የሚከሰቱ የስርቆትና ሌላው የወንጀል ድርጊት በመከላከል ረገድ የዛሬው ተመራቂ የፖሊስ አባላት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በአማራና ትግራይ ክልሎች መካከል የሚገኙና የወሰን ይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸውን አካባቢዎች በህገ መንግስቱ እና በህገ መንግስታዊ ስርዓቱ መሰረት በዘላቂነት እልባት ለመስጠት በብሔራዊ ደረጃ የተቋቋመው ኮሚቴ አፈጻጸም ተገመገመ
Mar 16, 2024 577
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2016(ኢዜአ)፦ በአማራና ትግራይ ክልሎች መካከል የሚገኙና የወሰን ይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸውን አካባቢዎች በህገ መንግስቱ እና በህገ መንግስታዊ ስርዓቱ መሰረት በዘላቂነት እልባት ለመስጠት በብሔራዊ ደረጃ የተቋቋመው ኮሚቴ አፈጻጸም ተገምግሟል። በአማራና ትግራይ ክልሎች መካከል የሚገኙና የወሰን ይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸውን አካባቢዎች በህገ መንግስቱ እና በህገ መንግስታዊ ስርዓቱ መሰረት በዘላቂነት እልባት ለመስጠት በብሔራዊ ደረጃ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሲሠራ ቆይቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የሁለቱ ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ተሳታፊዎች በተገኙበት የብሔራዊ ኮሚቴው አፈፃፀም ተገምግሟል። የተፈፀሙና ሊፈፀሙ ሲገባቸው የዘገዩ ጉዳዮች ተነስተው ግምገማ ተደርጎባቸዋል። በግምገማው መሰረት በአፈፃፀም ሂደቱ የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች የተለዩ ሲሆን የማንነትና የይገባኛል ጥያቄ ያለባቸውን አካባቢዎች ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በአፋጣኝና በዘላቂነት ሊፈታ እንደሚገባም ስምምነት ላይ ተደርሷል። ከዚህ አኳያ ተፈናቃዮችን በአጭር ጊዜ ወደቀያቸው የመመለስ ጉዳይ ቅድሚያ ተሰጥቶት በሚፈፀምበት አግባብ ላይ መተማመን ላይ መደረሱም ተጠቁሟል። በተጨማሪም በብሔራዊ ደረጃ ይህን እንዲያስፈፅም የተቋቋመው ኮሚቴ በቋሚ የጊዜ ሰሌዳ እየተገናኘ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለጉዳዩ እልባት እንዲሰጥ በዛሬው ዕለት በተደረገው ስብሰባ መወሰኑን ከብሔራዊ ኮሚቴው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ፖለቲካ
በአዲስ አበባ በሚገኘው የስዊዘርላንድ ኤምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሕንጻ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ
Mar 19, 2024 73
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2016(ኢዜአ)፦የስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢግናዚዮ ካሲስ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ጋር በመሆን በአዲስ አበባ በሚገኘው የስዊዘርላንድ ኤምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሕንጻ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ። በመርኃ ግብሩ የሁለቱ አገራት የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የሥራ ኃላፊዎች፣ የስዊዘርላንድ ፓርላማ ተወካዮችና ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል። በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ያሉት የስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢግናዚዮ ካሲስ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ጋር በሁለትዮሽ፣ በቀጣናዊና በዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያና ግሪክ ለዘመናት የቆየ ግንኙነታቸውን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርትና ስልጠናም ያጠናክራሉ - አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ
Mar 19, 2024 77
አዲስ አበባ፤መጋቢት 10/2016(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና ግሪክ ለዘመናት የቆየ ግንኙነታቸውን በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርትና ስልጠና ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ ገለጹ። ተቀማጭነታቸው በሮም ሆኖ በግሪክ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ ከግሪክ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር አምባሳደር አሌክሳንደራ ፓፓዶፖሉ ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸውም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ እና የባለ ብዙ ወገን ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። ሁለቱ ሀገሮች ያላቸውን ታሪካዊ ግንኙነት ያወሱት አምባሳደሯ ፣ በሀገራቱ መካከል ያለውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርትና ስልጠና ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል። ምክትል ሚኒስትሯ በበኩላቸው ግሪክ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ታሪካዊ ግንኙነት ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። አክለውም ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እንዲሁም በትምህርት ዘርፍ ያላትን ትብብር እንደምታሳድግ መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በመዲናዋ በሲቪል ሰርቪስ ተቋማት ላይ ለሚካሄደው የሪፎርም ትግበራ ውጤታማነት አመራሩ በትጋት መስራት ይጠበቅበታል
Mar 18, 2024 275
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2016(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ በ16 የሲቪል ሰርቪስ ተቋማት ላይ ለሚካሄደው ሪፎርም ትግበራ ውጤታማነት አመራሩ በትጋት መስራት እንዳለበት የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ገለጸ። ቢሮው በ16 ተቋማት ላይ የሪፎርም ስራ የዝግጅት ምዕራፍን በማጠናቀቅ ወደ ትግበራ መሸጋገሩን አስታውቋል፡፡ የቢሮው ኃላፊ ጣሰው ገብሬ(ዶ/ር ) ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት በተቋማት የአሰራር ስርዓት ለውጥ በማስፈለጉና ብቃት ያለው የሰው ኃይል አደረጃጀትና ተጠያቂነትን ለማስፈን በ2016 በጀት ዓመት በ16 ተቋማት ላይ የሪፎርም ስራ ሲሰራ ቆይቷል። ሪፎርሙን ተከትሎ የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ የማድረግና በሶስተኛ ወገን የሚሰሩ አገልግሎቶችንና ተቋማትን የመለየት ስራ ተከናውኗል ብለዋል። በቴክኖሎጂ የሚደገፉ አገልግሎቶች መለየታቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት መገንባት የሚያስችሉ 42 ፕሮጀክቶች እንደሚተገበሩ አብራርተዋል። የሰራተኛ ብቃት ምዘና በገለልተኛ ተቋማት መሰጠቱንም በመግለጫቸው አንስተዋል። የብቃት ምዘናው ከ19ሺህ በላይ የሆኑ ሰራተኞች መውሰዳቸውን ጠቅሰው ከተፈታኞቹ መካከል 33 ነጥብ 3 በመቶ አመራሮች እንዲሁም 50 ነጥብ 6 በመቶ ሠራተኞች ማለፋቸውን ተናግረዋል። ምዘናውን ካለፉት መካከል 99 በመቶ የሚሆኑ ኃላፊዎች፣ 88 በመቶ የቡድን መሪና ሰራተኞች መመደባቸውን ጠቁመው ፈተናውን ያላለፉትም በድልድል ደንቡ መሰረት ሁለት ደረጃ ዝቅ ብለው መመደባቸውን ገልጸዋል። ምዘናውን ተከትሎ ከ17 ሺህ በላይ ሰራተኞች በሁለት ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና መውሰዳቸውን ተናግረዋል። የሪፎርሙ የዝግጅት ምዕራፍ ተጠናቆ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ትግበራ መግባቱን ገልፀው እንደዝግጅት ምዕራፉ ሁሉ ለትግበራ ምዕራፉ ውጤታማነት በተለይ የተቋማት አመራሮች በትጋት መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
ኢትዮጵያና ስዊዘርላንድ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በተለያዩ የትብብር መስኮች ለማጠናከር ይሰራሉ
Mar 18, 2024 310
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2016(ኢዜአ)፦ለበርካታ ዓመታት የቆየውን ኢትዮጵያንና የስዊዘርላንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በተለያዩ የትብብር መስኮች ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰሩ የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ገለጹ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ካሉት ከስዊዘርላንድ አቻቸው ኢግናዚዮ ካሲስ ጋር በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት እንዲሁም በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ተወያይተዋል። የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ከውይይቱ በኋላ በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያና ስዊዘርላንድ ግንኙነታቸውን በተለያዩ የትብብር መስኮች ለማጠናከር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ሁለቱ ሀገራት ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው ብለዋል። በርካታ የስዊዘርላንድ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ በኢንቨስትመንት መሰማራታቸውን ጠቁመው ይህንን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል ከዚህ ቀደም የተደረሱ የትብብር ሥምምነቶች ተግባራዊ ለማድረግም እንዲሁ። በሌላ በኩል በፕሪቶሪያው የሠላም ሥምምነት፣ በሽግግር ፍትህና ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአፈፃጸም ሂደት ላይ አጽንኦት ሰጥተው መምከራቸውንም አንስተዋል። የስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢግናዚዮ ካሲስ በበኩላቸው፤ የሀገራቱን የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ተስማምተናል ነው ያሉት። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ልማት፣ ሰላምና ደኅንነት ወሳኝ ሚና የምትጫወት ሀገር መሆኗን ገልጸዋል። ስዊዘርላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በፍልሰት ጉዳዮች ላይ በትብብር እየሰራች መሆኑን ተናግረዋል። የሥራ ጉብኝታቸውም የስዊዘርላንድና ኢትዮጵያን የቆየ ታሪካዊ ወዳጅነት አጠናክሮ ለማስቀጠል ዓላማ ያደረገ መሆኑንም አንስተዋል።
በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ግዳጃቸውን በአኩሪ ገድል በመፈፀም ረገድ የሴቶች ሠራዊት አባላት ሚና እየጨመረ ነው
Mar 18, 2024 214
ድሬዳዋ ፤ መጋቢት 9/2016(ኢዜአ)፦ በተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ግዳጃቸውን በአኩሪ ገድል በመፈፀም ረገድ የሴቶች ሠራዊት አባላት ሚና እየጨመረ መሆኑን ብርጋዴር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ተናገሩ። ብርጋዴር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ይህን የተናገሩት ሁርሶ ኮንቲንጀንት ትምህርት ቤት ለሰላም ማስከበር ተግባር የሰለጠኑ የሠራዊት አባላት ባስመረቀበት ስነስርዓት ላይ ነው። በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት ብርጋዴር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ በዘመቻው ለሚሳተፉት ተመራቂ ሴት የሠራዊቱ አባላት ተሞክሯቸውን በማካፈል የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አበረታትተዋል። ብርጋዴር ጄኔራል ሁሉአገርሽ በዚሁ ወቅት ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ሴቶች የአገር መከላከያ ሠራዊትን ተቀላቅለው የአገራችንን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት በማስከበር ረገድ እያደረጉት የሚገኘው ተሳትፎና ውጤታማነት እየጨመረ ይገኛል። ከዚህ ጎን ለጎን በተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ አገራችን ያላትን ከፍታና ተመራጭነት በማሳደግ ረገድም አበርክቷቸው እየጎለበተ መምጣቱን በመግለፅ። ወደ ደቡብ ሱዳን ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ የተዘጋጁት ሴት የሠራዊት አባላትና አመራሮች ቁጥር ከምንጊዜውም በላይ ከፍ ማለቱን ለአብነት አንስተዋል። ይህም ሴቶች በአፍሪካ በተለይም በምስራቅ አፍሪካ አገሮችና ህዝቦች መካከል ትስስር በመፍጠርና አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ እንዲሰፍን እየፈፀሙ የሚገኙት ጀብድና ተቀባይነት እያደገ መምጣቱን ያመላክታል ብለዋል። በቀጣይም አገርን በአምባሳደርነት ወክለው ለሰላም ማስከበር በሚጓዙበት አካባቢዎች ህዝባዊ ባህሪያትን በመላበስ አገራዊና ተቋማዊ ግዳጆችን በብቃት በመወጣት የኢትዮጵያን ገፅታ ያሳድጋሉ ብለዋል። ለሰላም ማስከበር ዘመቻ ዝግጁ ከሆኑት የመከላከያ ሠራዊት መካከል ፍሬህይወት ግርማ በሰጠችው አስተያየት እናቶችና አያቶቼ ሴትነታቸው ሳይበግራቸው ለአገር ሉዓላዊነትና ነፃነት የከፈሉትን ዋጋ ተገንዝቤ እኔም ለአገሬ ክብርና ታላቅነት ሠራዊቱን ተቀላቅያለሁ" ብላለች። ይህን የአገር ክብርና ታላቅነት በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ በመድገም የሠራዊቱን ህዝባዊነትና ሙያዊ ትህትና ለማረጋገጥ መዘጋጀቷንም ገልጻለች። አገርንና ታላቁን የኢትዮጵያ ሠራዊት በመወከል ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ መታጨት በራሱ ሴቶች ያለንን ተሳትፎና ተቀባይነት እያደገ መምጣቱን ያመለክታል ያሉት ደግሞ ሌላዋ የሰላም አስከባሪ መቶ አለቃ ደጅጥኑ አያሌው ናቸው። በምንሰማራበት የሰላም ማስከበር ዘመቻ አኩሪ ገድል በመፈፀም ሠራዊቱ ያለውን ተቀባይነት ይበልጥ እንዲጨምር እተጋለሁ ብለዋል። በተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ለማሳካት ወደ ደቡብ ሱዳን ለመጓዝ ከሰለጠኑት መካከል 17 በመቶዎቹ ሴቶች መሆናቸውም በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል።
በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሩሲያውያን በአዲስ አበባ የሩሲያ ኤምባሲ በተዘጋጀ ድምጽ መስጫ ተገኝተው ድምጽ ሰጡ
Mar 17, 2024 301
የሩሲያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ስነ ስርዓት ከባለፈው አርብ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ቀጥሎ እየተካሄደ እንደሚገኝ ዘገባዎች ያመለክታሉ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8/2016 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሩሲያውያን በአዲስ አበባ የሩሲያ ኤምባሲ በተዘጋጀ ድምጽ መስጫ ተገኝተው በሀገራቸው እየተካሄደ ላለው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ድምጽ ሰጥተዋል። የሩሲያ ማእከላዊ የምርጫ ኮሚሽን በ2024 የሩሲያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር የሚፎካከሩ ሶስት እጩዎች መመዝገቡን አስታውቋል። በኢትየጵያ የሩሲያ አምባሳደርን ጨምሮ ሌሎች ሩሲያዊያን በኤምባሲው በተዘጋጀው የድምጽ መስጫ በምርጫው መሳተፋቸውን የኤምባሲው መረጃ ያሳያል፡፡ የሩሲያ ምርጫ ባለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ዛሬ ማምሻውን የሚጠናቀቅ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰላም ለማፅናት ለፀጥታ መዋቅር ሪፎርምና አቅም ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል- አቶ ኡሞድ ኡጁሉ
Mar 17, 2024 265
ጋምቤላ ፤ መጋቢት 8 /2016(ኢዜአ)፡-በጋምቤላ ክልል ያለውን ሰላም ለማፅናት ለፀጥታ መዋቅሩ ሪፎርምና አቅም ግንባታ ትኩረት ተሰጥቶ ወደ ተግባር መገባቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ገለጹ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በቦንጋ የፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም ያሰለጠናቸውን መደበኛ የፖሊስ አባላት ዛሬ አስመርቋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ለክልሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መቃናት ሰላም ወሳኝነት አለው፤ ለሰላም መከበር ደግሞ የፖሊስ አባላት የላቀ ቁርጠኝነት ይጠበቅባቸዋል። አገራዊ ለውጡን ተከትሎ ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች መካከል የፀጥታ መዋቅር ሪፎርም አንዱ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህንኑ መሠረት በማድረግ የክልሉን የፖሊስ አባላት አቅም የመገንባት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በዕለቱ የአቅም ግንባታ ስልጠና ወስደው ያጠናቀቁ የፖሊስ አባላት በቀጣይ የክልሉን ህዝብ ሰላምና ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ኃላፊነታቸውን በቁርጠኝነት ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቾል ኩን በበኩላቸው ፤ ክልሉ ሰፊ የድንበር ወሰን የሚጋራ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ ድንበር ዘለል ወንጀሎችን በመከላከሉ ረገድ ከዕለቱ ሰልጣኝ የፖሊስ አባላት ከፍተኛ ኃላፊነት ይጠበቃል ብለዋል። በተለይም ህገ ወጥ የጦር መሳሪያና ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እንዲሁም የቀንድ ከብት ዝርፊያ ወንጀሎችን ለመከላከል ለፖሊሶቹ የተሰጠው ስልጠና ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ተመራቂ የፖሊስ አባላት በክልሉ አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ የፀጥታ ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል አቅም የገነቡ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ኡሞድ ኡሞድ ናቸው። በተለይም በከተማ ውስጥ የሚከሰቱ የስርቆትና ሌላው የወንጀል ድርጊት በመከላከል ረገድ የዛሬው ተመራቂ የፖሊስ አባላት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በአማራና ትግራይ ክልሎች መካከል የሚገኙና የወሰን ይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸውን አካባቢዎች በህገ መንግስቱ እና በህገ መንግስታዊ ስርዓቱ መሰረት በዘላቂነት እልባት ለመስጠት በብሔራዊ ደረጃ የተቋቋመው ኮሚቴ አፈጻጸም ተገመገመ
Mar 16, 2024 577
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2016(ኢዜአ)፦ በአማራና ትግራይ ክልሎች መካከል የሚገኙና የወሰን ይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸውን አካባቢዎች በህገ መንግስቱ እና በህገ መንግስታዊ ስርዓቱ መሰረት በዘላቂነት እልባት ለመስጠት በብሔራዊ ደረጃ የተቋቋመው ኮሚቴ አፈጻጸም ተገምግሟል። በአማራና ትግራይ ክልሎች መካከል የሚገኙና የወሰን ይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸውን አካባቢዎች በህገ መንግስቱ እና በህገ መንግስታዊ ስርዓቱ መሰረት በዘላቂነት እልባት ለመስጠት በብሔራዊ ደረጃ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሲሠራ ቆይቷል። ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የሁለቱ ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ተሳታፊዎች በተገኙበት የብሔራዊ ኮሚቴው አፈፃፀም ተገምግሟል። የተፈፀሙና ሊፈፀሙ ሲገባቸው የዘገዩ ጉዳዮች ተነስተው ግምገማ ተደርጎባቸዋል። በግምገማው መሰረት በአፈፃፀም ሂደቱ የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች የተለዩ ሲሆን የማንነትና የይገባኛል ጥያቄ ያለባቸውን አካባቢዎች ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በአፋጣኝና በዘላቂነት ሊፈታ እንደሚገባም ስምምነት ላይ ተደርሷል። ከዚህ አኳያ ተፈናቃዮችን በአጭር ጊዜ ወደቀያቸው የመመለስ ጉዳይ ቅድሚያ ተሰጥቶት በሚፈፀምበት አግባብ ላይ መተማመን ላይ መደረሱም ተጠቁሟል። በተጨማሪም በብሔራዊ ደረጃ ይህን እንዲያስፈፅም የተቋቋመው ኮሚቴ በቋሚ የጊዜ ሰሌዳ እየተገናኘ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለጉዳዩ እልባት እንዲሰጥ በዛሬው ዕለት በተደረገው ስብሰባ መወሰኑን ከብሔራዊ ኮሚቴው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ማህበራዊ
በዞኑ ሰላምን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Mar 19, 2024 29
ደብረ ብርሃን፣መጋቢት 10 /2016 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሰላምን በዘላቂነት በማረጋገጥ የጽንፈኛውን ቡድን ሴራ ለማምከን እየተከነወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖሰት አስታወቀ። ኮማንድ ፖስቱ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሰረት የተከናወኑ የሰላም ማስፈንና የጸጥታ ተግባራትን በደብረ ብርሃን እየገመገመ ነው። የኮማንዶና አየር ወለድ አዛዥና የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብዴታ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ኮማንድ ፖስቱ የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት ለማረጋገጥ የጽንፈኛውን ቡድን ሴራ ለማምከን በትኩረት እየሰራ ነው። የመከላከያ ሰራዊት ከሌሎች የፌዴራልና የክልል የጸጥታ ሃይሎች ጋር በመተባበር በተከናወኑ የጸጥታ ማስከበር ተግባራት ሰላምን ማስፈን መቻሉን ተናግረዋል። የዛሬው መድረክ ዓላማም በኮማንድ ፖስት አባላት እስካሁን የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም የተመዘገቡ ተጨባጭ ለውጦችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና ክፍተቶችን በማረም ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅት የተገኘውን ሰላም ወደ ዘላቂ በማሸጋገር አካባቢውን ለልማትና መልካም አስተዳደር የተመቸ የሚያደርጉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን አስረድተዋል። በግምገማው መድረክ በአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ዶክተር አህመዲን መሀመድን ጨምሮ ከደብረ ብርሃን ከተማ እና ከሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት ስብራትን ለመፍታት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው --- ቢሮው
Mar 19, 2024 53
አርባ ምንጭ ፤ መጋቢት 10/2016(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በትምህርት ዘርፍ የገጠመውን ስብራት ፈትቶ ለውጥ ለማምጣት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። በክልሉ በትምህርት ተሃድሶ መርሃ-ግብር በተካሄደ የማህበረሰብ ንቅናቄ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ከ420 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡ ተመላክቷል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊና ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ዶክተር አበባየሁ ታደሰ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በክልሉ በትምህርት ዘርፍ የታየውን ስብራት ፈትቶ ለውጥ ለማምጣት እየተሰራ ነው። በክልሉ የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ጥራት ያለው ፈተና በመስጠት ተማሪዎች በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ሲሉም ገልጸዋል። አዲሱ ሥርአተ ትምህርት በሁሉም የትምህርት እርከኖች ተግባራዊ መደረጉን ጠቁመው፣ ከመዋዕለ ህፃናት ጀምሮ የትምህርት ግብአትን በማሟላት የትምህርት ጥራትና አግባብነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የትምህርት ባለድርሻዎችንና ህዝብን በማሳተፍ በትምህርት ቤቶች ግንባታ፣ በማስፋፊያና በእድሳት ሥራዎች እንዲሁም በቁሳቁስ ማሟላት ጠንካራ ተግባራት መከናወናቸውንም ዶክተር አበባየሁ ተናግረዋል። በክልሉ በትምህርት ተሃድሶ መርሃ-ግብር በተካሄደ የማህበረሰብ ንቅናቄ በግማሽ ዓመቱ ከ420 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡንም አስረድተዋል። የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማትና ግብአት በማሟላት የትምህርት ስብራትን በዘላቂነት ለመፍታት ባለድርሻ አካላትና ህዝቡ የጀመሩትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል። በክልሉ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ፍሬው ፍሻለው በበኩላቸው እንዳሉት፣ በዞኑ በትምህርት ዘርፍ ችግሮችን ፈትቶ ለውጥ ለማምጣት ማህበረሰቡን ያሳተፈ ሥራ እየተሰራ ነው። በዚህም የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻልና ትምህርት ቤቶችን ለተማሪዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ ለመምህራን አቅም ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን ነው የገለጹት። የትምህርት ጥራት በመንግስት ጥረት ብቻ እንደማይረጋገጥ የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው፣ "ባለድርሻ አካላትም የበኩላቸውን እንዲወጡ የሚያስችል አደረጃጀት ተፈጥሮ በቅንጅት እየተሠራ ነው" ብለዋል። ሁለንተናዊ ብልጽግና እንዲረጋገጥ በትምህርት ዘርፍ ለውጥ ለማምጣት የተጀመረው ሥራ መጠናከር እንዳለበት የገለጹት ደግሞ የክልሉ ምክር ቤት አባል ወይዘሮ ምስጋና ዋቀዮ ናቸው። በትምህርት ዘርፍ የሚሰራው ሥራ ለነገ መሰረት በመሆኑ የክልሉ ምክር ቤት አባላት በቁርጠኝነት የመደገፍና የመከታተል ሃላፊነታቸውን በመወጣት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። የመጻህፍት አቅርቦት፣ የመምህራን አቅም ግንባታ፣ የተማሪ መጻህፍና ክፍል ጥምርታ ማሻሻልን ጨምሮ ለትምህርት ዘርፍ ማነቆ የሆኑ ጉዳዮች እንዲፈቱ ከትምህርት ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራን ነው ብለዋል። የክልሉ ምክር ቤት በአርባ ምንጭ ከተማ ሰሞኑን ባካሄደው 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ አስፈጻሚ አካላትና የምክር ቤት አባላት ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ማስገንዘቡ የሚታወስ ነው።
ከፍተኛ የጸኃይ ጨረር በሰው ጤና ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል በሚል በማኅበራዊ ሚዲያው የሚሰራጨው መረጃ ኃሰተኛ ነው
Mar 18, 2024 218
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2016(ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ ከፍተኛ የጸኃይ ጨረር በሰው ጤና ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል በሚል ማኅበራዊ ሚዲያው የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ገለጸ። ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር ገፆች በአዲስ አበባ በጤና ላይ ጉዳት ሊያደርስ የሚችል ከፍተኛ የፀኃይ ጨረር እንደሚኖር ተደጋጋሚ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ። ይህን ተከትሎም አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ጉዳት ያደርስባቸዋል በሚል ከመማሪያ ክፍላቸው እንዳይወጡ ክልከላ ማድረጋቸውን ኢዜአ ከተለያዩ ምንጮች ማረጋገጥ ችሏል። አንዳንድ ወላጆችና የከተማዋ ነዋሪዎችም በዚሁ መረጃ ምክንያት መደናገር እንደተፈጠረባቸውም እንዲሁ። ጉዳዩን አስመልክቶ ኢዜአ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የስፔስና ፕላኔተሪ ሳይንስ ሥራ ክፍል መሪና ተመራማሪ ንጉሴ መዝገበ (ዶ/ር)ን አነጋግሯል። ባለሙያው፤ ከፍተኛ የጸኃይ ጨረር በሰው ጤና ላይ የከፋ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል በሚል በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው መረጃ ኃሰተኛና ከሳይንሱ ውጪ ነው ብለዋል። የጸኃይ ጨረር በሰዎች ጤና ላይ ሊያስከትል የሚችለው የጤና ጉዳት አለመኖሩንም አረጋግጠዋል። ያም ብቻ ሳይሆን ከጸኃይ የሚነሱ ሞገዶች ወይም ቅንጣቶች ወደ መሬት ወርደው ሰዎች ላይ ጉዳት የማድረስ አቅም የላቸውም ነው ያሉት። ይልቁንም ከጸኃይ የሚነሱ ጨረሮች በብዛት የሚያጠቁት ስፔስ ላይ ያሉ ሳተላይቶችን የመገናኛና የኮሙኑኬሽን መሣሪያዎችን መሆኑንም አብራርተዋል። አለም ዓቀፍ የስፔስ ትንበያዎች እንዲህ አይነት ጉዳት ሊያደርስ የሚችል ምንም አይነት ፍንጭ አለመስጠታቸውንና የተናፈሰው ሐሰተኛ መረጃ ምንጩ የማይታወቅ ነው ሲሉም ተናግረዋል። ኅብረተሰቡ የሚሰራጩ መረጃዎችን ትክክለኛነት ከሚመለከታቸው አካላት ማጣራት እንዳለበት ገልጸው፣ የእለት ተእለት እንቅስቃሴውን ያለምንም ሥጋት ሊቀጥል ይገባልም ብለዋል።
በኦሮሚያ ክልል የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተሰሩ ስራዎች ውጤት አስገኝተዋል - የክልሉ ጤና ቢሮ
Mar 18, 2024 97
ጅማ፤ መጋቢት 9/2016(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተሰሩ ስራዎች ውጤት ማስገኘታቸውን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያው አጋማሽ የወባና የቲቢ በሽታን ጨምሮ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከልና ቁጥጥር ስራዎች አፈጻጸም ግምገማ ዛሬ በጅማ ማካሄድ ጀምሯል። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ደረጀ አብደና በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ቢሮው በተለያዩ ምክንያቶች የጨመረውን የወባ በሽታ ለመከላከል ሕዝብን ያሳተፈ ተግባራትን አከናውኗል። በዚህም ከሰባት ሚሊዮን በላይ የአልጋ አጎበር ስርጭትና የኬሚካል ርጭት የተካሄደ ሰሆን፣ ኅብረተሰቡም በየአካባቢው ለወባ መራቢያ የሆኑ ቦታዎችን አጽድቷል ብለዋል። በክልሉ በሚገኙ የጤና ተቋማት ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ምርመራ ካካሄዱ 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን የሚሆኑት በወባ መያዛቸውን ገልጸዋል። በክልሉ ባለፉት ሶስት ዓመታት ይከሰት የነበረው የወባ በሽታ መጠን በዓመት ከ200 ሺህ የማይበልጥ እንደነበር ጠቁመዋል። የወባ በሽታን ለመከላከል የአካባቢን ጽዳት መጠበቅ፣ያቆረ ውሃን ማስወገድና አጎበርን በአግባቡ መጠቀም እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። ኅብረተሰቡ የበሽታው ምልክቶች ሲታይበት ፈጥኖ ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ሕክምናውን እንዲከታተልም ምክትል ቢሮ ኃላፊው አሳስበዋል። በአጠቃላይ ባለፉት ስድስት ወራት የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተሰሩ ስራዎች ውጤት ማስገኘታቸውን አስረድተዋል። የጅማ ዞን ጤና ጽህፈት ኃላፊ አቶ ፉአድ ሳሲት፣ በዞኑ በስምንት ወረዳዎች በበሽታው የተያዙ ከ26ሺህ በላይ ሰዎች ህክምና እንደተደረገላቸው ገልጸዋል። በኦሮሚያ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን ጤና ጽህፈት ቤት የወባ መከላከል ኦፊሰር ሲስተር ምስራቅ ዘነበ፣ በበኩላቸው በዞኑ የወባ በሽታ ለመከላከል እየተሰራ ቢሆንም፤ የመድኃኒትና የህክምና መሳሪያዎች እጥረት እንደገጠማቸው ተናግረዋል። ኅብረተሰቡ ራሱን ከወባ በሽታ መከላከል እንዲችል የግንዛቤ ማስረጽ ሥራ በስፋት መካሄዱን አስታውቀዋል። የበሽታው ምልክት የታየባቸው ሰዎች በፍጥነት ህክምና እንዲያገኙ መደረጉን ሲስተር ምስራቅ ገልጸዋል።
ኢኮኖሚ
የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትንና ካሳ የሚከፈልበት ረቂቅ አዋጅ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ተመራ
Mar 19, 2024 20
አዲስ አበባ፣መጋቢት 10 / 2016 (ኢዜአ)፡- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትን ካሳ የሚከፈልበትንና ተነሺዎች የሚቋቋሙበትን ረቂቅ አዋጅ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ18ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው እለት አካሂዷል። በመደበኛ ስብሰባውም የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት፣ ካሳ የሚከፈልበትና ተነሺዎች የሚቋቋሙበትን በተመለከተ በወጣው ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ሰፊ ውይይት አድርጓል። የረቂቅ አዋጁን አስፈላጊነት በተመለከተ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ፤ ለምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም አዋጁ ለልማት ተነሺዎች ተገቢ የሆነ የካሳ ክፍያ እንዲከናወን እንዲሁም የልማት መጓተት ችግርን የሚፈታ መሆኑን አስረድተዋል። አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት፣ካሳ የሚከፈልበትንና ተነሺዎች መልስው የሚቋቋሙበትን አሰራር የሚያሳልጥ ስለመሆኑም አብራርተዋል። የመሰረተ ልማት ስራዎች ሲከናወኑ የንብረት መገመት፣ የመክፈልና የማስነሳት ስራ ለክልሎችና ለከተማ አሥተዳደሮች የሚሰጥ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በአሰራር ሂደቱ የባለቤትነት ስሜት ለመፍጠርና ቀልጣፋ የአሰራር ስርአት ለመዘርጋት መሆኑ ተገልጿል። ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላም ለዝርዝር ዕይታ ለከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች እና ለሕግ እና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል።
በከተማ ግብርና ስራ ፈጥረን በመንቀሳቀስ የተሻለ ገቢ ማግኘት ችለናል - ወጣቶች
Mar 19, 2024 33
ሐረር መጋቢት 10/2016 (ኢዜአ)፦በከተማ ግብርና ስራ ፈጥረው በመንቀሳቀስ የተሻለ ገቢ ማግኘት መቻላቸውን በሐረር ከተማ ከስደት ተመላሽና የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተመራቂ ወጣቶች ተናገሩ። የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በክልሉ በመገኘት በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የተከናወኑ ሥራዎችን፣ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን፣ የወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚነትና በተለያዩ ዘርፎች የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ተመልክተዋል። በስራ ሃላፊዎቹ ስራቸው የተጎበኘላቸው ከስደት ተመላሽና የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተመራቂ ወጣቶች እንዳሉት በከተማ ግብርና ስራ ፈጥረው በመንቀሳቀስ የተሻለ ገቢ ማግኘት ችለዋል። ከወጣቶቹ መካከል በዱባይ በርካታ ዓመታትን በስደት ያሳለፈው ወጣት ነስረዲን አህመድ በርካታ አሳዛኝና መጥፎ ህይወትን ማሳለፉን ጠቅሷል። ወደ አገሩ በመመለስ በሱፐርማርኬት ስራ መጀመሩንና ስራውም አዋጭ ባለመሆኑ በልጅነት የሚመኘውን የንብ ማነብ ስራ ላይ ተሰማርቶ እንደሚገኝና ሁለት ሚሊየን ብር ካፒታል ማፍራት መቻሉን ተናግሯል። የክልሉ መንግስትም ተጨማሪ መስሪያ ቦታ እንዳስረከበው የሚጠቅሰው ወጣት ነስረዲን ወጣቶች የስደት ህይወትን በመተው በአገራቸው ሰርተው እንዲለወጡ መልዕክት አስተላልፏል። ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ማኔጅመንት በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀው ወጣት አንዋር ሸምሰዲን በሐረር ከተማ በዶሮ እርባታ ተሰማርቶ እራሱን ከመቻሉ ባለፈ ለሌሎች ሰባት ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። በአሁኑ ወቅትም በቀን የተጣራ 1ሺህ ሁለት መቶ ብር ገቢ እንደሚያገኝና በሚያገኘውም ገቢ እራሱንና ቤተሰቡን እየጠቀመ እንደሚገኝ ተናግሯል። ማንኛውም ስራ መጀመሪያ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ያጋጥሙታል የሚለው ወጣት አንዋር ይህንም እንደ ጸጋ በመውሰድ ለስኬት ለመብቃት መትጋት ያስፈልጋል ሲል ሃሳቡን ገልጿል። የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር በበኩላቸው የክልሉ መንግስት በከተማ ግብርና በማር ምርት፣ በዶሮ እርባታ፣ በወተት ሀብትና በሌሎች ለሚሳተፉ ወጣቶች አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። በተለይም በከተማው በማር ምርት እየተሳተፉ ለሚገኙ ከስደት ተመላሽ ወጣቶች በክላስተር ተደራጅተው ማር እንዲያመርቱ 1 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት መስጠቱን ተናግረዋል። በሌሎች በወተትና እንቁላል ተዋጽኦ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች የሚያጋጥማቸውን የመኖ አቅርቦት ለመፍታትም ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የወጣቶቹን ሥራ የተመለከቱ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል በሰጡት አስተያየት የክልሉ መንግስት ወጣቶችን በከተማ ግብርና ስራ በማሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እያከናወነ ያለው ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል ይገባል። በተለይም በከተማ ግብርና ስራ ፈጥረው የተንቀሳቀሱ ከስደት ተመላሽና የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተመራቂ ወጣቶች የተሻለ ገቢ ማግኘት መቻላቸውን መታዘባቸውን ገልጸዋል። ወጣቶቹ ከራሳቸው አልፈው ቤተሰቦቻቸውንና ሌሎች ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን መመልከት እንደቻሉ ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት ወጣቶችን በከተማ ግብርና ስራ በማሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በመሬት አቅርቦትና በሌሎች የሚያከናወነውን ስራ ማጠናከር ይገባል ሲሉም ሚኒስትሯ ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማን ኢንቨስትመንት ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ናቸው
Mar 19, 2024 34
ጎንደር ፤ መጋቢት 10 /2016 (ኢዜአ)፡-የጎንደር ከተማን ኢንቨስትመንት ለማሳደግና የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ለማሳካት የተከናወነው ተግባር አበረታች ውጤት የታየበት መሆኑ ተገለጸ። በከተማ አስተዳደሩ ባለፉት ስምንት ወራት ከ80 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ከ200 በላይ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የከተማው አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ባዩህ አቡሃይ አስታውቀዋል፡፡ በፍትህ ሚኒስትር ዶክተር ጌዲዮን ጤሞቲዎስ የተመራ የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ቡድን በጎንደር ከተማ የተከናወኑ የኢንቨስመንት፣ የሌማት ትሩፋት፣ የአረንጓዴ አሻራና የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እንቅስቃሴን ተዘዋውሮ ተመልክቷል። በዚህ ወቅት ዶክተር ጌዲዮን ጤሞቲዎስ እንደገለጹት፤ የከተማ አስተዳደሩ ሰላምን ከማስፈን በተጓዳኝ ያከናወናቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት አድናቆት የሚቸራቸው ናቸው፡፡ ባለሃብቱን በመደገፍ የከተማው የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲጨምር ያከናወናቸው ተግባራት አምራች ኢንዲስትሪዎች እንዲስፋፉና የሀገሪቱ የኤክስፖርት ምርት እንዲጠናከር የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በከተማው የተሰማሩ ባለሀብቶች ተግዳሮቶችን ተቋቁመው የዕለት ተዕለት ተግባራቸውን ለማከናወን እያደረጉት ያለው ጥረት የሚያበረታታ እንደሆነም ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል፡፡ በከተማው የወተት ፣የስጋና የእንቁላል ምርት ከፍ እንዲል በማድረግ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተፈጻሚ የተደረጉ ተግባራትም ገበያን በማረጋጋት የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የአካባቢን የልማት ጸጋዎች አሟጦ በመጠቀም ረገድ እንደ ሀገር የተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በሁሉም አካባቢዎች ውጤታማ መሆኑን በመስክ ምልከታችን አረጋግጠናል ብለዋል፡፡ በከተማው ስራ አጥ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ ከማድረግ ሌላ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርና ሌሎች የልማት ስራዎች አተገባበር አበረታች ውጤት የታየባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በመስክ ምልከታው ቡድኑ በቀጣይ ከተማ አስተዳደሩ የሚያስፈልገውን ድጋፍና እገዛ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ግብአት ማሰባሰብ እንዳስቻለውም የፍትህ ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡ ባለፉት ስምንት ወራት ብቻ ከ80 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ከ200 በላይ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ያስታወቁት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሃይ ናቸው፡፡ በተጨማሪም በከተማው በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ 56 ኢንተር ፕራይዞች ከ200 ሺህ በላይ የእንቁላል ጣይ ዶሮዎችን በማርባት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመው፤ በስራ እድል ፈጠራና የኑሮ ውድነትነትን በመቀነስ አበረታች ውጤት መመዝገቡን አስታውቀዋል፡፡ የፌደራል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎቹ የከተማው አስተዳደር የአመራር አባላት ባለሀብቱና ህዝቡ በመቀናጀት ያከናወኑዋቸውን ተግባራት ለመገምገምና ለመደገፍ በአካል መገኘታቸው ለቀጣይ ስራ ትልቅ የሞራል ስንቅ የሚሰጥ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በፌደራል በጀት የሚገነቡት የመገጭ የመስኖና የመጠጥ ውሃ ግድብና የአዘዞ የኮንክሪት አስፋልት መንገድ ግንባታ በአጭር ጊዜ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ቡድኑ ድጋፍ እንዲያደርግ አቶ ባዩህ ጠይቀዋል፡፡ የቲኬኬ አምራች ኢንዱስትሪ የጎንደር ቅርንጫፍ ስራ አስኪጅ አቶ አስናቀው ዘውዱ በበኩላቸው፤ በከተማው በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በ1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ወጪ የምግብ ዘይትና የሳሙና ማምረቻ ፋብሪካ በማቋቋም ወደ ስራ መግባቱን አስታውቀዋል፡፡ ፋብሪካው በአሁኑ ወቅት ከ600 በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የስራ እድል መፍጠሩን ጠቁመው የአካባቢውን የግብርና ምርቶች በጥሬ እቃነት በመጠቀም ምርቱን ወደ ውጪ በመላክ የውጪ ምንዛሬ ለማስገኘት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ ቡድኑ የአባይ ጋርመንት የአልባሳት ማምረቻን፣ የቲኬኬን የዘይትና የሳሙና ፋብሪካን፣ የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት የዳቦና ዱቄት ማምረቻና ሌሎች የልማት ስራዎችን እንቅስቃሴ ጎብኝቷል፡፡ በተጨማሪም በከተማው በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እየተከናወኑ የሚገኙ የዶሮ እርባታና የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎችን ተዘዋውሮ ምልከታ አካሂዷል፡፡
የደብረ ብርሃን ከተማ የመሬት አስተዳደር የካዳስተር ምዝገባ ስራው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እያስገኘ ነው - ነዋሪዎች
Mar 19, 2024 34
ደብረብርሃን፣መጋቢት 10/ 2016 (ኢዜአ)፡-በደብረ ብርሃን የከተማ መሬት አያያዝ ሥርዓትን በካዳስተር ቴክኖሎጂ በማዘመን የሚነሱ የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመፍታት የተሰራው ስራ አበረታች መሆኑን የከተማው ነዋሪዎች ገለፁ፡፡ እድሜ ጠገብ የሆነችው ደብረ ብርሃን የኢንዱስትሪና ኢንቨትስመንት ማዕከል የመሆኗን ያህል በዘመናዊ የመሬት አስተዳደር ረገድ በርካታ ሊከናወኑ የሚገቧቸው ተግባራት አሏት። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የከተማ አስተዳደሩ የመሬት አስተዳደርን ለማዘመን የሚረዱ የካዳስተር ምዝገባ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ነው። በዚህ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳሉት የካዳስተር ምዝገባ ስራው መሠራቱ የከተማዋን የመሬት ሀብት በአግባቡ ለአገልግሎት ለማዋል የጎላ ድርሻ አለው። ከከተማው ነዋሪዎች መካከል መምህር መርሻ ስማቸው እንደገለጹት ቀደም ሲል የነበረው የከተማው የመሬት አስተዳደር ስርዓት ባረጀው የወረቀት አያያዝ መሆኑ ለአጭበርባሪዎችና ለብልሹ አሰራር የተጋለጠ አድርጎት ቆይቷል፡፡ በዚህም በሐሰተኛ ማስረጃ ካርታ ማሰራት፣ የመንግስት መሬትን በህገ ወጥ መውረር፣ ከይዞታ ውጪ የሆኑ ቦታዎችን አካቶ መያዝና ሌሎች ችግሮች ይስተዋሉ እንደነበር በማሳያነት አንስተዋል፡፡ አሁን የከተማ አስተዳደሩ ካዳስተርን በመተግበር በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ የከተማ ቦታን መመዝገብና መረጃውን መያዝ መጀመሩ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን እየፈታ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ ዓለማየሁ ጨርቆስ በበኩላቸው አዲሱ የይዞታ ማረጋገጫ ምዝገባ በቴክኖሎጂ ታግዞ መካሄዱ ነዋሪዎች ሀብታቸውን በአግባቡ ለመጠቀምና ለማስተዳደር የሚያስችል ነው ብለዋል። ከዚህ በፊት ማዘጋጃ ቤት በመሄድ ዜጎች አገልግሎት ሲፈልጉ "ፋይል ጠፋ፣ ተበላሸ" በማለት ጉዳዩ በከንቲባ ኮሚቴ ተይቶ እስኪወሰን ከሁለት እስከ ሰባት ዓመት ይጓተት እንደነበር ጠቁመው፤ አዲሱ አሰራር ይሄን ችግር የሚፈታ ነው ብለዋል፡፡ የካዳስተር አሰራር መጀመሩ ያለ አግባብ የተያዙ የመንግስት መሬቶችን ለህዝባዊ ልማት እና ጥቅም ለማዋል የሚያስችል ነው" ያሉት ደግሞ ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ብርቱካን ገደቡ ናቸው። የከተማ አስተዳደሩ መሬት መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ እታለማሁ ይምታቱ እንደገለጹት የካዳስተር ምዝገባው አሠራር ዜጎች በህግ አግባብ ያፈሩትን ሀብት በነፃነት ለመጠቀም የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን በተሰራው የከተማው የካዳስተር ምዝገባ ስራ በሶሰት ክፍለ ከተሞች በ56 ሰፈሮች የሚገኙ ይዞታዎችን በካዳሳተር ስርዓት መረጃቸው እንዲያዝ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ የደብረ ብርሃን ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮሰትሬ በበኩላቸው የካዳስተርና የዲጅታላይዜሽን ስራው መካሄዱ ከተማዋን ለኢንቨስትመንት፣ ለኑሮና ቱሪዝም ልማት ተመራጭ እንድትሆን ያደርጋል ብለዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ በያዝነው ዓመት ከ39ሺህ 500 በላይ ባለ ይዞታዎችንና የመንግስት ቦታዎችን ወደ ዲጅታላይዜሽን ሲስተም የማስገባት ስራ መሰራቱን አስረድተዋል፡፡ ይህም ያለአግባብ የተያዙ የመንግስትና የህዝብ ሀብቶችን በመለየት የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን ግልጽነት ተጠያቂነትና ውጤታማነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና ፋሪስ ቴክኖሎጂ ግሩፕ በጋራ ለመስራት ተስማሙ
Mar 19, 2024 60
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2016(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና ፋሪስ ቴክኖሎጂ ግሩፕ በምርምርና በፈጠራ ስራ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል ። ስምምነቱን የዩኒቨርስቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) የፋሪስ ቴክኖሎጂ ግሩፕ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ ኤልያስ ይርዳው ተፈራርመዋል። ዶክተር ሳሙኤል በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ዩኒቨርስቲው የአምስት ዓመቱን ስትራቴጂ ለማሳካት ከተያዙ ግቦች መካከል አገራዊ ፋይዳ ካላቸው የግል ዘርፎች ጋር በትብብር መስራት አንዱ ነው ብለዋል። ከፋሪስ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ጋር የተደረገው ስምምነት የስትራቴጂው አካል መሆኑን ጠቅሰው፤ በጥናትና ምርምር እንዲሁም ፈጠራ ላይ በትብብር ይሰራል ብለዋል። ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ እንዳሉት የተማሪዎች የፈጠራ ሀሳብ ወደ ሀብት ለመለወጥ በሚደረገው ጥራት ስምምነቱ ፋይዳው የጎላ መሆኑን አብራርተዋል ። የፋሪስ ቴክኖሎጂ ግሩፕ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ ኤሊያስ ይርዳው በበኩላቸው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያለውን አምቅ አቅም ለመጠቀም ስምምነቱ መልካም አጋጣሚ መሆኑን ተናግረዋል። ግሩፑ ቴክኖሎጂ ነክ የሆኑ በርካታ ፕሮጀክቶች ቀርጾ እየሰራ መሆኑ ገልጸው፤ ስምምነቱ የፕሮጀክቶችን ውጤታማነት ይበልጥ ያሳድገዋል ብለዋል።
ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ተግባር ተኮር የስልጠናና የምርምር ስራዎችን በማከናወን ላይ ነው
Mar 18, 2024 111
ጋምቤላ መጋቢት 9/2016(ኢዜአ) ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ተግባር ተኮር የስልጠናና የምርምር ስራዎችን በማጠናከር ጥራቱን የጠበቀ የሰው ኃይልና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማፍለቅ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክትር ፓል ቦት ለኢዜአ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትና የምርምር ሪፎርም ስራዎችን በማጠናከር ብቃት ያለው የሰው ኃይልና ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን ለማፍለቅ እየሰራ ነው። ዩኒቨርሲቲው የሰው ሀብት ልማት፣ የምርምርና የማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ተልዕኮውን ለመወጣት ሰፊ የሪፎርም ስራዎችን እያካሄደ እንደሚገኝ በማከል። በተለይም ዩኒቨርሲቲው ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን በማጠናከር ተማሪዎችን ለመውጫ ፈተናው የማብቃት ስራዎችን ትኩረት ሰጥቶ እየተገበረ ነው ብለዋል። ከአሁን በፊት ሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብ ላይ ብቻ ተወስነው ሲፈተኑ የነበሩባቸውን የምርምር ስራዎች ተግባር ተኮር በማድረግ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎች ለማፍለቅም እየሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል። በተለይም የማህበረሰቡንና የመንግስትን የልማት ፖሊሲ ፍላጎትና አቅጫዎች ያገናዘቡ የግብርና፣ የማዕድን፣ የቱሪዝም፣ የሰላምና የጸጥታ የምርምር ዘርፎችን በመለየት ወደ ስራ መግባቱን ጠቁመዋል። ዩኒቨርሲቲው በዘንድሮው ዓመት ለግብርና ተማሪዎች ተግባር ተኮር ሰርቶ ማሳያና ለምርምር የሚውል ሰፊ የእርሻ መሬት ወስዶ ወደ ስራ መግባቱንም ዶክተር ፓል ጨምረው ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው የግብርና ትምህርት ክፍል መምህርና የእርሻ ስራ ተጠሪ መምህር ተሾመ ሞላ በበኩላቸው ከአሁን በፊት በግብርና ዘርፍ ተምረው ሲመረቁ የነበሩ ተማሪዎች የንድፈ ሃሰብ ስልጠና ብቻ ሲወስዱ እንደቆዩ ተናግረዋል፡፡ አሁን ላይ ግን ለሰልጣኞች በተግባርና በንድፈ ሃሳብ የተደገፈ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅት መደረጉን ጠቁመው፤ እየታረሰ ያለው መሬትም ከሰርቶ ማሳያነት ባለፉ ለምርምርና ለገቢ ማስገኛነት ጭምር እንደሚያግዝ ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የጀመረው የግብርና ልማት ስራ በዝናብና በመስኖ የውሃ አማራጮች በመታገዝ እንደሆነም ገልጸዋል።
በመዲናዋ ዘመናዊ ቦዲ ካሜራዎች ተግባራዊ መደረጉ የትራፊክ እንቅስቃሴ ቁጥጥር ግልፀኝነት የተሞላበት የማድረግ ሥራን እያገዘ ነው
Mar 16, 2024 211
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2016(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ዘመናዊ ቦዲ ካሜራዎች ተግባራዊ መደረጉ የትራፊክ እንቅስቃሴ ቁጥጥርን ተጠያቂነትና ፍትሃዊነትን የማስፈን ሥራን እያገዘ ነው ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። ከ400 በላይ ዘመናዊ ቦዲ ካሜራዎች ለትራፊክ ፖሊሶች ተከፋፍለው ሥራ ላይ ውለዋል። በትራፊክ እንቅስቃሴው ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በቴክኖሎጂ በተደገፈ አሠራር ለመፍታት የቦዲ ካሜራዎችን ቁጥር ለመጨመር እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል። ቦዲ ካሜራ ''በሕግ አስከባሪ አካላት ደንብ ልብሶችና በሌሎችም መሳሪያዎች ላይ የሚገጠም የካሜራ ቴክኖሎጂ'' በተለይ የሕግ ማስከበር ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ ይረዳል። ካሜራው ሕግ አስከባሪ አካላት በሥራ ላይ ባሉባቸው አካባቢዎች ያሉ እንቅስቃሴዎችን በመቅረጽ ከሕዝብ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በሚገባ ለመቃኘት ያገለግላል። በአዲስ አበባ ፖሊስ የትራፊክ ቁጥጥር መምሪያ ምክትል ዳይሬክተር ኮማንደር ፈቃዱ ወንድምገዙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ቦዲ ካሜራዎች ግልፀኝነት የተሞላበት አሠራር ለመፍጠር አጋዥ ናቸው። የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሬዲዮ ጋር የተገናኙ ከ400 በላይ ዘመናዊ ቦዲ ካሜራዎችን ለትራፊክ ፖሊሶች በማከፋፈል የትራፊክ እንቅስቃሴውን እየተከታተለ መሆኑን ተናግረዋል። የቦዲ ካሜራዎቹ ትራፊክ ፖሊሱ ባለበት አካባቢ ያለውን አጠቃላይ ሁኔታ የሚቀርጹና የተለያዩ መረጃዎችንም መዝግበው የሚያስቀምጡ መሆኑን ገልፀዋል። በዚህም ከትራፊክ እንቅስቃሴ ጋር የተያያዙ ሥራዎች ተጠያቂነትና ፍትሃዊነትን ባረጋገጠ አግባብ እንዲከናወኑ ምቹ መደላድል መፈጠሩን ገልፀዋል። ከዚህ ቀደም ለትራፊክ መጨናነቅና ተያያዥ ችግሮች መፍትሔ የሚሰጠው በሬዲዮ በሚደረግ ግንኙነት እንደነበር አስታውሰው፤ አዳዲሶቹ ቦዲ ካሜራዎች የተሽከርካሪ ሁኔታዎችን ጨምሮ ሌሎች ወንጀሎችንም ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል። ካሜራዎቹ በቀጥታ በማዕከል የሚመሩና ቁጥጥር የሚደረግባቸው ሲሆን፤ የትራፊክ ፍሰቱን ለማስተካከልና ለትራፊክ መጨናነቅም አፋጣኝ መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውን አንስተዋል። ቴክኖሎጂው በአሽከርካሪዎችና በትራፊክ ፖሊስ መካከል ለሚፈጠሩ አለመግባባቶች በተጨባጭ ማስረጃ የተደገፈ መፍትሔ በመስጠት ችግሮችን ለመፍታት ማስቻሉንም ነው የገለጹት። ካሜራዎቹ ውጤታማ ሥራ እየተሰራባቸው ነው ያሉት ኮማንደር ፈቃዱ፤ የካሜራዎቹን ብዛት ካሉት የትራፊክ ፖሊሶች ቁጥር ጋር ለማጣጣም የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የትራፊክ ዲቪዥን ኃላፊ ኢንስፔክተር ያደሳ ሚደቅሳ፤ ቴክኖሎጂው በተለይ ለትራፊክ መጨናነቅ መፍትሔ ለመስጠት ሰፊ እገዛ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ካሜራዎቹ እያንዳንዱን ክስተት የተመለከተ ማስረጃ ስለሚያቀርቡ ማኅበረሰቡ እንግልት እንዳይደርስበት የሕግ አስከባሪ አካላትም ለተለያዩ ጫናዎች እንዳይዳረጉ ይረዳል ብለዋል። በአዲስ አበባ ፖሊስ የትራፊክ ቁጥጥር መምሪያ የሞተር እጀባና ቁጥጥር አባል ምክትል ኢንስፔክተር ኃይለማርያም ዘሪሁን በበኩላቸው፤ ቴክኖሎጂው መጀመሩ ዘርፉን አስተማማኝ ለማድረግ የሚረዳ መሆኑን ገልፀዋል። ችግሮችን ለመለየትና ለማስተካከል ምቹ መደላድል የሚፈጥር በመሆኑ የሕግ አስከባሪ አካላትን አፈጻጸም ለማሻሻል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ 4 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል - ብሔራዊ የመታወቂያ ፕሮግራም
Mar 15, 2024 275
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 6/2016(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ 4 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆናቸውን ብሔራዊ የመታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በተለያዩ መስሪያ ቤቶች በፕሮጀክት ደረጃ ሲተገበር ቆይቷል። የፕሮግራሙን ተቋማዊ አሰራርና ውጤታማነት ለማሳደግ የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ 1284/2015 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አቤነዘር ፈለቀ በፕሮግራሙ አማካኝነት 4 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ማግኘታቸውን ለኢዜአ ገልጸዋል። በፕሮግራሙ የተቀመጠውን ቅድመ ሁኔታ ለሚያሟሉ ነዋሪዎች ባለ 12 አሃዝ ልዩ የፋይዳ መለያ ቁጥር እንደሚሰጥና ይህ መለያ ቁጥር ያላቸው ሰዎች የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ተደርገው እንደሚቆጠሩ አመልክተዋል። በ2016 በጀት ዓመት መጨረሻ የዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ ዜጎችን ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን ለማድረስ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ዜጎች መታወቂያውን እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገር አገልግሎቱን ከተለያዩ ተቋማት ጋር የማስተሳሰር ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ነው ዳይሬክተሩ የገለጹት። የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት እንዲሁም የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ከዲጂታል መታወቂያ ጋር የተገናኘ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቅርቡም ኢትዮጵያ ለስደተኞች የዲጂታል መታወቂያ መስጠት መጀመሯን አስታውሰው በባንኮች የፋይናንስ ግብይትና መሰል አገልግሎቶችን በመታወቂያው የመስጠት ስራ ለማስፋት ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል። ትምህርት፣ ጤናና ማህበራዊ ዋስትና በቀጣይ አገልግሎቱ የሚተገበርባቸው መስኮች መሆናቸውንም ነው የጠቆሙት። የዲጂታል መታወቂያ ከተቋማት ጋር መተሳሰሩ የአገልግሎቱን ተጠቃሚ ቁጥር ለማሳደግ ፋይዳ እንዳለው አመልክተዋል። አቶ አቤነዘር ከዲጂታል መታወቂያ ጋር በተያያዘ በአንዳንዶች ዘንድ ብዥታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው የዲጂታል መታወቂያው የተዘጋጀው የቀበሌ መታወቂያን ለመተካት አለመሆኑን ገልጸዋል። መታወቂያው የሚሰጠው አገልግሎት የቀበሌ መታወቂያን የሚመግብ እንጂ የሚተካ አይደለም ብለዋል። የዲጂታል መታወቂያ በኢትዮጵያ የሚኖር ማንኛውም ዜጋ የራሱን ማንነት የሚገልጽበት መለያ መሆኑን ተናግረዋል። የዲጂታል መታወቂያ ማውጣት አስገዳጅ ሊደረግ ነው የሚለው መረጃ ትክክል እንዳልሆነም ነው አቶ አቤነዘር የገለጹት። የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ ላይ ዜጎች መታወቂያውን የሚያወጡት በፈቃደኝነት ላይ ተመስረተው እንደሆነ በግልጽ እንደሚያስቀምጥ ጠቅሰው ተቋሙ ዜጎች መታወቂያውን በአስገዳጅነት እንዲያወጡ ማድረግ እንደማይችል ተናግረዋል። ይሁንና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለደንበኞቻቸው ለሚሰጡት አገልግሎት ዲጂታል መታወቂያን መጠቀምን እንደ ግዴታ ማስቀመጥ ይችላሉ ብለዋል። በዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ወቅት ከዜጎች የሚወሰዱ መረጃዎች ለሶስተኛ ወገን ተላልፈው እንደማይሰጡና ለዚህም የግል መረጃን መጠበቅ የሚያስችል የአሰራር ማዕቀፍ እንዳለ አንስተዋል። የዲጂታል መታወቂያ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል አካታች በማድረግ ማንነታቸውን የሚገልጽ ማስረጃ እንዲይዙ ማድረግ የሚያስችል አማራጭ መሆኑን ዳይሬክተሩ አክለዋል። በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት 90 ሚሊዮን ዜጎችን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ መታቃዱም ተገልጿል።
ስፖርት
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የታዳጊ ህጻናት የእግር ኳስ ፕሮጀክት ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት በማለም ስልጠና እየሰጠ ነው
Mar 18, 2024 472
