አዲስ አበባ እና ባኩ የእህትማማች ከተሞች ስምምነት ተፈራረሙ - ኢዜአ አማርኛ
አዲስ አበባ እና ባኩ የእህትማማች ከተሞች ስምምነት ተፈራረሙ
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ እና ባኩ የእህትማማች ከተሞች ስምምነት ተፈራርመዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ከአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ጋር የተፈረመው ስምምነት፤ በከተማ ልማት፣ በአገልግሎት ዲጂታላይዜሽን፣ በቤት ልማት፣ በቱሪዝም (ስፖርት ቱሪዝምን) ጨምሮ በሁለቱ ህዝቦች መካከል የባህልና የታሪክ ልውውጥን የሚያጠናክር መሆኑን አመልክተዋል።