ቀጥታ፡

የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሐቆች

👉የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስጀምረውታል።

👉የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ከባሕር ጠለል በላይ በ1 ሺህ 910 ሜትር ከፍታ ላይ እየተገነባ ይገኛል።

👉በዓመት እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ ዐቅም አለው።

👉አሁን ካለው የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የማስተናገድ ዐቅም ጋር ሲነጻጸር በ4 ነጥብ 4 እጥፍ ብልጫ ይኖረዋል።


 

👉‎ይህ ታሪካዊ ፕሮጀክት፣ ሀገራችንን ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ማዕከላት ተርታ ለማሰለፍ ሌሊትና ቀን በከፍተኛ ጥረት እየተገነባ ይገኛል።

👉የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአቪዬሽን መሠረተ-ልማት ፕሮጀክት ነው።

👉የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታው የሚከናወነው በሁለት ምዕራፍ ነው።

👉የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ 60 ሚሊየን መንገደኞች የማስተናገድ ዐቅም በመያዝ እንደ አውሮውፓውያን አቆጣጠር በ2030 እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

👉በዚህ ምዕራፍ አንድ እጅግ ትልቅና ዘመናዊ እንዲሁም አንድ መለስተኛ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናሎች ይገነባሉ።

👉በተጨማሪም በመጀመሪያው ምዕራፍ ሁለት በተጓዳኝ የሚሠሩ የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች እንዲሁም 180 አውሮፕላኖችን በአንድ ጊዜ ማቆም የሚያስችል ቦታ ይገነባል።


 

👉በዚሁ ምዕራፍ 350 ማረፊያ ክፍሎች ያሉት ዘመናዊ ሆቴል በተርሚናሉ ውስጥ ይገነባል።

👉በዓመት 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን ጭነት የሚያስተናግድ የካርጎ ተርሚናል እና የአውሮፕላን ጥገና ማዕከልም በዚሁ ምዕራፍ የሚገነባ ይሆናል።

👉ፕሮጀክቱ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ አህጉርም ትልቅ አርአያ ነው።

👉የአፍሪካ ነፃ አኅጉራዊ ንግድ ቀጣናን ተግባራዊነት ለማቀላጠፍና የአኅጉሪቱን የንግድና የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር ቁልፍ ሚና ይጫወታል።

👉የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጋር የሚያገናኝና በአንድ ጊዜ 12 ተሽከርካሪ ማስተናገድ የሚችል የፍጥነት መንገድ እንዲሁም ፈጣን የባቡር መንገድ ይገነባል።

👉የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የአፍሪካን አቪዬሽን እድገት አስሮ የያዘውን የመሠረተ-ልማት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው።

👉ይህ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክት ከፍተኛ የሥራ ዕድል ይፈጥራል።

👉ከአውሮፕላን ማረፊያው ጋር ተያይዞ የሚመሠረተው የኤርፖርት ከተማም በንግድ፣ በኢንዱስትሪና በቱሪዝም ዘርፎች ለአካባቢው ዕድገት ትልቅ አስተዋጽዖ ይኖረዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም