ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ-ጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለፁ - ኢዜአ አማርኛ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ-ጊዮርጊስ ህልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለፁ
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ-ጊዮርጊስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ሐዘን ገልፀዋል፡፡
ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ መልዕክት፤ ለአምባሳደር ቆንጂት ቤተሰቦች፣ ወዳጆች፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸው እና ለመላው ኢትዮጵያውያን ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።