የአርጆ ድንጋይ መፍጫ ፋብሪካ በኢትዮጵያ በዘርፉ የኢንዱስትሪ ልማት ዐቢይ ሚና ይጫወታል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) - ኢዜአ አማርኛ
የአርጆ ድንጋይ መፍጫ ፋብሪካ በኢትዮጵያ በዘርፉ የኢንዱስትሪ ልማት ዐቢይ ሚና ይጫወታል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2018(ኢዜአ)፦ የአርጆ ድንጋይ መፍጫ ፋብሪካ ከውጭ ሲገባ የነበረውን የተፈጨ ድንጋይ ፍላጎት በሀገር ውስጥ በማሟላት በኢትዮጵያ የዘርፉ የኢንዱስትሪ ልማት ዐቢይ ሚና ይጫወታል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ፋብሪካው ለሲሚንቶ፣ ለብረት እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎች አስፈላጊ ጥሬ ግብዓቶችን እንደሚያቀርብ አስታውቀዋል።
በተጨማሪም ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪ ልማትን እንደምታሳድግ ማሳያ መሆኑን አስገንዝበዋል።