ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል - ኢዜአ አማርኛ
ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል
አዲስ አበባ፤ ጥር 24/2018 (ኢዜአ)፡- በ18ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 ረትቷል።
10 ሠዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ፤ ፋሲል ከነማ የቅዱስ ጊዮርጊሱ ቶሎሳ ንጉሴ በራስ ላይ ባስቆጠራት ግብ አሸናፊ ሆኗል።
ቀደም ብሎ 9 ሠዓት ላይ በተካሄደው የዕለቱ መርሐ-ግብር መቀሌ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ ቡና አንድ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል።