የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአቪዬሽን መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ነው - ኢዜአ አማርኛ
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአቪዬሽን መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ነው
አዲስ አበባ፤ሰኔ 8/2018(ኢዜአ) ፦ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአቪዬሽን መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ይህ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅም በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ለማስተናገድ እንደሚችል ገልጸዋል።
የፕሮጀክቶ መጠናቀቅ ኢትዮጵያን ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ተርታ ለማሰለፍ የሚያስችል መሆኑን ገልጸው፥ ለዚህም ቀንና ሌሊት ባልተቋረጠ ቁርጠኝነት እየተገነባ ይገኛል ብለዋል።