ቀጥታ፡

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ምድረገነት ሽሬን በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሶስተኛ ከፍ አደረገ

አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 16/2018 (ኢዜአ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 11 ሳምንት መርሐ-ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ምድረገነት ሽሬን 1 0 አሸንፏል።

በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቤል ሀብታሙ 95ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት ተጠባቂ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ

የአፍሪካ ዋንጫ እና ሽልማቱ


 

በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ድሉን ያስመዘገበው ኢትዮ ኤሌክትሪክ 20 ነጥብ ደረጃውን ከአራተኛ ወደ ሶስተኛ ከፍ አድርጓል።

በአንጻሩ በሊጉ ሶስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ምድረገነት ሽሬ 14 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም