የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር መርሐ-ግብር ይፋ ሆነ - ኢዜአ አማርኛ
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር መርሐ-ግብር ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፤ ጥር 19/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በ14ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ይጀመራል።
የ14ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከየካቲት 7 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳሉ።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር የካቲት 7 ይጀመራል
በዚህም የሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከመቻል የሚያደርጉት ጨዋታ ከወዲሁ ተጠባቂ ነው።
ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ36 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዟል። መቻል በ29 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሸገር ከተማ ይጫወታል።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ32 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ በ27 ነጥብ አምስተኛ ደረጃን ይዟል።
በሌሎች የ14ኛ ሳምንት መርሐ-ግብሮች ሐዋሳ ከተማ ከአዳማ ከተማ፣ ቦሌ ክፍለ ከተማ ከሲዳማ ቡና፣ ይርጋጨፌ ቡና ከአርባምንጭ ከተማ፣ ድሬዳዋ ከተማ ከባህርዳር ከተማ እና አዲስ አበባ ከተማ ከልደታ ክፍለ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር መርሐ-ግብር በአበበ ቢቂላ ስታዲየም እንደሚደረግ ፌዴሬሽኑ ገልጿል።