ቀጥታ፡

የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከልደታ ክፍለ ከተማ ጋር ይጫወታል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1 /2018 (ኢዜአ) የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 18 ሳምንት ዛሬ ይጀመራል።

ከረፋዱ 5 ሠዓት ላ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከልደታ ክፍለ ከተማ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ።


 

ኢትዮ ኤሌክትሪክ በውድድር ዓመቱ 17 ጨዋታዎችን አድርጎ 15 ጨዋታዎችን ሲያሸንፍ፤ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይቷል። 39 ግቦችን ሲያስቆጥር ሰባት ጎሎች ተቆጥረውበታል።

ቡድኑ 46 ነጥብ ሊጉን እየመራ ነው።

ተጋጣሚው ልደታ ክፍለ ከተማ በሊጉ ባደረጋቸው 17 ጨዋታዎች አራቱን ሲያሸንፍ፤ 10 ተሸንፏል። በቀሪ ሦስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል።

በጨዋታዎቹ ላይ 19 ግቦችን ከመረብ ሲያሳርፍ 30 ጎሎችን አስተናግዷል። ልደታ ክፍለ ከተማ 115 ነጥብ 1 ደረጃን ይዟል።

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ካሸነፈ የሊጉን መሪነት ያጠናክራል።

ልደታ ክፍለ ከተማ 17ኛው ሳምንት ከቦሌ ክፍለ ከተማ ጋር ሁለት አቻ ተለያይቷል። ቡድኑ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ ይጫወታል።


 

በሌላኛው መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቦሌ ክፍለ ከተማ ከጠዋቱ ሦስት ሠዓት ላይ በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 17 ጨዋታዎችን አድርጎ 14 ጊዜ ሲያሸንፍ፤ አንድ ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርቷል። 45 ግቦችን ከመረብ ላይ ሲያሳርፍ ሥድስት ግቦች ተቆጥረውበታል።

ቡድኑ 44 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል።

ተጋጣሚው ቦሌ ክፍለ ከተማ በሊጉ ባካሄዳቸው 17 ጨዋታዎች ስምንቱን ሲያሸንፍ ሦስት ጊዜ ተሸንፏል። በቀሪው ሥድስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይቷል። 21 ግቦችን ከመረብ ጋር ሲያገናኝ 15 ግቦችን አስተናግዷል።

ቦሌ ክፍለ ከተማ 30 ነጥብ ሥድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በድል ጉዞ ለመቀጠል እና የዋንጫ ፉክክሩን ለማጠናከር ይጫወታል። ቦሌ ክፍለ ከተማ ወደ ድል ጉዞ ለመመለስ ይፋለማል።

ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ተጽእኖ ያላቸው ናቸው።

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ 18 ሳምንት እስከ መጋቢት 3 ቀን 2018 . ይቆያል።

የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን የኢትዮ ኤሌክትሪኳ ዳግማዊት ሰለሞን 19 ግቦች ትመራለች።  ረድኤት አስረሳኸኝ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 13 ጎሎች ትከተላለች።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም