በለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀቀ - ኢዜአ አማርኛ
በለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀቀ
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 18/2018(ኢዜአ)፦በተጠባቂው የወንዶች የለንደን ማራቶን ውድድር በለንደን ማራቶን ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል።
በ46ኛው የለንደን ማራቶን የወንዶች ምድብ ውድድር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ውድድሩን 1:59.41 በመግባት ሁለተኛ ወጥቷል።
ኬንያዊው አትሌት ሴባስቲያን ሳው ውድድሩን በበላይነት ሲያጠናቅቅ ዩጋንዳዊው ጃኮፕ ኪፕሊሞ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል።
#Ethiopian_News_Agency
#ኢዜአ