የኬፕ ቨርዴ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ጆሴ ማሪያ ፔሬራ ኔቪስ አዲስ አበባ ገቡ - ኢዜአ አማርኛ
የኬፕ ቨርዴ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ጆሴ ማሪያ ፔሬራ ኔቪስ አዲስ አበባ ገቡ
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018 (ኢዜአ)፡- የኬፕ ቨርዴ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ጆሴ ማሪያ ፔሬራ ኔቪስ በ39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዚዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል።
39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሐሳብ ነገ በአዲስ አበባ ይጀመራል።
በጉባዔው የሚሳተፉ መሪዎችም ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ በመግባት ላይ ናቸው።