ሀዋሳ ፤ መጋቢት 9/2016(ኢዜአ)፦ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የታዳጊ ህጻናት የእግር ኳስ ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ብሎም ክልሉን የሚተኩ ስፖርተኞችን ለማፍራት አልሞ በእግር ኳሱ ዘርፍ የሚጠበቅበትን ሀገራዊ ድርሻ ለመወጣት እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው የስልጠና ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት ዕድሜያቸው ከ13ና ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ከ60 በላይ ታዳጊ ህጻናትን በመቀበል በእግር ኳስ ስፖርት እያሰለጠነ ይገኛል። አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ረዳት ኃላፊ ፕሮፌሰር አንዷለም ገብረስላሴ እንዳሉት፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው ባሻገር በማህበረሰብ አገልግሎት በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ነው። ከዚህ ውስጥ አንዱ የስፖርቱ ዘርፍ ሲሆን ተተኪና ተወዳዳሪ ስፖርተኞችን በማፍራት የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ለማበርከት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። በተለይም በእግር ኳስ እንደ ሀገር የሚጠበቅበትን ለመወጣት የታዳጊ ህጻናት ፕሮጀክት በመክፈት በአካባቢው አቅሙና ፍላጎቱ ያላቸውን ታዳጊዎች በግልጽ ውድድር በመቀበል እያሰለጠነ እንደሚገኝ ተናግረዋል ። መደበኛ ተማሪዎችም በአካል ብቃትና በአዕምሮ ዳብረው አምራች ዜጋ ሆነው እንዲወጡ ለማስቻል ዩኒቨርሲቲው አበክሮ እየሰራ ነው ብለዋል። በስፖርቱ ዘርፍ በተለይም በርካታ ደጋፊ ባለውና ተወዳጅ በሆነው በእግር ኳስ ዘርፍ ተፎካካሪ ለመሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አስተዋጽኦን ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል ። አካባቢው ካለው እምቅ የእግር ኳስ አቅም አንጻር ለሀገር የሚተርፉ ተጨዋቾችን ለማፍራት ታሳቢ ተደርጎ ፕሮጀክት ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን የተናገሩት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የስፖርት ሳይንስ መምህርና ከ15 ዓመት በታች የእግር ኳስ ፕሮጀክት አሰልጣኝ ወንድወሰን ታዬ ናቸው። ባለፉት ሁለት ዓመታት በተደረገ ጥረት ከ60 በላይ ዕድሜያቸው ከ13ና ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊ ህፃናትን ይዘው በዩኒቨርሲቲው ሜዳና የስፖርት ግብአት እያሰለጠኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም በዩኒቨርሲቲው ፕሮጀክት የሰለጠኑ ልጆችን ወደ ሀዋሳ ከነማ እግር ኳስ ክለብና ወደ ሌሎች ክለቦች እንዲገቡ መደረጉን ተናግረው የስፖርቱ ዘርፍ የማህበረሰብ አገልግሎት አካል ሆኖ እንዲጠናከር እየተሰራ ነው ብለዋል። ሌላኛው የስፖርት ሳይንስ ክፍል መምህርና ከ13 ዓመት በታች ፕሮጀክት አሰልጣኝ አለማየሁ አሻንጎ በበኩላቸው የእግር ኳስ ዕድገት ከታሰበ በታዳጊዎች ላይ መሰራት እንዳለበት ገልጸው በዚህ ረገድ ታዳጊዎችን በመመልመል እያሰለጠንን እንገኛለን ብለዋል። በዚህ ዕድሜ ስልጠና የሚወስዱ ልጆች ለሀገር ኩራት እስከመሆን ሊደርሱ እንደሚችሉ ያላቸውንም ዕምነት ገልጸዋል። በዩኒቨርሲቲው ከ17 ዓመት በታች ፕሮጀክት በመታቀፍ እየሰለጠነ የሚገኘውና የ11ኛ ክፍል ተማሪው ብሩክ ዮሐንስ ባገኘው ዕድል ደስተኛ መሆኑን ተናግሮ ስፖርቱን ለማሳደግ በታዳጊዎች ላይ መስራት ወሳኝ መሆኑን ተነግሯል። በዩኒቨርሲቲው የሚሰጣቸው ስልጠና ከሜዳ አጠቃቀምና ሌሎች ቴክኒካል ጉዳዮች አንጻር ሳይንሳዊ መሰረት ያለው መሆኑን ጠቅሶ በቀጣይ በትልቅ ደረጃ ለመጫወት ማቀዱንም ገልጿል። በዩኒቨርሲቲው ፕሮጀክት ከ15 ዓመት በታች እየሰለጠነ የሚገኘው ታዳጊ ኤቤል አባተ በበኩሉ የ8ኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን በዩኒቨርሲቲው ባገኘው የስልጠና ዕድል ችሎታውን እያሻሻለ መሆኑን ገልጿል።
በስፔን የ10 ሺ ሜትር ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ አሸነፈ
Mar 17, 2024 136
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2016(ኢዜአ)፦ በስፔን ላሬዶ በተካሄደው የ10 ሺ ሜትር ሩጫ ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ርቀቱን 26 ደቂቃ ከ36 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት አሸንፏል፡፡ አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ውድድሩን የጨረሰበት ሰዓት የርቀቱ የምንግዜም ሶስተኛው ፈጣን ሰዓት ተብሎ ተመዝግቧል፡፡ አትሌቱ ውድድሩን ያሸነፈው የ5ሺ እና የ10ሺ ሜትር የሪከርድ ባለቤቱንና አሸናፊ ጆሹአ ቺፕቴግን አስከትሎ መሆኑን የአለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ አመልክቷል፡፡ ሪከርድ ለመስበር ለውድድሩ በቂ ዝግጅት አድርጌ ነበር ያለው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ሪከርዱ ባይሳካም ባገኘሁት ውጤት ተደስቻለሁ ብሏል።
21ኛው ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜትር የሩጫ ውድድር በአዲስ አበባ ተካሄደ
Mar 17, 2024 143
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2016(ኢዜአ)፦21ኛው ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜ. የሩጫ ውድድር ዛሬ ማለዳ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሚያዘጋጀውና ሴቶች ብቻ የሚወዳደሩበት የ5 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሄዷል፡፡ የ2016 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች የሚል መጠሪያ በተሰጠው የ5 ኪ.ሜ ሩጫ ውድድር 16 ሺህ ሴቶች ተሳትፈውበታል፡፡ "የሴቶችን አቅም እንደግፍ፤ ለውጥን እናፋጥን "በሚል መሪ ሃሳብ በተደረገው ውድድር የተካፈሉ ተሳታፊዎች ቁጥር በውድድሩ ታሪክ ከፍተኛው መሆኑ ተገልጿል፡፡ በውድድሩ ላይ ከአገር ውስጥ በተጨማሪ ከተለያዩ አገሮች የመጡ ከአርባ በላይ ሴቶች መሳተፋቸው ታውቋል፡፡ ኢትዮጵያና አየርላንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበትን 30ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ 35 አየርላንዳውያን በውድድሩ ተሳትፈዋል፡፡ ታላቁ ሩጫ የ21ኛ ዓመት ምሥረታ በዓሉን አስመልክቶ ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያና አጋሮቹ በሴቶች ዙሪያ ለሚከናወኑ ተግባራት እያደረጉት ላለው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸው ይታወሳል። የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ዳግማዊት አማረ ተቋሙ ባለፉት 21 ዓመታት ሴቶችን ለማብቃትና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ሴቶችንና በጎ አድራጎት ተቋማትን ለመደገፍ መቻሉን በመግለጫው ላይ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ በማስጀመሪያ መርኃ-ግብሩ ላይ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሂሩት ካሰው፣ አትሌት መሰረት ደፋርና ሌሎች ታዋቂ ግለሰቦች ተገኝተዋል። በውድድር ጉታኒ ሻንቆ 1ኛ፣ ብርነሽ ደሴ 2ኛ ፣ መቅደስ ሽመልስ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል፡፡
ስፖርቱን ከመንግስት ድጎማ ጥገኝነት አላቆ ራሱን እንዲችል ለማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ ነው - የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
Mar 16, 2024 212
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2016(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የስፖርቱን ዘርፍ ከመንግስት ድጎማ ጥገኝነት አላቆ ራሱን እንዲችል ለማድረግ ለፌዴሬሽኖችና ማህበራት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ የከተማዋ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ። በመዲናዋ ከሚገኙ የስፖርት ፌዴሬሽኖችና ማህበራት ውስጥ 10ሩ ራሳቸውን ከድጎማ ማላቀቅ የሚያስችሉ የመመዘኛ መስፈርቶችን የማሟላት ሂደት በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙ ቢሮው ገልጿል። ቢሮው ይህን ያለው የአዲስ አበባ ከተማ ስፖርት ምክር ቤት 14ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ በአዲስ አበባ ባካሄደበት ወቅት ነው። የቢሮው ኃላፊና የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ በላይ ደጀን ባለፈው አንድ ዓመት በስፖርቱ ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን አስመልክቶ ለጠቅላላ ጉባኤው ሪፖርት አቅርበዋል። በ2015 ዓ.ም የአዲስ አበባ ስፖርት ምክር ቤት ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፥ ምክር ቤቱ ስፖርቱን ከበጀት ድጎማ ለማላቀቅ በትኩረት መስራት እንዳለበት አሳስበው ነበር። የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊው በላይ ደጀን በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት ቢሮው በመዲናዋ የሚገኙ 36 የስፖርት ፌዴሬሽኖችና ማህበራት ከመንግስት በጀት እንዲላቀቁ እየሰራ ነው። በዚህም የተለያዩ ስፖርቶች ራሳቸውን ችለዋል የሚያስብላቸውን መመዘኛዎች እንዲያሟሉ ቢሮው ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል። ብስክሌት፣ ውሃ ዋና፣ ወርልድ ቴኳንዶ፣ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶና ጅምናስቲክ የስፖርት ማህበራትና ፌዴሬሽኖች መስፈርቶቹን ለማሟላት እየሰሩ ከሚገኙት መካከል ይጠቀሳሉ። በራስ አቅም በጀት መመደብ፣ የሰው ኃይል መቅጠር፣ አደረጃጀትና ሀብት ማሰባሰብ ላይ የሚሰራ የገበያ ቡድን ማወቀር ከመመዘኛዎቹ መካከል እንደሚገኙበት ነው ኃላፊው ያነሱት። አትሌቲክስና እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች በራሳቸው አቅም ከመንቀሳቀስ አኳያ እንደ መልካም ተሞክሮ እንደሚነሱ አመልክተዋል። ሌሎችም የስፖርት ፌዴሬሽኖችና ማህበራት ከድጎማ በጀት እንዲላቀቁ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በ2016 በጀት ዓመት ለስፖርት ፌዴሬሽኖችና ማህበራት ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡንና ይህም ከባለፈው በጀት ዓመት አንጻር የ4 ሚሊዮን ብር ገደማ ብልጫ እንዳለው አንስተዋል። ከስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ጋር በተገናኘም በመዲናዋ 1 ሺህ 236 የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን 741ዱ ባለፉት አምስት ዓመታት የተገነቡ መሆናቸውን ነው ኃላፊው የገለጹት። በ2015 ዓ.ም 13 የመደመር ትውልድ የሕጻናት እና ወጣቶች የመጫወቻና የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች መገንባታቸውን ጠቅሰው፥ በ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት እስከ አሁን 38 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንደተገነቡ ገልጸዋል። በሌላ በኩል በአዲስ አበባ በ11ዱም ክፍለ ከተሞች በ19 የስፖርት ዓይነት 123 የታዳጊ ፕሮጀክቶች መከፈታቸውንም ነው ያነሱት። ስፖርትን ባህሉ ያደረገ ማኅበረሰብ ለመፍጠር በመኖሪያ፣ በመማሪያና በስራ አካባቢ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ፕሮግራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም የአካባቢ የጤና ቡድኖችን በማጠናከር ሕብረተሰቡ ጤናውን ከመጠበቅ ባሻገር የእርስ በእርስ ግንኙነቱን እንዲያዳብር እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በጠቅላላ ጉባኤው የአዲስ አበባ ከተማ ስፖርት ምክር ቤት ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉና የስፖርት አፍቃሪ ጌታ ዘሩ ለሀገር የስፖርት እድገት ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የእውቅና ሽልማት አበርክቷል። ጠቅላላ ጉባኤው በስፖርት ማህበራት ስራ አስፈጻሚነት ከአራት ዓመት በላይ ለሰሩ 47 ሰዎች የእውቅና ሽልማት በመስጠት በክብር አሰናብቷል። በተጨማሪም ጉባኤው ለመዲናዋ ሁለንተናዊ የስፖርት ዕድገት አስተዋጽኦ እያበረከቱ ላሉ ክለቦች፣ ተቋማትና ማህበራት እውቅና ሰጥቷል።
አካባቢ ጥበቃ
በዞኑ ከ6 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት መልሶ እንዲያገግም የማድረግ ተግባር እየተከናወነ ነው
Mar 19, 2024 28
ሽሬ እንዳስላሴ ፤ መጋቢት 10/2016(ኢዜአ)፦ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች የተመናመኑ ከ6 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት መልሶ እንዲያገግም ለማድረግ እየተከናወነ መሆኑን በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን የተፈጥሮ ሀብት ፅህፈት ቤት አስታወቀ። አስተባባሪው አቶ ሃብተስላሴ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በዞኑ በሚገኙ አራት ወረዳዎች የሚገኝ ከ6 ሺህ ሄክታር በላይ ደን መልሶ እንዲያገግም ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ በመከለል ጥበቃና እንክብካቤ እየተደረገለት ነው። በአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፎ ተከልሎ እንዲጠበቅና እንክብካቤ እየተደረገለት ያለው ደን በአብዛኛው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባለው የእጣን ዛፍ የተሸፈነ እንደሆነ አስተባባሪው ገልፀዋል። ጉዳት የደረሰበት ይኸው የተፈጥሮ ደን መልሶ እንዲያገግም በህዝብ ነፃ ተሳትፎ የተለያዩ ጎርፍ አልባ እርከኖች እየተገነቡለት መሆኑን አስረድተዋል። እንዲሁም ጉዳት የደረሰበትን የደን ክፍል መልሶ ለማልማት የተለያዩ አገር በቀል ችግኞችን ለመትከል የችግኝ ማፍላት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ደኑ ሙሉ በሙሉ ካገገመ በኋላ በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ንብ በማነብና እጣን በማምረት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እድል እንደሚፈጠርላቸውም አስተባባሪው ተናግረዋል። በዞኑ አስገደ ወረዳ ፀሊሞይ በተባለ የገጠር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ገብረመድህን በላይ በሰጡት አሰተያየት በተከለለው ደን ውስጥ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ስራ በማከናወን ደኑ መልሶ እንዲለማና ወደ ቀድሞ ይዞታው እንዲመለስ ጥረት እያደረጉ እንደሆነ ገልፀዋል። ሌላው የዚሁ ገጠር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አስገደ ግርማይ በበኩላቸው ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ ሆኖ እንዲከለል የተደረገው ደን ሙሉ በሙሉ አስኪያገግም ከመጠበቅና ከመንከባከብ ወደ ኋላ እንደማይሉ ቃል ገብተዋል። በዞኑ በደን የተሸፈነው 52 ሺህ ሄክታር መሬት በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች የተጎዳ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በክልሉ በሰፈነው ሰላምም በየዓመቱ ቢያንስ ከአምስት ሺህ በላይ ሄክታር ደን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነጻ በማድረግ መልሶ እንዲያገግም እየተሰራ መሆኑን ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
የለሙ ተፋሰሶች የገቢ ምንጭ ሆኖናል- በማዕከላዊ ጎንደር አርሶ አደሮች
Mar 19, 2024 58
ጎንደር፣መጋቢት 10 / 2016(ኢዜአ)፡-በአካባቢያቸው ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ሥራዎች የለሙ ተፋሰሶችን ለገቢ ማስገኛ በማዋል ተጠቃሚ መሆናቸውን በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ አርሶ አደሮች ገለጹ፡፡ በዞኑ አርሶ አደሮች ከሰብል ማምረት ባሻገር የለሙ 144 ተፋሰሶችን ተጠቅመው በንብ ማነብ፣ በእንስሳት ማድለብና በፍራፍሬ ልማት ላይ መሰማራታቸውን የዞኑ ግብርና መምሪያ አመልክቷል፡፡ አርሶ አደር መንበሩ ቻላቸው በላይ አርማጭሆ ወረዳ የግንድ መጣያ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ፤ ባለፉት ዓመታት በአካባቢያቸው የተከናወነው ተፋሰስ ልማት ለእንስሳት መኖ አቅርቦት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ለኢዜአ ተናግረዋል። በዚህም ሁለት በሬዎችን አድልበው ሸጠው ካገኙት 120 ሺህ ብር ገቢ ሁለት የወተት ላሞችን ባለፈው ክረምት መግዛታቸውን ገልጸዋል። በላሞቹ በቀን 15 ሊትር ወተት በማለብና ለጎንደር ከተማ ገበያ በማቅረብ ገቢ እያገኙ መሆኑን አመልከተዋል፡፡ የምዕራብ ደንቢያ ወረዳ አርሶ አደር ሙላት በየነ በበኩላቸው፤ ተፋሰስን መሰረት በማድረግ ስድስት ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን በመጠቀም የማነብ ስራውን አጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ባለፈው መኸርም ከስድስቱ ቀፎዎች 180 ኪሎ ግራም ማር በመቁረጥ ለገበያ አቅርበው በመሸጥ 63ሺህ ብር ገቢ ማግኘታቸውን አስረድተዋል፡፡ በአካባቢያቸው በሚገኝ ተፋሰስ ያለሙት የአቦካዶ ፍራፍሬ አሁን ላይ ምርት መስጠት መጀመሩን የገለጹት ደግሞ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ የምጥርሃ ቀበሌ አርሶ አደር ሞላ ግስሜ ናቸው። ባለፉት ዓመታት በተከታታይ የአፈርና ውሃ እቀባ ስራ በማከናወን የመሬታቸው የአፈር ለምነት መጨመሩን አመልክተው፤ ምርታማነቱ ከፍ እያለ ተጠቃሚነታቸውም እያደገ መሆኑን አብራርተዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በዞኑ በለሙ 144 ተፋሰሶች ከአራት ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ከሰብል ማምረት ባሻገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ሆኗቸዋል። አርሶ አደሮቹ ተፋሰሶች ውስጥ በንብ ማነብ፣ በእንስሳት ማድለብና በፍራፍሬ ልማት ዘርፍ የተሰማሩ የዞኑ አርሶ አደሮች በግማሽ የበጀት ዓመቱ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም በተፋሰሶቹ በንብ ማነብ ስራ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ከ20ሺህ ኪሎ ግራም በላይ ማርና 10ሺ የደለቡ የእርድ እንስሳት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ መቻላቸውን ጠቁመዋል፡፡ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት ስራዎች ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ የተከለሉ አንድ ሺህ 236 ተፋሰሶች እንደሚገኙ ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡
በአገሪቱ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖዎች ለመቋቋም በገጠር ቀበሌዎች በመተግበር ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች ውጤቶች እያስገኙ ነው
Mar 18, 2024 99
ድሬዳዋ ፤ መጋቢት 9/2016 (ኢዜአ)፡- በአገሪቱ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖዎች ለመቋቋም በገጠር ቀበሌዎች በመተግበር ላይ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ውጤቶች እያስገኙ መሆናቸው ተመለከተ። በገንዘብ ሚኒስቴር አስተባባሪነት በመንግስትና በ'ግሪን ክላይሜት ፈንድ' በድሬዳዋ ገጠር ቀበሌዎች በተሰሩ ልማቶች ላይ ውይይትና የልምድ ልውውጥ እየተካሄደ ነው። ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት እየተገበረ ያለው ስትራቴጂ ዕውን እንዲሆን እየደገፉ ከሚገኙ መካከል አንዱ በመንግስትና በ'ግሪን ክላይሜት ፈንድ' የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች ተጠቃሽ ናቸው። በ50 ሚሊዮን ዶላር ለድርቅ ተጋላጭ በሆኑ 66 የአገሪቷ ቀበሌዎች በመተግበር ላይ የሚገኘው ይህ ፕሮጀክት በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ 330 ሺህ የህብረተሰብ ክፍሎችን በቀጥታና 930 ሺህ የሚሆኑትን ደግሞ በተዘዋዋሪ በዘላቂነት ለመቋቋም እንዲችሉ ማገዝ እንደሆነ ተገልጿል። በገንዘብ ሚኒስቴር የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ምስጋናው እያሱ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ባለፉት አራት ዓመታት በ66 የአገሪቷ ገጠር ቀበሌዎች በፕሮጀክቱ የተከናወኑ ስራዎች አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመፍጠር የሚሰሩ ስራዎችን በማገዝ ረገድ አበርክቶው የጎላ ነው። በድሬዳዋ ዛሬ የተጀመረው አገር አቀፍ የልምድ ልውውጡ በድሬዳዋ አምስት ገጠር ቀበሌዎች የተከናወኑት የተፈጥሮ ሃብትና የውሃ ጥበቃ እንዲሁም የደን ልማት ስራዎችን በመገምገም የተሻለ ተሞክሮ ለመቀመር ያስችላል ብለዋል። የተከናወኑት የንጹህ መጠጥና የአነሰተኛ መስኖ የውሃ ፕሮጀክቶች፣ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የደን ልማት ፕሮጀክቶች ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚን ለመፍጠር የተጀመረው የተቀናጀ ጥረት እንዲጠናከር የሚያግዙ መሆናቸውን ገልፀዋል። በድሬዳዋ የተጀመረው በሐረሪ ክልልም ቀጥሎ የሚካሄደው የተሞክሮ ልውውጥን በመቀመር በቀጣይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ይሰራል ብለዋል። የድሬዳዋ ፕሮጀክቶችን የሚያስተባብረው የአስተዳደሩ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ በበኩላቸው፤ በመንግስትና በ"ግሪን ክላይሜት ፈንድ" የተተገበሩ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና የውሃ ሃብት የማልማት ስራዎች በቤተሰብ ደረጃም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን እያገዙ ናቸው ብለዋል። የተጠናቀቁት የንጹህ መጠጥ ውሃና የአነስተኛ መስኖ ስራዎች የገጠሩን ህብረተሰብ ማህበራዊ ችግሮች እያቃለሉና የገቢ ምንጭን እያሳደጉ መሆናቸውን ለአብነት በማንሳት። እነዚህ ጅምር ውጤታማ ተግባራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት እየተሰራ ያለውን ስትራቴጂ ስኬታማ እንዲሆን እያገዙ መሆናቸውን ነው የገለፁት። ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ሌሎች አጋር ተቋማት የተውጣጡ የአመራር አባላት በድሬዳዋ ገጠር ቀበሌዎች የተከናወኑ ፕሮጀክቶችን ከነገ ጀምሮ እስከ ሚቀጥለው ሐሙስ እንደሚመለከቱም ከወጣው መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እየተገኙ መሆኑ ተገለጸ
Mar 17, 2024 138
አሶሳ፤ መጋቢት 8/2016(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እየተገኙ መሆኑ ተገለጸ። በክልሉ ግብርና ቢሮ የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ደሳለኝ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ ካለፈው የካቲት ወር አጋማሽ የተጀመረው የዘንድሮ የበጋ ተፋሰስ ልማት ዘመቻ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ለሁለት ወራት በሚካሄደው በዚሁ ዘመቻ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ 15 ሺህ 500 የሚጠጋ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ስራ ተከናውነዋል ብለዋል፡፡ በተፋሰስ ልማቱ ከሁለት ሚሊዮን በላይ የክልሉ ነዋሪዎች መሳተፋቸውን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡ የበጋ ተፋሰስ ልማት ዘመቻው በእስካሁን ስራ የተሳተፉ ሰዎች በጉልበት ሲለካም ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሆነ አቶ ፍቃዱ አመልክተዋል፡፡ ስራው እስከ መጋቢት ወር መጨረሻ እንደሚቀጥል ጠቁመው፤ እቅዱን ለማሳካት ስልጠናን ጨምሮ የተፈጥሮ ሃብት ባለሙያዎች ተከታታይ ክትትልና ድጋፍ እያካሄዱ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡ በተፋሰስ ልማት እየተሳተፉ ከሚገኙ የክልሉ አርሶ አደሮች መካከል በአሶሳ ዞን የብራሞ ወረዳ ነዋሪ አቶ አደም ይመር እንዳሉት ባለፉት 10 ዓመታት በዘመቻ በተከናወኑ የበጋ ተፋሰስ ስራ የተራቆቱ አካባቢዎች መልሰው አገግመዋል፡፡ በዚህ ዓመት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራውን ያከናወኑባቸው ቦታዎች ከእንስሳት እና ሌሎችም ንክኪዎች በመጠበቅ በመጪው ክረምት ችግኝ ተከላ ለማስቀጠል መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል፡፡ የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ተበጀ ጌታሁን በበኩላቸው በተፋሰስ ልማት ስራው ከጥቅም ውጪ የሆነ መሬት እንዲያገግም ማስቻሉ ተናግረዋል ፡፡ የተፋሰስ ልማት በተከናወነባቸው ስፍራዎች የተተከሉ ማንጎ፣ አቮካዶ፣ ፓፓዬ እና ሌሎችም ተክሎች ለምግብነት እየተጠቀሙ መሆኑን አመልክተዋው የቤት እንስሳትም በቂ መኖ እንዲያገኙ ማስቻሉንም አስታውቀዋል፡፡ ያገኘነውን ጥቅም ዘላቂ ለማድረግ ያለማንም ቅስቀሳ በሳምንት ከሁለት ቀናት በላይ ጊዜአቸውን ለተፋሰስ ልማት ዘመቻው እያዋሉ መሆኑን አርሶ አደሩ አስታውቀዋል፡፡ በክልሉ በዘንድሮ ዓመት የበጋ ተፋሰስ ልማት ዘመቻ በአጠቃላይ ከ39 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ለማከናወን መታቀዱን ከቢሮው የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የቻይና- አፍሪካ የንግድ ልውውጥ ዕድገት
Mar 14, 2024 241
የቻይና አፍሪካ ግንኙነት ባለፉት አስርት አመታት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ በመምጣቱ ቻይና በአፍሪካ አህጉር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት ዝርጋታ ዋነኛ ተዋናይ ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ አድርጓታል። በቻይና እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ በተያዘው የፈረንጆች ዓመት ከ47 ቢሊዮን ዶላር በላይ መድረሱን የስፑትኒክ ዘገባ ያመለክታል። የንግድ ልውውጡ በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሁለት ወራት ብቻ በ13.9 በመቶ ዕድገት አሳይቷል። ቻይና ወደ አፍሪካ የምትልከው ምርት በ21 በመቶ ማደጉን ያመለከተው ስፑትኒክ በአንፃሩ ቻይና ከአፍሪካ ሀገራት የምታስገባው ምርት መጠን በ4.5 በመቶ ዕድገት አሳይቷል። በፈረንጆቹ 2021 ይፋ የሆነው የቻይና አፍሪካ ትብብር ራዕይ 2035፤ "በአፍሪካ የተሰራ" የሚሉ ብራንዶችን በመፍጠር እና በማቋቋም ረገድ የአፍሪካ ምርቶች በዓለም ገቢያ ተመራጭ እንዲሆኑ ቻይና እየሠራች እንደሆነ ዘገባው አመልክቷል። የቻይና አፍሪካ 2035 ራዕይ አፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን እንድታሳድግ እና ከአለም አቀፍ የኢንዱስትሪ እና የአቅርቦት ሰንሰለት ጋር እንድትተሳሰር ለማድረግ እቅድ እንዳለውም በዘገባው ተጠቁሟል። ባሳለፍነው የፈረንጆቹ 2023 መገባደጃ ላይ ቻይና ኢትዮጵያን ጨምሮ ስድስት የአፍሪካ ሀገራት ምርቶቻቸውን ከቀረጥ ነፃ ወደ ሀገሯ እንዲገቡ መፍቀዷን ያስታወሰው ዘገባው፤ ይህም የአፍሪካ ቻይና የንግድ ትስስርንና ትብብርን ከፍ እንዲል አድርጓል ብሏል። ከአፍሪካ ሀገራት ደቡብ አፍሪካ የቻይና ትልቁ የንግድ አጋር መሆኗን ያመለከተው ዘገባው፤ ናይጄሪያ፣ አንጎላ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እንደቅደም ተከተላቸው የቻይና የንግድ አጋር መሆናቸውን መረጃው ያመለክታል።
በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች በኢትዮጵያ
Mar 14, 2024 252
ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባውን የነዳጅ ፍጆታ ለመቀነስ እና የአየር ብክለትን ለመከላከል የሚደረገውን ሰፊ ጥረት እውን ለማድረግ ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ለህዝብ ማመላለሻ አገልግሎት በማዋል ከፍተኛ እምርታን አስመዝግባለች ይላል የአፍሪካ 24 ድረ ገጽ ዘገባ። በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ እየተዘዋወሩ የሚገኙት የኤሌክትሪክ ሚኒባሶች ድምጽ አልባና ለአካባቢው ተስማሚ መሆናቸውን ያተተው የአፍሪካ 24 ድረ ገጽ ዘገባ፤ ይህ የለውጥ ጅማሮ እየጨመረ በመጣው ፍላጎት እና በመንግስት ጠንካራ ድጋፍ የተገኘ መሆኑን አመልክቷል። መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በረጅም የጊዜ ማእቀፍ ውስጥ ከጎዳናዎች የማስወጣት እቅድ ነድፎ እየሰራበት በመሆኑ ምክንያት አሮጌዎቹን የነዳጅ ተሽከርካሪዎች ተክተው ለዜጎች ንጹህና ጤናማ አገልግሎት የሚሰጡት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ከፍ ያሉ ማበረታቻዎች እየተደረገላቸው መሆኑንም ዘገባው አመልክቷል። ከእነዚህ ማበረታቻዎች መካከልም ለአካባቢ ጥበቃና ለጤና ምቹ ናቸው የተባሉት በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ያለምንም ቀረጥ አሊያም በዝቅተኛ ቀረጥ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ወይም በከፊል ገብተው እንገጣጠሙ ማድረግ ተጠቃሽ ነው። እነዚህ ተሽከርካሪዎች ሃገር ውስጥ ገብተው መገጣጠማቸው ለኢትዮጵያውያን የእውቀትና የሙያ ሽግግር ከማድረጋቸው ባለፈ ለወጣት ክፍል የስራ እድሎችን እንደሚፈጥሩ ዘገባው አመልክቷል። በሃገር ውስጥ የተገጣጠሙት ተሽከርካሪዎች የዜጎችን እንቅስቃሴ ከማሳለጥ አኳያም ጉልህ አበርክቶ እንዳላቸውም ጠቁሟል። የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መስፋፋት ለነዳጅ ግዥ የሚወጣውን ከፍተኛ የሃገር ሃብት ለሌላ ልማት ለማዋልና ከአካባቢ ጥበቃና ከዜጎች ጤና ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ መንግስት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት መሆኑን ያነሳው ዘገባው ተሽከርካሪዎቹ በስፋት ጥቅም ላይ ሲውሉ የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ከማሻሻላቸውም ባሻገር ጤናማ የከተሞች ውስጥ እንቅስቀሴ በመፍጠር የአረንጓዴ አሻራ ትልሙን በማሳካት ያግዛሉ ብሏል።
በህንድ አንድ እቃ ጫኝ ባቡር ያለ አሽከርካሪ 70 ኪሎ ሜትሮች መጓዙ ተነገረ
Feb 26, 2024 793
አዲስ አበባ ፤የካቲት 18/2016 (ኢዜአ)፦በህንድ አንድ እቃ ጫኝ ባቡር ያለ አሽከርካሪ 70 ኪሎ ሜትሮች መጓዙን ተከትሎ የሀገሪቱ የባቡር አስተዳደር ምርመራ እያካሄደ መሆኑን ገልጿል። በህንድ አንድ እቃ ጫኝ ባቡር ያለ አሽከርካሪ መንቀሳቀሱን የሚያሳዩ ምስሎች በማህበራዊ ሚዲያ መሰራጨታቸውን ተከትሎ ጉዳዩ አነጋጋሪ ሆኗል። የህንድ የባቡር አስተዳደር ባለስልጣናት ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ መነሻውን ከካሽሚር ግዛት ወደ ጃሙ ያደረገ እቃ ጫኝ ባቡር ያለ አሽከርካሪ እሁድ ከቀኑ 7፡15 እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ድረስ መጓዙን ተናግረዋል። በ53 ፍርጎዎች ለቤትና መንገድ ግንባታ የሚያገለግሉ የድንጋይ ጠጠሮችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረው ባቡሩ በሰዓት 100 ኪሎ ሜትር ፍጥነት እንደነበረውም ተነግሯል። ሆኖም በሰው ህይወት ላይ ምንም አይነት ጉዳት ሳያደርስ ባቡሩን ማስቆም እንደተቻለ ነው ሃላፊዎቹ የገለጹት። በካቱሃ ግዛት የአሽከርካሪዎችና ባለሙያዎች ቅይይር ሲደረግ ችግሩ ሊፈጠር እንደቻለ የተነገረ ሲሆን 70 ኪሎ ሜትሮችን ያለ አሽከርካሪ እንዴት ሊጓዝ ቻለ የሚለው ጉዳይ ላይ በጥብቅ ምርመራ እንደሚደረግ ቢቢሲ ዘግቧል። የቁጥጥር ባለሙያዎች ባቡሩን ለማስቆም የዛፍ ግንዶች እንደተጠቀሙ ያስነበበው ዘገባው በዚህም የባቡሩን ፍጥነት በመቀነስና በካቱሃ ግዛት እንዲቆም መደረጉን አስነብቧል።
የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የኢትዮጵያ ድል በአፍሪካ ታሪክ ጉልህ ስፍራ እንዳለው ማሳያ ነው
Feb 17, 2024 1073
አዲስ አበባ፤ የካቲት 9/2016(ኢዜአ)፡- የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የኢትዮጵያን ድል የሚዘክር እና ድሉ በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ አገሪቱ ያላትን ጉልህ ስፍራ የሚያሳይ መሆኑ ተገለጸ። የዓድዋ ድል ኢትዮጵያውያን ከ128 ዓመታት በፊት በአንድነት ተሰልፈው ድል በመንሳት ነፃነታቸውን ያስከበሩበት መሆኑን ሩሲያ የዜና አገልግሎት ስፑትኒክ ዘግቧል። ስፑትኒክ የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ምረቃን አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አማካሪ ልደት ሙለታ ጋር ቃለምልልስ አድርጓል። በዚሁ ቃለምልልስ ላይ ልደት ሙለታ ሙዚየሙ በመሀል አዲስ አበባ ላይ እንዲገነባ የተወሰነው ቦታው ለመላው ኢትዮጵያውያን ካለው ታሪካዊ ፋይዳ አንጻር መሆኑን አስረድተዋል። ሙዚየሙ የተገነባበት ቦታ ኢትዮጵያውያን ወደ አድዋ ከመዝመታቸው በፊት ከሁሉም የአገሪቱ አቅጣጫዎች በመትመም የተሰበሰቡበት መሆኑን አማካሪዋ አስገንዝበዋል። መታሰቢያ ሙዚየሙ የኢትዮጵያውያን የአንድነት ምልክት ሆኖ ከማገልገሉም በተጨማሪ የአድዋ ድል መነሻ መሆኑንም ያሳያል ብለዋል። በዚህ ታሪካዊ የአDዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በርካታ ታሪካዊ ቅርሶች የያዘ መሆኑን ያስረዱት ልደት ሙለታ ከእነዚህ መካከል በጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ከተሰረቀበት ጣሊያን አገር እንዲመለስ የተደረገው እ.አ.አ በ1935 ኢትዮጵያውያን ከጀርመን ኢንጂነሮች ጋር በመተባበር የሰሩት የመጀመሪያ የኢትዮጵያ አውሮፕላን እንደሚገኝበት አስረድተዋል። አማካሪዋ ከአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም መገንባት ማዕከላዊ ሀሳቦች መካከል አንዱ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ወረራ ያሳየችውን ተቃውሞና አልገዛም ባይነት ለማስታወስ እና የሀገሪቱን ድል ለመዘከር ነው ብለዋል። ሁሉን አቀፍና አካታች የሆኑ ቀጠናዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብሮችን በስፋት መጠቀም እንደሚያስፈልግ ያብራሩት አማካሪዋ ጂኦ ፖለቲካል አሰላለፎችን በመገንዘብ የታዳጊ ሀገራትን ድምጽ የሚያጎሉ ቁልፍ ዓለም አቀፍ መድረኮችን መጠቀም እንደሚገባም ጠቁመዋል። አማካሪዋ አክለውም፤ ኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ በብሪክስ (BRICS) ውስጥ በአባልነት መካተቷ በአለም አቀፍ ዲፕሎማሲ እና በአለም ዙሪያ ካሉ አገራት ጋር በሚደረገው የትብብር ሂደት እያደገ የመጣውን ተጽእኖ ፈጣሪነቷ ያሳያል ብለዋል።
ሐተታዎች
በከፍታ የታጀበ ስኬት
Mar 15, 2024 221
ለህጻናትና ታዳጊዎች መልካም ስብእና የሚያግዙ ጽሁፎችን ያዘጋጀችው ኤሪን ሶዴርበርግ ዶውኒንግ 'JUST KEEP WALKING' በሚለው መጽሃፏ ባደራጀችው ገጸባህሪ አማካይነት “አንተ መልካምና ስኬታማ ሆነህ ሳለ ጥቂት ሰዎች ስለአንተ መጥፎነት አብዝተው መጨነቅና ማውራት ከጀመሩ የምትሄድበት መንገድም ሆነ አካሄድህ ትክክል ነውና መራመድህን አታቁም። ብዙሃኑ የስኬትህ ተካፋይና የስኬትህ አጋር ስለሆኑ የጥቂቶቹን ጫጫታ ከምንም ካለመቁጠር ተራመድ ብዙ አፍራሽ ወሬዎች ያንተን ስኬት የመመስከር አቅማቸው ከፍተኛ መሆኑን አትዘንጋ። መቆም የሽንፈት ምልክት ነውና” ትለናለች። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት 78 ዓመታት በከፍታ የዘለቀ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስምና ዝናው የገነነ ተቋም ነው። አየር መንገዱ ታህሳስ 21 ቀን 1938 ዓ.ም ተመስርቶ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ በረራውን መጋቢት 30 ቀን 1938 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ካይሮ አድርጓል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በየዘመኑ በአቪዬሽን ቴክኖሎጂዎችን በመታጠቅና አሰራሮችን በማዘመን ራሱን እያደራጀ የኢትዮጵያ ኩራት ከመሆን አልፎ የአፍሪካ ምልክት ሆኖ ዘልቋል። ዛሬ ላይ የ152 ዘመናዊ አውሮፕላኖች ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በምስረታው ወቅት ከአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል የተገዙና በሁለተኛው ዓለም ጦርነት ያገለገሉ አምስት አውሮፕላኖች ብቻ እንደነበሩት መረጃዎች ያመለክታሉ። በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በዓመት ከ22 ሚሊዮን በላይ መንገደኞችን እንደሚያስተናግድ የሚነገርለት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመንገደኞችን ፍላጎትና ምቾት ለመጠበቅ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን ጨምሮ 31 አውሮፕላኖች ለመግዛት ከአውሮፕላን አምራቹ ቦይንግ ጋር ስምምነት ላይ ደርሷል። እነዚህን ተጨማሪ አዳዲስ አውሮፕላኖችን ቁጥር ጨምሮ የሚገነባቸው ዘመናዊ አየር መንገዶች ሲደመሩ በአፍሪካ ግዙፍ ተቋምነቱን ይበልጥ የሚያረጋግጥ ያደርገዋል። የበረራ አድማሱን በየጊዜው እያሰፋ የሚገኘው አየር መንገዱ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ 134 መዳረሻዎች ያሉት ሲሆን በሀገር ውስጥ ወደ 22 መዳረሻዎች ይበራል። ከዚህ ውስጥ 60 የበረራ መዳረሻዎቹ አፍሪካ ውስጥ ነው። አየር መንገዱ ከ55 ሚሊየን ዶላር በላይ አስገንብቶ ወደ ስራ ያስገባው ዘመናዊ የካርጎ ማእከል ከምስራቅ አፍሪካ ብሎም ከአፍሪካ ከፍተኛ ተብሎ ተመዝግቦለታል። በ15 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ግንባታው ያረፈው የካርጎ ማዕከል ለኤሌክትሮኒክስ ግብይት (ኢ ኮሜርስ) አገልግሎት የሚውል ሲሆን የካርጎ አገልግሎት እየሰፋ መምጣት አየር መንገዱ የሚሰራቸው ተያያዝ በርካታ ተግባራት መስፋት፣እንዲሁም የዲጂታል ግብይት ተመራጭ መሆን ለማእከሉ ግንባታ ምክንያት ተብለው ተጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በማህበራዊ መስክ ከሚታወቅባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ ሴቶችን በማብቃትና የጾታ እኩልነትን በማስተግበር ረገድ አርአያነት ያለው ተግባር መፈጸሙ ነው። በየዓመቱ የሚታሰበው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በአውሮፓውያኑ የቀን አቆጣጠር ማርች 8 በሚከበርበት ዕለት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለፉት በርካታ አመታት ወደ ተለያዩ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ሙሉ ለሙሉ በሴቶች ብቻ የተመራ በረራን በማደረግ ዓለም አቀፍ ዝናን አትርፏል። አየር መንገዱ ዘንድሮ ለ9ኛ ጊዜ "ሴቶችን በማብቃት አፍሪካን ማስተሳሰር" በሚል መሪ ቃል ከአዲስ አበባ ወደ ለንደን በሴቶች ብቻ የተመራ የተሳካ በረራ አድርጓል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመንገደኞች በሚሰጠው ዘመኑን የዋጀና ቀልጣፋ አገልግሎት በየጊዜው የተለያዩ ሽልማቶች ባለቤት መሆን የቻለ ተቋም ነው። ለአብነት የቅርብ ጊዜያቶችን ለማንሳት ያህል ባሳለፍነው ዓመት በአየርላንዷ ደብሊን በተዘጋጀ መርሐ-ግብር ላይ በዓመታዊው የ“አፔክስ” የመንገደኞች ምርጫ “ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ” ሽልማትን አሸንፏል፡፡ በተመሳሳይ ዓለም አቀፍ የአየር ጭነት ኢንዱስትሪ ጉባኤ "ኤር ካርጎ ኤሮፕ" እ.አ.አ በ2021 ባካሄደው የበይነ መረብ የሽልማት ስነ ስርዓት ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የካርጎና የሎጅስቲክ አገልግሎት የ2021 የአየር ጭነት ኢንዱስትሪ የደንበኞች እንክብካቤ ዘርፍ ሽልማት አግኝቷል። በአውሮፓውያኑ 2024 ዓመታዊውን የብሪክስ አባል ሀገራት የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት የ2024 ሽልማት ላይ “የኮርፖሬት የዘላቂነት ስኬት ሽልማት” አሸናፊ ሆኗል። አየር መንገዱ በትላልቅ ስኬቶች የማለፉን ያህል ከባድ ፈተናዎችንም ተጋፍጦ በጽናትና በስኬት አልፏል። መላውን ዓለም ያዳረሰው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ አንዱ ማሳያ ነው። በዚያን ጊዜ የመንገደኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነሱ ምክንያት በዓለም ደረጃ በርካታ አየር መንገዶች በረራ በማቋረጥ ችግር ውስጥ ወድቀዋል። በዚህ ፈታኝ ወቅት አየር መንገዱ የስትራቴጂ ለውጥ በማድረግ አንዳንድ የመንገደኞች አውሮፕላኖቹን ወደ ዕቃ ጫኝ በመቀየር ጭምር ትኩረቱን ጭነት ማጓጓዝ ላይ አድርጓል። በዚያን ፈታኝ ወቅት አየር መንገዱ የቀየሰውን ስትራቴጂ በመቃወም ከውስጥም ከውጭም ከተለያዩ አቅጣጫዎች ትችትን አስተናግዷል። ይሁን እንጂ አየር መንገዱ ፈተናውን በመቋቋም እንደሌሎቹ ሀገራት አውሮፕላኖች በረራ የማቋረጥ እጣ ሳይገጥመው በታላቅ ብልሃት ማለፍ የቻለ ተቋም መሆኑ ተመስክሮለታል። በዚህም በካርጎ አገልግሎት ገቢ ከማገኘቱም ባሻገር ክትባትን ለዓለም በማዳረስ ወረርሽኙ ለመግታት በተደረገው ዓለም አቀፍ ጥረት ውስጥ የራሱን አሻራ አኑሯል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የራሱ የአውሮፕላን አብራሪዎች ማሰልጠኛ ትምሕርት ቤት ሲኖረው የግል አብራሪ እና የንግድ አውሮፕላን አብራሪ ፈቃድ በመስጠት የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ ዜጎችን በማሰልጠን ከአራት አስርተ ዓመታ በላይ ልምድ አካብቷል። አየር መንገዱ በሚያስተዳድረው ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የበረራ ባለሙያዎችን በቅርቡ ያስመረቀ ሲሆን ምሩቃኑ ከታንዛንያ ከደቡብ ሱዳን ከኒጀር ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከቶጎ እና ከማዳጋስካር መሆናቸው ደግሞ የአየር መንገዱን የፓንአፍሪካኒስት መንፈስ አጉልቶ ያሳየ አድርጎታል። ስኬቶቹ በዚህ ያላበቁት አየር መንገዱ የእድገት ግስጋሴውን እንደቀጠለ ይገኛል። ከሰሞኑ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአድዋ ድል መታሰቢያ በተካሄደ ደማቅ ስነ-ስርዓት ላይ ለአምስት ተቋማት ‘የኢትዮጵያ ተቋማት ስኬት ሽልማትን’ አበርክተዋል። በዚህ ወቅት ከተሸለሙት ተቋማት መካከል አንዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲሆን ሽልማቱ ለወደፊትም ለላቀ ስኬት የሚያዘጋጀው እንደሆነ ይታመናል።
አድዋን የዘከሩ ስንኞች
Feb 29, 2024 622
የታሪክ ድርሳናት የአድዋ ድልን በተለያየ መንገድ ዘክረውታል። ምሁራንም አንድምታውን በየዐውዱ ዘርዝረዋል። በዚህም ለሰው ልጆች በተለይም ለጥቁሮች አዲስ ምዕራፍ የከፈተ እንደሆነ ደምድመዋል። በርግጥም የአድዋ ድል ታሪክም፣ ትርክትም የለወጠ ትልቅ ሁነት ነው። በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ምዕራባዊያን 'አቢሲኒያ' በሚሏት ጥንታዊት አፍሪቃዊት ምድር የነበረው ክስተት ቀለምና ዘር ቀመስ በሆኑ በሰው ልጆች መካከል ድል መንሳትና መነሳት፣ ተስፋ እና ቀቢፀ ተስፋ፣ ሀሜትና ሀሞት፣ ብስራትና መርዶ... እያፈራረቀ አበሰረ። ለሀገሬው ዘመን-አይሽሬ አሻራ አነበረ። ውርስም ቅርስም ሆነ!! ይህ ክስተት በታሪኩ ልክ በኪነ ጥበብ ተዘክሯል ባይባልም ቅሉ በጥበብ ፈርጁ ተወስቷል። የኪነ-ጥበብ ሰዎች በየመክሊቶቻቸው ድሉን ለመዘከር ጥረዋል። ሙዚቀኞች በዜማዎቻቸው፣ የሲኒማ ሰዎች እና ፀሐፈ ተውኔቶች በተውኔታቸው፣ ሊቃውንት በቅኔዎቻቸው አድዋን ዘክረዋል። ዕውቅ ገጣሚያን ደግሞ ቃላት እያዋደዱ፣ በዘይቤና ዘመን እያዋሃዱ፣ ምዕናብና ገሀድ እያዛነቁ፣ ታሪክና ትዝብት እያሰባረቁ ... አድዋን በግሩም ስንኞቻቸው ከትበውታል። በአድዋ ድል ምርጥ ግጥሞች መካከል "ጥቂት ስንኞች" እየመዘዝን በወፍ በረር ቅኝት እንመልከት። ባለቅኔው ፀጋዬ ገብረመድህን በ‘እሳት ወይ አበባ’ ግጥም መድብሉ አድዋን መልክዓ ምድራዊና ሃሳባዊ ወሰኗን አድማስ ተሻጋሪ፣ ሰማይ ታካኪ፣ ታሪካዊ ስፍራዋ የአጽም ርስትና የደም ትቢያ የተሸበለለባት መቀነት አድርጎ መስሏታል። በዚህች ታሪካዊ ስፍራ በተከፈለው መስዋዕትነት ከባርነትና ነጻነት ስርየትን ሲያጎናጽፍ፣ የኩራት ቅርስ መሆኗንም ሰፊውን ታሪክ በጥቂት ስንኞች እንዲህ ቋጥሯል። ".... አድዋ ሩቅዋ፣ የዓለት ምሰሶ የአድማስ ጥግዋ፣ ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ... ዓድዋ የዘር አፅመ ርስትዋ- የደም ትቢያ መቀነትዋ ከሞት ከባርነት ሥርየት- በደም ለነጻነት ስለት አበው የተሰውብሽ እ’ለት የኩሩ ትውልድ ቅርስዋ- የኢትዮጵያዊነት ምስክርዋ..." ገጣሚው አለፍ ሲልም በጦርነቱ የዋሉ መሳሪያዎችን፣ የጦር መሪዎችን እጅና ጓንትነት በፈረስ ስሞቻቸው በመቋጠር /ለአብነትም የዳግማዊ ምኒልክ፣ የራስ መኮንን፣ የደጃች ባልቻ ሳፎ፣ የፊታውራሪ ገበየሁና ሌሎችም/ ኢትዮጵያዊያንን ጀግንነትና ወኔ በአጭሩ ቋጥሮታል። ...ድው-እልም ሲል ጋሻዋ- ሲያስተጋባ ከበሮዋ፣ ሲያስገመግም ዳኘው መድፍዋ፣ ያባ መቻል ያባ ዳኘው፤ ያባ ነፍሶ ያባ ቃኘው፣ ያባ ጎራው፣ ያባ በለው በለው ሲለው..." በሚል። ደራሲና ጋዜጠኛ ነብይ መኮነን ‘ስውር ስፌት’ በተሰኘ የግጥም መድብሉ የአድዋን ድል ሲያመሰጥረው አድዋን ‘በደም ግብርነት’ ይገልጸዋል፤ ታሪኩንም ላጥፋህ ቢሉት የማይጠፋ ሕያው ቀንዲል አድርጎታል። “አድዋ የደም ግብር ነው፤ አበው የለኮሱት ቀንዲል፣ አድዋ የአፍሪካ ዱካ ነው፤ አበሽ የከተበው ፊደል፣ ላጥፋህ ቢሉት መች ይጠፋል፤ ጠላት በልቶ ያፈራ ተክል፣ ለዛሬም ታሪክ ነው፣ ‘ነገም ሌላ ቀን ነው’ ለሚል...” የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ ምሁር ሰይፉ መታፈሪያ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) “የተስፋ እግር ብረት” መጽሐፍ “የድል በዓል ማለዳ” በሚል ርዕስ የአድዋን ድባብ ከማለዳው ምናባዊ ትዕይንት ጀምሮ ይቃኛል። ገጣሚው የሰንደቁን መውለብለብ፣ የሕብረ ቀለሙን ድምቀት ከልክ በላይ ውስጥን ኮርኩሮ የሚያስፈግግ ሐሴት እንዳለው በዘይቤያዊ ቃላት ገልፆታል። ገጣሚው በቅኔው የሠራዊቱን ቆራጥነት፣ በወኔ በደም ሲቅላላ፣ የመድፍ አረር ሲያፋጭ ይስለዋል። በስሜት ስካር አድዋ ደፍርሶ በስዕለ ህሊናው የነበረውን የጦርነቱ ማለዳዊ ድባብም እንዲህ ያብራራዋል። ዐይነ-ልቦናዬ ዐጽም ያያል፤ የድል ሜዳውን ይቃኛል። ባድዋ ድል በዓሉ ማለዳ፤ የበዓል መድፍ ሲንዱዋዱዋ (ዱዋ ዱዋ ዱዋ ዱዋ!) ከሞት እንቅልፍ ተቀስቅሶ፤ ያ-ዐጽም ዙርያውን ደባብሶ ጉሮሮውን ጠረገ፣ እህህህህ! እህህህህ!... እያለ ይቀጥላል። በአድዋ ኮረብታማ ተራሮች የተኙ ጀግኖችን በሕይወት ተኝተው የሚያንኮራፉ አስመስሎም አቅርቧቸዋል። ...ድንጋይ ተንተርሶ፤ አፈር ቅጠሉን ለብሶ፣ ከዚያን ያንኮራፋል፤ እንደዚሁም በቅብልብል የወደቀበቱ ሜዳው፣ ተረተሩ፤ ቀን የማይለውጠው ምስክሩ የዚያ ጀግና፣ የዚያ ኩሩ። ገጣሚ አበረ አያሌው “ፍርድና ዕርድ” በተሰኘው የግጥም ስብስቡ ባሰፈራቸው ስንኞች ‘ነገረ አድዋ’ን ከመንደር ወደ አገር፣ ከአገር ወደ አህጉር በመጨረሻም ከአህጉር አተልቆ ‘ዓለም’ ያደርገዋል፤ አድዋን የአፍሪካ ብርሀን ፈንጣቂ፤ ለእብሪተኞች ደግሞ የትካዜና ቅስም መስበሪያ ምስጢር አድርጓታል። በተለይም ኢትዮጵያ ለገጠማት አሁናዊ የዘር ፖለቲካ አዙሪት አድዋን ለሚያሳንሱ ወገኖች በቅኔው ምላሽ ይሰጣል። "...እነ ምኒልክ ጦር ይዘው ከመድፍ የተዋደቁ ጎራዴ መዘው የሮጡ በጠብ-መንጃ አፍ ያለቁ ለጓጉለት ነጻነት -ደማቸውን ያፈሰሱ ለሰፈር ብቻ አይደለም- የአህጉር ድል አታሳንሱ። ... ዓድዋ ሰፈር አይደለም - ዓድዋ መንደር አይደለም እሱ ዓለም ናት ዓድዋ ቤቱ - ሃገር ናት የድል ትራሱ ለጠበበ የዘር ቅኔ - የደም ድል አታሳንሱ!..." በማለት ገልጾታል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት ምሁሩ ተሻገር ሽፈራው (ዶ/ር) ‘የነፍስ ርችቶች’ በተሰኘ የግጥም ስብስብ መፅሃፉ ከቋጠራቸው ስንኞች መካከል በአድዋ 100ኛ ዓመት ክብረ በዓል የግጥም ውድድር ያሸነፈበትን ረጅምና ድንቅ ግጥም አካቷል። የዶክተር ተሻገር ግጥም አንጓ እና ስንኞች የአድዋን ምጡቅነት፣ ዝና፣ ነቅዓ ፍትሕ፣ ውበትና ቅኔ በውብ ቃላት ገልጠውታል። "... ዓድዋ አንቺ የዝና አጽናፍ ሕዝቦች እፍ ያሉብሽ ቁጣ - የነበልባል እቶን ጫፍ እጹብ ክስተት፤ ደቂቅ ረቂቅ፤ ምጡቅ ጠሊቅ ኬላ ድንበር፣ አድማስ ሰበር፣ የቅርብ ሩቅ ለትንግርትሽ ብቻ መጥኔ ትንግርት እውነት፣ ታምር ሁነት፣ የብርቅ ብርቅ፣ የድንቅ ድንቅ ለሰጠሽው ፍትህ መጠን - ለፍርድሽ ሚዛን ብያኔ ለንግስትሽ ሥነ ውበት - ለታሪክሽ ምስጢር ቅኔ…" ገጣሚው "... በምን ቀሰም፣ በምን ቀለም - በምን ብዕራና ሊከትበው..." ሲል የአፍሪካዊያን ሁሉን አቀፍ ድል ለመግለጽ የቀለም፣ የአንደበትና የብራና ወኔ እንዳጣባት ይናገራል። በመጨረሻም ይህችን የድል ቁንጮ የማትሞቺ ህያው ጀንበር ሁልጊዜም ተዘመሪ፤ ተወደሽ" ይላታል። "… እና ዓድዋ አንቺ በኩር የድል መኸር የቅኝ ግዛት ቀንበር ሰንሰለቱ እንዲሰበር ተጠቂዎች አጥናፍ አጥናፍ የመረጡሽ የትግል ዘር ህይወት ከፍለው እልፍ - ያርጉሽ የመረጡሽ ከአገር አገር የማታልፊ የማትከስሚ - የማትሞቺ ህያው ጀንበር ሰብዓዊ ድል ነሽና - ስምሽ ይወደስ ይዘመር…" (በአየለ ያረጋል)
ከተሜው ገበሬ - ኮማንደር ጥላሁን ጸጋዬ
Feb 20, 2024 994
የከተማ ግብርና ሥራ ኢኮኖሚን ከመደገፍ ባለፈ ጤናማ ማህበረሰብ እንዲፈጠር አበርክቶው የጎላ ነው። አዲስ አበባ በመኖሪያ እና በተቋማት ቅጥር ግቢዎች የጓሮ አትክልት፣ ፍራፍሬና መሰል የግብርና ልማት ስራዎች እየተስፋፉባቸው ከመጡ ከተሞች መካከል አንዷ ናት። በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎች በግቢያቸው በሚያለሟቸው አትክልትና ፍራፍሬዎች ራሳቸውን ከመመገብ ባለፈ ለሌሎች መትረፍ ችለዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እህት ኩባንያ የሆነው ኮሜርሻል ኖሚኒስ ዳይሬክተር ጄኔራል የሆኑት ኮማንደር ጥላሁን ጸጋዬ በከተማ ግብርና አርአያ የሆነ ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ። በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ አካባቢ ተወልደው ያደጉት ኮማንደር ጥላሁን የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ በማምረት ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ የገቢ ምንጭም ሆኗቸዋል። የከተማ ግብርና ስራን ከቤተሰቦቻቸው መውረሳቸውን ያስታወሱት ኮማንደር ጥላሁን የከተማ ግብርና የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም ከማገዙ ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እድል እንደሚፈጥር ይገልጻሉ። ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን እንደ ጥቅል ጎመን፣ ቆስጣ፣ ሰላጣ፣ አፕል፣ ሙዝ፣ ቡና፣ ማር፤ ዘይቱን እና ሌሎች ተክሎችን በጓሯቸው በማምረት ለቤተሰቦቻቸው ፍጆታ እየተጠቀሙ ይገኛሉ። ከዚህም ባለፈ ቡና፣ ሸንኮራ፣ ማር በማምረት ከራስ ፍጆታ አልፎ ለሌሎችም መትረፍ መቻላቸውን ይናገራሉ። በተለይም በከተማ ግብርና ለመሰማራት ወሳኙ ሰፊ ወይም ጠባብ ቦታ መኖር ሳይሆን ያለውን ሃብት በአግባቡ በመጠቀም በፍላጎት መስራት መሆኑን ያነሳሉ። በዶሮ እርባታም በስፋት ለመሰማራት እየሰሩ ሲሆን በዚህም ከራሳቸው ፍጆታ አልፈው ቢያንስ ለአካባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ እንቁላል ለማቅረብ ተዘጋጅተዋል። አሁን ላይ በመንግስት እየተተገበረ ያለው የከተማ ግብርና ከድህነት ለማምለጥ ሁነኛ መፍትሄ መሆኑን ገልጸዋል። በቀጣይም በተለይም ስራውን ይበልጥ በማስፋት ከራሳቸው አልፈው ምርቶቻቸውን ለማህበረሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ እየሰሩ እንደሆነ ተናግረዋል። ማንም ሰው ምንም አይነት ስራ ለመስራት በመጀመሪያ ደረጃ ፍላጎት ሊኖረው እንደሚገባ የገለጹት ኮማንደር ጥላሁን፤ በፍላጎት ወደ ስራ ከተገባ ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ተናግረዋል። ሁሉም የቤተሰቡ አባላት አትክልትና ፍራፍሬዎችን በመንከባከብ የሚያደርጉት አስተዋጽኦ ለውጤታማነታቸው መሰረት መሆኑን ገልጸው አንድን ነገር ለማሳካት በቤተሰብ ውስጥ የሀሳብ መግባባትና መተባበር ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል።
የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ትኩረት የሚያደረግባቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች
Feb 17, 2024 1051
የዘንድሮው 37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ ረፋዱ ላይ የሚጀመር ሲሆን የአህጉሪቱ የረጅም ጊዜ እቅድ የ2063 አጀንዳ (የምንፈልጋትን አፍሪካ) እውን ለማድረግ በተጣሉ አንኳር ግቦች ማዕቀፍ በአብይት ጉዳዮች ምክከር አድርጎ የመፍትሔ ኃሳቦችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል። 1. የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት የዘንድሮ የፈረንጆች ዓመት የትምህርት ዘመን ተብሎ መሰየሙን ተከትሎ የኅብረቱ ጉባኤ በአህጉሪቱ የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ሊሰሩ በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። የመንግሥታቱ ድርጅት መረጃ እንደሚያሳየው፤ በአፍሪካ በተለይም ከሰሃራ በታች በሚገኘው የአህጉሪቱ ቀጣና በዓለም የትምህርት ተደራሽነት ካልተረጋገጠበት አከባቢ ቀዳሚ ነው። ለአብነትም አጠቃላይ በአህጉሪቱ ከሚገኙ እድሜያቸው ከ15 እስከ 17 የመሆኑ ታዳጊ ወጣቶች 60 በመቶ የሚሆኑት ከትምህርት ገበታ ውጪ ናቸው። ትምህርታቸውን የሚያቋርጡ ታዳጊዎች ቁጥርም አጅግ ከፍተኛ ነው። ብቂ መምህራን የማሰማራት እንዲሁም አህጉሪቱን ለመለወጥ የሚያስችሉ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉ የተግባር ትምህርቶች ተደራሽነትም ከሚፈለገው በታቸ ነው። ይህንን የተገነዘበው የመሪዎች ጉባኤውም የመፍትሄ ውሳኔዎች ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል። 2. አህጉራዊ ምጣኔ ኃብታዊ ትስስር የአፍሪካን ከውጭ የፋይናንስ ጥገኝነት ለማላቀቅና ዘርፈ ብዙ ማኅበራዊና ምጣኔ ኃብታው ችግሮችን ለመቅረፍ የውስጥ አቅምን አሟጦ መጠቀም በተመለከተ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል። በዚህ ረገድ በተለይም ትልቅ ግምት የተሰጠው አሁን በሙከራ ደረጃ ላይ የሚገኘው አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የእስካሁኑ ሂደትና ቀጣይ አቅጣጫ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ይጠበቃል። ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገባ በአህጉሪቱ 30 ሚለየን ሰዎችን ከድኅነት የማውጣት እንዲሁም እንደ አውሮፓውያኑ አቆጠጣር በ2035 በአፍሪካ ገቢን በ7 በመቶ እንደሚጨምር ተስፋ የተጣለበት ይኸው የንግድ ቀጣና በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ አገራት ከታሪፍና ከሌሎች የንግድ ሂደት ጋር ያሉ ውስብስብ አሰራሮችን እንዲያስወግዱ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይገመታል። የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርትና ምርታማነት እንዲሁም ጥራት የማረገጋጥ ጉዳይም ሌላው ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። 3. አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሥፍራ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ተቋማት ያላትን ውክልና ተገቢውን ሥፍራ እንድትይዝ በተለይም በመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ያላትን ውክልና በተመለከተ ለበርካታ ዓመታት ስትጠይቅ ቆይታለች። ይህንን ጨምሮ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማትም የአፍሪካን ፍላጎት ያገናዘበ ቁመና ሊኖረው ይገባል የሚለውም አጀንዳ የዘንድሮው ጉባኤ ተጠባቂ አጀንዳ ይሆናል የሚል ግምት አለ። አፍሪካ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን መድረኮች ጋር በተለይም አሁን አፍሪካ የቡድን 20 አገራት አባል መሆኗን ተከትሎ እንዲሁም ተጽዕኖ ፈጣሪነቱ እየገነነ ከመጣው ከብሪክስ ጋር ባላትና ሊኖራት በሚችለው ግንኙነት ዙሪያም ምክክር ይደረጋል። በተለይም አፍሪካ እንደ ተጨማሪ የቡድን 20 አባልነቷ፤ ምን ይዛ ልትሄድና ልታመጣ ትችላለች እንዲሁም አባልነቷን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ለበርካታ ዓመታት ተፈልጎ የታጣውን ውክልና ለመካስ ወይም የአህጉሪቱን ድምጽ ይበልጥ ለማሰማት በሚቻልባቸው ምቹ ሁኔታዎች ዙሪያ ምክክር እንደሚደረግ ይጠበቃል። 4. የሠላምና ደኅንነት ተግዳሮቶችና መፍትሄያቸው የመሪዎቹ ጉባኤ ዘንድሮም በአፍሪካ የጸጥታ ችግሮች ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። አህጉሪቱን ከድኅረ -ነጻነት በኋላ በእጅጉ እየፈተኑ ከሚገኙ ከነገረ ፖለቲካዊ ጉዳዮች መካከል ቀዳሚውን ሥፍራየሚይዘው የጸጥታ መደፍረስ ነው። ሽብርተኝነት፣ ኢ-ሕገ-መንግሥታዊ የሥልጣን መቆናጠጥ፣ ግጭቶችና ከምርጫ ጋር የተያያዙ የፖለቲካ አለመረጋጋት እና ሌሎች መሰል ቸግሮች አሁንም ለአፍሪካ ፈተና ሆነው ቀጥለዋል። እነዚህ የፖለቲካ ቀውሶች አህጉሪቱ በየትኛውም ማኅበራዊና ምጣኔ ኃብታዊ መስክ ወደፊት ፈቅ እንዳትል ካደረጓት ምክንያቶ ዋነኛው መሆኑን ነው የተለያዩ ጥናቶች የሚያሳዩት። እነዚህን ግጭቶች ባሉበት ለማቆምና ሌሎችም በቀጣይ እንዳይከሰቱ በተለይም የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል (ውይይት) ብቸኛ አማራጭ ለማድረግ ኅብረቱ ከዚህ ቀደም የጀመራቸውን ሥራዎችና ሌሎች ተግባራትን ለማጠናከር በሚያስቸሉ ጉዳዮች ላይ መሪዎቹ ውይይት እንደሚያደረጉና የመፍትሄ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጡ ይጠበቃል። ጉባኤው "ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣ የሕይወት ዘመን፣ ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት“ በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬና ነገ የሚካሄድ ይሆናል።
ትንታኔዎች
ሞክሼዎቹ - የአድዋ መንገሻዎች
Mar 2, 2024 621
ሞክሼዎቹ - የአድዋ መንገሻዎች (ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም እና ራስ መንገሻ ዮሐንስ) የአድዋ አድማስ ዘለል ገድል ሲወሳ የድሉ መገኘት የጦር አበጋዞች ከፊት ይመጣሉ። ከንጉሠ ነገሥቱ ጀምሮ ራስ፣ ደጃዝማች፣ ፊታውራሪ፣ ቀኛዝማች፣ ግራዝማች፣ ባላምባራስ እና ሌሎች ባለማዕረግ አዋጊዎች የድሉ የጀርባ አጥንት መሆናቸው እሙን ነው። ከመላ ሀገሪቷ ጠረፍ ተነቃንቆ ስንቅና ትጥቁን ታጥቆ፣ ድል ሰንቆ እስከ ግማሽ ዓመት ድረስ በባዶ እግሩ የተመመውን የሀገሬው ሰራዊት በቅጡ መርተው አዋግተዋል። ከመነሻ ሰፈር እስከ አድዋ ተረተር፣ ከአምባላጌ ኮረብቶች እስከ መቀሌ ጋራና ቁልቁለቶች፣ ከእንደአባ ገሪማ እስከ ማሪያም ሸዊቶ ሸለቋማ ቋጥኞች፣ ከምንድብድብ መስክ እስከ በገሠሦ አቆበቶች፣ .... ድልና ገድል በደምና በላብ ሲጻፍ የጠላትን የ'ክዱ' ማባባያ የጠሉ፣ ለሀገር ለመሰዋት የቆረጡ ጀግና አዋጊዎች፣ የሀገር ባለውለታዎች ነበሩ። በአድዋ ድል መታሰቢያ 12 የአድዋ ጦር አበጋዞች (ጀኔራሎች) ሀውልት ቆሞላቸዋል። እነሱም፤- ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ ጉርሙ (አባ ጎራው)፣ ልዑል ራስ መኮንን ወልደ ሚካኤል ጉዲሳ (አባ ቃኘው)፣ ንጉስ ተክለሃይማኖት ተሰማ ጎሹ (አባ ጠና)፣ ንጉስ ሚካኤል አሊ አባ ቡላ (አባ ሻንቆ)፣ ደጃዝማች ባልቻ ሳፎ ሮቢ (አባ ጠለስ)፣ ራስ ቢተወደድ መንገሻ አቲከም ቢተርፉ (አባ ገድብ)፣ ራስ ወሌ ብጡል ሃይለማሪያም (አባ ጠጣው)፣ ዋግሹም ጓንጉል ብሩ ገብረመድህን (አባ መርከብ)፣ ራስ አባተ ቧያለው ንጉሱ (አባ ይትረፍ)፣ ራስ አሉላ እንግዳ ቁቢ (አባ ነጋ)፣ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ (ቁሴ) ዲነግዴ ሁንዱል (አባ መቻል) እና ራስ መንገሻ ዮሃንስ ምርጫ (አባ ግጠም) ናቸው። ከነዚህ የአገር ባለውለታዎች መካከል ሁለት ስመ ሞክሼ ጀግኖችን እንዘክራለን። ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም እና ራስ መንገሻ ዮሐንስን። ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም ከዳግማዊ አፄ ምኒልክ ቀዳሚዎች ስምንት ራሶች መካከል ብቸኛው የራስ ቢትወደድ (ከንጉሥነት በታች) ባለማዕረግ ናቸው። በፈረስ ስማቸው አባ-ገድብ ይሰኛሉ። በልጅነታቸው የዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስ ባለሟል ሳሉ ከእስረኛው ምኒልክ ጋር ተዋወቁ። ምኒልክ ከአፄ ቴዎድሮስ አምልጠው ሸዋ ከገቡ በኋላ ከእቴጌ ጣይቱ ብጡል ወንድሞች ራስ ወሌ እና ፊታውራሪ አሉላ ብጡልን ይዘው ከመቅደላ ወደ ሸዋ ተሻገሩ፤ የምኒልክ ሁነኛ ሰው ሆኑ። ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም በሞት እስኪለዩ ድረስ በክፉም በደጉም ዘመን የአጼ ምኒልክ ከፍተኛ አማካሪና ተወዳጅ መስፍን እንደነበሩ፣ ከጦር ሜዳ እስከ ሽምግልናም ሁነኛ ሰው ሆነው ስለማገልገላችው በታሪክ ድርሳናት ተጠቅሷል። በሸዋ፣ ወሎ፣ ጎንደር፣ ዳሞት(ጎጃም) ተዘዋውረው በተለያዩ ግዛቶች በአስተዳዳሪነት ሰርተዋል። ድሕረ መተማ ጦርነት ምርኮኞች እንዲመለሱ፣ ድንበር እንዲካለል በመስራትም የዲፕሎማሲ ስራቸው ይጠቅሳል። ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም ከተሳተፉባቸው ደማቅ ታሪኮች መካከል የአድዋ ድል ይጠቅሳል። ጦርነቱ አሀዱ ብሎ የጀመረው ሕዳር 28 ቀን 1888 አምባላጌ ነው። ለሁለት ሰዓታት በዘለቀው በዚህ ጦርነት ጀኔራል ቶዚሊ የተባለው የጠላት ጦር መሪ የተገደለበት ነው። በዚህ ዐውደ ውጊያ አባ ገድብ አንዱ ወሳኝ የጦር አበጋዝ ነበሩ። በተለያዩ የታሪክ ድርሳናት እንደተመዘገበው ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም ከግዛታቸው ከዳሞትና አገው ምድር የተውጣጣ ስድስት ሺህ እግረኛ እና ፈረሰኛ ጦር ይዘው አድዋ ዘምተዋል። “አባ ገደብ መንጌ እያለ ኧረ ጐራው አምባ ላጌን ሰብሮ ቶዘሊን አስጐራው” የተባለው ለዚህ ይመስላል። አባ ገድብ ጥቅምት 11 ቀን 1903 ምሸት ከራስ ቢትወደድ ተሰማ ናደው ጋር እየተጫወቱ ካለምንም ህመም ድንገት አርፈው ቅድስት ሥላሴ ተቀበሩ። ራስ ቢትወደድ መንገሻ ልጆቻቸውን ከተለያዩ መኳንንት ጋር በጋብቻ በማጣመር በኢትዮጰያ ታሪክ ተጠቃሽ መሆን ችለዋል። ለአብነትም ዘውዲቱ መንገሻ ጠቅላይ ሚኒስትር መኮንን እንዳልካቸውን፣ አስካለማርያም መንገሻ ልዑል ራስ ኅይሉን አግብተው የልጅ ኢያሱን ባለቤት ሠብለወንጌል ኅይሉን ወልደዋል። ደጃዝማች ጀኔራል አበበ ዳምጠውን ያገቡት ወሰንየለሽ መንገሻ ደግሞ የአልጋወራሽ አስፋወሰን ባለቤት ልዕልት መድፈሪያሽ ወርቅ አበበን ወልደዋል። ሌላው የአድዋ ጀግና የጦር መሪ ራስ መንገሻ ዮሐንስ (አባ ግጠም) ናችው። ትውልዳቸው ትግራይ፣ ዘመኑም 1857 ዓ.ም ነው። የአድዋ ጦር ውሎ ቁልፍ ሰው ራስ መንገሻ የአጼ ዮሐንስ (አባ በዝብዝ) ልጅ ናቸው። አጼ ዮሐንስ በተሰዉበት በመተማው ጦርነት ተሳትፈዋል። አባታቸው ከሞቱ በኋላም የትግራይ አገረ ገዥ ሆነዋል። በአድዋ ዘመቻ 12 ሺህ ጦር አሰልፈው በብርቱ ተዋግተዋል። ራስ መንገሻ ዮሐንስ ከአድዋ ጦርነት ቀደም ብሎ በአጼ ምኒልክ ላይ እንዲያምጹ ኢጣሊያኖች ሲገፋፋቸውና ሲያባብላቸው ቢቆዩም ከስልጣን ሽኩቻ ይልቅ የኢትዮጵያን ነጻነት መርጠዋል። ከአጼ ምኒልክ ጋር ቢኳረፉም በሀገር ሉዓላዊነት ግን አልተደራደሩም። የኢጣሊያ ወራሪ ጦር ትግራይ ሲገባም ራስ መንገሻ የወገን ደጀን ጦር እስኪደርስ ወደራያ አፈግፍገው፣ በአምባላጌ ጦር ሜዳ አንዱ ተሳታፊ የጦር ጀግና ነበሩ። ራስ መንገሻ የትግራይ ሀገረ ገዥ በመሆናቸውም የእርሳቸው እና በስራቸው የነበሩት የራስ አሉላ እንግዳ ጦር በጄኔራል አልቤርቶኔ ከሚመራው ጠላት ሃይል ቀዳሚው ተፋላሚ እንዲሆኑ አድርጎታል። “አይከፈት በሩ መግቢያ መውጫችን በል ተነስ መንገሻ ግጠም በር በሩን ይህን ጎሽ ጠላ ማን አይቀምሰው መንገሻ ዮሐነስ አንተን ገፍተው...” ተብሎ የተገጠመላቸውም ለዚህ ነው። የጠላት መግቢያ በር ዘብ በመሆናቸው። አባ ግጠም በአድዋው ታሪካዊ ጦርነት አሰላለፋቸው ማርያም ሸዊቶ በተሰኘው ተራራ በኩል ሲሆን ከራስ አሉላ፣ ከዋግሹም ጓንጉል ብሩና ከደጃዝማች ሀጎስ ጋር በመሆን ነበር። የጠላትን የመጀመሪያ ጥቃትን ያስተናገዱትም ራስ መንገሻ ዮሐንስ ናቸው። የአድዋ ድል ከተበሰረ በኋላ አጼ ምኒልክ ራስ መንገሻን ሹመውና ሸልመው ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል። አጼ ምኒልክ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ሲመለሱ ማህበረሰቡ በጦርነት ስፍራ በመሆኑ ለደረሰበት ጉዳት 30 ሺህ ብር ድጋፍ ማድራገቸውን የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል የጻፉት ፀሐፊ ትዕዛዝ ገብረ ሥላሴ ወልደአረጋይ ተርከዋል። ከአድዋ ድል ከጥቂት ዓመታት በኋላ ራስ መንገሻ በአጼ ምኒልክ ላይ በማመጻቸው ተይዘው በቁጥጥር ስር ዋሉ። ሕዳር 6 ቀን 1899 ዓ.ም አንኮበር ግዞት ላይ አንዳሉ ማረፋቸውን የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ። ራስ መንገሻ ዮሐንስ ከራስ መንገሻ አቲከም ግዛት ከአገው ምድር እመይቴ ተዋበች ጋር ትዳር መስርተው ዕውቁን የትግራይ መስፍን ራስ ሥዩም መንገሻን እንዲሁም ከእቴጌ ጣይቱ የወንድም ልጅ ወይዘሮ ከፈይ ወሌ ብጡል አግብተው አስቴር መንገሻን፣ አልማዝ መንገሻንና ብርሃኔ መንገሻን ወልደዋል፡፡ ለአብነት ያክል የሞክሼዎቹን ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም እና ራስ መንገሻ ዮሐንስ አነሳን እንጂ የዛሬ የ128 ዓመት በአድዋ ጦርነት ዓለም የተደመመበትና ዛሬ ድረስ እንቆቅልሽ የሆነበት ደማቅ ታሪክ የጻፉ ጀግኖች ቁጥር ስፍር የላቸውም። ጀግኖቹን የመሩ የጦር መሪዎችም ብዙና ተጋድሏቸው የገዘፈ ነው። ከ11 ሺህ በላይ የጣሊያንን ሠራዊት ሙትና ቁስለኛ ያደረጉ፣ 4ሺህ የሚሆኑትን እጅ ያሰጡና የማረኩ እንዲሁም 56 መድፎች፣ በርካታ መትረየሶች እና ሌሎች አውቶማቲክ መሳሪያዎቹን ለወገን ጦር እንዲያስረክብ ያደረጉ ኢትዮጵያውያን ሁል ጊዜም ክብር ይገባቸዋል። የጣሊያን ወራሪ ኃይል ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት ስር አድርጎ ለመበዝበዝ ቢመጣም ጀግንነት፣ ሕብረ ብሔራዊ አንድነት፣ እንዲሁም የአልገዛም ባይነት ወኔን የታጠቁ ኢትዮጵያውያን በሶሎዳ ተራሮች ግርጌ ቅስሙን በመስበር የአገራቸውን ክብርና ነጻነት አጽንተዋል። በዚህ አኩሪ ድል ኢትዮጵያ ለበርካታ አገራት በተምሳሌትነት ትጠቀሳለች። የአድዋ ድል ደግሞ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህዝቦች የጀግንነት ተምሳሌትና የነጻነት ዓርማ እንድትሆን ያስቻለ ታላቅ አፍሪካዊ ድል ነው። (በአየለ ያረጋል)
ትላንትን ከዛሬ ባስተሳሰረው የአድዋ ድል መታሰቢያ የሚገኙ እውነታዎች
Mar 2, 2024 755
ትላንትን ከዛሬ ባስተሳሰረው የአድዋ ድል መታሰቢያ የሚገኙ እውነታዎች ለመነሻ እኤአ በ1885 ጀርመን በተካሄደው የበርሊን ኮንፈረንስ አውሮፓውያን መላ አፍሪካን በካርታ ላይ የተከፋፈሉትን በተግባር መሬት ላይ ለመቀራመት ጦራቸውን ሰብቀው፣ ስንቃቸውን ጭነውና ትጥቃቸውን አጥብቀው ያካሄዱት ዘመቻና የወረራ ጉዞ የተገታባት አድዋ እና እለቷ ዛሬ ድረስ በተገፉ ህዝቦች ልብ ታትማ በአዕምሮ ውስጥ ተቀርጻ ትኖራለች። ጣሊያን የኢትዮጵያን መሬት፣ የአየር ንብረትና መልክዓ ምድር ተቆጣጥሮ ሀብቷን ለሮምና ለመላው አውሮፓ ለማቅረብ የቋመጠበት የዘመናት ህልሙ የተኮላሸበት ቦታ ጭምር ናት - አድዋ። ይህ ወራሪ ኃይል ሊቢያን በእጁ ካስገባ በኋላ ጉዞውን በቀይ ባሕር አስመራ አድርጎ መላ ኢትዮጵያን የመቆጣጠር ግብ ነበረው። ጄነራል ባራቴሪ የመደባቸው ጄነራል አልበርቶኒ፣ ጄኔራል አሪሞንዲ እና ጄነራል ቦርሜዳ በግንባር የተሰለፈውን ጦር ሲመሩ የኋላ ደጀንም እንደነበራቸው የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። ከ17 ሺህ በላይ የጣሊያን ሠራዊት 66 የሚሆኑ መድፎች፣ በርካታ መትረየሶች እና አውቶማቲክ መሳሪያዎችን ታጥቆ የግንባር ሜዳው ላይ ስለመድረሱ "የኢትዮጵያ ታሪክ ከመጀመሪያው እስካሁኑ ዘመን" በሚል በአንድርዜይ ባርይትኒስኪ እና ዮዓና ማንቴል-ኒየችኮ ተጽፎ በዓለማየሁ አበበ የተተረጎመው መጽሐፍ ያስረዳል። የዛሬ የ128 ዓመት፤ ዕለቱም የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በአድዋ ጦርነት ዓለም የተደመመበትና ዛሬ ድረስ እንቆቅልሽ የሆነበት ደማቅ ታሪክ በጀግኖች አባቶች ተሰራ። በጦርነቱ የጣሊያን መንግስት የጎመጀውን የኢትዮጵያን መሬት ሊያገኝ ይቅርና ከ11 ሺህ በላይ ሠራዊቱ ሙትና ቁስለኛ ሆኑ። 4ሺህ የሚሆኑት ደግሞ ለጀግኖች አባቶቻችን እጃቸውን ሰጥተው ተማረኩ። እንዲሁም 56 መድፎች፣ በርካታ መትረየሶች እና ሌሎች አውቶማቲክ መሳሪያዎቹን ለወገን ጦር አስረከበ። የቀረው የፋሽስት ሠራዊትም ተንጠባጥቦ እግሬ አውጪኝ ብሎ ፈረጠጠ። ጀግኖች ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ክብር፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት በአውደ ግንባሩ በፈጸሙት የጀግንነት ተጋድሎ ዓለምን ያስደመመና መላውን ጥቁር ሕዝብ ያኮራ ድል ተጎናጽፈዋል። በወቅቱ ነጭን ታግሎ ማሸነፍ አይቻልም የሚለውን አስተሳሰብ በይቻላል ተክቶ ሌሎችም ለነፃነታቸው እንዲታገሉ ያነሳሳ ደማቅ የታሪክ አሻራ አኑረዋል። የጣሊያን ወራሪ ኃይል ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት ስር አድርጎ ለመበዝበዝ ቢመጣም ጀግንነት፣ ሕብረ ብሔራዊ አንድነት፣ እንዲሁም የአልገዛም ባይነት ወኔን የታጠቁ ኢትዮጵያውያን በሶሎዳ ተራሮች ግርጌ ቅስሙን በመስበር የአገራቸውን ክብርና ነጻነት አጽንተዋል። በዚህ አኩሪ ድል ኢትዮጵያ ለበርካታ አገራት በተምሳሌትነት ትጠቀሳለች። የአድዋ ድል ደግሞ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህዝቦች የጀግንነት ተምሳሌትና የነጻነት ዓርማ እንድትሆን ያስቻለ ታላቅ አፍሪካዊ ድል ነው። ኢትዮጵያውያን በብሔር፣ በሃይማኖት፣ በአካባቢና በሌሎች ልዩነቶች ሳይነጣጠሉ ለአገራቸው ክብርና ነጻነት በአንድነት ቆመውና መስዋት ከፍለው ያስመዘገቡት የጀግንነት ታሪክ ነው። በዓድዋ ድል ኢትዮጵያ ለአፍሪካና ለመላው የጥቁር ህዝቦች ኩራትና የነፃነት ምልክት ሆናለች፡፡ የሰው ልጆችን እኩልነት በደም ዋጋ አረጋግጣለች። የአድዋ ድል መታሰቢያ የአድዋ ድል ደማቅና ታላቅ ቢሆንም በሚመጥነው ልክ መታሰቢያ አልነበረውም። ዛሬ ግን እነዚያ ዋጋ የከፈሉ ጀግኖችን በሚመጥን ሁኔታ በአዲስ አበባ ፒያሳ “የዓድዋ ድል መታሰቢያ” ተገንብቷል። ከአድዋ ድል 128 ዓመታት በኋላ፣ የተሰራው የአድዋ ድል መታሰቢያ በጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የካቲት 3 ቀን 2016 ዓ.ም ተመርቆ ተከፍቷል። የአድዋ ድል መታሰቢያ በአምስት ሄክታር ላይ ያረፈ ሲሆን በአንድነት የተከፈለውን መስዋትነት፣ የአርሶ አደሮችን ተሳትፎ፣ የሴቶችን ተጋድሎ በሚያሳይ መልኩ፣ በአስገራሚ የኪነ-ህንጻ ጥበብ የታነጸ ነው። የአድዋ ድል መታሰቢያ የተገነባበት ስፍራ አገር በውጭ ወራሪ ኃይሎች እጅ እንዳትወድቅ የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉ የዓድዋ ጅግኖች የዘመቻቸው መነሻ እንዲሁም ከድል በኋላ ተሰባስበው ደስታቸውን የተጋሩበት ታሪካዊ ስፍራ ነው። የአድዋ ድል በዓል 7ኛ ዓመት ዳግማዊ ምኒልክ፣ ከአርበኞች፣ ከየአካባቢው ገዢዎች፣ ከውጭ አገር ዲፕሎማቶችና ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በደማቅ ሁኔታ በዚሁ ስፍራ አክብረውታል። ስፍራው ዛሬ የታላቁ የአድዋ ድል መታሰቢያ ሳይገነባበት በፊት በተለያዩ ጊዜያት ለተለያዩ የልማት ስራዎች ቢታጭም ውጤታማ ስራ ሳይሰራበት ቆይቷል። አካባቢው ለረጅም ዘመናት ታጥሮ ሳይለማ በመቆየቱ እጅግ የቆሸሸ፣ ሰዎች ለዝርፊያ የሚዳረጉበት ስፍራ ሆኖ ቆይቷል። ዘመናትን ተሻግሮ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በከተማዋ ከሚገነቡ ትላልቅ ፕሮጀክቶች በዓይነቱ ልዩ የሆነው የዓድዋ ድል መታሰቢያ እንዲሰራበት ተደረገ። የዓድዋ ድል መታሰቢያ እጅግ በሚስብ ኪነ ህንፃ፤ የኢትዮጵያውያንን ህያው የድል ታሪክ የሚዘክር ሆኖ ተሰርቷል። የአድዋ ድል መታሰቢያ መግቢያ በሮች የኢትዮጵያውያን የድል ብስራት፣ የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ኩራት የሆነው የአድዋ ድል መታሰቢያ መግቢያ በሮች የራሳቸው የሆነ ስያሜ ተሰጥቷቸዋል። የምሥራቅ ጀግኖች በር፣ የምዕራብ ጀግኖች በር፣ የሰሜን ጀግኖች በር፣ የደቡብ ጀግኖች በር፣ የፈረሰኞች በር፣ የአርበኞች በር፣ የፓን አፍሪካኒዝም በር ተብለው የተሰየሙ ናቸው። በአራቱም አቅጣጫዎች የተሰየሙ በሮች ተምሳሌትነት በዓድዋ ድል ከአራቱም አቅጣጫ ኢትዮጵያውያን በጋራ የተሳተፉበት የጋራ ድላቸው መሆኑን ያመለክታል፡፡ መታሰቢያው በውስጡ ምን ይዟል? በዋናው መግቢያ:- የኢትዮጵያውያንና አፍሪካውያን ነጻነት ድል መገለጫ የሆነው የአድዋ ድል መታሰቢያ ሃውልትና የሁሉም ከተሞች ርቀት ልኬት መነሻ የአድዋ ዜሮ ኪሎ ሜትር ምልክት ይገኛል። የዓድዋ ጦርነት ዘመቻን ያስተባበሩትና የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት የዳግማዊ አፄ ምኒልክ እና የባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ ብጡል ሀውልትም በዚሁ መግቢያ በኩል ይገኛል። ሃውልት የቆመላቸው 12 የጦር መሪዎች:- በመታሰቢያው የአድዋን ጦርነት በታላቅ ጀግንነት በመምራት ለጥቁር ህዝቦች ድል ያበሰሩ 12 ዋና ዋና የጦር መሪዎች ሃውልት ተቀምጧል፣ እነሱም፤- ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ ጉርሙ (አባ ጎራው)፣ ልዑል ራስ መኮንን ወልደ ሚካኤል ጉዲሳ (አባ ቃኘው)፣ ንጉስ ተክለሃይማኖት ተሰማ ጎሹ ( አባ ጠና)፣ ንጉስ ሚካኤል አሊ አባ ቡላ (አባ ሻንቆ)፣ ደጃዝማች ባልቻ ሳፎ ሮቢ (አባ ጠለስ)፣ ራስ ቢተወደድ መንገሻ አቲከም ቢተርፉ (አባ ገድብ)፣ ራስ ወሌ ብጡል ሃይለማሪያም (አባ ጠጣው)፣ ዋግሹም ጓንጉል ብሩ ገብረመድህን (አባ መርከብ)፣ ራስ አባተ ቧያለው ንጉሱ (አባ ይትረፍ)፣ ራስ አሉላ እንግዳ ቁቢ ( አባ ነጋ)፣ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ (ቁሴ) ዲነግዴ ሁንዱል (አባ መቻል) እና ራስ መንገሻ ዮሃንስ ምርጫ (አባ ግጠም) ናቸው። በስተቀኝ በኩል፤- እስከ 3 ሺ እንግዶችን ማስተናገድ የሚችል ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት የስብሰባ አዳራሽ የሚገኝ ሲሆን በመጀመሪያው ኮሪደር ላይ ደግሞ ህዝቡ የጦርነት ክተት አዋጅ ጥሪ ሲሰማ ሁሉም ልዩነቱን ወደ ጎን በመተው አገሩን ከወራሪ ለመታደግ በመወኔ መነሳቱን፣ ወደ ጦር ግንባር መትመሙን እንዲሁም በጀግንነት መፋለሙን የሚሳየዩ ትዕይንቶች በእስክሪኖች ይታያሉ። በክፍሉ መሐል ላይ፤- ጦርነቱ የተጎሰመበት ግዙፍ ነጋሪት የተቀመጠ ሲሆን በነጋሪቱ ግራና ቀኝ ለጦርነቱ መንስኤ የሆነው የውጫሌው ውል አንቀጽ 17፣ የአድዋ ታሪክ እንዲሁም ከድል ወደ ሰላም የሚለው የአዲስ አበባ ስምምነት ሰነድ ተዘርግቶ ይገኛል። ከድል መልስ ግልጋሎት ላይ የዋሉ ጋሻዎች፣ መሳሪያዎች፣ አልባሳት፣ መመገቢያ ቁሳቁሶችን ጨምሮ በርካታ ቅርሶች፣ ስዕሎች፣ ፎቶዎች ይገኛሉ። ወደ ውስጥ መግቢያ በሆነው በምዕራብ በር ላይ የወቅቱ የኢትዮጵያ መሪ የነበሩት አጼ ሚኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱ ብጡል ሃውልት በክብር ተቀምጦ ይገኛል። በአድዋ ጦርነት ወቅት ጠላት ለመጠጥነት ይጠቀምበት የነበረውን የምንጭ ውሃ እቴጌ ጣይቱ ብልሃት በተሞላበት መልኩ በኢትዮጵያ ሰራዊት እንዲከበብና ጠላት በውሃ ጥም እንዲዳከም በማድረግ ማሸነፍ የተቻለበት የጦር እስትራቴጂ የሚዘክር ገንዳ ከእቴጌ ጣይቱ ሃውልት ፊት ለፊት ተቀምጦ ይገኛል። የአድዋ ሰንሰለታማ ተራሮች፤- ጦርነቱ የተካሄደበትን ቦታ የሚያሳየው የአሸዋ ገበታ ሌላው የአድዋ ድል መታሰቢያ ውበትም ታሪክም ነው፡፡ የአድዋ ሰንሰለታማ ተራሮች፣ መልከዓ-ምድር የሚሳየው የመሬት ላይ ንድፍ ስራ በዚሁ መታሰቢያ መቀመጡ ኢትዮጵያውያን በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለነጻነት የከፈሉትን መስዋትነት ያመላክታል። ከተራሮች አጠገብ በጦርነት ወቅት ጥቅም ላይ ከዋሉ ጣሊያናዊ ስሪት የሆነ "ቶሪኖ 1883" የሚል ጽሁፍ ያለበት መድፍ ይገኛል። በጦርነቱ ተዋጊዎችን ያጓጓዙ 45 ሺህ ፈረሰኞች የሰሩትን ጀብድ ሊወክልና ሊዘክራቸው የሚችል ‘የአድዋ ፈረሰኞች የድል ሀውልት’ ቆሞላቸዋል፡፡ የአድዋ ጀግኖች ኢትዮጵያን ከወራሪው ጣሊያን ለማዳን ዘር፣ ቀለም፣ ሃይማኖት ሳይለዩ በአንድነት ተሰባስበው የተመሙበትን የሚወክል ‘የአንድነት ድልድይ’ በሚል ተሰርቷል፡፡ የሁሉንም ተሳትፎ የሚያሳዩ የተለያዩ ሁነቶች በጦርነቱ ወቅት ህዝብና አገርን በታማኝነት ሲያስተዳድሩ የነበሩ እንደራሴዎች የሚያሳይ ስዕላዊ በመታሰቢያ የተቀመጠ ሲሆን በጦርነቱ ወቅት የነበረውን የህዝቡን እንቅስቃሴ የሚገልጹ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችና የመገልገያ ቁሳቁሶች፣ ስዕሎችና ቅርጾችም ይገኛሉ። የገበሬዎችና ሴቶች ተሳትፎ የሚያሳዩ ስራዎች በአድዋ ጦርነት ከ120 ሺህ በላይ ገበሬዎች የግብርና ስራቸውን አቋርጠው "አገራችን ተነካች" በማለት ታጥቀው ድል ያጎናጸፉ፣ ለጥቁር ህዝቦች ትልቅ ታሪክ ያስቀመጡ ጀግኖች ናቸው። በዚህ መታሰቢያ የአንድነት ማዕከል፣ የአፍሪካ ነጻነት ማስታወሻ የኢትዮጵያ ጀግኖችን ጉዞ የሚያሳዩ ምስሎች ይገኛሉ። በጦርነት ወቅት ሴቶች የቤት ሃላፊነትን ከመወጣት በተጨማሪ በአዋጊነት፣ በመረጃ ሰጪነት ቁስለኞችን በመንከባከብ ለሰሩት ስራ የተሰየመ ማስታወሻም በአድዋ ድል መታሰቢያ በክብር ተቀምጦ ይገኛል። የአሁኑ ትውልድ አሻራ፣- የኢትዮጵያ ልጆች በአንድነት ተባብረው አፍሪካ በራሷ አቅም መልማት እንደምትችል ያሳዩበት፣ አፍሪካዊ ተምሳሌት የሆነው የህዳሴ ግድብ ፏፏቴ በመታሰቢያው ይገኛል። ኢትዮጵያውያን ለጥቁር ህዝቦች ነጻነት ላደረጉት ተጋድሎ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ የፓን-አፍሪካ ሃውልትም ተካቷል። ሌሎችም የአድዋ ድል መታሰቢያ የአድዋን ጦርነት ሁነቶች ብቻ ሳይሆን ለተለያያዩ ዝግጅቶች የሚሆኑ አዳራሾችን፣ ካፍቴሪያዎችን፣ ሲኒማ ቤቶችንና ሌሎች ለበርካታ አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችንን አካቶ የተሰራ ነው። ከ2500 በላይ እንግዶችን መያዝ የሚችል ፓን አፍሪካን አዳራሽ፣ 300 ሰዎች የሚይዝ የአድዋ አዳራሽ፣ 160 ሰዎች የሚይዝ መካከለኛ አዳራሽ፣ 300 ሰው በአንድ የሚያስተናግዱ ሬስቶራንቶች፣ ሁለት ካፍቴሪያዎችና የህጻናት ሙዚየም በውስጡ አካቷል። በሌላ በኩል በአንድ ጊዜ 1000 ተሽከርካሪ መያዝ የሚችሉ ፓርኪንግ፣ ዘመናዊ ጂምና ሌሎችም ተካተዋል። የአድዋ ድል መታሰቢያ አድዋ ጊዜ የማይሽረው፣ ዘመን የማይለውጠው የጀግንነትና የአንድነት ምልክት መሆኑን ማሳያ፣ ለነጻነት የታገሉና የተሰዉ ጀግኖች የሚታሰቡበት የታሪክ ማስታወሻ ነው። የአድዋ ድል ትሩፋቶችን ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝብ በየትውልዱ ለማስተማር የሚያግዝ የዘመናት የነጻነት መንፈስን የሚያስተጋባ፣ ለመጪው ትውልድ የሚሻገር እውነት ነው። እናም የአድዋ ድል መታሰቢያ የወል ታሪካችንን የምንገነባበት የማዕዘን ድንጋይ ነው።
ሴቶች - የአድዋ ድል ሁለንተናዎች
Mar 1, 2024 640
ሴቶች - የአድዋ ድል ሁለንተናዎች በአየለ ያረጋል "... መጨረሻም ድምሩን ስገምተው አድዋ ድል የተገኘው በሴቶች አገልጋዮችና በበቅሎዎች ብርታት መሆኑ ይታወቀኛል..." ይህን ያሉት ታላቁ ምሁር እና የአድዋ ዘማች ፊታውራሪ ተክለሐዋሪያት ተክለማርያም ናቸው። በርግጥ በአድዋ ዘመቻ ያልዘመተ የለም። የሀይማኖት መሪዎች፣ ንጉሱ፣ ንግስቲቱ፣ ገበሬው፣ አገሬው ከነማንነቱ… ገድል ፈጽሟል። በጦር ሜዳ ገድሎች የሴቶች አበርከቶ እምብዛም አይታወስም። ሴቶች የዋሉበት ግንባር አይዘከርም። ቅሉ ሴቶች በኪነ-አድዋ ያልተዘመረላቸው ‘’ደብዛዛዎቹ ጀግኖች” ናቸው። እቴጌ ጣይቱን መሰል የአድዋ ሴት የጦር ፊታውራሪዎች አሉ። አዝማሪ ጣዲቄና መሰል አዝማሪዎች የሰራዊቱ ስነ ልቦና ገንቢዎች ናችው። ሴቶች የሎጂስቲክስ አሳላጮች፣ የቁስለኛ ሀኪሞች፣ የጀግና አበርቺዎች፣ የስንቅ ሰናቂዎች፣….በጥቅሉ ሴቶች የአድዋ ድል ሁለንተናዎች ነበሩ። ለዚህ ደግሞ እቴጌ ጣይቱ ብጡል ቀዳሚ ምስክር ናቸው። እቴጌ ጣይቱ ከውጫሌ እስከ መቀሌ፣ ከእንጦጦ እስከ ማርያም ሸዊቶ መላ መቺም፣ ጦር አዝማችም ነበሩ። የዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዜና መዕዋል ከታቢ ጸሐፌ ትዕዛዝ ገብረሥላሴ ወልደአረጋይ ‘ታሪከ ዘመን ዘዳግማዊ ምኒልክ’ በተሰኘው መጽሐፋቸው የሴቶችን ሚና በተመለከተ እንዲህ ይላሉ። “እንዲህም እየሆነ፣ አጤ ምኒልክ ባዳራሹ እቴጌ ጣይቱ በእልፍኝ ባለሟሎችን ወይዛዝርቱን ይዘው ግብሩ አንድ ቀን ሳይጎድል፣ ይዘምታሉ። ከዘመቻ ላይ ጠጁ ማሩ አለመጉደሉ፣ ስለምንድነው ያልህ እንደሆነ ይህን ታሪክ መመልከት ነው። በስድስት ድንኳን እንጀራው ሲጋገር ሲያድር፣ በአራት ድንኳን ወጡ ሲሠራ ሲያድር፣ ጠጁ በቀንድ በኮዳ ደግሞ ሦስት መቶ ስድስት መቶ የሚሆን ገንቦኛ ሲጓዝ ግብሩ ይጎድል ይመስልሀል” (ገጽ-241) ፀሐፊ ትዕዛዝ ገብረስላሴ ይቀጥላሉ። “… ጥቂቱን ጻፍን እንጅ በአድዋ ጦርነት ዐይናቸን እንዳየው ጆሯችን እንደሰማው መጻፍ አይቻለንም። እቴጌ በዚያን ጊዜ በግምባርዎ ተደፍተው በጉልበትም ተንበርክከው ድንጋይ ተሸክመው እግዚአብሄር እያመለከቱ ሲያዝኑ ሲጨነቁ ነበር። … ሴት ወይዛዝርቱም የንጉሠ ነገሥቱ ልጅ ወይዘሮ ዘውዲቱም ደንገጡሮችንም ተከትለው ነበር። የኋላው ሰልፈኛ እንደመወዝወዝ ሲል ባዩ ጊዜ ቃልዎን አፈፍ አድርገው ተናገሩ። አይዞህ አንተ ምን ሆነሃል! ድሉ የኛ ነው በለው! አሉት… ጣሊያ ድል ከሆነ በኋላ ወንዱ በርኮር፣ ሴቱ በገንቦ ውሃ ያዙ ብለው አዘው ለተጠማውና ለቆሰለው ውሃ ሲያጠቱት ዋሉ። እንኳን ኢትዮጵያ ሰው የኢጣሊያው ስንኳ ቁስለኛ ከዚያ ስፍራ የተገኘ ከዚህ ከእቴጌ ካዘዙት ውሃ አልቀረበትም“ይላሉ። ከጽሁፉ መረዳት እንደሚቻለው እቴጌ ጣይቱና መሰሎቻቸው አንድም በጸሎታቸው፣ አንድም ተዋጊዎችን በማደፋፈር ወኔያቸው፣ አንድም በጦር መሪነት ሚናቸውን ተወጥተዋል። ዋናው ደግሞ ቁስለኞችን የማከምና ሰብዓዊነት ሙያቸው ነው። ፀሃፊ ትዕዛዝ ገብረስላሴ “… ሙሉ ግብር እየበላ የተጓዘ እንጂ ወታደር የስንቅ አቁማዳዉን አልፈታም“ ሲሉ የአድዋ ሴቶች ገድል ምንኛ ገናና እንደሆነ መገመት እንደሚቻል ይጠቅሳሉ። እንደ ፀሐፊ ትዕዛዝ ገብረስላሴ ስለዘመቻው አጓኳን በማስታወሻቸው እንደገለጡት ድንኳን ተካይ፤ ዕንጨት አቅራቢው፣ ወጥ ሰሪው፣ እንጀራ ጋጋሪው፣ እህል ውሃ ተሸካሚው፣ መልከኛው (አራጁ)፣ በቅሎ ጫኙ፤ ተዋጊው ሁሉም በየፊናው እንስሳቱም ሳይቀር ተደራጅቶ ዘምቷል። በርካታ የታሪክ ምንጮች የአድዋ ጦርነት ተሳታፊዎች ገሚሶቹ ሴቶች እንደሆኑ ይገልጻሉ። የታሪክ ምሁሩ ዶክተር አልማው ክፍሌ ደግሞ በአንድ ወቅት ሚዲያ ላይ ቀርበው “በአድዋ ጦርነት ዘማቾች 75 በመቶ ሴቶች ነበሩ” ብለው ነበር። በአድዋ ጦርነት ሴቶች በተለያዩ ሙያዎች ተመድበው ከካምፕ እስከ ጦር ሜዳ ከመመገብ እስከ ማጀገን፣ ከማከም እስከ መዋጋት ድንቅ ሚና ተወጥተዋል። ድርብ ድርብርብ ኃላፊነት ይዘው የዘመቱ፣ ለወንዶችም ልብ፣ ሞራልና ወኔ አቀባዮች ነበሩ። ደራሲ በዕውቀቱ ሥዩም ‘ከአሜን ባሻገር’ በተሰኘ መጽሐፉ ‘ሴቶች በዋሉበት’ በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ሴቶች ተጋድሎና ሚና “ከቁስ ባሻገር ከልብ ያቀርባሉ” ይላቸዋል። “ሴቶች ባዋላጅነት ከነበራቸው የማይተናነስ ሚና በጦር ሜዳ ተጫውተዋል። እናቶቻችን በጦር ወቅት፣ መሳሪያ ያቀርቡ ነበር። ምግብ ያቀርቡ ነበር። ሃሳብ ያቀርቡ ነበር። ልብ ያቀርቡ ነበር። ደስታ ያቀርቡ ነበር። ኧረ ምኑ ቅጡ። ሴቶች ባንድ በሙቀጫ ዙሪያ፣ ማኅበረሰቡን ኬሚስት፣ ገጣሚና የፖለቲካ ተንታኝ ሆነው ማገልገላቸውን ልብ እንበል” ይላል። (ገጽ-138) የራስ መኮንን ባለሟል የነበሩት ፊታውራሪ ተክለሐዋሪያት ተክለማሪያም ገና በ15 ዓመት ዕድሜያቸው አድዋ ዘማች ነበሩ። "የሕይወቴ ታሪክ’ (ኦውቶባዮግራፊ) በተሰኘው ግለ ታሪካቸው ከሐረር እስከ አድዋ በዘለቀው ጉዟቸው ሴቷ (አገልጋያቸው) የነበራትን ሚና ለማብራራት ቃላት ያጥርባቸውና እንዲህ ብለው የአንባቢን ህሊና ይነካሉ። “… ከቶ እሷ ባትኖር ኖሮ እንዴት እሆን ኖሯል! እያልኩ ዘወትር ሳስበው ያደንቀኛል። ዕቃ ተሸክማ ስትሄድ ትውላለች። ከሰፈርን በኋል ውሃ ቀድታ፣ እንጨት ለቅማ፣ ቂጣ ጋግራ፣ ወጥ ሰርታ፣ ታበላናለች። ወዲያውኑ እንዲዚህ ለማታ ታሰናዳለች። እንደዚህ የወለተ አማኑኤልን አገልግሎት እያሰብኩ ስደነቅ ደግሞ በየሰፈሩ እንደርሷ ስንት ሴቶች እንደሚያገለግሉ ይታሰበኛል። የሴቶቹን አገልግሎት ስገምት ደግሞ የበቅሎዎች አገልግሎት ይታወሰኛል። በመጨረሻም ድምሩን ስገምተው አድዋ ድል የተገኘው በሴቶች አገልጋዮችና በበቅሎዎች ብርታት መሆኑ ይታወቀኛል። ሁሉንም አያይዥ በደምሳሳው ስመለከተው የኢትዮጵያን መንግስት ነጻነቱን ጠብቀው፤ እዚህ አሁን የደረስንበት ኑሮ ያደረሱት እነዚህ የዘመቻ ሃይሎች መሆናቸውን አልስተውም። የኢትዮጰያ መንግስት የተባለው ተቋም፣ ላገልጋዮቹ ውለታ ምላሽ ሆኗል ወይ? የዚህን ምላሽ ለመስጠት ሳስበው እልቅ የሌለው መንገድ ይገጥመኛል። ሲሄዱ መኖር ይሆንብኛል። የማልዘልቀው እየሆነብኝ፣ እየተከዝኩ እተወዋለሁ” በማለት በቁጭት ጽፈዋል። በርግጥም ሴቶች በኪነ-አድዋ በልካቸው ያልተዘመረላቸው፣ ‘’ደብዛዛዎቹ ጀግኖች” ናቸው።
በአጭር ጊዜ ትልቅ እመርታ በሌማት ትሩፋት
Feb 6, 2024 1440
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል የምግብ ዋስትናን ለማረጋጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን የተመለከቱ ጥያቄዎች ይጠቀሳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ በግብርና ልማት በተለይም በስንዴ ላይ እየተሰራ ያለው ስራ በምግብ እራስን ለመቻል ለሚደረገው ጥረት ውጤታማነት ትልቅ ድርሻ እንዳለው አብራርተዋል። በግብርና ልማት እየተከናወኑ ባሉ ውጤታማ ስራዎች ላይ የሌማት ትሩፋት ተግባራት ሲታከሉ ከምግብ ዋስትና ባለፈ ስርአተ ምግብን በማስተካከል ረገድ አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል። ለመሆኑ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ስርአተ ምግብን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት ውስጥ የሚኖረው ፋይዳ እንዴት ይታያል? በእስካሁኑ አካሄድስ ምን ውጤቶች ተገኙ? ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ ‘የሌማት ትሩፋት’ መርሃ ግብርን ካስጀመሩ በኋላ በመህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ሌማት አርሶ አደሩን፣ አርብቶ አደሩን እና ሸማቹን የሚያገናኝ ድልድይ መሆኑን ገልጸው ነበር። በወቅቱ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በቂ እና አመርቂ ምግብ ማግኘት መሆኑን ገልጸው በቂ የመጠን፣ አመርቂ የይዘት ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል። አክለውም በምግብ ራስን መቻል ከሀገር ሉዓላዊነትና ክብር ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳለው ገልጸዋል። የሌማት ትሩፋት መርኃ-ግብር ዓላማ የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥና ክብርን ማስጠበቅ ሲሆን በተለይም ስጋ፣ እንቁላል፣ ማር እና ወተት ትርፍ ምርት ሆነው እንዲገኙ ማልማትና መጠቀምን መሰረት ያደረገ ነው። መርኃ-ግብሩ የኢትዮጵያን ደካማ የአምራችነት ታሪክ በመቀየር የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና የኢኮኖሚ እድገትን የማፋጠን ግብ የሰነቀ መሆኑ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሌማት ትሩፋት ዘመቻው በቤተሰብ፣ ብሎም በሀገር ደረጃ በምግብ ራሳችንን ለመቻል የምናደርገውን ጥረት የሚያፋጥን ነው ብለዋል። የወተት፣ የዶሮ፣ የዕንቁላል፣ የማር፣ የዓሣ እና የሥጋ ምርቶችን ለማሻሻል ሀገራዊ የመንግሥት ፕሮግራም ሆኖ ከጥቅምት 2015 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት በብዙ መልኩ ውጤት እያስገኘ ነው። በእርግጥም የሌማት ትሩፋት በአንድ ዓመት ጉዞው በተለይ በወተት፣ በእንቁላል፣ በዶሮና ስጋ ምርት መጠን አርሶ አደሩን፣ አርብቶ አደሩን እና ሸማቹን የሚያገናኝ ድልድይ መሆኑ የተረጋገጠበት ውጤት ተመዝግቧል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም በ2015 ዓ.ም፣ የወተት፣ የዶሮ እና የሥጋ ምርት መጠን በዕቅዱ መሠረት ጥሩ ውጤት ማምጣቱንና በተያዘው ዓመትም በበለጠ ለማሳካት የሁሉም ጥረት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። የግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና አሣ ሃብት ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ጽጌረዳ ፍቃዱ በሌማት ትሩፋት መርኃ-ግብር በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች በማር፣ በወተትና በዶሮ ልማት ከ20 ሺህ በላይ መንደሮችን በመለየት ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ለኢዜአ ገልጸዋል። ለአብነትም በወተት ልማት በተሰሩ ስራዎች 6 ነጥብ 9 ቢሊዮን ሊትር የነበረውን የማምረት አቅም ወደ 8 ነጥብ 6 በሊዮን ሊትር ከፍ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። በመጪዎቹ ዓመታትም ወደ 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን ሊትር ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በእንቁላል ምርት ውጤታማ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው የጫጩቶች ስርጭት ከነበረበት 26 ሚሊዮን ወደ 42 ሚሊዮን ማደጉን ተናግረዋል። የሌማት ትሩፋት መርኃ- ግብር የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን የሚናገሩት የግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና አሣ ሃብት ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ጽጌረዳ ፍቃዱ በእንስሳት ሃብት ልማት ብቻ በዓመት ለ259 ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም ለዘርፉ ትኩረት ባለመሰጠቱ ምክንያት አመርቂ ውጤት ሳያገኝ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን፤ ዘርፉ በቅንጅት ከተመራ፣ በቴክኖሎጂ ከታገዘ የምግብ አማራጭን ማብዛት ይቻላል። ወተት፣ ማር፣ ስጋ እና እንቁላል መሰል የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በገበያ ላይ ማትረፍረፍ፣ የሌማቱ በረከት ማብዛት የሚለው የብዙሃኑ እምነት ነው። የምግብ ዋስትና ጉዳይ ከተመጣጠነ ምግብ ጋር ያለው ቁርኝት የማይነጣጠል በመሆኑ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ፋይዳው ብዙ ነው። በሌማት ትሩፋት ገበታን በተመጣጠነ ምግብ መሙላት ከተቻለ የእናቶችንና የህጻናትን ፍላጎት በማሟላት በአካል የዳበረና በአዕምሮ የበለጸገ ትውልድ መገንባት ይቻላል። በተቃራኒው ያልተመጣጠነ አመጋገብ ጤና ላይ ከሚፈጥረው ችግር ባለፈ በሰዎች መካከል ያለውን የኑሮ አለመመጣጠን በማስፋት፣ ማህበራዊ ቀውስን በመፈልፈልና ኢኮኖሚውን በመጉዳት ምርትና ምርታማነትን ወደ ኋላ የሚጎትት ይሆናል። ይህ ደግሞ እንደ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት በከባድ ትግል ላይ የሚገኙ ሀገራትን የልማት ግስጋሴ በመግታት ቀድሞ ወደነበሩበት የድህነት አረንቋ እንዲመለሱ ያደርጋቸዋል። በኢትዮጵያ ከሚገኙና እድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች ከሆኑ ህፃናት ከ30 በመቶ በላይ የሚሆኑት በዕድሜያቸው ልክ ዕድገት የማያስመዘግቡ ወይም የመቀንጨር ችግር ያለባቸው መሆናቸውን መረጃዎች ያመላክታሉ። ለዚህ ነው በምግብ ራስን ከመቻል ጎን ለጎን የተመጣጠነ ምግብን ተደራሽ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ የሚሆነው። በዚህ ረገድ የሌማት ትሩፋት እየተጫወተ ያለው ሚና ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም። የተለያዩ ምግቦችን በገበታ ላይ ማካተት የሚያስችል ስልጠናን ከተግባራዊ የልማት ስራዎች ጋር ያካተተ ሲሆን አዲስ የአመጋገብ ባህልን የሚያለማምድ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ ለተሰሩ ስራዎችና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ላሳዩት የአመራር ቁርጠኝነት በተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያ ተሸልመዋል። ሽልማቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ አመራር እና ቁርጠኝነት፣ ብሎም ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ ዕውቅና ለመስጠት የተበረከተ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ረሀብን ዜሮ ለማድረስ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ብቻ ሳይሆን የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ሀገራዊ ብልጽግናን እውን እንደምታደርግ ገልጸዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የተሰሩት ስራዎች ለመጪው ትውልድ ጥሩ መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያን ለአብነት አንስተዋል። የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ጉዟችንን በፅናት እናስቀጥላለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግብርና ስራችን የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ የተመጣጠነ ምግብን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል። የሌማት ትሩፋት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር የኢኮኖሚ ሉዓላዊነቷን ያስከበረች ነጻ አገር እውን ማድረግን ያለመ መሆኑን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አመራሩ ይህንን ተገንዝቦ እንዲሰራ አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ህልም የሚመስሉ በርካታ አገራዊ ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ የቻለችው በዜጎቿ የተባበረ ክንድ መሆኑ እሙን ነው። ከዚህ አኳያ በምግብ ራስን ከመቻል በላይ የኢትዮጵያን የአምራችነት ታሪክ የመቀየር ግብ ለሰነቀው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር ስኬታማነት ከመቼውም ጊዜ በላይ በትብብር መስራት ይጠበቃል።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 8203
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 13285
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት። እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
በጂንካ ከተማ የተመረተው 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው የስኳር ድንች "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል ተመዘገበ
Mar 13, 2023 6593
ጂንካ መጋቢት 4/2015 (ኢዜአ):- በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር የተመረተው እና 23 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ስኳር ድንች በአፍሪካ የድንቃ ድንቆች መዝገብ "በአፍሪካ ትልቁ ስኳር ድንች" በሚል መመዝገቡ ተገለጸ። በአዲስ አበባ በተካሄደው የእውቅና ስነስርዓት ላይ የአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አለም ለስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜአለው የእውቅና ምስክር ወረቀት አስረክበዋል። ከዚህ ቀደም በአፍሪካ 10 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መቅረቡን አቶ አሸናፊ ለኢዜአ ገልጸዋል። “ነገር ግን 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች በአፍሪካ ደረጃ ሲቀርብ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው” ብለዋል። በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ 37 ኪሎ ግራም የሚመዝን ስኳር ድንች መመዝገቡንና በደሙዝ ሰፈር የተገኘው ስኳር ድንች በ14 ኪሎ ግራም ዝቅ ብሎ ከዓለም የ”ሁለተኛነት” ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው አመልክተዋል። የስኳር ድንቹ ባለቤት አቶ ኢሳያስ ጊዜያለው ስኳር ድንቹ በአፍሪካ ድንቃ ድንቆች መዝገብ ላይ በመስፈር የኢትዮጵያን ስም በማስጠራቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል። ስኳር ድንቹ እውቅና እንዲያገኝ የዜና ሽፋን ለሰጠው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምስጋቸውን አቅርበዋል። ኢዜአ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም “በጂንካ ከተማ ደሙዝ ሰፈር 23 ኪሎ ግራም የሚመዝን አንድ የስኳር ድንች መመረቱ ተገለጸ” በሚል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና አገኙ
Mar 9, 2023 7566
አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 30/2015 የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤና ልማት ዘርፍ በሴት አመራርነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው በአፍሪካ ዓለም አቀፍ የጤና አጀንዳ ኮንፈረንስ (AHAIC)2023 ላይ እውቅና ተሰጣቸው። ሚኒስትሯ በሩዋንዳ ኪጋሊ ትላንት በተካሄደው Africa Health Agenda International Conference (AHAIC) 2023 ላይ የተበረከተላቸውን Women in Global Health Award የእውቅና ሽልማት በተወካያቸዉ በኩል ተቀብለዋል። እውቅናው በጤና ልማት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቋቋምና በመፍታት፣ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ላይ ትኩረት ሰጥተው ለሚሰሩ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑም ተመላክቷል። ለመጪዎቹ ትውልዶች አርዓያ ለሆኑ የአፍሪካ ሴት መሪዎች የሚሰጠው ሽልማቱ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰም ለዜጎች የተሻለና ዘላቂ ጤናን ለማምጣት በሚደረግ ጥረት ውስጥ ላበረከቱት የላቀ የመሪነት ሚና ከአምሪፍ ሄልዝ አፍሪካ እውቅናውን አግኝተዋል።
መጣጥፍ
በድላችን ሐውልት ክላሽንኮቭ መሳሪያ ይዘው ሐውልት የተቀረጸላቸው የካራማራው ዘማች አቶ በቀለ ገመቹ
Mar 5, 2024 568
አቶ በቀለ ገመቹ ወይም በቅፅል ስማቸው አሚኮ ይባላሉ፤ በሙያቸው ኤሌክትሪሺያን ናቸው። በ1969 ዓ.ም በዚያድባሬ የሚመራው የሶማሊያ አገዛዝ ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ሀገር ስትደፈር ቁጭት ተሰምቷቸው ወደ ጦር ሜዳ መዝመታቸውን ይናገራሉ። ጦር ሜዳ ከመዝመታቸው ባሻገር የኤሌክትሪክ ባለሙያ በመሆናቸው "በራ በራ የድል ጮራ" የተሰኘውን ዓርማ በመቅረጽ በ14ቱ ክፍላተ ሀገር እንዲበራ ማድረጋቸውንም ያነሳሉ። በዚህም ከወቅቱ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም እና ከኩባው ፕሬዝዳንት ፊደል ካስትሮ መሸለማችውን ያወሳሉ። ታንክ ማራኪው አሊ በርኬ ጓደኛቸው እንደሆኑ የሚናገሩት አቶ በቀለ፤ በተለያዩ ዐውደ ግንባሮች መሳተፋቸውን አስታውሰዋል። አቶ በቀለ ጥቁር አንበሳ በሚገኘው የኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት ፓርክ በሚገኘው የድላችን ሐውልት ላይ ክላሽንኮቭ መሳሪያ ይዘው ሐውልት ተቀርጾላቸዋል። ሐውልት እንዲቀረጽ የተደረገበት ፎቶግራፍ በያኔው ሶስተኛው አንበሳው ክፍለ ጦር በኋለኛው ምሰራቅ ዕዝ በር ላይ በቀኝ እጃቸው መሳሪያ ከፍ አድርገው ይዘው የተነሱት ፎቶ ግራፍ እንደሆነ ገልጸው፤ በዚህም ደስተኛ እንደሆኑ ይናገራሉ። ከእርሳቸው ጎንም መንበረ የምትባል ሌላ ኢትዮጵያዊ ዘማችና መትረጊስ ተኳሽ ሴት ባደረገችው አስተዋፅኦና በደረሰባት አካል ጉዳት ሐውልት እንደተቀረጸላት ያነሳሉ። የካራማራ ድል ታላቅ ድል ነው የሚሉት አቶ በቀለ ገመቹ፣ በርካታ ኢትዮጵያውያን መስዋዕትነት ከፍለውበት የተገኘና ሀገርን ያስከበረ መሆኑንም ይገልጻሉ። የካራማራ ዘማቹ አቶ በቀለ ገመቹ አሁናዊ ኑሯቸው ችግር ላይ እንደሚገኙና ድጋፍ እንደሚሹም ተናግረዋል። ሶማሊያን ለ21 ዓመታት ያስተዳደሩት ዚያድባሬ 'ታላቋን የሶማሊያ ሪፐብሊክ ለመመስረት' በሚል "ድንበራችን እስከ አዋሽ ይደርሳል" እያሉ በመዛት የጦርነት ነጋሪት መጎሰማቸው የሚታወስ ነው። ይሄን እውን ለማድረግ በ1969 በኢትዮጵያ ላይ ግልጽ ወረራ ፈጸሙ። የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ.ም የኢትዮጵያ ጦር የእብሪተኛውን የዚያድባሬ ጦር ካራ ማራ ላይ ድል አደረገ፤ የኢትዮጵያ አሸናፊነትም በአደባባይ ታወጀ። ድሉ በየዓመቱ የካቲት 26 ቀን የሚታሰብ ሲሆን ዘንድሮም 46ኛ ዓመቱ ላይ ደርሷል።
የአፍሪካ ዋንጫን በመሀል ዳኝነት የመራችው ብቸኛዋ ሴት ዳኛ
Jan 28, 2024 1677
በይስሐቅ ቀለመወርቅ እንደ መነሻ፡- በእግር ኳስ ውድድሮች የመሃል ዳኝነቱን ቦታ በብዛት የሚይዙት ወንዶች ሲሆኑ፤ አሁን ላይ አልፎ አልፎ ሴቶች ትልልቅ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን ሲዳኙ አስተውለናል። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2022 በኳታር አስተናጋጅነት በተከናወነው 22ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ፤ ፈረንሳዊቷ ስቴፋኒ ፍራፓርት፤ ኮስታሪካ እና ጀርመን ያደረጉትን ጨዋታ በመሀል ዳኛነት መርታለች። በዚህም በወንዶች ዓለም ዋንጫ ታሪክ በመሀል ዳኝነት የእግር ኳስ ጨዋታን የመራች የመጀመሪያዋ ሴት በመሆን ታሪክ ሰርታለች ። ዘንድሮ ደግሞ በኮትዲቯር አስተናጋጅነት እየተከናወነ በሚገኘው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ሞሮኳዊቷ ቦችራ ካርቡቢ፤ ውድድሩን እንዲመሩ ከተመረጡት 32 የመሀል ዳኞች መካከል ብቸኛዋ ሴት ናት። በዚህም በውድድሩ በጊኒ ቢሳውና በናይጄሪያ መካከል የተከናወነውን ሦስተኛ የምድብ ጨዋታ፤ በመሀል ዳኝት በመምራት፤ ታሪክ ጽፋለች። የሞሮኮ ዓለም አቀፍ ማኅበር የእግር ኳስ ዳኛ የሆነችው ቦችራ ካርቡቢ፤ በወንዶችም ሆነ በሴቶች አህጉራዊ የእግር ኳስ ውድድሮች ላይ በርካታ የመጨረሻ ምዕራፍ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን ዳኝታለች። 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫን ብቸኛ የሴት ዳኛ ሆና የመራችው ቦችራ ካርቡቢ ማናት? ቦችራ ካርቡቢ በሞሮኮ ሰሜናዊ ክፍል በምትገኘው "ታዛ" ከተማ፤ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1987 ተወለደች። የዘር ግንዷ በሰሜን ምሥራቅ ሞሮኮ ከሚገኙት ሪፊያን ከሚባሉት የበርበር ጎሳ ዝርያ ካላቸው ሕዝቦች የሚመዘዝ ሲሆን፤ ለቤተሰቦቿ አምስተኛና የመጨረሻ ልጅ ነች። ገና በልጅነቷ ለእግር ኳስ ፍቅር ያደረባት ቦችራ ካርቡቢ፤ ኳስ መጫወት የጀመረችው በአንድ ትንሽ የወጣቶች ቡድን ውስጥ ነበር። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2001 በተወለደችበት ከተማ "ታዛ"፤ ለወንዶችና ለሴቶች የእግር ኳስ ዳኝነት ሥልጠና የሚሰጥበት ትምህርት ቤት ተከፈተ ። ይኼ ትምህርት ቤት ቀልቧን የሳበው ቦችራ፤ ሥልጠናውን መውሰድ ጀመረች። "እግር ኳስን እወዳለሁ፤ ራሴንም ላስተምር ፈለኩ።ለምን አላደርገውም ብዬ ፍላጎቴን በመከተል የእግር ኳስ ጨዋታን ደንብ መማር ጀመርኩ" ስትል የእግር ኳስ ዳኝነት ትምህርት የጀመረችበትን ጊዜ ታስታውሳለች። ይኼ ድርጊቷ ካልተዋጠላቸውና፤ በበጎ ጎኑ ካልተመለከቱት ውስጥ ደግሞ፤ ወንድሞቿ ቀዳሚዎች ነበሩ። "በምኖርበት ከተማ አንድ ሴት አጭር ቁምጣ ለብሳ ከወንዶች ጋር ሥልጠና ስትወስድ መታየቷ፤ እንደ አሳፋሪ ድርጊት ስለሚታይ መነጋገሪያ ሆኜ ነበር" ትላለች። የቦችራ ካርቡቢ የዳኝነት ጉዞ እንደ አውሮፓውያን ቆጣጠር በ2007፤ ሞሮኮ ብሔራዊ የሴቶች እግር ኳስ ሻምፒዮናን ጀመረች። ይህ መሆኑ ቡችራ ካርቡቢ ብሔራዊ ዳኛ እንድትሆን ዕድል የፈጠረላት ሲሆን፤ መኖሪያዋንም ከትውልድ ሥፍራዋ "ታዛ" ወደ ሞሮኮ ሌላኛዋ ከተማ "ሚከንስ" እንድትቀይር አደረጋት። "ይህን ዕድል ማግኘቴ ቤተሰቦቼ እንዲረዱኝና ሙያዊ ለሆነ ጉዳይ እንደምሄድ እንዲያምኑ አድርጓቸዋል" በማለት የዳኝነት ሙያዋን በመጨረሻ እንደተቀበሉት ታስረዳለች። በሚከንስ ከተማ በእግር ኳስ ዳኝነት ሥልጠና ላይ እያለች፤ አንድ ቀን አባቷ መጥቶ እንደተመለከታትና፤ ወንድሞቿ ምርጫዋን ሊያከብሩላት እንደሚገባ እንደነገራቸውም ገልፃለች። የ19 ዓመት ወጣት እያለችም፤ በሞሮኮ የሴቶች አንደኛ እና ሁለተኛ የሊግ ውድድር በመዳኘት፤ የዳኝነት ሥራዋን አንድ ብላ ጀመረች። ይህ ከሆነ ከ10 ዓመት በኋላ፤ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2016 ደግሞ፤ ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ዳኛ በመሆን ራሷን ወደ ሌላ ምዕራፍ አሸጋገረች። ከሁለት ዓመት በኋላም በ2018 በጋና አስተናጋጅነት በተከናወነው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ፤ በዛምቢያና በኢኳቶሪያል ጊኒ መካከል የተደረገውን ጨዋታ በመሀል ዳኝነት አጫወተች። ይህም በአህጉራዊ የውድድር መድረክ ለመጀመሪያ ጊዜ በመሀል ዳኝነት ያጫወተችው ጨዋታ ሆኖ ተመዘገበላት። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2020፤ "ቦቶላ" እየተባለ በሚጠራው በሞሮኮ የወንዶች ከፍተኛ የሊግ ውድድር ላይ በመሀል ዳኝነት በመዳኘት፤ የመጀመሪያዋ ሴት ሆነች ። ከአንድ ዓመት በኋላም በካሜሮን አስተናጋጅነት በተከናወነው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ፤ ሴኔጋልና ግብፅ ባደረጉት የፍፃሜ ጨዋታ የቫር ዳኛ (video assistant referee) በመሆን ሰርታለች። ከዛሬ ሁለት ዓመት በፊትም የሞሮኮ የንጉሱ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታን በመዳኘትም ቀዳሚዋ ሴት ናት። አሁን ላይ እየተከናወነ ባለው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ወድድርም፤ በጊኒ ቢሳውና በናይጄሪያ መካከል የተከናወነውን ሦስተኛ የምድብ ጨዋታ በመሀል ዳኝት በመምራት፤ የመጀመሪያዋ ሰሜን አፍሪካዊት የአረብ ሴት ሆናለች። ቡችራ ካርቡቢ ከእግር ኳስ ዳኝነት ሥራዋ በተጨማሪ፤ የፖሊስ ኦፊሰር በመሆን ሀገሯን እያገለገለች ትገኛለች።