ቀጥታ፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከፕሬዝደንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት በመያዝ የመጡትን የጂቡቲ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ እና አለምአቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማርን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀበሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(/) ከፕሬዝደንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት በመያዝ የመጡትን የጂቡቲ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ እና አለምአቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማርን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዛሬ ጠዋት ከፕሬዝደንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት በመያዝ የመጡትን የጂቡቲ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ እና አለምአቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማርን በጽሕፈት ቤታችን ተቀብያለሁ ብለዋል።

በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብርም ተወያይተናል ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም