ኢትዮጵያ ኮስታሪካን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜው አለፈች - ኢዜአ አማርኛ
ኢትዮጵያ ኮስታሪካን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜው አለፈች
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 3 /2018 (ኢዜአ)፦ በ"UEFA Frendship Cup" ጨዋታ የኢትዮጵያ ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ኮስታሪካን 1 ለ 0 አሸንፏል።
በሪቫ ስታዲየም በተካሄደው የምድብ ሁለት ጨዋታ ህዳአት ካሡ በ37ኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥራለች።
ምትኬ ብርሃኑ በጨዋታው በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥታለች።
ኢትዮጵያ የቁጥር ብልጫ ቢወሰድባትም ውጤቷን አስጠብቃ ወጥታለች።
ውጤቱን ተከትሎ የኢትዮጵያ ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በስድስት ነጥብ ወደ ግማሽ ፍጻሜው አልፏል።
በቻለው ለሜቻ የሚመራው ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያው ጨዋታ ኮስታሪካን 3 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው።
በዚሁ ምድብ ዛሬ በተደረገው ሌላኛው ጨዋታ ኖርዌይ ዩራጓይን 6 ለ 0 በመርታት በተመሳሳይ በስድስት ነጥብ ወደ ግማሽ ፍጻሜው አልፋለች።
ከምድባቸው ያለፉት ኢትዮጵያ እና ኖርዌይ ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የሚያደርጉት ጨዋታ ከወዲሁ ይጠበቃል።
የወዳጅነት ዋንጫው ከውድድር ባለፈ የክፍለ አህጉራዊ እግር ኳስ ልማት ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው።
የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ያዘጋጀው እና በቱርኪዬ እየተካሄደ የሚገኘው የ"UEFA Frendship Cup" ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ውድድር እስከ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።