ቀጥታ፡

ማንችስተር ዩናይትድ እና ባየር ሙኒክ  ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ትናንት ማምሻውን አራት ጨዋታዎች ተካሄደዋል።

በኦልትራፎርድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድ ሳባህን 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል።

ማትያስ ኩንያ፣ ብሩኖ ፈርናንዴዝ፣ ቤንጃሚን ሼሽኮ እና ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

ባለሜዳው ማንችስተር ዩናይትድ ብልጫ ወስዶ ተጫውቷል።

የአዘርባጃኑ ሳባህ በውድድሩ ላይ ሲሳተፍ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

በሌላኛው መርሐ ግብር ባየር ሙኒክ ቦዶ ግሊምትን 5 ለ 0 ረትቷል።

ማይክል ኦሊሴ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ጀማል ሙሲያላ፣ ሃሪ ኬን እና አልፎንሶ ዴቪስ ቀሪዎቹን ጎሎች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል።

የጀርመኑ ክለብ በመጀመሪያ አጋማሽ ከተጋጣሚው ፈተና ቢገጥመውም በሁለተኛው ክፍለ ጊዜ ግቦቹን በማስቆጠር ማሸነፍ ችሏል።




በሻምፒዮንስ ሊጉ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተሳተፈ የሚገኘው የጣልያኑ ክለብ ኮሞ አርቢ ላፕዚግን 4 ለ 1 አሸንፏል።

ሌንስ ስላቪያ ፕራግን 3 ለ 2 ማሸነፍ ችሏል።

ትናንት አስቀድመው በተደረጉ ጨዋታዎች ፊነርባቼ ከሮማ ፣ ፒኤስቪ ከሻካታር ዶኔስክ በተመሳሳይ አንድ አቻ ተለያይተዋል።

ጨዋታዎቹን ተከትሎ የመጀመሪያ ዙር መርሐ ግብር ተጠናቋል።

ሁለተኛ ዙር የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም መግቢያ ይካሄዳሉ።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም