ቀጥታ፡

የኢትዮጵያ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ ተጋጣሚዎች ታውቀዋል

አዲስ አበባ፤ ጥር 16/2018 (ኢዜአ) የኢትዮጵያ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ እጣ ማውጣት ሥነ-ርዓት ዛሬ ተካሄዷል።

በዚሁ መሠረት ነገሌ አርሲ ከሲዳማ ቡና፣ ቤንች ማጂ ቡና ከኢትዮጵያ መድን፣ መቻል ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ እና ቦዲቲ ከተማ ከመቀሌ 70 እንደርታ በሩብ ፍጻሜው ይጫወታሉ።

የሩብ ፍጻሜ መርሐ-ግብር መጋቢት 12 እና 13 ቀን 2018 . በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ዋንጫን የሚያሸንፈው ቡድን በቀጣዩ ዓመት ኢትዮጵያን ወክሎ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ይሳተፋል።

1937 . የተጀመረው የኢትዮጵያ ዋንጫ 81 ዓመታትን ያስቆጠረ አንጋፋ ውድድር ነው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም