ቀጥታ፡

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጸደቀ

ጋምቤላ፤ ነሀሴ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ኡማን አሙሉ (ዶ/ር) የክልሉን  የ2019 ረቂቅ በጀት  ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።


 

የክልሉ የ2019 በጀት ዓመት የስራ ዕቅድ ማስፈፀሚያ 18 ቢሊዮን 577 ሚሊዮን 523 ሺህ 685 ብር ረቂቅ በጀት መሆኑን ለጉባኤው በዝርዝር አቅርበዋል ።

በጀቱ ከክልሉ ከሚሰበሰብ ገቢና ከፌዴራል መንግስት የሚሸፈን መሆኑን አመልክተዋል ።


 

ምክር ቤቱ  በረቂቅ በጀቱ ላይ ተወያይቶ አጽድቋል ።

 

 

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም