ቀጥታ፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 6/2018 (ኢዜአ)፦  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ራንገል ጋር ውይይት አድርገዋል። 


 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ከፖርቹጋል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነት እና ቀጣይ ትብብሮችን  ማጠናከር በሚቻልባቸው ቁልፍ መስኮች ዙሪያ መምከራቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም