ሊቨርፑል፣ ኖቲንግሃም ፎረስት እና አስቶንቪላ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል - ኢዜአ አማርኛ
ሊቨርፑል፣ ኖቲንግሃም ፎረስት እና አስቶንቪላ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ተካሂደዋል።
በመርሲሳይድ ደርቢ ከኤቨርተን ጋር ጨዋታውን ያደረገው ሊቨርፑል 2 ለ 1 ሲያሸንፍ፤ ሞሀመድ ሳላህ እና ቨርጂል ቫንዳይክ ለሊቨርፑል እንዲሁም ቤቶ ለኤቨርተን ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡
በሌላ የጨዋታ መርሐ-ግብር በቪላ ፓርክ ስታዲየም ሰንደርላንድን ያስተናገደው አስቶን ቪላ 4 ለ 3 ረትቷል።
በዚህ ጨዋታ ኦሌ ዋትኪንስ (2)፣ ሞርጋን ሮጀርስ እና ታሚ አብርሃም ለአስቶንቪላ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል።
እንዲሁም ክሪስ ሪግ፣ ትራይ ሀም እና ዊልሰን ኢስዶር የሰንደርላንድን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡
ኖቲንግሃም ፎረስት ደግሞ በርንሌይን 4 ለ 1 ማሸነፍ ችሏል።