ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ በይፋ አስጀመሩ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ በይፋ አስጀመሩ
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት
የክረምቱ ወቅት ሲደርስ፣ እኛም ለወገኖቻችን የምንዘረጋው የደግነት እጅ አብሮ ይጀግናል ሲሉ ገልጸዋል።
በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ ጎሮ ወረዳ የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ ዛሬ በይፋ ማስጀመራቸውን ጠቁመዋል።
የገጠር ኮሪደር ልማት መርሃ-ግብር አካል በሆነው ዲዛይን መሠረት 20 ቤቶች በአካባቢው እንደሚገነቡ አመልክተዋል።
ሀገራችንን በጋራ ማንሳት የምንችለው አንዳችን ለሌላችን እጃችንን ስንዘረጋ ብቻ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለሆነም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በዚህ ሥራ እንዲሳተፍ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።