መቻል ወደ ድል ተመልሷል - ኢዜአ አማርኛ
መቻል ወደ ድል ተመልሷል
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር መቻል አርባ ምንጭ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል።
በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቸርነት ጉግሳ በ68ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት እና ዩጋንዳዊው ቻርልስ ሙሲጌ በ91ኛው ደቂቃ በጨዋታ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
ከሦስት ተከታታይ ሽንፈቶች በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው መቻል በ23 ነጥብ ደረጃውን ከሰባተኛ ወደ ስድስተኛ ከፍ አድርጓል።
በሊጉም ስድስተኛ ድሉን አስመዝግቧል።
በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሰባተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው አርባ ምንጭ ከተማ በስምንት ነጥብ በደረጃ ሠንጠረዡ ግርጌ ላይ ተቀምጧል።
አርባ ምንጭ ከተማ በሊጉ እስከ አሁን ምንም ጨዋታ ያላሸነፈ ብቸኛው ክለብ ነው።