በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለሚተጋ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅተናል - ኢዜአ አማርኛ
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለሚተጋ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት ተዘጋጅተናል
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ በ7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ለኢትዮጵያ ዕድገትና ለህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ለሚተጋ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን በሸገር ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ።
የዘንድሮው ኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ማሳወቁ ይታወቃል።
በዚህም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትና ማኒፌስቷቸውን በማስተዋወቅ ላይ ናቸው።
ዜጎችም በመጪው ግንቦት በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ መስጠት የሚችሉበትን ካርድ ለመውሰድ እየተጠባበቁ ይገኛል።
የሸገር ከተማ ነዋሪ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለኢዜአ እንዳሉትም፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለህዝብና ለሀገር ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት በማፋጠን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅምና አንድነት ለሚሰራ የፓለቲካ ፓርቲ ድምጽ በመስጠት በምርጫ ሂደቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ከአስተያየት ሰጪ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ነጋሽ ኢደኦ እንዳሉት፤ ምርጫ ዜጎች ለሀገርና ህዝብ አንድነት ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ የሚመርጡበት ዕድል መሆኑን ተናግረዋል።
በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫም የሀገርን ዕድገት፣ የህዝብን አንድነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትጋት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ሀዳ ሲንቄ ጫልቱ ቀነዓ በበኩላቸው፤ ሀገራዊ ምርጫ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በማፋጠን ለሀገር ዕድገት የሚረዳ ወሳኝ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።
በቀጣዩ ጠቅላላ ምርጫም የኢትዮጵያን ሰላም፣ ልማትና ዕድገት በማሳለጥ ለዜጎች አንድነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
ምርጫ የአንድ ሀገር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መገለጫ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ድጋፌ ኤዪ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ናቸው።
በዚህም በቀጣዩ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ለህዝቦች ሕብረብሔራዊ አንድነትና ተጠቃሚነት እንዲሁም ለሀገር ዕድገት ለሚሰራ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
ዜጎችም ሀገርን በሚገባ በማስተዳደር ዕድገትና ልማትን ያፋጥናል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ በመስጠት ምርጫው ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሕዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የማድረግ ኃላፊነት አለብን ብለዋል።
የሸገር ከተማ ነዋሪ ወጣት ኢፌ ባልቻ በበኩሏ፤ በጠቅላላ ምርጫው ላይ ለሀገርና ህዝብ ይበጃል የምለውን የፖለቲካ ፓርቲ በመምረጥ ድምጽ ለመስጠት ጊዜውን እየተጠባበኩ ነው ብላለች።
በተለይም የኢትዮጵያና የሸገር ከተማን ልማት በማፋጠን የህዝቦች አንድነት፣ የሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚነት ለሚያረጋግጥ የፖለቲካ ፓርቲ ድምጽ እንደምትሰጥ ገልፃለች።
ወጣቶችም በመጪው ግንቦት ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማነት የሚጠበቅባቸውን ገንቢ ኃላፊነት መወጣት እንደሚኖርባቸው ጠቅሳለች።