ቀጥታ፡

በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 2/2019 (ኢዜአ):- በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የመጀመሪያ ቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሱዳኑን ሂላል አል-ሳሂልን 2 ለ 1 አሸንፏል።

በድሬዳዋ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ካርሎስ ዳምጠው በ50ኛው እና በ56ኛው ደቂቃ ግቦቹን አስቆጥሯል።

ኢንሳ ሰኢድ ለሂላል አል-ሳሂል ጎሉን ከመረብ ላይ አሳርፏል።

ሁለቱ ቡድኖች በድምር ውጤት ሶስት አቻ መሆናቸውን ተከትሎ ጨዋታው ወደ መለያ ምት አምርቷል።

በዚህም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በመለያ ምት 4 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ሁለተኛ ዙር ማጣሪያ አልፏል።

ወልዋሎ በሁለተኛው ዙር ከዛንዚባሩ ኬኤምኬኤም እና ከሊቢያው አል አህሊ ትሪፖሊ አሸናፊ ጋር ይጫወታል።

አል አህሊ ትሪፖሊ በመጀመሪያው ጨዋታ 3 ለ 0 ያሸነፈ ሲሆን የመልሱ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ ይደረጋል።

ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በአህጉራዊ መድረክ ሲሳተፍ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

የውድድሩ ተሳትፎውን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ዋንጫ ማሸነፉን ተከትሎ ነው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም