ቅዱስ ጊዮርጊስ ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመለሰ - ኢዜአ አማርኛ
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመለሰ
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሬዳዋ ከተማን 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል።
በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አምበሉ አቤል ያለው በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር፤ ሀብታሙ ጉልላት እና ፍጹም ጥላሁን ደግሞ ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ ላይ አሳርፈዋል።
የድሬዳዋ ከተማው አማካይ ሄኖክ ሀሰን በ22ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። ይህም በጨዋታው ላይ ተጽእኖ አሳድሯል።
ከስድስት የሊጉ ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ በ22 ነጥብ ደረጃውን ከ10ኛ ወደ 7ኛ ከፍ አድርጓል።
በውድድር ዓመቱም ስድስተኛ ድሉን አሳክቷል።
በአንጻሩ በሊጉ አምስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በ18 ነጥብ ከነበረበት 12ኛ ደረጃ ወደ 13ኛ ዝቅ ብሏል።