ቀጥታ፡

ሪያል ሶሲዬዳድ ለስፔን ጥሎ ማለፍ ፍጻሜ አለፈ

አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ (ኮፓ ዴል ሬይ) የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ ሪያል ሶሲዬዳድ አትሌቲኮ ቢልባኦን 1 ለ 0 አሸንፏል።

በአኖኤታ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማይክል ኦያርዛባል በ87ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥሯል።

ሁለቱ ቡድኖች ተመጣጣኝ ፉክክር አድርገዋል።



ሪያል ሶሲዬዳድ በድምር ውጤት 2 ለ 0 በማሸነፍ ለፍጻሜ አልፏል።

የባስኩ ክለብ በመጀመሪያው ጨዋታ 1 ለ 0 ማሸነፉ አይዘነጋም።

ሪያል ሶሲዬዳድ በፍጻሜው ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ይጫወታል።

የፍጻሜው ጨዋታ ሚያዚያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።



አትሌቲኮ ማድሪድ ባርሴሎናን በድምር ውጤት 4 ለ 3 በማሸነፍ ለፍጻሜ ማለፉ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም