ቀጥታ፡

በአረንጓዴ አሻራው በመዲናዋ 6 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅደን እየሰራን እንገኛለን-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 6 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅደን እየሰራን እንገኛለን ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች ዛሬ ከጽ/ቤታቸው አመራሮችና ሰራተኞች ጋር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በኤአይ( AI) ዩኒቨርሲቲ አካሂደዋል።


 

በዚህም በዘንድሮው ክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በከተማችን 6 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅደን እየሰራን እንገኛለን ነው ያሉት።

የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ሰኔ 7/2018 ዓ.ም አስጀምረን እስካሁን 4 ሚሊዮን 469 ሺህ 710 ችግኞችን ተክለናል ብለዋል።


 

የችግኝ ተከላ አፈፃፀሙም 75 በመቶ ደርሷል ያሉ ሲሆን ችግኝ መትከል ብቻውን ከምናልመው ግብ ስለማያደርሰን የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራም እንሰራለን በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም