ቀጥታ፡

የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ምሽቱ ሳያግዳቸው የዜግነት መብታቸውን ድምጽ በመስጠት እያረጋገጡ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 24/2018(ኢዜአ)፦ የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ምሽቱ ሳያግዳቸው የዜግነት መብታቸውን ድምጽ በመስጠት እያረጋገጡ ይገኛሉ።


 

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ማራዘሙ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ምሽቱ ሳያግዳቸው በተራዘመው የድምጽ መስጫ ሰዓት መብታቸውን ለመጠቀም ድምጽ እየሰጡ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም