ቀጥታ፡

ሐዋሳ ከተማ ከመቀሌ 70 እንደርታ ጋር ይጫወታል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1 /2018 (ኢዜአ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 23 ሳምንት መርሐ-ግብር ዛሬ በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጠናቀቃል።

ከቀኑ 9 ሠዓት ላይ ሐዋሳ ከተማ ከመቀሌ 70 እንደርታ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ሐዋሳ ከተማ በሊጉ 22 ጨዋታዎችን አድርጎ 10 ድል ሲቀናው፤ በአምስቱ ተሸንፏል። በቀሪ ሰባት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። በጨዋታዎቹ ላይ 25 ግቦችን ሲያስቆጥር 14 ግቦች ተቆጥረውበታል። ቡድኑ 37 ነጥብ ሦስተኛ ደረጃን ይዟል።

ተጋጣሚው መቀሌ 70 እንደርታ በሊጉ ካከናወናቸው 22 ጨዋታዎች መካከል አራቱን ሲያሸንፍ በስምንቱ ሽንፈት አስተናግዷል። በቀሪ 10 ጨዋታዎች ነጥብ ጥሏል። 15 ግቦችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ 24 ግቦች ተቆጥረውበታል።

መቀሌ 70 እንደርታ 22 ነጥብ 19 ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል።

ሐዋሳ ከተማ ባለፉት ሦስት ጨዋታዎች እንዲሁም መቀሌ 70 እንደርታ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አላሸነፉም።

ጨዋታው ሁለቱ ቡድኖች ወደ ድል መንገድ ለመመለስ የሚያደርጉት ነው።

ሐዋሳ ከተማ ካሸነፈ ሁለተኛ ደረጃን ከነገሌ አርሲ ይረከባል። ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ ያደርጋል።

በሌላኛው መርሐ-ግብር አዳማ ከተማ ከአርባምንጭ ከቀኑ 10 ሠዓት ላይ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያከናውናሉ።

በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው 22 ጨዋታዎች መካከል ሰባቱን ያሸነፈው አዳማ ከተማ በሦስቱ ሽንፈት አስተናግዷል። 12 ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። 22 ጨዋታዎች 20 ግቦችን ሲያስቆጥር፤ 18 ጎሎችን አስተናግዷል።

አዳማ ከተማ 33 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃን ይዟል።

ተጋጣሚው አርባምንጭ ከተማ በበኩሉ 22 ጨዋታዎች ሁለቱን አሸንፎ 10 ሽንፈት አስተናግዶ በተመሳሳይ 10 ጊዜ አቻ ወጥቷል። 14 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ 27 ጎሎች ተቆጥረውበታል።

አርባምንጭ ከተማ 16 ነጥብ የመጨረሻውን 20 ደረጃ ይዟል።

አዳማ ከተማ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 22 ሳምንት አርባምንጭ ከተማ በኢትዮ ኤሌክትሪክ 4 1 ሽንፈት አስተናግዷል።

ጨዋታው ሁለቱም ቡድኖች ወደ ድል መንገድ ለመመለስ የሚያደርጉት ነው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም