ቀጥታ፡

በዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው የፍጻሜ ውድድሮች ይካሄዳሉ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በፖላንድ እየተካሄደ የሚገኘው 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል።

ምሽት 3 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ላይ የሴቶች የ3000 ሜትር የፍጻሜ ውድድር ይካሄዳል።

ፍሬወይኒ ኃይሉ እና ባለሽኝ ባወቀ ኢትዮጵያን ወክለው ይወዳደራሉ።

በውድድሩ ላይ 15 አትሌቶች ይሳተፋሉ።

ምሽት 3 ሰዓት ከ22 ደቂቃ ላይ በሚካሄደው የ3000 ሜትር ወንዶች ፍጻሜ ጌትነት ዋለ እና አዲስ ይሁኔ የሚሳተፉ ይሆናል።

ከፍጻሜው ውድድር በተጨማሪ ከቀኑ 8 ሰዓት ከ22 በ800 ሜትር ግማሽ ፍጻሜ ማጣሪያ አትሌት ንግስት ጌታቸው ትወዳደራለች።

በሶስት ምድብ ተከፍሎ በሚደረገው ማጣሪያ ከእያንዳንዱ ምድብ አንደኛ እና ሁለተኛ የሚወጡ አትሌቶች ለፍጻሜው ያልፋሉ።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም