ቀጥታ፡

በአማራ ክልል 1 ሺህ 224 የህግ ታራሚዎች በይቅርታ እንዲፈቱ ተወሰነ

ባህር ዳር፤መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል 1 ሺህ 224 የህግ ታራሚዎች በይቅርታ እንዲፈቱ መወሰኑን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አያሌው አባተ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ በይቅርታው ተጠቃሚ የሆኑት ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው የባህሪ ለውጥ ያመጡና የይቅርታ መመሪያውን ያሟሉ ናቸው ብለዋል።

በተጨማሪም እርቅና ካሳ የፈፀሙ፣ በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ታንፀው መልካም ስነ- ምግባር ያሳዩ የሚገኙበት መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም መሰረት 1 ሺህ 224 የህግ ታራሚዎች በይቅርታ እንዲፈቱ መወሰኑን ተናግረዋል።

በመሆኑም ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ የወንጀልን አስከፊነት ከማስተማር ባለፈ የበደሉትን ለመካስና የልማት አርበኛ እና የሰላም አምባሳደር ሆነው ለማገልገል መዘጋጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም