ቀጥታ፡

ማንችስተር ሲቲ ኤክስተር ሲቲን 10 ለ 1 በማሸነፍ በኤፍኤ ካፕ ቀጣዩን ዙር ተቀላቀለ 

አዲስ አበባ፤ ጥር 2 /2018 (ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ኤፍኤካፕ የሶስተኛ ዙር መርሃ ግብር ማንችስተር ሲቲ ኤክስተር ሲቲን 10 ለ 1 ረቷል። 

ማምሻውን በኢትሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሮድሪ፣ ራያን ማይካዶ፣ ማክስ አሊይን፣ ሪኮ ሉዊስ፣ አንቶዋን ሴሜንዮ፣ ናታን አኬ፣ ቲጃኒ ራይንደርስ፣ ኒኮ ኦራይሊ እንዲሁም የኤክስተሮቹ ጃክ ፊትዝዋተር እና ጃክ ዶይል-ሄይስ በራሳቸው ላይ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል። 

ጆርጅ ቢርች ለኤክስተር ብቸኛውን ጎል አስቆጥሯል።

ከቦርንማውዝ የፈረመው አንቶዋን ሴሜኒዮ የመጀመሪያ ጎሉን ለሲቲ አስቆጥሯል። 

ውጤቱን ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ ወደ አራተኛ ዙር አልፏል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም