ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሊያው ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሊያው ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ መሐሙድ ጋር በሁለትዮሽ ሀገራዊ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
በውይይታቸው ወቅትም፤ በኢኮኖሚያዊ ትሥሥር፣ በሰላምና ደኅንነት እንዲሁም በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ መምከራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስታውቀዋል።
ሀገራቱ የሚጋሩት ከድንበር ያለፈ ሕዝቦቻቸውንና መፃዒ መዳረሻቸውን ጭምር መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት።