ቀጥታ፡

ኢትዮጵያ ቡና እና ሐዋሳ ከተማ ነጥብ ተጋሩ

አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 15 ሳምንት ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና እና ሐዋሳ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል።


 

በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ናይጄሪያዊው ዲቫይን ዋቹኩዋ 38ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ኢትዮጵያ ቡና መሪ ሆኗል።

ጌታነህ ከበደ 93ኛው ደቂቃ ለሐዋሳ ከተማ የአቻነቷን ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል።

ውጤቱን ተከትሎም ኢትዮጵያ ቡና 19 ነጥብ 11 ደረጃን ይዟል።


 

ሐዋሳ ከተማ 25 ነጥብ ደረጃውን ከአምስተኛ ወደ አራተኛ ከፍ ማድረግ ችሏል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም