በዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ሁለተኛ በመሆን ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ ልዑክ አቀባበል ተደረገለት - ኢዜአ አማርኛ
በዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ሁለተኛ በመሆን ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ ልዑክ አቀባበል ተደረገለት
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ በአሜሪካ ፍሎሪዳ በተካሄደው 46ኛው የዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን አቀባበል ተደርጎለታል።
ልዑካን ቡድኑ ዛሬ ማለዳ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ፣ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች አቀባበል አድርገውታል ።
ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በሶስት የወርቅ፣ ሁለት የብር እና ሁለት የነሐስ በአጠቃላይ ሰባት ሜዳሊያዎችን በማግኘት ኬንያን ተከትላ ከዓለም ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።