ቀጥታ፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአፍሪካ ሕብረት ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ ፤ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ24ኛ የአፍሪካ ሕብረት ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ጀምሮ እስከ አሁኑ የአፍሪካ ሕብረት ድረስ በአህጉሪቱ ጉዞ ውስጥ ጽኑ ድምፅ ሆና የቆየችና አሁንም ያለች ሀገር ነች፤ አዲስ አበባም የአህጉራዊ ሕብረታችን መኖሪያ ሆና ታገለግላለች ብለዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም