ሐዋሳ ከተማ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ነጥብ ተጋሩ - ኢዜአ አማርኛ
ሐዋሳ ከተማ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ነጥብ ተጋሩ
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)፡- በ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት የተገናኙት ሀዋሳ ከተማ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ 2 አቻ ተለያይተዋል።
ጨዋታው የተካሄደው 10 ሠዓት ላይ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ነው።
በዚሁ ጨዋታም ያሬድ ብሩክ እና ሽመልስ በቀለ ለሐዋሳ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
እንዲሁም ነጻነት ገ/መድኅን እና ዳዊት ገብሩ ለወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ግቦቹን ከመረብ አሳርፈዋል።
ቀደም ብሎ 9 ሠዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ ነጌሌ አርሲ አዳማ ከተማን 2 ለ 1 ረትቷል።