ቀጥታ፡

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ላካ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት ምክንያት ህይወታቸው ያለፉትን ዜጎች በማስመልከት ብሔራዊ የሀዘን ቀን አወጀ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2018(ኢዜአ)፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ላካ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት ምክንያት ህይወታቸው ያለፉትን ዜጎች በማስመልከት ብሔራዊ የሀዘን ቀን አውጇል።

ብሔራዊ የሀዘን ቀኑ ከመጋቢት 5 ቀን 2018 ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ቀናት እንደሚሆንም ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም