ቀጥታ፡

ዋልያዎቹ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታ ኢትዮጵያ ማላዊን 1 ለ 0 አሸንፋለች።

ማምሻውን በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ፍጹም ጥላሁን ጨዋታው በተጀመረ በአንደኛው ደቂቃ ግቧን አስቆጥሯል።

ጨዋታው ተመጣጣኝ የሚባል ፉክክር ተደርጎበታል።


ብሔራዊ ቡድኖቹ ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታቸውን ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በድሬዳዋ ስታዲየም ያደርጋሉ።

ኢትዮጵያ ጨዋታውን የምታደርገው፣ የፊፋ ዓለም አቀፍ የብሔራዊ ቡድኖች የጨዋታ ቀናትን (FIFA Window) በመጠቀም መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
 

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም