ቀጥታ፡

የዜጎችን አኗኗር ምቹ እና ዘመናዊ ማድረግ የኮሪደር ልማት መርሃ-ግብራችን ዋነኛ ግብ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሰኔ 26/2018 (ኢዜአ)፦የዜጎችን አኗኗር ምቹ እና ዘመናዊ ማድረግ የኮሪደር ልማት መርሃ-ግብራችን ዋነኛ ግብ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።


 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ያየነው የአርባ ምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት፤ ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ እና መብራቶችን እና ዲጂታል ስክሪኖችን ያካተተ ሲሆን በተጠናቀቁት የኮሪደር ስራዎች ላይ አገልግሎቱ ተጀምሯል ብለዋል።


 

‎ጥራቱን የጠበቀ ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን ከአረንጓዴ ልማት ጋር በማስተሳሰር የከተሞቻችንን ምቹነት የማረጋገጥ ስራችን ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።


 

በመሆኑም የዜጎችን አኗኗር ምቹ እና ዘመናዊ ማድረግ የኮሪደር ልማት መርሃ-ግብራችን ዋነኛ ግብ ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም