ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው በባኩ የክብር አደባባይ እና የድል ሀውልት የአበባ ጉንጉን የማስቀመጥ ስነ-ስርዓት አከናወኑ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው በባኩ የክብር አደባባይ እና የድል ሀውልት የአበባ ጉንጉን የማስቀመጥ ስነ-ስርዓት አከናወኑ
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው በባኩ የክብር አደባባይ እና የድል ሀውልት የአበባ ጉንጉን የማስቀመጥ ስነ-ስርዓት አከናውነዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው ከአዘርባጃን ፕሬዝደንት ኢልሃም አልየቭ ጋር ከሚያደርጉት ውይይቱ ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ልዑካቸው በባኩ የክብር አደባባይ እና የድል ሀውልት የአበባ ጉንጉን የማስቀመጥ ስነ-ስርዓት አከናውነዋል።
እነዚህ ሀውልቶች የህዝቡን የማይበገር አንድነት የሚወክሉ ሲሆን፤ ለአዘርባጃን አንድነት መስዋዕትነት ለከፈሉ ሁሉ ያለንን ጥልቅ ክብር መግለጽ እንወዳለን ሲልም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል።