በ800 ሜትር ሴቶች ማጣሪያ አትሌት ንግስት ጌታቸው ለፍጻሜ አለፈች - ኢዜአ አማርኛ
በ800 ሜትር ሴቶች ማጣሪያ አትሌት ንግስት ጌታቸው ለፍጻሜ አለፈች
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በፖላንድ ቶሩን ከተማ መካሄዱን ቀጥሏል።
በ800 ሜትር ሴቶች ግማሽ ፍጻሜ ማጣሪያ በምድብ ሁለት የተወዳደረችው አትሌት ንግስት ጌታቸው 1 ደቂቃ ከ59 ሴኮንድ ከ46 ማይክሮ ሴኮንድ ሁለተኛ በመውጣት ለፍጻሜ አልፋለች።
በሶስት ምድብ በተካሄደው የማጣሪያ ውድድር ከየምድቡ አንደኛ እና ሁለተኛ የወጡ አትሌቶች ለፍጻሜ አልፈዋል።
የፍጻሜው ውድድር ነገ ምሽት 3 ሰዓት ከ53 ላይ ይካሄዳል።