በሸገር ደርቢ ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 3 ለ 1 አሸነፈ - ኢዜአ አማርኛ
በሸገር ደርቢ ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 3 ለ 1 አሸነፈ
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 18/2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡናን ከቅዱስ ጊዮርጊስ ያገናኘው ሸገር ደርቢ በቡና አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
በአዲስ አበባ ስታዲዮም በተደረገው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና 3 ለ 1 ሲያሸንፍ ኦካይ ጁል፤ቢንያም ጌታቸው እና ዘላለም አባተ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡
ለቅዱስ ጊዮርጊስ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ፍጹም ጥላሁን ነው።
ቡድኖቹ በሊጉ እርስ በእርስ ሲገናኙ የአሁኑ ለ52ኛ ጊዜ ነው።