ጨፌ ኦሮሚያ 11ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ - ኢዜአ አማርኛ
ጨፌ ኦሮሚያ 11ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ ጨፌ ኦሮሚያ 6ኛ የስራ ዘመን 5ኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአዳማ ገልመ ጨፌ ማካሄድ ጀምሯል።
ጉባኤው የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫዎች እንዲሁም በበጀት ዓመቱ በተከናወኑ የሰላምና የልማት ሥራዎች ላይ በጥልቀት በመምከር ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሏል።
በተጨማሪም የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የጠቅላይ ኦዲት መስሪያ ቤት ሪፖርቶችን መርምሮ ያጸድቃል ተብሎም ይጠበቃል።
እንዲሁም የ2019 ዓ.ም የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቅድ ማስፈጸሚያ በጀትን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት መክሮ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።